Digital Amhara.

Digital Amhara. እውነተኛ መረጃ

ዘመነ ካሴ እና የጎጃም ቀጠና ፋኖ ተለያዩ!         የዘመነ ካሴ ትግል አብቅቶለታል። የዘመነ ካሴ አደረጃጀት ከጎጃም ቀጠና ካለው የፋኖ አደረጃጀት እና ከዲያስፖራው ጋር የነበረው የግንኙ...
31/05/2026

ዘመነ ካሴ እና የጎጃም ቀጠና ፋኖ ተለያዩ!

የዘመነ ካሴ ትግል አብቅቶለታል። የዘመነ ካሴ አደረጃጀት ከጎጃም ቀጠና ካለው የፋኖ አደረጃጀት እና ከዲያስፖራው ጋር የነበረው የግንኙነት ገመድ ተበጥሷል። በአስረስ ማረ ዳምጤ የሚመራው የጎጃም ቀጠና የፋኖ አደረጃጀት በዘመነ የትግል ስልት ተስፋ ቆርጦ የሚዲያ ዘመቻ ጀምሮበታል።

የዘመነ ካሴ ፖለቲካ የ Selfi ፎቶ ነበር፤ ለትግል ሳይሆን ለፎቶ ያለው ፍቅር ትግሉን አደጋ ውስጥ ጥሎታል፣ በዘመድ አዝማድ አመራር እያደራጀ ሃብት አሽሽቷል በሚል ከፋኖ ታጣቂዎች ተቃውሞ እንደገጠመው ታውቋል።

የከሸፉ የጥፋት ስምሪቶች!ኢትዮጵያ 7ኛውን ሀገራዊ ምርጫ በሰላም ለማከናወን ጥቂት ቀናት ብቻ ቀርተዋታል። ይህ ሂደት ዜጎች መንግስታቸውን በጠመንጃ ሳይሆን በነጻነትና በካርዳቸው የሚመርጡበት ...
30/05/2026

የከሸፉ የጥፋት ስምሪቶች!

ኢትዮጵያ 7ኛውን ሀገራዊ ምርጫ በሰላም ለማከናወን ጥቂት ቀናት ብቻ ቀርተዋታል። ይህ ሂደት ዜጎች መንግስታቸውን በጠመንጃ ሳይሆን በነጻነትና በካርዳቸው የሚመርጡበት የታሪክ ክስተት ነው። ሆኖም ግን፣ ይህ የዴሞክራሲ ጉዞ እንቅልፍ የነሳቸው በርካታ የውስጥና የውጭ ኃይሎች፣ ምርጫውን ለማስተጓጎልና ሀገሪቱን ወደ ትርምስ ለመክተት ያልፈነቀሉት ድንጋይ የለም።

ከቅርብ ሳምንታት ወዲህ የተሰነዘሩት “የከሸፉ የጥፋት ስምሪቶች” የሴራ መረብ ምን ያህል ሰፊ እንደነበር ያሳያሉ።

በሰሜን የፕሪቶሪያን ስምምነትና ጊዜያዊ አስተዳደሩን በማፍረስ የተደረገው የፖለቲካ ቁማር፣ በኦሮሚያና በአማራ ክልል የሚንቀሳቀሱ ጽንፈኛ ታጣቂዎች በቅንጅት የፈጠሩት የሁከት ግንባር፣ እንዲሁም በአፋር ንጹሃን ላይ የተሰነዘረው የሽብር ጥቃት በሙሉ የአንድ ትልቅ ሴራ አካላት ነበሩ።

የአርሶ አደሩን ማዳበሪያና የምርት ግብዓት ለማደናቀፍ ለቀናት መንገድ መዝጋትና በከተሞች ሁከት ለመቀስቀስ መሞከርም የዚሁ ስምሪት አካል ነበር።

ይህ የውስጥ የጥፋት ስራ በባዕዳንና በጎረቤት ሀገራት (ሱዳንና ሶማሊያ) ጂኦፖለቲካዊ ትንኮሳዎች የታገዘ ሲሆን፣ እንደ ቢቢሲና አልጀዚራ ያሉ ዓለም አቀፍ ሚዲያዎች ደግሞ የተዛባ መረጃ በመንዛት ኢትዮጵያን በሁሉም አቅጣጫ ወጥሮ የመያዝ ስትራቴጂ ተከትለው ነበር።

