Kedir Nursebo Elos

Kedir Nursebo Elos بسم الله الرحمن الرحیم

ቱርክ 3ኛ ትውልድ/Third GENERATION/ የተባለውንና በጀነራል አልታይ ስም የሰየመችውን አልታይ ታንክ ያስመረቀች ሲሆን ይህ ምርቷ ቱርክን ዓለም ላይ ካሉት ታንኮችን በማምረት ከሚታወቁ...
30/10/2025

ቱርክ 3ኛ ትውልድ/Third GENERATION/ የተባለውንና
በጀነራል አልታይ ስም የሰየመችውን አልታይ ታንክ ያስመረቀች ሲሆን ይህ ምርቷ ቱርክን ዓለም ላይ ካሉት ታንኮችን በማምረት ከሚታወቁት ከአሜሪካ፣ ራሺያ፣ ደቡብ ኮሪያ እና ጀርመን ጋር ተወዳዳሪ ያደርጋታል ተብሏል::

70 ፐርሰንት የሚሆኑ ፍልስጤማውያን ሀማስ ትጥቅ እንዲፈታ አንፈልግም አሉጥቅምት 20/2018በጋዛ የሚገኘው የጥናት ምርምር ማዕከል የሆነው ፒ.ሲ.ፒ.ኤስ.አር ድርጅት ፍልስጤማውያን ሀማስ ትጥ...
30/10/2025

70 ፐርሰንት የሚሆኑ ፍልስጤማውያን ሀማስ ትጥቅ እንዲፈታ አንፈልግም አሉ

ጥቅምት 20/2018

በጋዛ የሚገኘው የጥናት ምርምር ማዕከል የሆነው ፒ.ሲ.ፒ.ኤስ.አር ድርጅት ፍልስጤማውያን ሀማስ ትጥቅ እንዲፈታ እንማይፈልጉ ገልፆል።

ድርጅቱ ጥናቱን ያከናወነው በጋዛና ዌስት ባንክ የሚገኙ ፍልስጤማውያን በመጠየቅ እንደሆነ አስታውቋል።

አስተያየት ሰጪዎቹም በትራንፕ በቀረበውን የሰላም ስምምነት ላይ እምነት የለንም ብለዋል።

ሀማስ ትጥቅ ቢፈታም የእስራኤል ወታደሮች ጥቃት ከመሰንዘር ሊታቀቡ አይችሉም በማለት ስጋታቸው ገልፀዋል።

የእስራኤል ወታደሮች 125 ጊዜ ስምምነቱን በመጣስ ጥቃት መሰንዘራቸውን ይታወሳል።

30/10/2025

UN Secretary-General Antonio Guterres on Wednesday “strongly” condemned recent Israeli airstrikes across the Gaza Strip.

“The Secretary-General strongly condemns the killings due to Israeli airstrikes of civilians in Gaza yesterday, including many children,” his spokesperson Stephane Dujarric said at a news conference, adding that Guterres also “condemns all actions that undermine the ceasefire and endanger civilian lives.”

Noting the “importance of the parties and renewed assurances to implement the ceasefire,” the UN chief also stressed that the “commitments must be upheld in full.”

“Any acts that risk harm to civilians or obstruct humanitarian operations must be avoided,” Dujarric added.

Read: https://www.middleeastmonitor.com/20251029-un-chief-strongly-condemns-recent-deadly-israeli-airstrikes-in-gaza/

በአስደናቂ ውጤት የተጠናቀቀው የፕሬዚዳንት ትራምፕና ሺ ጂንፒንግ ውይይት…የአሜሪካ ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ እና የቻይና አቻቸው ሺ ጂንፒንግ በደቡብ ኮሪያ በተለያዩ ጉዳዮች ላይ ተወያይተዋል...
30/10/2025

በአስደናቂ ውጤት የተጠናቀቀው የፕሬዚዳንት ትራምፕና ሺ ጂንፒንግ ውይይት…

የአሜሪካ ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ እና የቻይና አቻቸው ሺ ጂንፒንግ በደቡብ ኮሪያ በተለያዩ ጉዳዮች ላይ ተወያይተዋል፡፡

በውይይታቸው በተለያዩ ጉዳዮች ላይ በትብብር መስራት በሚቻልባቸው ሁኔታዎች እና በጋራ ተጠቃሚነት ላይ በትኩረት መክረዋል፡፡

ፕሬዚዳንት ትራምፕ ጉዳዩን አስመልክተው በሰጡት ማብራሪያ÷ ከቻይና አቻቸው ሺ ጂንፒንግ ጋር ያደረጉት ውይይት አስደናቂ እንደነበር ተናግረዋል፡፡

