Berekah Tube

Berekah Tube የነቃ ትውልድ!

ቻይና የኢትዮጵያ ዕዳ መክፈያ ጊዜ የሚያራዝም አወቃቀር ለመደገፍ የሚያስችል የመግባቢያ ስምምነት ተፈራረሙ****የኢትዮጵያ መንግሥት የሀገሪቱን ዕዳ መክፈል አቅቶት ከአበዳሪ ተቋማትና ሀገራት ...
16/10/2025

ቻይና የኢትዮጵያ ዕዳ መክፈያ ጊዜ የሚያራዝም አወቃቀር ለመደገፍ የሚያስችል የመግባቢያ ስምምነት ተፈራረሙ
****
የኢትዮጵያ መንግሥት የሀገሪቱን ዕዳ መክፈል አቅቶት ከአበዳሪ ተቋማትና ሀገራት ጋር ያልተሳካ ድርድር እያደረገ ባለበት ጊዜ ከቻይና መንግሥት አዎንታዊ ምላሽ አግኝቷል።

የቻይና መንግሥት የኢትዮጵያ እዳ ክፍያ ጫና ያቃልላል የተባለ አዲስ የክፍያ አወቃቀር መግባቢያ ስምምነት መፈራረማቸውን በቻይና የኢትዮጵያ ኤምባሲ አስታውቋል።

ስምምነቱ ኢትዮጵያ ከቻይና የፋይናንስ ተቋማት እና ሌሎች አበዳሪዎች ጋር ያላት ግንኙነት የበለጠ ውጤታማ እንድትሆን የሚያስችል ትልቅ እድገት ነው ብሎታል ኤምባሲው።

የመግባቢያ ሰነዱ የኢትዮጵያን የዕዳ ጫና ለማቃለል ብቻ ሳይሆን ወደፊትም አዳዲስ የትብብር እና የጋራ ዕድገት ዕድሎችን ለመፍጠር ያለመ ነው ተብሏል።

©️ማለዳ ሚዲያ

በቄሶች ቡራኬ የሚላከው ፋኖ «የአሁኑ ጭፍ*ጨፋ አላረካንም፤ ተጨማሪ መስጂዶችን መድ'ፈር፤ ተጨማሪ ኢማሞችን መግ*ደል፤ ተጨማሪ የመጅሊስ አመራሮችን መረ'ሸን፤ ወሎን መውረ'ር…» ይጠበቅብናል ...
06/10/2025

በቄሶች ቡራኬ የሚላከው ፋኖ «የአሁኑ ጭፍ*ጨፋ አላረካንም፤ ተጨማሪ መስጂዶችን መድ'ፈር፤ ተጨማሪ ኢማሞችን መግ*ደል፤ ተጨማሪ የመጅሊስ አመራሮችን መረ'ሸን፤ ወሎን መውረ'ር…» ይጠበቅብናል እያለ ነው።

(ዘ-ሐበሻ) ምሽቱ የመካነ ሰላም ከተማን ጸጥታ አልብሷት ነበር። በታላቁ የኑር መስጂድ ውስጥ፣ ምዕመናን የቀኑን የመጨረሻ ጸሎት (የኢሻ ሰላት) አድርሰው ወደ ፈጣሪያቸው ሰላምን፣ ጤና፣ ፍቅር...
06/10/2025

(ዘ-ሐበሻ) ምሽቱ የመካነ ሰላም ከተማን ጸጥታ አልብሷት ነበር። በታላቁ የኑር መስጂድ ውስጥ፣ ምዕመናን የቀኑን የመጨረሻ ጸሎት (የኢሻ ሰላት) አድርሰው ወደ ፈጣሪያቸው ሰላምን፣ ጤና፣ ፍቅርን፣ ወዘተ.. እየለመኑ ነበር። ይህች የተቀደሰች ስፍራ፣ የሰላምና የእምነት ማዕከል፣ በቅጽበት ወደ ሰቆቃና የሽብር አውድማነት እንደምትቀየር በወቅቱ ማንም አላሰበም ነበር።

ነገር ግን ይህ የሰዓታት ጸጥታ፣ በድንገተኛ የሽብር ጩኸትና በተተኮሱ ጥይቶች ተሰበረ። ታጣቂዎች መስጂዱን ከበው፣ በእጃቸው በያዙት የስም ዝርዝር መሰረት፣ የማህበረሰቡ መሪዎችና አባቶች ናቸው ያሉዋቸውን አምስት ንጹሃን አማኞችን ለይተው በግፍ ገደሏቸው። በጸሎት ላይ የነበሩ እጆች፣ ሳይጨርሱ ተቆረጡ፤ ወደ ፈጣሪ ያነሱ አይኖች፣ ሳይመለሱ ጨፈኑ።