ነገር ግን፣ እነዚህ ሁሉ የተደገሱ የጥፋት ድግሶች ሊከሽፉ የቻሉት በሁለት ዋና ዋና ምሰሶዎች ጥንካሬ ነው፦

የመጀመሪያው፣ ኢትዮጵያ የገነባችው ግዙፍና ጠንካራ የመከላከያ ሰራዊት የውስጥና የውጭ ስጋቶችን በአስተማማኝ ሁኔታ መመከት መቻሉ ሲሆን፤ ሁለተኛውና ዋናው ደግሞ፣ የኢትዮጵያ ህዝብ የጽንፈኞችን የሽብር ጥሪ ውድቅ በማድረግ ያሳየው የበሰለ የፖለቲካ ንቃትና ጽናት ነው። ህዝቡ የጥፋት ኃይሎችን በመንጠል፣ ምርጫው የህልውናው መወሰኛ መሆኑን በተግባር አሳይቷል።

ምንም እንኳን ዋና ዋናዎቹ የጥፋት ስምሪቶች ቢከሽፉም፣ ስጋቱ ሙሉ በሙሉ አላበቃም። በቀጣዮቹ ጥቂት የምርጫና የድምጽ ቆጠራ ቀናት፣ በጥቃቅን ቦታዎች ጥይት በመተኮስና የውሸት ወሬዎችን በመንዛት ምርጫውን ጥላሸት ለመቀባት መሞከራቸው አይቀሬ ነው።

ስለሆነም፣ መላው የሀገራችን ህዝብ በእነዚህ ወሳኝ ቀናት ነቅቶ መጠበቅና እያንዳንዱን መረጃ ማሰላሰል ይኖርበታል። ኢትዮጵያ በምርጫ የምትመሰርተው ጠንካራ መንግስት የባዕዳንን ቅዠት የሚቀብር በመሆኑ፣ ድምጻችንን በሰላም በመስጠት ሀገራዊ ታሪካችንን በገዛ እጃችን እንድንጽፍ እናሳስባለን።

ኢትዮጵያ በልጆቿ ጽናትና በድምጿ ወደፊት ትሻገራለች!

የባዕዳን ተልዕኮን ተሸክሞ የሚንቀሳቀሰው ፅንፈኛ ኃይል ላይ በሁሉም አቅጣጫ እየተወሰደ ያለው እርምጃ ተጠናክሮ ቀጥሏል።********ሀገራችን የጀመረችውን ሁለንተናዊ የብልጽግና ጉዞ ለማደናቀፍ...
29/05/2026

የባዕዳን ተልዕኮን ተሸክሞ የሚንቀሳቀሰው ፅንፈኛ ኃይል ላይ በሁሉም አቅጣጫ እየተወሰደ ያለው እርምጃ ተጠናክሮ ቀጥሏል።
********
ሀገራችን የጀመረችውን ሁለንተናዊ የብልጽግና ጉዞ ለማደናቀፍ ባዕዳንና ባንዳዎች ግንባር ፈጥረው ያልፈነቀሉት ድንጋይ፣ ያልጎነጎኑት ሴራ የለም። የሀገርን ሰላም፣ አንድነትና የሕዝብን ተስፋ ለማፍረስ በተለያዩ መንገዶች ሲንቀሳቀሱ ቆይተዋል።

ዳሩ ግን “ከመላዕክት መካከል የገባ ሰይጣን በአካሄዱ ይታወቃል” እንደሚባለው፣ የፅንፈኛው ኃይል እኩይ ተልዕኮና መዳረሻ ግቡ በንድፈ ሐሳብ ሳይሆን በተግባር በሕዝባችን ፊት ተጋልጧል። በዚህም የተነሳ እውነታው እየተገለጠ ሲመጣ፣ ከባሕር የወጣ ዓሣ ይመስል የሲቃ ድምፅ እያሰማ ይገኛል።

የባዕዳንን ተልዕኮ ዳር ለማድረስ ዘርፈ ብዙ እንቅስቃሴ የሚያደርገው ይህ ኃይል፣ የሐሰት መረጃዎችን በመልቀቅ ሕዝቡን ለማደናገር ቢሞክርም፣ እውነታው ግን ጀግናው የሀገር መከላከያ ሠራዊትና ጥምር ጦሩ በወሰዱት ቆራጥ እርምጃ በርካታ የፅንፈኛውን አባላት በመደምሰስ፣ ቀሪዎቹንም ከነ ሙሉ ትጥቃቸው ተማርከዋል፤ በመማረክም ላይ ይገኛሉ።

