Berekah Tube

Berekah Tube የነቃ ትውልድ!

በአዲስ አበባና በሌሎች የኢትዮጽያ ክፍሎች ለሥራ ተሰማርተው የሚገኙ ወጣቶች በግዳጅ ለውትድርና እየተመለመሉ መሆናቸውን ተናገሩ። ******በአካባቢያችን ባለው የሥራ ዕድል ማጣት ምክንያት ቀዬ...
27/04/2025

በአዲስ አበባና በሌሎች የኢትዮጽያ ክፍሎች ለሥራ ተሰማርተው የሚገኙ ወጣቶች በግዳጅ ለውትድርና እየተመለመሉ መሆናቸውን ተናገሩ።
******
በአካባቢያችን ባለው የሥራ ዕድል ማጣት ምክንያት ቀዬአችንን ለቀን ለመውጣት ተገደናል ያሉን ለሚዲያችን አቤቱታ ያቀረቡ ወጣቶች ያለ ፈቃዳቸው በግዳጅ ለውትድርና እየተመለመሉ መሆናቸውን አቤቱታ አሰምተዋል።

በአዲስ አበባ ከተማ በግንባታ ሥራ ላይ ተሰማርተው እንደሚገኙ የተናገሩ እነዚህ ወጣቶች፣ ወደ ሥራ ስሄዱና ስመለሱ ሚሊሻ ነን ያሉ ሰዎች አፍነው በመውሰድ ደህንነቱ ያልተጠበቀ ካምፕ ውስጥ እንደሚያጉሯቸው በመግለጽ ለሥራ ወቶ መግባት ስቃይ ሆኖብናል በማለት እየደረሰባቸው የሚገኘውን ምሬት ተናግረዋል።

‛‛ሚሊሻዎች መንገድ ላይ አይናቸውን ያየውን ሰው ሁሉ ያፍናሉ፣ ይሁን እንጂ በተለይም ከሲዳማ የመጣን ወጣቶች በርከት ብለን በምንገኝበት የግንባታ ጣቢያዎች የተለየ ኢላማ አድርገው በርካታ ጓደኞቻችንን አፍነው ወስደዋቸው‛‛ ሲሉ አክለዋል።

በተከራዩት አንድ ክፍል ውስጥ ሰብሰብ ብለው እንደሚኖሩ የነገሩን ወጣቶቹ በዚህ ምክንያት ሚሊሻዎቹ ማታ ቤት ሰብረው እየገቡ ጭምር ጓደኞቻቸውን እያፈሱባቸው እንደሚገኙ ነው ሚዲያችን የገለጹት።

እስራኤል ወደ ጋዛ ማንኛውም እርዳታ እንዳይገባ ካገደች አንድ ወር አለፈ በተባበሩት መንግሥታት የሚደገፉ ዳቦ ቤቶች በሙሉ መዘጋታቸው ተገለፀ። በጋዛ የሚገኙ ገበያዎችም ቢሆን አትክልቶች አይገ...
04/04/2025

እስራኤል ወደ ጋዛ ማንኛውም እርዳታ እንዳይገባ ካገደች አንድ ወር አለፈ

በተባበሩት መንግሥታት የሚደገፉ ዳቦ ቤቶች በሙሉ መዘጋታቸው ተገለፀ። በጋዛ የሚገኙ ገበያዎችም ቢሆን አትክልቶች አይገኙባቸውም። ሆስፒታሎች ለታካሚዎቻቸው የሕመም ማስታገሻዎች እና ፀረ ተህዋሲያንን መድሃኒት (አንቲባዮቲኮችን) በፈረቃ እያከፋፈሉ መሆኑን ተናግረዋል።

እስራኤል ከሃማስ ጋር ለ18 ወራት እያካሄደችው ባለው ጦርነት ውስጥ የተጣለ ረዥሙ እገዳ ነው። በዚህ ሳምንት በተከበረው የዒድ አል-ፈጥር በዓል ላይ ብዙ ጋዛውያን "ርቦናል" ሲሉ ተሰምቷል።

