Digital Amhara.

Digital Amhara. እውነተኛ መረጃ

 |፡ የኢትዮጵያ አየር ኃይል ዛሬም ደገመው 🇪🇹         ~~~~//~~~~በሃገር ሉዓላዊነት የማይደራደረው የኢትዮጵያ አየር ኃይል ዛሬም ታሪክ ሰርቷል። ከደማዚን (ኩምሩክ ) ግንባር ተነ...
03/08/2026

|፡ የኢትዮጵያ አየር ኃይል ዛሬም ደገመው 🇪🇹
~~~~//~~~~
በሃገር ሉዓላዊነት የማይደራደረው የኢትዮጵያ አየር ኃይል ዛሬም ታሪክ ሰርቷል።

ከደማዚን (ኩምሩክ ) ግንባር ተነስቶ ወደ ሸረሪና መጥቶ እንዲያጠቃ መመሪያ የተቀበለው የአርሚ 70 2ኛ ኮርና ወዲ ነጩ ኮማንዶ ተብየው ታጣቂ ኃይል ከነአመራሩ #ሲንጃ ወይም ልዩ ስሙ በተባለ አካባቢ በጀግናው የኢትዮጵያ አየር ኃይል ወደ አመድነት ተቀይሯል።

 #ሰበር  #መረጃ!!!የአርሚ 70 አዛዥ ጀነራል ሙዘይ መኮነን በሸረሪናው ውጊያ ቀኝ እጁን አጦ ካርቱም ሆስፒታል ገብቷል!!ለሱዳን ጦር ተሽጦ በባዕድ ሀገር ጦርነት ቅጥረኛ ሁኖ የትግራይ ወጣ...
03/08/2026

#ሰበር #መረጃ!!!

የአርሚ 70 አዛዥ ጀነራል ሙዘይ መኮነን በሸረሪናው ውጊያ ቀኝ እጁን አጦ ካርቱም ሆስፒታል ገብቷል!!

ለሱዳን ጦር ተሽጦ በባዕድ ሀገር ጦርነት ቅጥረኛ ሁኖ የትግራይ ወጣትን በጦርነት እሳት እንዲለበለብ እያደረገ ያለውን የህወሓት አርሚ 70ን ጀነራል ሙዘይ መኮነን እንደሚመራርው የሚታወቅ ጉዳይ ነው።

ታዲያ ከቀናት በፊት በሸረሪና በኩል ጥቃት በመክፈት ይፋዊ ጦርነት የጀመረው የህወሓት አርሚ 70 ነገሮች እንዳሰበው ሳይሆኑለት ቀርተው በርካታ ኪሳራዎች ደርሰውበታል።

በዚህም የአርሚ 70 ከከፍተኛ አመራሮች እስከ ተራ ታጣቂዎች በእብሪተኝነት በጀመሩት ጦርነት እንደተገደሉ ለማወቅ ተችሏል።ከዚህ በተጨማሪም በርካታ የነፍስ ወከብ እና የቡድን መሳሪያዎች ተማርኮባቸዋል።

በተለይ የአርሚ 70 ዋና አዛዥ የሆነው ጀነራል ሙዘይ መኮነን በሸረሪናው ጦር'ነት ከፍተኛ ጉ'ዳ'ት እንደደረሰበት ታውቋል።በተለይ ቀኝ እጁ ከጥቅም ውጭ እንደሆነ እና ለህክምና ወደ ካርቱም ሆስፒታል ማቅናቱን የደረሱን መረጃዎች ያሳያሉ።

01/08/2026

ጥቁር አንበሳ አይጀምርም፤ ከጀመረ ሳይጨርስ አያቆምም!

ኤርትራን አቋርጦ በሱዳን አዋሳኝ ድንበር #ሸረሪና በኩል ጠዋት 12፡00 ሰዓት በኢትዮጵያ ጦር ሰራዊት ላይ ውጊያ የከፈተው የግብፅ ዘበኛ የሆነው የአርሚ 70 መካናይዝድ ሃይል እና ከአርሚ 15/13 የተውጣጣ ሁለት መካናይዝድ ሃይል ከጥቅም ውጭ ሆኗል — እንሆ ግብፅ ታላቅ ኪሳራን ተከናነበች 💪

ለባለፉት አመታት የአርሚ 70 የጦር ቤዝ የነበረው #ሸረሪና በወገን እጅ ገብቷል። የጥቁር አንበሳ ምርኳቸውን እየቆጠሩ ይገኛሉ። ለጽንፈኛ ቡድኑ ከግብፅ የተሰጠ ሞርታር፣ ዙ-23፣ ዲሽቃ፣ ብሬን እና ስናይፐርን ጨምሮ እጅግ በርካታ የነፍስ ወከፍና የቡድን የጦር መሣሪያዎች እንዲሁም ተተኳሾች በቁጥጥር ሥር ውለዋል።

የተለያዩ ተተኳሽ የጫኑ የከባድ ተሽከርካሪዎች ፋንዳታ እስከአሁን ድረስ እንዳልቆመ ከቦታው መረጃ ደርሶናል።

📼- በምስሉ ❝ ኑ! እባካችሁ ወደዚህ ኑ ቁስለኛ እናንሳ አግዙኝ...❞ ሲል ይደመጣል።

"ጅራፍ እራሱ ገርፎ እራሱ ይጮሃል" ማለት አሁን ነው‼     ~~~~//~~~~ዛሬ በሐምሌ 25 ቀን 2018 ዓ.ም ህወሓት ባወጣው መግለጫ የትግራይን ህዝብ ዋሽቷል፣ ለትግራይ ህዝብ ያለውን ን...
01/08/2026

"ጅራፍ እራሱ ገርፎ እራሱ ይጮሃል" ማለት አሁን ነው‼
~~~~//~~~~
ዛሬ በሐምሌ 25 ቀን 2018 ዓ.ም ህወሓት ባወጣው መግለጫ የትግራይን ህዝብ ዋሽቷል፣ ለትግራይ ህዝብ ያለውን ንቀትም በአደባባይ በራሱ አንደበቱ መስክሯል።