በሁሉም ጉዳዮች በሚባል ደረጃ ስምምነት ላይ መደረሱን ጠቁመው ÷ ይህም የሁለቱን ሃያላን ሀገራት ሁለንተናዊ ትብብር ይበልጥ የሚያጠናክር ነው ብለዋል፡፡

በስምምነቱ መሰረት አሜሪካ በቻይና ሸቀጦች ላይ ጥላው የነበረውን ቀረጥ ከ57 በመቶ ወደ 47 በመቶ እንደምትቀንስ ነው ያስረዱት፡፡

ሀገራቱ በቅርቡ የንግድ ስምምነት የሚፈራረሙ ሲሆን ÷ ስምምነቱም ሁለቱ ወገኖች በኢኮኖሚ ዘርፍ የገቡበትን ውጥረት እንደሚያረግብው ይጠበቃል፡፡

ፕሬዚዳንት ሺ ጂንፒንግ በበኩላቸው ÷ ቻይና እና አሜሪካ በተለያዩ ዘርፎች በትብብር በመስራት አጋርነታቸውንና ወንድማማችነታቸውን ይበልጥ ማጠናከር አለባቸው ብለዋል፡፡

ግዙፍ ኢኮኖሚ ያላቸው ሀገራቱ ለዓለም ኢኮኖሚ የሚጠበቅባቸውን ሃላፊነት መወጣት አለባቸው ፤ ለዚህም ቀና ትብብርና የጋራ ተጠቃሚነት ወሳኝ ነው ሲሉ አጽንኦት ሰጥተዋል፡፡

በውይይቱ ከሞላ ጎደል በሁሉም ጉዳዮች ስምምነት ላይ መደረሱን ጠቁመው÷ ስምምነቱን ለመተግበርና የኢኮኖሚ መረጋጋት ለመፍጠር በትብብርና በቁርጠኝነት ይሰራል ነው ያሉት፡፡

በሌላ በኩል ሀገራቱ በሳይበር ጥቃት፣ በሕገ ወጥ የገንዘብ ዝውውር፣ በሕገ ወጥ ስደተኞች አያያዝ እና በአርቴፊሻል ኢንተለጀንስ ዘርፎች በትብብር ለመስራት ተስፋ ሰጪ ምክክር ማድረጋቸውን ቢቢሲ ዘግቧል፡፡

ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ በእስያ የነበራቸውን ይፋዊ የሥራ ጉብኝት ያጠናቀቁ ሲሆን ÷ በቀጣዩ ሚያዝያ ወርም በቻይና የሥራ ጉብኝት እንደሚያደርጉ ተመላክቷል፡፡

ጂቡቲ-> ኢትዮጵያ-> ደቡብ ሱዳን->ኡጋንዳ የመንገድ ኮሪደር ልማት ባለስልጣን ልቋቋም ነው::የመንገድ ልማቱን በተመለከተ  #ጂቡቲ ተገኝተው የመንገድ ኮሪደር ልማት ባለስልጣኑን ስለማቋቋምና ...
26/10/2025

ጂቡቲ-> ኢትዮጵያ-> ደቡብ ሱዳን->ኡጋንዳ የመንገድ ኮሪደር ልማት ባለስልጣን ልቋቋም ነው::

የመንገድ ልማቱን በተመለከተ #ጂቡቲ ተገኝተው የመንገድ ኮሪደር ልማት ባለስልጣኑን ስለማቋቋምና በሌሎች ቴክኒካል ጉዳዮች ላይ የተወያዩት የአራቱ አገራት ሚንስትሮች

MOU የተፈራረሙ ስሆን ቅርብ ጊዜ ውስጥ አዲስ አበባ ላይ ተገናኝተው #ባለስልጣኑን በይፋ በማቋቋም ወደ ስራ ይገባሉ ተብሎ ይጠበቃል::

ኢትዮጵያ ባለፈው ዓመት ለመንገድ ፕሮጀክት የሚውል የ738 ሚልየን US ዶላር #ብድር ለደቡብ ሱዳን መስጠቷና የብድር ስምምነቱ

ለህዝብ ተወካዮች ቀርቦ ምክርቤቱ በስፋት ከመከረበት በኃላ መፅደቁ የሚታወስ ሲሆን #በምላሹ ደቡብ ሱዳን ለኢትዮጵያ የነዳጅ ምርቶችን እንደሚታቀርብ መነገሩም የሚታወስ ነው::