ከበይተ ላሂያ የተፈናቀለችው ኡሙ አሊ ሃማድ በጋዛ ከተማ ምግብ እየፈለገች መሆኑን ለቢቢሲ ገልጻ "ይህ ለእኛ ከመቼውም ጊዜ ይበልጥ የከፋው ዒድ ነበር" ብላለች። "መብላትም ሆነ መጠጣት አልቻልንም። መዝናናት አልቻልንም፤ ደክሞናል።"
"ከእንግዲህ እንደ ቲማቲም፣ ስኳር ወይም ዘይት ያሉ ነገሮች ማግኘት አንችልም። አይገኙም። በቀን አንድ ምግብ የማገኘው በመከራ ነው። አሁን የምግብ ድጋፍ የሚያደርጉ ድርጅቶች የሉም" ስትል አክላለች።

የእፎይ ጉዳይ ከምን ደረሰ?''''''''''''''''''''''''''''''''''''''''''''''''''''''''''''''''''''''''''''''በነብዩ ሙሀመድ "ﷺ" ላይ ጸያፍ ቃላትን...
03/04/2025

የእፎይ ጉዳይ ከምን ደረሰ?
''''''''''''''''''''''''''''''''''''''''''''''''''''''''''''''''''''''''''''''
በነብዩ ሙሀመድ "ﷺ" ላይ ጸያፍ ቃላትን በመሰንዘር ድንበር ያለፈውን ግለሰብ አስመልክቶ ያለው የህግ ሒደት ምን ላይ ደርሷል?

ከሳምንታት በፊት በነብዩ ሙሀመድ "ﷺ" ላይ ድንበር ያለፈውን "እፎይ" የተባለ ግለሰብ መጅሊሱ በህግ ክፍሉ በኩል ክስ መመስረቱን መግለፁ ይታወሳል።

ይህንኑ ጉዳይ አስመልክቶ ሀሩን ሚዲያ የክሱ ሂደት ምን ላይ ደረሰ? ስንል ጠይቀናል። የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት ዋና ስራአስኪያጅ ሀጂ ከማል ከሀሩን ሚዲያ ጋር በነበራቸው ቆይታ በሰጡት ምላሽ የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት በነብዩ ሙሀመድ ላይ ድንበር ያለፈውን ግለሰብ አስመልክቶ በህግ ክፍሉ በኩል ምስክሮችን በማጠናከር ክስ መመስረቱን ገልጸዋል።

ይሁንና ግለሰቡ እስካሁን በህግ ቁጥጥር ስር አለመዋሉ የተገለፀ ሲሆን መጅሊሱ ግለሰቡ በህግ ቁጥጥር ስር እስከሚውል ክትትሉን እንደሚቀጥል ገልጸዋል።

በነብዩ ሙሀመድ "ﷺ" ላይ ድንበር የሚያልፉ ግለሰቦችን ፈፅሞ እንደማይታገስ የገለፀው ጠቅላይ ምክር ቤቱ መሰል ጥፋት በሚፈጽሙ ግለሰቦች ላይ በህግ አግባብ የጀመረውን እርምጃ እንደሚቀጥል ገልጸዋል።

ክስ የተመሰረበት ግለሰብ ክሱ ተጠናቅሮ ለፖሊስ ቀርቦ የእስር ማዘዣ የወጣ ቢሆንም እስካሁን በቁጥጥር ስር አለመዋሉ ይታወቃል። ©ሀሩን ሚዲያ

በጊንጭ ከተማ የመስጂድ መሬት በሀይል ለመውረር ያሰቡ ሀይሎች በኡስታዞች ላይ ድብደባ መፈፀማቸው ተሰማ! መጋቢት 25/2017በኦሮሚያ ክልል ጊንጪ ከተማ የሙስሊሙ ማህበረሰብ የመስጅድ እና የመ...
03/04/2025