ህውሓት ዛሬ በበረከትና በሽረሪና በኩል ትንኮሳ ካደረገ በኋላ "ጅራፍ እራሱ ገርፎ እራሱ ይጮሃል" እንዲሉ መንግሥት ጦርነት ከፈተብኝ ሲል አሹፏል። አርሚ 70 ብለው የሚጠሩት ይህ የትህነግ ጨ:ፍ:ጫ:ፊ ኃይል ተንኩሶ ወደ ኋላ መሸሹም ተሰምቷል።

ሸረሪና ❗️🦁ድል አድራጊው ጥቁር አንበሳ ሸረሪና ላይ በድል እያገሳ ነው [የሸረሪና ምሽግ በወገን እጅ ገብቷል]። አዳሩን የድል ዜና አዘጋጅቶ ለላኪዎቹና ለደጋፊዎቹ የብስራት ዜና ለመናገር ጠ...
01/08/2026

ሸረሪና ❗️

🦁

ድል አድራጊው ጥቁር አንበሳ ሸረሪና ላይ በድል እያገሳ ነው [የሸረሪና ምሽግ በወገን እጅ ገብቷል]። አዳሩን የድል ዜና አዘጋጅቶ ለላኪዎቹና ለደጋፊዎቹ የብስራት ዜና ለመናገር ጠዋት 12፡00 ሰዓት በጀግናው የኢትዮጵያ ጦር ሰራዊት ላይ ጥቃት የከፈተው የፈርዖን ዘበኛ ምላሹ ታምራዊ ሆኖበት በደምብ ሲቀ'ጠቀጥ የድል ዜናውን ወርውሮ የድረሱልኝ ጥሪ አሰምቷል።

የወገን ጦር የጥፋት ሴራ ሲጎነጎንበት የነበረውን የሸረሪና ምሽግና የሎጀስቲክስ ማዕከል ተቆጣጥሮ ለቀጣይ ስምሪት እየመከረ ነው።

በፅንፈኛው ወገን የደረሰውን ኪሳራ ከገብሬ ገብረመድህን (2G) የባሱ የጽንፈኛው አፈቀላጤዎች አቀናብረው ይነግሩን ዘንድ እንጠብቃለን።

የሸረሪና ግምባር መረጃ እንሆ በዚህ ተደምድሟል !!