Knb

ጅቡቲ የፕሬዝደንትነት እድሜ ገደብ አነሳች፣ ለ6ኛ ጊዜ የ እስማኤል ኦማር ጉሌህ የስልጣን ዘመን ጥርጊያ መንገድ አዘጋጅታለች።
26/10/2025

ጅቡቲ የፕሬዝደንትነት እድሜ ገደብ አነሳች፣ ለ6ኛ ጊዜ የ እስማኤል ኦማር ጉሌህ የስልጣን ዘመን ጥርጊያ መንገድ አዘጋጅታለች።

እኛም አድስ ነገር ይኖራል ብለን እንጠብቅ እንዴትጠቅላይ ሚኒስትር ዐብይ አሕመድ ከነገ በስቲያ ፓርላማ ሊቀርቡ ነውየሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ከነገ በስቲያ  ጥቅምት 18/2018 ዓ.ም. በሚ...
26/10/2025

እኛም አድስ ነገር ይኖራል ብለን እንጠብቅ እንዴት
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐብይ አሕመድ ከነገ በስቲያ ፓርላማ ሊቀርቡ ነው

የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ከነገ በስቲያ ጥቅምት 18/2018 ዓ.ም. በሚያካሄደው መደበኛ ስብሰባው፤ የፓርላማ አባላት ላቀረቧቸው ጥያቄዎች ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ ምላሽ እና ማብራሪያ እንደሚሰጡ ኢትዮጵያ ኢንሳይደር ዘግባለች። የፓርላማ አባላቱ ጥያቄዎቻቸውን አስገብተው እንዲያጠናቅቁ የተነገራቸው በዚህ ሳምንት መጀመሪያ ላይ መሆኑንም ገልጸዋል።

ምክር ቤቱ የአምስተኛ ዓመት ሁለተኛ መደበኛ ስብሰባውን ከነገ በስቲያ ማክሰኞ እንደሚያካሄድ ለፓርላማ አባላት መረጃዎችን በሚያሰራጭበት የቴሌግራም ቻናሉ በትላንትናው ዕለት ቢያስታውቅም፤ አጀንዳውን ከመግለጽ መቆጠቡን ምንጮች ገልጸዋል። ሆኖም ለጉዳዩ ቅርብ የሆኑ አንድ የፓርላማ አባል፤ በዚሁ ዕለት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ በተወካዮች ምክር ቤት ተገኝተው ለጥያቄዎች ምላሽ እንደሚሰጡ ማረጋገጣቸውን ዘገባው ጠቅሷል።

በዚሁ ስብሰባ ላይ እንዲገኙ ለዲፕሎማቶች እና ለተጋባዥ እንግዶች ጥሪ መዘጋጀቱን እንደተመለከቱም እኚሁ የፓርላማ አባል አክለዋል። የተቃዋሚ ፓርቲ የፓርላማ አባል ደግሞ ለጠቅላይ ሚኒስትሩ ጥያቄ እንዲያቀርቡ መረጃ የተላከላቸው ባለፈው ሳምንት ሐሙስ እንደነበር ገልጸዋል።

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐብይ ከፓርላማ አባላት ለቀረቡላቸው ጥያቄዎች ለመጨረሻ ጊዜ ምላሽ የሰጡት ባለፈው ዓመት ሰኔ ወር ማገባደጃ ላይ ነው። ሶስት ገደማ ከፈጀው ከጠቅላይ ሚኒስትሩ ምላሽ፤ ቅድሚያውን እና ሰፊውን ጊዜ የወሰደው የኢኮኖሚ ጉዳይ ነበር። አንድ ሰዓት ያልሞላ ጊዜ በተሰጠው የጠቅላይ ሚኒስትሩ የሰላም እና ጸጥታ ጉዳዮች ማብራሪያ፤ ትግራይ እና ኤርትራን የተመለከቱ ምላሾች መነሳታቸው ይ

"የትግራይ ተፈናቃዮች ወደ ቤታቸው እንዴት እንደሚመለሱ አቶ ጌታቸው ረዳ ባዛሬው ቀን በሑመራ ከተማ  ከነ ኮሎኔል ደመቀ  ጋር ተቀምጠው እየመከሩ ነው።
26/10/2025

"የትግራይ ተፈናቃዮች ወደ ቤታቸው እንዴት እንደሚመለሱ አቶ ጌታቸው ረዳ ባዛሬው ቀን በሑመራ ከተማ ከነ ኮሎኔል ደመቀ ጋር ተቀምጠው እየመከሩ ነው።