በጊንጭ ከተማ የመስጂድ መሬት በሀይል ለመውረር ያሰቡ ሀይሎች በኡስታዞች ላይ ድብደባ መፈፀማቸው ተሰማ! መጋቢት 25/2017

በኦሮሚያ ክልል ጊንጪ ከተማ የሙስሊሙ ማህበረሰብ የመስጅድ እና የመቃብር ስፍራ የሆነ መሬቱን በሀይል ለመውረር የሞከሩ አካላቶች ኡስታዞች ላይ ድብደባ መፈፀማቸውን ከስፍራው ለሀሩን ሚዲያ የደረሰው መረጃ ያመላክታል።

ከ40 አመት በፊት ጀምሮ የአካባቢው ሙስሊም ማህበረሰብ እየተጠቀመበት የሚገኘው ህጋዊ የሆነ የሙስሊሙ ማህበረሰብ የመቃብር ቦታ የአካባቢው መጅሊስም ሆነ የመስጅዱ ኮሚቴዎች ባላወቁት መልኩ አጥሩ እንዲፈርስ መደረጉን ገልፀዋል።

ከዚህ በተጨማሪም ያለምንም ደብዳቤ ግሬደር ይዞ በመምጣት ህጋዊ የመስጅድ እና የመቃብር ቦታ እንዲቆፈር ማድረጋቸው ተገልጿል። ይህንኑ ጉዳይ ለከተማው ከፍተኛ አመራሮች በማሳወቅ የእግድ ደብዳቤ ያስፃፉ የመስጅድ ኡስታዞች ላይ ድብደባ መፈፀሙ ነው የተገለፀው።

ከአዲስአበባ በቅርብ ርቀት በምትገኘው ጊንጭ ከተማ በሙስሊሙ ማህበረሰብ ላይ ከፍተኛ በደል እየተፈፀመባቸው መሆኑን የሚገልፁት የአካባቢው ሙስሊሞች የሚመለከተው አካል በአስቸኳይ እልባት እንዲሰጣቸው ጠይቀዋል። © ሀሩን ሚዲያ

ወሎ ኮምቦልቻዎች አደባባያቸውን በዚህ መልኩ አሸብርቀውታል 🥰🥰🥰
30/03/2025

ወሎ ኮምቦልቻዎች አደባባያቸውን በዚህ መልኩ አሸብርቀውታል 🥰🥰🥰

የትግራይ ክልል ትምህርት ቢሮ በአክሱም ትምህርት ቤቶች የተጣለው የሂጃብ እገዳ አዲስ መመሪያ ያልወጣበት በመሆኑ በነበረው  የአለባበስ ሥርዓት እንዲቀጥል አሳስቧል!- ካለምንም መመሪያ ይህን ...
31/12/2024

የትግራይ ክልል ትምህርት ቢሮ በአክሱም ትምህርት ቤቶች የተጣለው የሂጃብ እገዳ አዲስ መመሪያ ያልወጣበት በመሆኑ በነበረው የአለባበስ ሥርዓት እንዲቀጥል አሳስቧል!

- ካለምንም መመሪያ ይህን የህግ ጥሰት በፈፀሙ አካላት ላይ ግን ቢሮው ምንም ያለው ነገር የለም

ሀሩን ሚድያ ታህሳስ 22/2017

የትግራይ ክልል ትምህርት ቢሮ እንደገለፀው በትምህርት ቤቶች ውስጥ ያሉ የተማሪዎች የአለባበስ ሥርዓት መመሪያና አሰራር እንዳለ ጠቅሷል። በዚህም በአክሱም ውስጥ የሚገኙ ሁሉም ትምህርት ቤቶች በተለመደው አሰራር መሰረት እየሰሩ ባሉበት ወቅት በአክሱም አጠቃላይ 2ኛ ደረጃ ት/ቤት ሂጃብ መከልከሉን እና ይህ እንዲስተካከል ጥያቄ ቀርቦላቸው እንደነበር ማወቁን ገልጿል።

ይህንን ችግር ለመፍታት ከትግራይ ትምህርት ቢሮ ከተላኩት ባለሙያዎች ጋር ስምምነት ላይ ቢደረስም የትግራይ እስልምና ጉዳዮች ከፍተኛ ምክር ቤት በ17/04/2017 በደብዳቤ ቁጥር ኢ1/060/03/17 በፃፈው መሰረት በአክሱም ከተማ ሙስሊም ተማሪዎች ችግር እንዳልተፈታ ቅሬታ መቅረቡን ገልጿል