"ሀገር የማን ናት? የዜጎች ወይስ የብሔር ብሔረሰቦች?"🔴🔴🔴🔴🔴🔴🔴🔴🔴🔴🔴🔴🔴በሀገራዊ ምክክር ላይ በሀገር ግንባታ ንዑስ ቡድን ላይ ተመድቤ ዉይይት ጀመርን።የመጀመሪያው የዉይይታችን ጥያቄ "ሀ...
27/07/2026

"ሀገር የማን ናት? የዜጎች ወይስ የብሔር ብሔረሰቦች?"
🔴🔴🔴🔴🔴🔴🔴🔴🔴🔴🔴🔴🔴
በሀገራዊ ምክክር ላይ በሀገር ግንባታ ንዑስ ቡድን ላይ ተመድቤ ዉይይት ጀመርን።የመጀመሪያው የዉይይታችን ጥያቄ "ሀገር የማን ናት? የዜጎች ወይስ የብሔር ብሔረሰቦች? "የሚል ነበር። እናንተም በጉዳዮ ላይ ትነጋገሩበት ዘንድ ይህችን ጽሁፍ አጋራሁዋችሁ።ጽሁፉም ሆነ ሀሳቡ የምክክር ኮሚሽኑ ሳይሆን የግል ነው።መልካም ንባብ።

"ሀገር የማንናት?" የሚለው ጥያቄ በኢትዮጵያ ፖለቲካ ውስጥ እስካሁን እልባት ያላገኘና ትልቅ ክርክር የሚያስነሳ መሠረታዊ አጀንዳ ነው።

የሀገር ባለቤትነትን "በዜግነት ብቻ" ወይም "በብሔር ብቻ" ብሎ በአንድ ወገን መወሰን አደገኛ መሆኑን መገንዘብ ያስፈልጋል።

የኢትዮጵያ ሕገ-መንግሥት መግቢያ የሀገሪቱን ሉዓላዊ ሥልጣንና ባለቤትነት ለ«ብሔር፣ ብሔረሰቦች እና ሕዝቦች» ብቻ መስጠቱ በሀገረ-መንግሥት ግንባታውና በእኩልነት ላይ መዋቅራዊ ችግሮችን ፈጥሯል። ይህን አካሄድና የሚያስከትለውን ተጽዕኖ በሦስት ዋና ዋና ነጥቦች ከፍሎ ማየት ይቻላል፦

1. የእምነት ማኅበረሰቦችን መዋቅራዊ በሆነ መንገድ ማግለል
🔴🔴🔴🔴🔴🔴🔴🔴🔴🔴🔴🔴

የሕገ-መንግሥቱ መነሻ ብሔርን ብቻ ማዕከል ያደረገ በመሆኑ፣ የሀገሪቱን ታሪካዊና ማኅበራዊ መሠረት ለሆኑት ሃይማኖቶች ሕገ-መንግሥታዊ ዕውቅና ሳይሰጥ ቀርቷል። ይህ አካሄድ በመላ ሀገሪቱ የተበተኑ ትልልቅ የእምነት ማኅበረሰቦች (ለምሳሌ እንደ ሙስሊሙ ማኅበረሰብ ያሉ) በሕግ እንደ አንድ ትልቅ ማኅበራዊ ኃይል ተቆጥረው በሀገር ግንባታው ውስጥ መዋቅራዊ ጥቅሞቻቸውን እንዳይደራደሩና የባለቤትነት ቦታ እንዳይኖራቸው አድርጓቸዋል።