በድር የተሰኘው ዓለም አቀፍ የኢትዮጵያውያን ሙስሊሞች ድርጅት ባወገዘበትና ለዘ-ሐበሻ በላከው መግለጫው፣ ጥቃቱ ድንገተኛ ሳይሆን በቂ ዝግጅት ተደርጎበትና ታቅዶበት የተፈጸመ ዘግናኝ ወንጀል ነው ይላል። ድርጅቱ እንደሚለው፣ ከጥቃቱ ቀናት በፊት በማህበራዊ ሚዲያ "በኑር መስጂድ የመከላከያ ሰራዊትና ባለስልጣናት መሽገዋል" የሚል የሀሰት ውንጀላ ሲሰራጭ ነበር። ይህ፣ ንጹሃኑን ለጥቃት ለማመቻቸት የተነዛ የጥላቻ ዘመቻ እንደነበር ድርጅቱ ያምናል።

ይህ የመካነ ሰላም ጥቃት፣ በክልሉ ለዓመታት ሲፈጸሙ የነበሩና ፍትህ ያላገኙ የጥቃት ሰንሰለቶች የመጨረሻው አሳዛኝ ምዕራፍ ነው። ከዚህ ቀደም በሞጣ፣ በጎንደር፣ በቆቦና በሌሎች አካባቢዎች ሙስሊሞች ላይ የተፈጸሙት ግድያዎችና የንብረት ውድመቶች ተጠያቂነት ባለማግኘታቸው፣ ነብሰ ገዳዮች ዛሬም በድፍረት ወንጀላቸውን እንዲቀጥሉ እንዳደረጋቸው ድርጅቱ በምሬት ይገልጻል። የእነዚያ ንጹሃን ደም "ፍትህ" እያለ ሲጮህ፣ መልስ ባለማግኘቱ ሌላ ደም ፈሰሰ።

ከትላንት ወዲያ ምሽት የተገደሉት የአምስቱ አባቶች የቀብር ስነስርዓት ትናንት ተፈጽሟል። ቤተሰቦቻቸው ልብ በሚሰብር ሀዘን ውስጥ ሆነው፣ የሀገሪቱ የሰላም ችግር ወደ ሃይማኖት ግጭት እንዳያመራ ስጋታቸውን እየገለጹ ነው።

በድር በመግለጫው ማጠቃለያ ላይ ይህ ጥቃት በሀገሪቱ ላይ የከፋ የሃይማኖት ግጭት ለመጫር የታለመ እኩይ ተግባር መሆኑን በመግለጽ፣ መንግስት ወንጀለኞቹን በአስቸኳይ ለህግ እንዲያቀርብና በክልሉ የሚገኙ ሙስሊሞች ራሳቸውን የሚከላከሉበት ሁኔታ እንዲመቻች አጥብቆ ጠይቋል። የሟቾቹ ቤተሰቦች ፍትህን፣ የማህበረሰቡ አባላት ደግሞ ለነገው ህይወታቸው ዋስትናን ይሻሉ። የኑር መስጂድ ጸጥታ ግን ዛሬ ላይ የሀዘንና የስጋት ጸጥታ ሆኗል።

☪️የኦሮሞ ብሔረሰብ ዞን እስልምና ጉዳዮች ም/ቤት በመካነሰላሙ ጭፍጨፋ ዙሪያ መግለጫ አወጣ  !!
06/10/2025

☪️የኦሮሞ ብሔረሰብ ዞን እስልምና ጉዳዮች ም/ቤት በመካነሰላሙ ጭፍጨፋ ዙሪያ መግለጫ አወጣ

!!

 ደቡብ ወሎዎችም ግዕዝ እንዲጫንብን አንፈቅድም ብለዋል!
12/09/2025



ደቡብ ወሎዎችም ግዕዝ እንዲጫንብን አንፈቅድም ብለዋል!

የመጀመሪያዋ AI ሚኒስትር! አልባኒያ በአርቲፊሻል ኢንተሊጀንስ የተፈጠረ በዓለም ለመጀመሪያ ጊዜ የመንግስት ሚኒስትር አደረገች፡፡ በአልባኒያ ባህላዊ ልብስ ተውባ የታየችው ሚኒስትሯ ስሟም Di...
12/09/2025

የመጀመሪያዋ AI ሚኒስትር!