ስለዚህ በዚህ ጊዜ የተለየ አዲስ መመሪያ እስካልወጣ ድረስ አዲስ እገዳም ሆነ አዲስ ጥያቄ (Demand) ተቀባይነት የሌለው በመሆኑ በነበረው የአለባበስ ስርዓት እንዲቀጥል ሲል በደብዳቤ አሳውቋል።

የትግራይ ክልል ትምህርት ቢሮ በአክሱም ትምህርት ቤቶች ያለምንም መመሪያ የሂጃብ ክልከላና መጉላላት በፈጸሙ አካላት ላይ ግን ምንም ያለው ነገር የለም።

© ሀሩን ሚድያ

በጫጉላ ምሽት ባለቤቱን በአሰቃቂ ሁኔታ የገደለው ተከሳሽ የሞት ፍርድ ተፈረደበት! ታህሳስ 16/2017 ዓ.ልበጫጉላ ምሽት ባለቤቱን በአሰቃቂ ሁኔታ የገደለው ተከሳሽ የሞት ፍርድ የተፈረደበት ...
25/12/2024

በጫጉላ ምሽት ባለቤቱን በአሰቃቂ ሁኔታ የገደለው ተከሳሽ የሞት ፍርድ ተፈረደበት! ታህሳስ 16/2017 ዓ.ል

በጫጉላ ምሽት ባለቤቱን በአሰቃቂ ሁኔታ የገደለው ተከሳሽ የሞት ፍርድ የተፈረደበት ሲሆን የሀላባ ዞን ከፍተኛ ፍርድ ቤት በሀላባ ፍትህ መምሪያ አቃቤ ህግ የቀረበለት መዝገብ ሲመረምር ቆይቶ ሟች ሪባቴ ያሲንን በአሰቃቂ ሁኔታ የገደለው ተከሳሽ ሱልጣን ሸ/ሙንዲኖ በሞት እንዲቀጣ ውሳኔ ሰጥቷል።

የሀለባ ዞንከፍተኛ ፍርድ ቤት በዛሬው ዕለት 1ኛ ተከሳሽ ሱልጣን ሙንዲኖ በሞት እንዲቀጣ ሲወስን ከ2ኛ -7ኛ ያሉትን ተከሳሾችን ደግሞ (3ኛ ተከሳሽ ሲቀር) ሌሎቹን ተከሳሾች በ6 ወር ቀላል እስራት እንዲቀጡ ወስኗል።
በ3ኛ ደረጃ ስሙ የተጠቀሰውን ተከሳሽ ደግሞ ክሱ ጥፋተኛ ስለማያደርገው ፍርድ ቤቱ በነፃ አሰናብቶቷል።

8ኛ ተከሳሽ የጨቅላ ህፃን እናት መሆኗን ከግምት ውስጥ በማስገባት የ2 ዓመት የፈተና ጊዜ ተሰጥቷት ከማንኛውም የወንጀል ተግባር ታቅባ እንዲትቆይ የተወሰናባት ሲሆን የ6 ወራት ቀላል የእስር ውሳኔው ለሁለት ዓመት ታግዶ እንዲቆይ ብይን ሰጥቷል።

የሟች ወንድሞችን በፍርዱ ውሳኔ ዙሪያ ስሜታቸውን እንዲያጋሩን የጠየቅን ሲሆን "እህታችን በህይወት ባትመለስም የዛሬው ውሳኔ ሪባቴ ዛሬ የተወለደች ያህል እንዲሰማን አድርጓል" ሲሉ ገልጸዋል። በመጨረሻም በእህታቸው ሞት ላዘኑ እና ላጽናኗቸው ሁሉ ምስጋናቸውን አቅርበዋል።

- ችሎቱ ላይ የተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎች የተካፈሉ ሲሆን የሀሩን ሚዲያ ደቡብ ስቱዲዮ በስፍራው ተገኝቶ ያጠናቀረው ዘገባ በተከታይ ወደእናንተ የሚደርስ ይሆናል።

