
21/08/2024
አሳዛኝ ዜና
በጣም የሚያሳዝን መርዶ
ዶ/ር ደረጄ ዘለቀ አረፈ::
በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የሕግ ትምህርት ክፍል መምህር የነበረው ዶ/ር ደረጀ ዘለቀ፣ ከቅርብ ዓመታት ወዲህ፣ በኢትዮጵያ ፖለቲካ መድረክ ብቅ ብሎ የሰላ ሒስ በመተቸት ይቴወቅ ነበር።
አዲስ አበባ ፈረንሳይ ለጋሲዮን ተወልዶ ያደገው ዶ/ር ደረጀ ዘለቀ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ያዝ ለቀቅ የሚያደርገው ህመም በርትቶበት በተለያዩ ሆስፒታሎች ሲታከም ቆይቶ ዛሬ ከረፋዱ 4:00 ሰዓት ላይ አርፏል:: :
ነፍስ ይማር!
የዶ/ር ደረጀ ዘለቀ የቀብር ሥነ ስርዓት ነገ፣ ነሐሴ 16 ቀን 9:00 ሰዓት ጴጥሮስ ወጳውሎስ ቤተክርስቲያን ይፈጸማል::😭