ሀገርን የብሔር ብሔረሰቦች ስብስብ ብቻ አድርጎ መሳል፣ የሙስሊሙን ማኅበረሰብ ሁለንተናዊ ሃይማኖታዊና ማኅበራዊ አንድነት (ኡማህ) በቋንቋ ከፋፍሎ ተጽዕኖውን ያዳክመዋል።

2. ዜግነትን ማዳከምና መብትን ከመሬትና ከብሔር ጋር ማያያዝ
⭕⭕⭕⭕⭕⭕⭕⭕⭕⭕⭕⭕⭕

የአሁኑ የብሔር ፌዴራሊዝምና ሕገ-መንግሥታዊ መዋቅር የሰዎችን መብት ከመሬትና ከብሔር ማንነት ጋር ብቻ አያይዞታል። ሀገርን በዜግነት ማዕቀፍ ብቻ ስንተረጉማት ደግሞ በታሪክ አጋጣሚ የባህልና የሃይማኖት የበላይነት የነበራቸው ወገኖች የራሳቸውን ማንነት እንደ ብቸኛ የኢትዮጵያዊነት መለኪያ አድርገው እንዲጭኑና ሌሎችን ወደ ዳር እንዲገፉ መንገድ ይከፍታል።

በሌላ በኩል ደግሞ የሀገር ባለቤትነትን በብሔር ላይ ብቻ መገደቡ፣ ዜጎች ከራሳቸው የብሔር ክልል ውጭ በሚኖሩበት ጊዜ ሙሉ የእኩል ዜግነት መብታቸው እንዳይከበርና እንደ ሁለተኛ ዜጋ እንዲገፉ ዋነኛ ምክንያት ሆኗል።

3. ታሪካዊ የሃይማኖት ጭቆናዎችን ዕውቅና አለመስጠት
📕📕📕📕📕📕📕📕📕📕📕📕📕

በሕገ-መንግሥቱ መግቢያ ላይ ብሔርን ብቻ የባለቤትነት ምንጭ ማድረግ፣ በኢትዮጵያ ታሪክ ውስጥ የነበረውን ጥልቅ የሃይማኖት ጭቆናና መገለል ዕውቅና እንዳያገኝ አድርጎታል።

ዘላቂ የመፍትሔ አቅጣጫዎች፦ የአራቱ ምሰሶዎች አስፈላጊነት
✅✅✅✅✅✅✅✅✅✅✅✅✅

እውነተኛ አካታችነትና ሀገራዊ ስምምነት እንዲኖር ከተፈለገ፣ የወደፊቱ ሕገ-መንግሥት ከብሔር ጠባብነት ወጥቶ በሀገሪቱ የነበረውን የታሪክ የሃይማኖት ጭቆና ማመንና ለሞራላዊ እሴቶች መገዛት አለበት። የሀገር ባለቤትነትን በሚከተሉት አራት መሠረታዊና እርስ በእርስ በሚደጋገፉ ምሰሶዎች ላይ መገንባት ያስፈልጋል፦

1) ዜግነት
⭕⭕⭕⭕

እያንዳንዱ ሰው በሕግ ፊት እኩል የሚሆንበት፣ ሰብዓዊና ፖለቲካዊ መብቱ የሚከበርበት፣ ንብረት የማፈራትና በየትኛውም የሀገሪቱ ክፍል የመንቀሳቀስና የመኖር ሙሉ ነፃነቱ የሚረጋገጥበት የጋራ መሠረት ነው።

2) ብሔር/ብሔረሰቦች
✅✅✅✅✅✅✅

ማኅበረሰቦች ታሪካቸውን፣ ባህላቸውንና ቋንቋቸውን ጠብቀው እንዲያሳድጉና በራሳቸው አካባቢ ራስን በራስ የማስተዳደር መብታቸው የሚከበርበት ምሰሶ ነው።