አልባኒያ በአርቲፊሻል ኢንተሊጀንስ የተፈጠረ በዓለም ለመጀመሪያ ጊዜ የመንግስት ሚኒስትር አደረገች፡፡ በአልባኒያ ባህላዊ ልብስ ተውባ የታየችው ሚኒስትሯ ስሟም Diella ተብሎ የተሰየመ ሲሆን ትርጉሙም በአልባንኛ ቋንቋ ፀሀይ ማለት ነው። ይህች በAI የተፈጠረች ቦት የመንግስት ውሎችን ማስተዳደርና ማስመራት ትችላለች፡፡

ጠ/ሚኒስትር ኤዲ ራማ በSeptember 11 ቀን አዲሱን ካቢኔያቸውን ሲያስተዋዉቁ ነው ይህን ዜና ያበሰሩት። እስካሁን ድረስም Diella 36,600 ዲጂታል ሰነዶች እና 1,000 የሚሆኑ አገልግሎቶችን እንደሰጠች ተዘግቧል።

ደሴዎች ማሻአላህ ❤
12/09/2025

ደሴዎች ማሻአላህ ❤

የወሎ ሙስሊሞች ግዕዝን አንማርም አሉ!============================የአማራ ክልል ትምህርት ቢሮ ከያዝነው የትምህርት ዘመን ጀምሮ ግዕዝ ከመደበኛ ትምህርት ጋር ተካቶ እንዲሰጥ ...
12/09/2025

የወሎ ሙስሊሞች ግዕዝን አንማርም አሉ!
============================
የአማራ ክልል ትምህርት ቢሮ ከያዝነው የትምህርት ዘመን ጀምሮ ግዕዝ ከመደበኛ ትምህርት ጋር ተካቶ እንዲሰጥ ውሳኔ ማሳለፉ ተገልጿል።

የክልሉ ትምህርት ቢሮ በቀን 13/12/2017 በተጻፈ ደብዳቤ በ2018 የትምህርት ዘመን በክልሉ ባሉ የመጀመሪያ ደረጃ ት/ቤቶች ከ3ኛ ክፍል ጀምሮ የግዕዝ ትምህርት እንዲሰጥ አስገዳጅ መሆኑን መገለፁ ነው የተነገረው።

ይህን ተከትሎ የደቡብ ወሎ ዞን እስልምና ጉዳዮች ምክር ቤት፤ የደሴ እና የኮምቦልቻ ከተማ መጅሊስ ግዕዝ የትምህርት ዓይነት ሙስሊሙን ማህበረሰብ ታሳቢ ያላደረገና ውይይት ያልተደረገበት በመሆኑ፣ እንዲሁም በሕገ መንግስቱ እንዲሰጡ ታሳቢ ካደረጋቸው ትምህርቶች ውስጥ ያልተካተተ ባለመሆኑና የማህበረሰብ ውይይት ያልተደረገበት በመሆኑ በክልሉ ትምህርቱ እንዲሰጥ ፈቃደኛ አለመሆናቸውን ገልፀዋል።

ከዚሁ ጋር በተያያዘ የደቡብ ወሎ ዞን እስልምና ጉዳዮች ምክር ቤት፤ የደሴ ከተማ እስልምና ጉዳዮች ም/ቤት ቅሬታቸውን የሚገልጽ ደብዳቤ ለሚመለከታቸው የመንግስት ተቋማት ማስገባታቸውን ገልፀዋል።

በተጨማሪም በዛሬው ዕለት በተለያዩ የወሎ አካባቢዎች የተደረገው የጁምአ ኹጥባ የግዕዝ ቋንቋ በመደበኛ ትምህርት ተካቶ መሰጠቱ አግባብ አለመሆኑን የሚገልፁ እና የሚቃወሙ እንደነበሩ ተመላክቷል። © ሀሩን ሚዲያ

በአዲስ አበባና በሌሎች የኢትዮጽያ ክፍሎች ለሥራ ተሰማርተው የሚገኙ ወጣቶች በግዳጅ ለውትድርና እየተመለመሉ መሆናቸውን ተናገሩ። ******በአካባቢያችን ባለው የሥራ ዕድል ማጣት ምክንያት ቀዬ...
27/04/2025

በአዲስ አበባና በሌሎች የኢትዮጽያ ክፍሎች ለሥራ ተሰማርተው የሚገኙ ወጣቶች በግዳጅ ለውትድርና እየተመለመሉ መሆናቸውን ተናገሩ።
******
በአካባቢያችን ባለው የሥራ ዕድል ማጣት ምክንያት ቀዬአችንን ለቀን ለመውጣት ተገደናል ያሉን ለሚዲያችን አቤቱታ ያቀረቡ ወጣቶች ያለ ፈቃዳቸው በግዳጅ ለውትድርና እየተመለመሉ መሆናቸውን አቤቱታ አሰምተዋል።