በዚህ ድል የተነሳ የፅንፈኛውን ኃይል በስውር ሲደግፉ የነበሩ ኃይሎች ከፍተኛ ጭንቀትና ድንጋጤ ውስጥ ገብተዋል። የጥምር ጦሩ ውጤታማ እንቅስቃሴ የጠላትን ተስፋ እያከሸፈ ሲሆን፣ የሕዝቡን መንፈስና እምነት ይበልጥ አጠናክሯል።

ጥምር ሠራዊቱ መንግሥትና ሕዝብ የሰጡትን ተልዕኮ በብቃት በመፈጸም፣ አስቸጋሪና ፈታኝ የመሬት ገጽታዎችን ጥሶ በማለፍ፣ “ለሰላም አልገዛም” ብሎ በአካባቢው ተደብቆ የአካባቢውን ሕዝብ ሲዘርፍና ሲያሸብር የቆየውን ፅንፈኛ ቡድን በመደምሰስ፣ ዘላቂ ሰላማችን ቅርብ መሆኑን በተግባር አረጋግጧል።

የሀገራችን የሰላምና የልማት ጉዞ በማንም ኃይል የሚቆም አይደለም። ሕዝባችን በአንድነት ቆሞ ለሀገሩ ሰላምና ሉዓላዊነት ያደረገው ትግል ውጤት እያሳየ ሲሆን፣ የጠላት ሴራ ሁሉ እየከሸፈ ይገኛል።

የጎጃም ፋኖ ፈርሷል‼️በጎጃም ቀጠና ያለው ፋኖ ቁመና በአሁኑ ወቅት ሙሉ በሙሉ የመፍረክረክ ደረጃ ላይ የደረሰ ሲሆን ጥቂት የገጠር ቀበሌዎች ውስጥ ከመሸሸግ ባለፈ ዋና ዋና የወረዳ ከተሞችንና...
29/05/2026

የጎጃም ፋኖ ፈርሷል‼️

በጎጃም ቀጠና ያለው ፋኖ ቁመና በአሁኑ ወቅት ሙሉ በሙሉ የመፍረክረክ ደረጃ ላይ የደረሰ ሲሆን ጥቂት የገጠር ቀበሌዎች ውስጥ ከመሸሸግ ባለፈ ዋና ዋና የወረዳ ከተሞችንና ቁልፍ መንገዶችን የመቆጣጠር አንዳችም ወታደራዊ አቅም የሌለው ደካማ ስብስብ ሆኖ ቀርቷል።

በፋኖ ውስጥ ያለው የዕርስበርስ መተማመን ፈርሶ ዝናቡ የህዝብ ግንኙነት ሀላፊውን ማርሸትን ማፈኑና መግረፉ፣ ይህን ተከትሎም አባላቱ በየፊናቸው ጎራ ለይተው እርስበርስ ሊጠፋፋ ቀን እየጠበቀ ነው።

ዘመነ ካሴ ይህንን ቀውስ የመፍታት ብቃቱ ስለሌለው ሱዳን፣ ኤርትራ እና ትግራይ ቱሪስት ሆኗል። በውስጥ መከፋፈል የሚናወጠው ይህ አቅመ-ቢስ ቡድን በጦርነት አሸንፎ መንግስት መሆን ይቅርና ለተራ ድርድር የሚበቃ ቁመና የሌለው እንደሆነ ተደምድሟል።

ብዙኅኑ ፋኖ የውጭ ኃይሎች ጉዳይ አስፈጻሚ ከመሆን የዘለለ አንዳችም ሚና እንደሌለው መሬት ላይ ያለው ተጨባጭ እውነት ያረጋግጣል የሚል አስተያየት እየሰነዘሩ ይገኛል።

አስረስ ማረ ውስጥ ለውስጡን በሚሰራው ሴ*ራ ዘመነ ካሴን ሊገ*ለብ*ጠ*ው ከ*ጫ*ፍ ደር*ሷል!!የጎጃሙ ጽን*ፈኛ ዋና እና ቀንደኛ ዘዋሪዎች የሆኑት ዘመነ እና አስረስ ውስጥ ውስጡን የጀመሩት የ...
29/05/2026

አስረስ ማረ ውስጥ ለውስጡን በሚሰራው ሴ*ራ ዘመነ ካሴን ሊገ*ለብ*ጠ*ው ከ*ጫ*ፍ ደር*ሷል!!