24/10/2025

የቀኔን ትካዜ በቅኔ ለውጨ
(በእውቀቱ ስዩም)

የደረሰኝ ደስታ፥ ከልቦናሽ ፈልቆ
እንደ ንፉግ ምጽዋት፥ አለ ሲባል አልቆ፤

ማለዳ ላይ ፍቅር ፥ ቀትር ላይ ትዝታ
ያቀድነውን ሁሉ
እንደ ኦሪት ሽሮት፥ ጊዜና ቸልታ፤

ስትቀመጭበት በነበረው ወንበር
አሁን ተቀምጬ
እምባየን ወደ ውስጥ ፥ እንደ ክኒን ውጬ፤
የቀኔን ትካዜ፤ በቅኔ ለውጬ
እንደዚህ እላለሁ፦

“ ጊዜ ውስጡ ጨካኝ፤ ከላይ ከላይ ገራም
ሕይወትን ያልማረ፤ ለፍቅር አይራራም::

📌 Beautiful three bedroomed residential layout 📌 Designed  by: K/N/B/ Design & Construction
22/10/2025

📌 Beautiful three bedroomed residential layout

📌 Designed by: K/N/B/ Design & Construction

የሱዳን ፈጥኖ ደራሽ ሀይሎች መሪ መሀመድ ሀምዳን ደጎሎ ኤርትራን አስጠነቀቁ።‼️ መሃመድ ሀምዳን ደጋሎ (ሄሜቲ) የኤርትራ መንግሥት በፖርት ሱዳን በኩል ተዋጊ ጀት፣ድሮን እና የጦር አውሮፕላኖ...
22/10/2025

የሱዳን ፈጥኖ ደራሽ ሀይሎች መሪ መሀመድ ሀምዳን ደጎሎ ኤርትራን አስጠነቀቁ።
‼️
መሃመድ ሀምዳን ደጋሎ (ሄሜቲ) የኤርትራ መንግሥት በፖርት ሱዳን በኩል ተዋጊ ጀት፣ድሮን እና የጦር አውሮፕላኖችን ለሱዳን ወታደራዊ መንግሥት ድጋፍ እያደረገች ነው ብለዋል።

ኤርትራ ከዚህ ድርጊቷ እንድትቆጠብ አስጠንቅቀዋል።
ኤርትራ በየቦታው በሚካሄዱ ግጭቶች ጣልቃ እየገባች ታቀጣጥላለች ከዚህ ድርጊት ካልታቀበች እርምጃ እንወስዳለን ብለዋል።

የኤርትራው መሪ በጦርነቱ ተሳታፊ ሆኖ የሚቀጥል ከሆነ ምላሹን ከእጃችን ይጠብቅ ሲሉ አሳስበዋል።

ለፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ተገልጋዮች በሙሉ  የፍትሐብሄር ይግባኝ ችሎት የስራ ቦታ ለውጥ******************************************የፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት የፍት...
22/10/2025

ለፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ተገልጋዮች በሙሉ

የፍትሐብሄር ይግባኝ ችሎት የስራ ቦታ ለውጥ
******************************************
የፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት የፍትሐብሄር ይግባኝ ችሎት አራት ኪሎ ባለው የኢትዮ-ፓስታ ህንፃ ላይ አገልግሎት እየሰጠ መሆኑ ይታወቃል፡፡

ይሁን እንጂ ከጥቅምት 3 ቀን (ሰኞ) 2018 ዓ.ም ጀምሮ የፍትሐብሄር ይግባኝ ችሎቱ አራት ኪሎ ከአብረሆት ላይብረሪ ወደ ፒያሳ መሄጃ 100 ሜትር ወረድ ብሎ ፍርድ ቤቱ እያስገነባ ወደሚገኘው አዲሱ ህንፃ ተዛውሮ አገልግሎት መስጠት የሚጀምር መሆኑን እየገለፅን ከላይ ከተጠቀሰው ቀን ጀምሮ የይግባኝ ችሎቱ ተገልጋዮች አገልግሎት ማግኘት የሚችሉት በአዲሱ ህንፃ መሆኑን እናሳውቃለን፡፡

በአማራጭ የጎግል ማፕ (google map) ሊንክ 2QH6+VC7, Addis Ababa በመጠቀም አቅጣጫውን ማግኘት ይችላሉ።

የፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት

Address

Addis Ababa

Telephone

+251707005428

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Kedir Nursebo Elos posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share