በአዲስ አበባ ከተማ በግንባታ ሥራ ላይ ተሰማርተው እንደሚገኙ የተናገሩ እነዚህ ወጣቶች፣ ወደ ሥራ ስሄዱና ስመለሱ ሚሊሻ ነን ያሉ ሰዎች አፍነው በመውሰድ ደህንነቱ ያልተጠበቀ ካምፕ ውስጥ እንደሚያጉሯቸው በመግለጽ ለሥራ ወቶ መግባት ስቃይ ሆኖብናል በማለት እየደረሰባቸው የሚገኘውን ምሬት ተናግረዋል።

‛‛ሚሊሻዎች መንገድ ላይ አይናቸውን ያየውን ሰው ሁሉ ያፍናሉ፣ ይሁን እንጂ በተለይም ከሲዳማ የመጣን ወጣቶች በርከት ብለን በምንገኝበት የግንባታ ጣቢያዎች የተለየ ኢላማ አድርገው በርካታ ጓደኞቻችንን አፍነው ወስደዋቸው‛‛ ሲሉ አክለዋል።

በተከራዩት አንድ ክፍል ውስጥ ሰብሰብ ብለው እንደሚኖሩ የነገሩን ወጣቶቹ በዚህ ምክንያት ሚሊሻዎቹ ማታ ቤት ሰብረው እየገቡ ጭምር ጓደኞቻቸውን እያፈሱባቸው እንደሚገኙ ነው ሚዲያችን የገለጹት።

እስራኤል ወደ ጋዛ ማንኛውም እርዳታ እንዳይገባ ካገደች አንድ ወር አለፈ በተባበሩት መንግሥታት የሚደገፉ ዳቦ ቤቶች በሙሉ መዘጋታቸው ተገለፀ። በጋዛ የሚገኙ ገበያዎችም ቢሆን አትክልቶች አይገ...
04/04/2025

እስራኤል ወደ ጋዛ ማንኛውም እርዳታ እንዳይገባ ካገደች አንድ ወር አለፈ

በተባበሩት መንግሥታት የሚደገፉ ዳቦ ቤቶች በሙሉ መዘጋታቸው ተገለፀ። በጋዛ የሚገኙ ገበያዎችም ቢሆን አትክልቶች አይገኙባቸውም። ሆስፒታሎች ለታካሚዎቻቸው የሕመም ማስታገሻዎች እና ፀረ ተህዋሲያንን መድሃኒት (አንቲባዮቲኮችን) በፈረቃ እያከፋፈሉ መሆኑን ተናግረዋል።

እስራኤል ከሃማስ ጋር ለ18 ወራት እያካሄደችው ባለው ጦርነት ውስጥ የተጣለ ረዥሙ እገዳ ነው። በዚህ ሳምንት በተከበረው የዒድ አል-ፈጥር በዓል ላይ ብዙ ጋዛውያን "ርቦናል" ሲሉ ተሰምቷል።

ከበይተ ላሂያ የተፈናቀለችው ኡሙ አሊ ሃማድ በጋዛ ከተማ ምግብ እየፈለገች መሆኑን ለቢቢሲ ገልጻ "ይህ ለእኛ ከመቼውም ጊዜ ይበልጥ የከፋው ዒድ ነበር" ብላለች። "መብላትም ሆነ መጠጣት አልቻልንም። መዝናናት አልቻልንም፤ ደክሞናል።"
"ከእንግዲህ እንደ ቲማቲም፣ ስኳር ወይም ዘይት ያሉ ነገሮች ማግኘት አንችልም። አይገኙም። በቀን አንድ ምግብ የማገኘው በመከራ ነው። አሁን የምግብ ድጋፍ የሚያደርጉ ድርጅቶች የሉም" ስትል አክላለች።

የእፎይ ጉዳይ ከምን ደረሰ?''''''''''''''''''''''''''''''''''''''''''''''''''''''''''''''''''''''''''''''በነብዩ ሙሀመድ "ﷺ" ላይ ጸያፍ ቃላትን...
03/04/2025

የእፎይ ጉዳይ ከምን ደረሰ?
''''''''''''''''''''''''''''''''''''''''''''''''''''''''''''''''''''''''''''''
በነብዩ ሙሀመድ "ﷺ" ላይ ጸያፍ ቃላትን በመሰንዘር ድንበር ያለፈውን ግለሰብ አስመልክቶ ያለው የህግ ሒደት ምን ላይ ደርሷል?