በጎንደር ዙሪያ ወረዳ እንፍራንዝ ተብሎ በሚጠራው አከባቢ 4 ሙስሊሞች መገደላቸውና በርካቶች መፈናቀላቸው ተሰምቷል!በአማራ ክልል የተለያዩ አካባቢዎች በሙስሊሞች ላይ ያነጣጠሩ ግዲያ አፈና እና...
21/04/2024

በጎንደር ዙሪያ ወረዳ እንፍራንዝ ተብሎ በሚጠራው አከባቢ 4 ሙስሊሞች መገደላቸውና በርካቶች መፈናቀላቸው ተሰምቷል!

በአማራ ክልል የተለያዩ አካባቢዎች በሙስሊሞች ላይ ያነጣጠሩ ግዲያ አፈና እና እገታ ቀጥሏል።ከሰሞኑ በጎንደር ዙሪያ ወረዳ እንፍራንዝ ተብሎ በሚጠራው አከባቢ 4 ሙስሊሞች መገደላቸው በርካታ ሰዎች ደግሞ ከቀያቸው መፈናቀላቸው ተገልጿል። ህይወታቸው ካለፉት ሰዎች ሁለቱ በተለምዶ ውሻ ጥርስ ተብሎ በሚጠራው ሀሪማ የሸይኽ ኢብራሂም መህሊ ደረሳዎች መሆናቸውን እንዲሁም አንድ ሙአዚንና አንድ የአከባቢው ነዋሪ መሆናቸው ተገልጿል።..
በአማራ ክልል በተለይ በጎንደር ከተማ የሚገኙ ሙስሊሞች በእምነታቸው ምክኒያት የሚደርስባቸው ጫና እና ጥቃት አመታትን ያስቆጠረ ቢሆንም ከሰሞኑ እንደ አዲስ በተጀመረው ጥቃት የእውቀት ማዕከል የሆኑ ሀሪማዎችን የማፈናቀል ስራ መሰራቱ ከአከባቢው ነዋሪዎች ያገኘነው መረጃ ያመላክታል።በዚህ ሂደትም በዋናነት የፈርቃ እና ደልዳሊት ሀሪማ የነበሩ በእያንዳንዳቸው እስከ 200 የሚቆጠሩ ደረሳዎችን ጨምሮ ማክሰኚት ተብሎ ወደሚጠራው አከባቢ መሸሻቸው ተረጋግጧል።..
ቀደም ሲል አከባቢውን ለቀው እንዲወጡ የተለያዩ ዛቻ እና ማስፈራሪያዎችን ሲያስተናግዱ መቆየታቸውን እና በተለምዶ ውሻ ጥርስ ተብሎ በሚጠራው ሀሪማ ሀሪማዬን አሳልፌ አልሰጥም በማለታቸው በተከፈተው ተኩስ የአራት ሰዎች ህይወት ማለፉ ተገልጿል።ይህ ሀሪማ እና በውስጡ የሚገኙ ሸይኽ እና ደረሳዎችን ጨምሮ አደጋ ላይ የሚገኙ ሲሆን በቁጥጥር ስር የዋሉ ሀሪማዎችም ክብራቸው ተደፍሮ የጦር ምሽግ መደረጋቸውን ከአከባቢው ነዋሪዎች ያገኘነው መረጃ ያስረዳል።..
በአማራ ክልል የሰሞኑን ሳይጨምር ባለፉት ስምንት ወራት ብቻ ከ80 በላይ ሙስሊሞች በክልሉ የተለያዩ አካባቢዎች በግፍ መገደላቸውን እና በ10 ሺዎች መፈናቀላቸውን በርካቶች መታገታቸውን የክልሉ መጅሊስ ባወጣው መግለጫ ማስታወቁ ይታወሳል።..
©ሀሩን ሚዲያ

የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ም/ቤት ፕሬዝዳንት የመሩት ልዑክ መቐለ ከተማ ገባ! ረቡዕ ጥር 29፣ 2016 የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት (መጅሊስ) ፕሬዝዳንት ሸይኽ ...
07/02/2024

የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ም/ቤት ፕሬዝዳንት የመሩት ልዑክ መቐለ ከተማ ገባ! ረቡዕ ጥር 29፣ 2016

የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት (መጅሊስ) ፕሬዝዳንት ሸይኽ ሐጅ ኢብራሂም ቱፋ የመሩት ልዑክ ዛሬ ረቡዕ ጥር 29፣ 2016 ትግራይ ክልል መቀመጫ መቐ ከተማ መግባቱ ታውቋል፡፡ የልዑካን ቡድኑ ዛሬ ወደ ከተማው ያደረገው ጉዞ በትግራይ ጦርነት ምክንያት የክልሉ ከፍተኛ ምክር ቤት በፌዴራል መጅሊስ ላይ ያቀረበውን ቅሬታ ካነሳ በኋላ የመጀመርያው ነው፡፡

የትግራይ ክልል እስልምና ጉዳዮች ምክር ቤት ጥር 16፣ 2016 አደረግኩት ባለው አስቸኳይ ጉባኤ፤ የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት ጥር 7፣ 2016 በጻፈው ደብዳቤ፤ በክልሉ ምክር ቤት ከዚህ ቀደም የቀረበውን ጦርነቱን ያለ ማውገዝ አካሄድ ስህተት እንደነበር አምኖ ይቅርታ በመጠየቁ መቀበሉን አሳውቆ ነበር፡፡

ይህንኑ ተከትሎ የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት ጥር 18፣ 2016 ባወጣው መግለጫ፤ የትግራይ እስልምና ጉዳዮች ምክር ቤት ያወጣውን ‹‹የአብሮነት መግለጫ በደስታ›› መቀበሉን ገልጧል፡፡

የፌደራል መጅሊሱ በዚሁ መግለጫ ላይ የትግራይ ክልል እስልምና ጉዳዮች ከፍተኛ ምክር ቤት በእስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት ማቋቋሚያ አዋጅ እና በምክር ቤቱ ደንብ እንደሚመራ አሳውቋል፡፡

ሊንኩን ተከትለው ተጨማሪ ያንብቡ https://ambadigital.net/2024/15776/

ከተባበርን እራሳችን ለማስከበር ከበቂ በላይ ነን!——————————————————አንዳንድ ግለሰቦች በተለየዩ ተቋማት ስር ተወሽቀው በተቋሙ ስም የግለል ፍላጎቶቻቸውን ሲያራምዱ ማየት የተለመደ ነ...
06/02/2024

ከተባበርን እራሳችን ለማስከበር ከበቂ በላይ ነን!
——————————————————

አንዳንድ ግለሰቦች በተለየዩ ተቋማት ስር ተወሽቀው በተቋሙ ስም የግለል ፍላጎቶቻቸውን ሲያራምዱ ማየት የተለመደ ነገር ሆኖ ቆይቷል። ጠያቂ ስለሌለ ተቋማቱም በስማቸው የተሰራን ሸፍጥ ከማስቆም ይልቅ በዝምታ ማለፍን መርጠው ኖረዋል። አሁን ግን መብቱንም ሆነ ግዴታውን የሚያውቅ ትውልድ ተፈጥሯል።

በተቋማት ስም የተቋማት ሰራተኞች የሚሰሯቸው ድንበር አለፍ ስህተት የግለሰቡ ብቻ ነው ብሎ እንዲታለፍ ተቋሙ በይፋ ይቅርታ መጠየቅ እና በስሙ ስህተት የሰራ ሰራተኛው ላይ እርምጃ ሊወስድ ግድ ነው።

አቢሲኒያ ባንክ ይህን ብልሃት የታከለበት እርምጃ መውሰዱ መልካም ነው። አሁንም ወደፊትም የጋራ በሆኑ ችግሮቻችን ላይ በጋራ መስራት ሊተኮርበት የሚገባ ጉዳይ ነው። የተሰራውን ስህተት የተቃወማችሁ እና ለመብታችን አቤት ያላችሁ እህት ወንድሞች አላህ ኸይር ጀዛችሁን ይክፈላችሁ!