3) የእምነት ማኅበረሰቦች
♦♦♦♦♦♦♦♦

ሃይማኖት የግል ጉዳይ ብቻ ሳይሆን የሕዝቦችን ማኅበራዊ መሠረት፣ የሞራል እሴትና ታሪካዊ ሥልጣኔ የገነባ ትልቅ አካል ነው። የእምነት ተከታዮች የሀገሪቱ ታሪክና ባህል ባለቤቶች በመሆናቸው በሕገ-መንግሥታዊ ሥርዓቱ ውስጥ ተገቢውን ዕውቅና ማግኘት አለባቸው።

4) ጾታ
🔺🔺🔺
ሴቶች የሕዝቡን ግማሽ ቁጥር ይይዛሉ። ያለእነሱ እውነተኛ ባለቤትነትና ውሳኔ ሰጪነት ሀገር ሙሉ ልትሆን አትችልም። በመሆኑም የሴቶችን ማኅበራዊና ኢኮኖሚያዊ አቅም ማጎልበትና ፍትሕን ማረጋገጥ የዚሁ ባለቤትነት አካል ነው።

ማጠቃለያ
💢💢💢💢

ኢትዮጵያ የግለሰብ ዜጎች ሰብዓዊና ፖለቲካዊ መብቶች የሚከበሩባት፣ በተመሳሳይ ጊዜ ደግሞ የብሔሮች፣ የሴቶችና የእምነት ማኅበረሰቦች ማንነት የሚጠበቅባትና የሚጎለምስባት የጋራ መኖሪያችን ልትሆን ይገባል። እውነተኛ ሀገራዊ ስምምነት ሊመጣ የሚችለው ማንኛውም ዜጋ በሃይማኖቱም ሆነ በብሔሩ ሳይገለል ሙሉ የእኩል ዜግነት መብቱ ሲረጋገጥ ብቻ ነው።

  ዛሬ ሐምሌ 20/2028የምስራቅ ዕዝ ኮር በፅንፈኛው ቡድን ላይ በወሰደው የተቀናጀ የፀረ-ሽምቅ ስልት ከፍተኛ ጉዳት ማድረሱ ተገለፀ። የምስራቅ ዕዝ ኮር ሠራዊት በአማራ ክልል ምዕራብ ጎጃም...
27/07/2026


ዛሬ ሐምሌ 20/2028

የምስራቅ ዕዝ ኮር በፅንፈኛው ቡድን ላይ በወሰደው የተቀናጀ የፀረ-ሽምቅ ስልት ከፍተኛ ጉዳት ማድረሱ ተገለፀ።

የምስራቅ ዕዝ ኮር ሠራዊት በአማራ ክልል ምዕራብ ጎጃም ዞን ደጋ ዳሞት ዙሪያ ተፈጥሯዊና ሰው ሰራሽ መሰናክሎችን ተቋቁሞ በወሰደው ጠንካራና የተቀናጀ እርምጃ በፅንፈኛዉ ቡድን ላይ ከፍተኛ ምት በማሳረፍ ሰብአዊና ቁሳዊ ጉዳት ማድረሱን የኮሩ አዛዥ ብርጋዲየር ጄኔራል አዲሱ መሀመድ አስታውቀዋል።

ኮሩ ካደረሰው ሰብዓዊና ቁሳዊ ጉዳት በተጨማሪ የታገቱ የህዝብ መኪናዎችን ከነአሽከርካሪዎቻቸው እና ፅንፈኛው ከህዝብ አስገድዶ የዘረፈውን እህል እንዲሁም ሌሎች የሎጅስቲክስ ቁሳቁሶችን ማስመለስ መቻሉን ተናግረዋል።