ከሳምንታት በፊት በነብዩ ሙሀመድ "ﷺ" ላይ ድንበር ያለፈውን "እፎይ" የተባለ ግለሰብ መጅሊሱ በህግ ክፍሉ በኩል ክስ መመስረቱን መግለፁ ይታወሳል።

ይህንኑ ጉዳይ አስመልክቶ ሀሩን ሚዲያ የክሱ ሂደት ምን ላይ ደረሰ? ስንል ጠይቀናል። የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት ዋና ስራአስኪያጅ ሀጂ ከማል ከሀሩን ሚዲያ ጋር በነበራቸው ቆይታ በሰጡት ምላሽ የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት በነብዩ ሙሀመድ ላይ ድንበር ያለፈውን ግለሰብ አስመልክቶ በህግ ክፍሉ በኩል ምስክሮችን በማጠናከር ክስ መመስረቱን ገልጸዋል።

ይሁንና ግለሰቡ እስካሁን በህግ ቁጥጥር ስር አለመዋሉ የተገለፀ ሲሆን መጅሊሱ ግለሰቡ በህግ ቁጥጥር ስር እስከሚውል ክትትሉን እንደሚቀጥል ገልጸዋል።

በነብዩ ሙሀመድ "ﷺ" ላይ ድንበር የሚያልፉ ግለሰቦችን ፈፅሞ እንደማይታገስ የገለፀው ጠቅላይ ምክር ቤቱ መሰል ጥፋት በሚፈጽሙ ግለሰቦች ላይ በህግ አግባብ የጀመረውን እርምጃ እንደሚቀጥል ገልጸዋል።

ክስ የተመሰረበት ግለሰብ ክሱ ተጠናቅሮ ለፖሊስ ቀርቦ የእስር ማዘዣ የወጣ ቢሆንም እስካሁን በቁጥጥር ስር አለመዋሉ ይታወቃል። ©ሀሩን ሚዲያ

በጊንጭ ከተማ የመስጂድ መሬት በሀይል ለመውረር ያሰቡ ሀይሎች በኡስታዞች ላይ ድብደባ መፈፀማቸው ተሰማ! መጋቢት 25/2017በኦሮሚያ ክልል ጊንጪ ከተማ የሙስሊሙ ማህበረሰብ የመስጅድ እና የመ...
03/04/2025

በጊንጭ ከተማ የመስጂድ መሬት በሀይል ለመውረር ያሰቡ ሀይሎች በኡስታዞች ላይ ድብደባ መፈፀማቸው ተሰማ! መጋቢት 25/2017

በኦሮሚያ ክልል ጊንጪ ከተማ የሙስሊሙ ማህበረሰብ የመስጅድ እና የመቃብር ስፍራ የሆነ መሬቱን በሀይል ለመውረር የሞከሩ አካላቶች ኡስታዞች ላይ ድብደባ መፈፀማቸውን ከስፍራው ለሀሩን ሚዲያ የደረሰው መረጃ ያመላክታል።

ከ40 አመት በፊት ጀምሮ የአካባቢው ሙስሊም ማህበረሰብ እየተጠቀመበት የሚገኘው ህጋዊ የሆነ የሙስሊሙ ማህበረሰብ የመቃብር ቦታ የአካባቢው መጅሊስም ሆነ የመስጅዱ ኮሚቴዎች ባላወቁት መልኩ አጥሩ እንዲፈርስ መደረጉን ገልፀዋል።

ከዚህ በተጨማሪም ያለምንም ደብዳቤ ግሬደር ይዞ በመምጣት ህጋዊ የመስጅድ እና የመቃብር ቦታ እንዲቆፈር ማድረጋቸው ተገልጿል። ይህንኑ ጉዳይ ለከተማው ከፍተኛ አመራሮች በማሳወቅ የእግድ ደብዳቤ ያስፃፉ የመስጅድ ኡስታዞች ላይ ድብደባ መፈፀሙ ነው የተገለፀው።

ከአዲስአበባ በቅርብ ርቀት በምትገኘው ጊንጭ ከተማ በሙስሊሙ ማህበረሰብ ላይ ከፍተኛ በደል እየተፈፀመባቸው መሆኑን የሚገልፁት የአካባቢው ሙስሊሞች የሚመለከተው አካል በአስቸኳይ እልባት እንዲሰጣቸው ጠይቀዋል። © ሀሩን ሚዲያ

Address

Addis Ababa

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Berekah Tube posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to Berekah Tube:

Share