የጎጃሙ ጽን*ፈኛ ዋና እና ቀንደኛ ዘዋሪዎች የሆኑት ዘመነ እና አስረስ ውስጥ ውስጡን የጀመሩት የትክሻና እኔ በልጥ የምትል የስልጣን ሽኩቻ ተከታይ ጀሌዎቻቸውን እያ*ጫ*ረሳቸ*ው ይገኛል።

ለአብነትም ዘመነ አስረስ ለማዳከም በሚል ሰበብ የእሱን ተከታይ የሆኑትን ማርሸትን እና የመሳሰሉትን ቀጥታ የግሉ እስር ቤት በመክተት ቁ*ም ስ*ቅ*ላቸ*ውን በማሳ*የት ለ*ሞ*ት እስኪደ*ርሱ ድርስ እያ*ደረገ መል*ቀቅ ከጀመረ ሰነባ*ብቷል። ለዚህ ነው ማርሸት ቁ*ሞ መሽ*ናት እስኪቸግረው ድረስ ደርሶ ወደ አስመራ ለህክምና የተላከው።

ይህን የተመለከትው አስረስም በዘመነ ላይ ሴ*ራ በመጎ*ንጎን ከእ*ሱ ተቃ*ራኒ የሆኑን ታጣቂዎችን ከምዕራብ ጎጃም ጭምር ማደራ*ጀት ከጀመረ ሰነባብቷል። እንዲሁም ከዚህ ቀደም ከዘመነ ጋር ተጋ*ጭተው የነበሩ ታጣቂዎችን ጭምር ከጎንደር ማደራጀት ጀምሯል። አስረስ ይህን ሁሉ ሴራ በዘመነ ላይ እየጎነ*ጎነ ያለው ዘመነ በአስረስ ላይ ተኝ*ቶ እንደማ*ያድር በመገንዘቡ የተነሳ ሲሆን አሁን ላይ ውስጥ ውስጡን በሚያደ*ራጀው ታጣቂ ከጎጃም ብሎም ከአፋብን ድርጅት መሪነት ዘመነን ገል*ብጦ ሊ*ጥ*ለ*ው ጫ*ፍ ላይ ይገኛል።

ትላንትና ዛሬ አንድ አይደሉም!ያለፈው አልፏል፤ ታሪክም ተቀይሯል። የክልላችንን ሰላምና ልማት ወደኋላ ለመጎተት የሚሰሩ፣ ህዝብን ከህዝብ ለመለየት የሚጥሩ እና የራሳቸውን ድብቅ የፖለቲካ አጀን...
28/05/2026

ትላንትና ዛሬ አንድ አይደሉም!

ያለፈው አልፏል፤ ታሪክም ተቀይሯል። የክልላችንን ሰላምና ልማት ወደኋላ ለመጎተት የሚሰሩ፣ ህዝብን ከህዝብ ለመለየት የሚጥሩ እና የራሳቸውን ድብቅ የፖለቲካ አጀንዳ ለማሳካት የሚራወጡ ፅንፈኛ ኃይሎች የሚነዙት የሀሰት ትርክትና ወሬ ዛሬ ላይ የሚያታልለው አንድም የአማራ ህዝብ የለም።

የአማራ ህዝብ አስተዋይ፣ የሰላምን ዋጋ ጠንቅቆ የሚያውቅና ከጥፋት ይልቅ በልማት ላይ ያተኮረ ኩሩ ህዝብ ነው። የሴረኞችንና የከፋፋዮችን የሀሰት ፕሮፓጋንዳ ነቅቶ የመጠበቅና የመመከት ሙሉ አቅም አለው። ማንኛውንም አይነት የክልሉን እንቅስቃሴና ጉዞ ለማደናቀፍ የሚደረግ ሙከራ ፍፁም ተቀባይነት የለውም፤ የሚዘጋም መንገድ አይኖርም!