የኮሩ ዋና አዛዥ ብርጋዲየር ጀኔራል አዲሱ መሀመድ እንደገለፁት ፤ በዚህ ድንገተኛ የጸረ-ሽምቅ ስምሪት ፣ የፅንፈኛው ቡድን የሚተማመንበት ዋነኛ የሰው ሀይሉ ተመትቶበታል፡፡ ከዚህ በፊት ንጹሃን ዜጎችን በማገት ፣ አሽከርካሪዎችን በማስፈራራትና ከአርሶ አደሩ እህልና ንብረት በመዝረፍ የአካባቢውን ማህበረሰብ ሲያሰቃይ ቢቆይም ፣ የኮሩ ሠራዊት ማንኛውንም የደጋና የቆላ ተፈጥሯዊ መሰናክል እንዲሁም የጠላትን ምሽጎች በመስበር የፅንፈኛውን አከርካሪ መስበር ችሏል፡፡

በዋሸራ ፣ ጫት ዋርካ ፣ ሀሙሲት፣ አስተርዮ ዋይፍይ ፣ ልጅየጉስ ከቸች ቦታዎች በተደረገው አሰሳና የተቀናጀ ኦፕሬሽን በርካታ የፅንፈኛው አባላት የተደመሰሰና የተማረከ ሲሆን ፣ ቡድኑ ለጥፋት ተግባሩና ለሎጅስቲክስ ይጠቀምባቸዉ የነበሩ ቁሳቁሶች በሠራዊቱ ቁጥጥር ስር ውለዋል። እንደ ጤፍና ስንዴ የመሰለ የተከዘነ እህልም ተይዟል።

የታገቱ ተሽከርካሪዎችና አሽከርካሪዎች ነፃ በማውጣት ፅንፈኛው ቡድን ገንዘብ ካላመጣችሁ አንለቅም ብሎ አግቷቸው የነበሩ የከባድ መኪና (አይሱዙ፣ ሲኖትራክ) እና የህክምና አምቡላንስ ጨምሮ በርካታ የሃርድቶፕ ቲዮታ ላንድ ክሮዘር ተሽከርካሪዎችን ከፅንፈኛው እጅ ማሥመለስ እንደተቻለም አዛዡ ገልፀዋል።

የተለያዩ ዓይነት በርካታ መሳሪያዎች፣ የሎጅስቲክስ ቁሳቁሶች ፣ ጄኔሬተር ፣ ቦንብ ፣ድጅታል ካሜራ ፣ የብሬን ፣ የክላሽና የድሽቃ ጥይት ፣ የወገብና የደረት ትጥቆች ፣ የኮንትሮባንድ ሲጋራዎች ፣ መድሃኒቶች ፣ የኤሌክትሮኒክስና የፎርጅድ ዕቃዎች፣ የፅንፈኛው ቡድን ለእንቅስቃሴ ይጠቀምባቸው የነበሩ ሞተር ሳይክሎች፣ የምግብ ዘይት ፣ የመኪና ነዳጅ ፣ በኮሩ ሠራዊት እጅ ገብቷል።

ብርጋዲየር ጀኔራል አዲሱ መሀመድ ፣ ፅንፈኛው ቡድንና ተላላኪዎቹ ሰላምን እስካልመረጡ ድረስ ሠራዊቱ የትኛውንም አይነት አስቸጋሪ ሁኔታዎችን ተቋቁሞ የህዝብን ሰላም የማስከበር ፣ የህግ የበላይነትን የማረጋገጥና የጥፋት ኃይሎችን የማጽዳት ግዳጁን አጠናክሮ እንደሚቀጥል ተናግረዋል!

ወደ ቆቦ አቅጣጫ‼የህወሃት ታጣቂዎች ከአላማጣ ወደ ቆቦ በባቡሩን መንገድ እንቅስቃሴ መጀመራቸው ተሰምቷል።ህውሃት በዚህ ክረምት ግጭት ለመቀስቀስ ተደጋጋሚ ፉከራዎች ሲያሰማ ቆይቷል።ጠቅላይ ሚን...
27/07/2026