የህዝብ ተወካዮች ም/ቤት መደበኛ ጉባኤ ነገ ይካሄዳል!የሕዝብ ተወካዮች ም/ቤት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ በተገኙበት 14ኛ መደበኛ ጉባዔውን ነገ ጥር 28/2016 ከጠዋቱ 2፡00 ጀምሮ ...
05/02/2024

የህዝብ ተወካዮች ም/ቤት መደበኛ ጉባኤ ነገ ይካሄዳል!

የሕዝብ ተወካዮች ም/ቤት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ በተገኙበት 14ኛ መደበኛ ጉባዔውን ነገ ጥር 28/2016 ከጠዋቱ 2፡00 ጀምሮ ያካሂዳል።

ፓርላማው የወንጀል ክሶች እንዳይቋረጡ ለፍትሕ ሚኒስቴር ማሳሰቢያ ሰጠ። ሰኞ ጥር 27፣ 2016የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የሕዝብና የመንግሥት ጥቅምን የተመለከቱ የወንጀል ጉዳዮችን፣ በተለይም...
05/02/2024

ፓርላማው የወንጀል ክሶች እንዳይቋረጡ ለፍትሕ ሚኒስቴር ማሳሰቢያ ሰጠ። ሰኞ ጥር 27፣ 2016

የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የሕዝብና የመንግሥት ጥቅምን የተመለከቱ የወንጀል ጉዳዮችን፣ በተለይም ከሙስና ጋር የተያያዙ ክሶችን አሳማኝ በሆነ ምክንያት ካልሆነ በስተቀር መቋረጥ የለባቸውም ሲል ለፍትሕ ሚኒስቴር ማሳሰቢያ ሰጥቷል፡፡
የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ይህንን ማሳሰቢያ የሰጠው የፍትሕ ሚኒስቴርን የስድስት ወራት የሥራ አፈጻጸም ሪፖርት ካዳመጠ በኋላ ነው።

በዚህ መደበኛ ስብሰባ የፍትሕ ሚኒስቴር የስድስት ወራት የሥራ አፈጻጸም በተደመጠበት ስብሰባ የፍትሕ ሚኒስትሩ የሙስና ወንጀሎችን የተመለከቱ እንዲሁም የተመዘበሩ የሕዝብና መንግሥት ሀብቶችን በማስመለስ ረገድ ተከናወኑ ያሏቸውን ጉዳዮች አቅርበዋል፡፡

የፍትሕ ሚኒስቴርን የሚከታተለው ቋሚ ኮሚቴም የተናወኑ ጉዳዮችን በአዎንታ ተቀብሎ፣ በመንግሥት ተቋማት የሚፈጸም የሀብት ምዝበራን አስመልክቶ የፌዴራል ዋና ኦዲተር የሚያቀርባቸው የኦዲት ግኝቶችን መሠረት በማድረግ፣ የተቋማቱን መሪዎች በሕግ ተጠያቂ ከማድረግ አኳያ ክፍተት መኖሩን በጥያቄ አንስቷል።

ፍትሕ ሚኒስትሩ ጌድዮን ጢሞቲዮስ (ዶ/ር) የተጠቀሰው ክፍተት መኖሩን ተቀብለው በሰጡት ተጠማሪ ማብራሪያ፣ የፋይናንስ ኦዲት ሪፖርትን መሠረት አድርጎ የሕግ ተጠያቂነትን ለማረጋገጥ ተጨማሪ የፎረንሲክ ምርመራ ማካሄድና በመንግሥት ላይ ለደረሰው ጉዳት ትክክለኛውን ተጠያቂ መለየት እንደሚያስፈልግ ገልጸዋል።

አክለውም፣ የሕዝብና የመንግሥት ጥቅምን የተመለከቱ የወንጀል ክሶች በተለይም ከሙስና ጋር የተያያዙ ጉዳዮች እንደሚቋረጡ በማንሳት ይህ አካሄድ እንዲስተካከል መጠየቃቸውን ሪፖርተር ዘግቧል፡፡

Address


Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Berekah Tube posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to Berekah Tube:

  • Want your business to be the top-listed Media Company?

Share