አማራን ለማጥፋት ህወሓት ፋኖን ያለበሰው አዲሱ ዩኒፎርም‼️ሰሞኑን በስፋት እየተስተዋለ ያለው አዲሱ የፋኖ የደንብ ልብስ ለውጥ፣ ከተራ ወታደራዊ ዝግጅት ያለፈና የአማራን ህዝብ ደህንነት ለአደ...
28/05/2026

አማራን ለማጥፋት ህወሓት ፋኖን ያለበሰው አዲሱ ዩኒፎርም‼️

ሰሞኑን በስፋት እየተስተዋለ ያለው አዲሱ የፋኖ የደንብ ልብስ ለውጥ፣ ከተራ ወታደራዊ ዝግጅት ያለፈና የአማራን ህዝብ ደህንነት ለአደጋ የጣለ አደገኛ ሴራ ነው።

ይህ ዩኒፎርም ከህወሓትና ከሻቢያ ሰራዊት አልባሳት ጋር አንድ ዓይነት እንዲሆን መደረጉ፣ በአማራ ማህበረሰብ ላይ የሚፈጸሙ ግፎችን ለመደበቅና ወንጀለኞቹን ከህዝብ እይታ ለመሰወር የተዘረጋ ወጥመድ ነው።

ከዚህም በላይ፣ የደንብ ልብሱ መመሣሠል ህወሓት በአማራ ክልል የሚፈጽመውን ጭፍጨፋ፣ ግድያና አስገድዶ መድፈር ወንጀል በቀጥታ ለፋኖ ለማስመሰል እና ራሱን ከወንጀል ተጠያቂነት ሙሉ በሙሉ ለመከላከል የዘየደው ስልት ነው።

የዚህ ሴራ ዋና ዓላማ ወንጀል እየፈጸሙ ወንጀለኞቹን መደበቅ፣ እንዲሁም አማራውን በእጅ አዙር የማጥፋት እቅድን በህወሓት የበላይነት ማስፈጸም ነው።

መከላከያ ሠራዊታችን መለያው አንድነት፣ ጽናትና ድል ነው!ክብር ለኢትዮጵያ የጀርባ አጥንት ለሆነው መከላከያ ሰራዊታችን🇪🇹‼️
24/05/2026

መከላከያ ሠራዊታችን መለያው አንድነት፣ ጽናትና ድል ነው!

ክብር ለኢትዮጵያ የጀርባ አጥንት ለሆነው መከላከያ ሰራዊታችን🇪🇹‼️

ምርጫ ለማደናቀፍ ኤርትራ ሰልጥኖ የመጣው ጽ"ን"ፈ'ኛ ተደመሰሰ! ከትናንት በስቲያ በምዕራብ ጎጃም የሚጓጓዘውን የምርጫ ቁሳቁስ ለማደናቀፍ ከተለያየ ቦታ የተሰባሰበው ፅንፈኛ ተደምስሷል።በዚህም...
22/05/2026

ምርጫ ለማደናቀፍ ኤርትራ ሰልጥኖ የመጣው ጽ"ን"ፈ'ኛ ተደመሰሰ!

ከትናንት በስቲያ በምዕራብ ጎጃም የሚጓጓዘውን የምርጫ ቁሳቁስ ለማደናቀፍ ከተለያየ ቦታ የተሰባሰበው ፅንፈኛ ተደምስሷል።

በዚህም 8 ሲደመሰስ፤ 7 ቁ'ስ'ለ'ኛ ሆኗል።

✍️ የተደመሰሱ ሰም ዝርዝር

1ኛ/ አበረ ያየህ
2ኛ/ አበሉ ፋሲል
3ኛ/ ጌትነት ይባላል
4ኛ/ አበበ ልመንህ ሻ/ል መሪ
5ኛ/ አሰቻለዉ
6ኛ/ ይከበር ቡሬ
7ኛ ቢተዉ አበበ ቲም/መሪ
8ኛ ምህረት አለልኝ

✍️ የቆሰሉ ስም ዝርዝር

1ኛ/ ዳዊትአሰማረ ዘመቻ መሪ
2ኛ/ ድንቾ
3ኛ/ ፈንታዉ አበጄ
4ኛ/ ቢሻዉ ፈረደ ም/ ሻ/ቃ/ መሪ
5ኛ/ ደረጄ ሹመቴ
6ኛ/ ሙልየለት
7ኛ/ ካሳ ታደሰ

Address

Sheger
Addis Ababa
ONE

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Digital Amhara. posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to Digital Amhara.:

Share