ወደ ቆቦ አቅጣጫ‼

የህወሃት ታጣቂዎች ከአላማጣ ወደ ቆቦ በባቡሩን መንገድ እንቅስቃሴ መጀመራቸው ተሰምቷል።

ህውሃት በዚህ ክረምት ግጭት ለመቀስቀስ ተደጋጋሚ ፉከራዎች ሲያሰማ ቆይቷል።

ጠቅላይ ሚንስትር አብይ ሰኔ 30/2018 በፓርላማ ቀርበው"እኛ ስላልፈለግን እንጅ ህውሃት ወደ ጦርነት እንድንገባ በተደጋጋሚ ትንኮሳ እየፈፀመ ነው።በቂ ምክንያት ነበረን"በማለት ሂደቱን ገልፀው ነበር።

ክረምትን እየጠበቀ የሚቀሰቀሰው ግጭት ዘንድሮ ኤርትራን እንደሚጨምር ሲጠቀስ ነበር።የዛሬ የታጣቂዎቹ እንቅስቃሴ ጭፍራን ኢላማ ያደረገ ትንኮሳ ሊሆን እንደሚችል ምንጮቼ ጠቁመዋል።

በጎንደር ፋኖ አደረጃጀት ውስጥ የተፈጠረው ውጥረት‼️በጎንደር ፋኖ አደረጃጀት ውስጥ ተሰንቅሮ ለህውሃት ከማሸርገድ የማይቆጠበውና መቸም ታጥቦ የማይጠራው ሳሙኤል ባለድል ላይ ሃብቴ ወልዴ የሚያ...
27/07/2026

በጎንደር ፋኖ አደረጃጀት ውስጥ የተፈጠረው ውጥረት‼️

በጎንደር ፋኖ አደረጃጀት ውስጥ ተሰንቅሮ ለህውሃት ከማሸርገድ የማይቆጠበውና መቸም ታጥቦ የማይጠራው ሳሙኤል ባለድል ላይ ሃብቴ ወልዴ የሚያደርገውን ዘመቻ አጠናክሮ በመቀጠል ይህን ባንዳ ከቀጠናው ነቅሎ በማስወጣት ለትግሉ ውለታ ሊሰራ ይገባል ።

የትግሉን ሕሊናዊ ጥራት ለማስጠበቅና የሕዝቡን መስዋዕትነት ለህውሓት ፍላጎት አሳልፈው የሚሰጡ ተከፋይ ሰላዮችን ከአደረጃጀቱ በፍጥነት ማጽዳት ወሳኝ ነው፡፡

እርስ በእርስ ለመጣላት የቀጠረው ጽምዶ !ጭድ ፣ቤንዚንና እሳት ለመተባበር ተጣምደዋል። እነዚህ ያሰቡትን ጥፋት ሳያደርሱ መጨረሻቸው በተቀመጡበት  እርስ በእርስ መጠፋፋት ነው።ቀድሞም ላይሆን ...
27/07/2026

እርስ በእርስ ለመጣላት የቀጠረው ጽምዶ !

ጭድ ፣ቤንዚንና እሳት ለመተባበር ተጣምደዋል። እነዚህ ያሰቡትን ጥፋት ሳያደርሱ መጨረሻቸው በተቀመጡበት እርስ በእርስ መጠፋፋት ነው።

ቀድሞም ላይሆን የተጣመዱት ጠላ #ታ #ችንን የኢትዮጵያን መንግስት ከጣልን በኋላ እርስ በእርስ መጣላታችን አይቀርም እያሉን ነው።

ህወሀት፣ ሻዕቢያና ፋኖ ጄኖሳይደር ናቸው፣መንግስትን ከጣልን በኋላ ከእነሱ ጋር የምናወራርደው ሂሳብ አለ ብሎ እንግርግሪያ ይዟል።

ጽምዶ የኢትዮጵያን መንግስት ለመጣል ቀርቶ ለማንገዳገድ የሚያስችል አቅም ባይኖረውም፣ እርስ በእርስ ለመጣላት የያዘው ቀጠሮ ግን በቅርቡ እንደሚሳካላቸው አንጠራጠርም !

Address

Sheger
Addis Ababa
ONE

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Digital Amhara. posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to Digital Amhara.:

Shortcuts

Share