የስኬት መርሆዎች-Principles for Success

የስኬት መርሆዎች-Principles for Success ከታላላቅ ሰዎች የህይወት ተሞክሮ!!!

ንስር አሞራ እስከ 70 አመት የሚኖር የእድሜ ባለፀጋ ነው የሚል ሰምተህ ወይም አንብበህ ሊሆን ይችላል። ትክክል ነው! ነገር ግን 70 አመት ሙሉ በደስታ ከመኖሩ በፊት በእድሜው አጋማሽ ማለት...
09/07/2025

ንስር አሞራ እስከ 70 አመት የሚኖር የእድሜ ባለፀጋ ነው የሚል ሰምተህ ወይም አንብበህ ሊሆን ይችላል።
ትክክል ነው!

ነገር ግን 70 አመት ሙሉ በደስታ ከመኖሩ በፊት በእድሜው አጋማሽ ማለትም በ35 - 40 ባለው እድሜው ላይ ከባድ ነገር ይገጥመዋል ...

የመጀመሪያው :- ምግቡን ለማደን የሚገለገልበት ጥፍሮቹ ከመጠን በላይ ስለሚያድጉ ምግቡን ከመሬት ላይ ማንሳት ያቅተዋል ...

ሁለተኛው :- አጥንትን ሳይቀር መስበር አቅም ያለው አፉ(መንቁሩ) ስለሚታጠፍና ስለሚጣመም ምግቡን እንደወትሮው መመገብ ይሳነዋል ...

ሶስተኛው:- ክንፉና በአካሉ ላይ ያሉ ላባዎች ስለሚከብዱት ያ ሰማየ ሰማያትን እየሰነጠቀ ይበር የነበረው ሀይሉ ይክደዋል።

እነዚህ ሶስት ከባድ ነገሮች ንስር አሞራ በእድሜው አጋማሽ የሚያጋጥሙት ከባድ ችግሮች ናቸው። አሁን ንስር አሞራ ያለው ምርጫ ሁለት ነው።

1ኛ. ካረጀ አካሉ ጋር ዝም ብሎ በመቀመጥ ሞቱን መጠበቅ ?
2ኛ. አምስት ወር የሚፈጅ ስቃይና መከራ ያለበት መስዋዕትነትን ከፍሎ ቀሪውን 35 አመት በደስታ ማሳለፍ ?

የመጀመሪያውን ከመረጠ በእድሜው አጋማሽ ይሞታልና ታሪኩ እዛ ጋር ያበቃል።

ሁለተኛውን ምርጫ ከመረጠ ግን እነዚህን አምስት መስዋዕትነቶች ማለፍ ይኖርበታል።

፩ኛ. ከፍተኛ ተራራ ላይ በመውጣት የብቻውን ጎጆ ይቀልሳል።

፪ኛ. ጎጆ ከቀለሰ በኋላ የመጀመርያ ስራዉ የአፉን መንቁር ከአለት ጋር በማጋጨት ነቅሎ ይጥላል።

፫ኛ. ይህን ካደረገ በኋላ አዲስ መንቁር ይወጣለታል፡፡ መንቁሩ እስኪያድግ ድረስ ታግሶ በጎጆው ምንም አይነት ምግብ ሳይመገብ መቆየት ግዴታው ይሆናል፡፡

፬ኛ. አዲስ መንቁር ከበቀለለት በኋላ በአዲሱ መንቁሩ የገዛ እግሩን አሮጌ ጥፍር ነቃቅሎ ይጥለዋል።

፭ኛ. አዲሱ የእግር ጥፍር ከበቀለለት በኋላ ደግሞ ይህንን አዲስ ጥፍር እንደ መሳርያ በመጠቀም በሰዉነቱ የተጣበቁትን እንዳይበር እንቅፋት የሆኑትን የገዘፉና ያረጁ ላባዎችን ነቃቅሎ ይጥላል። በምትኩ አዲስ ላባ ያበቅላል።

ይህን 5 ወር በዚህ መልኩ በጀግንነት ከተወጣ በኋላ እንደገና ራሱን በራሱ ወልዶና ወጣት ሆኖ ወደ ንስሮች መንደር ብቅ ይላል፡፡




አንተም በተመሳሳይ መንገድ አልፈህ በአዲስ ህይወት ከፍ ብለህ መብረር ትችል ዘንድ .....ከንስር አሞራ ህይወት ተማርበት!

የ ገፃችን👇👇👇 ቤተሰብ ይሁኑ
የስኬት መርሆዎች-Principles for Success

የስኬት መርሆዎች

09/07/2025

ወንዶች ከድህነት የሚወጡባቸው 6 ስነ-ልቦናዊ መንገዶች፤

እንደ የስነ-ልቦና ባለሙያ፣ የሰዎችን አስተሳሰብ እና ባህሪ እንረዳለን። ድህነት የገንዘብ እጦት ብቻ ሳይሆን የአስተሳሰብ ችግርም ጭምር ነው። ወንዶች ከድህነት እንዲወጡ የሚረዷቸው 6 የስነ-ልቦና መርሆችን እነሆ፦

1. የምትረዳህን ሴት ምረጥ፡-

ብዙ ወንዶች በመልክ ብቻ ተስበው የተሳሳተ ምርጫ ያደርጋሉ። ስነ-ልቦና እንዲህ ይላል፦ የትዳር አጋርህ የህይወትህ ትልቁ የድጋፍ ምሰሶ ወይም አጥፊ ልትሆን ትችላለች። አስተዋይ፣ አበረታች እና ራዕይህን የምትደግፍ ሴት ስትመርጥ፣ የአእምሮ ሰላም ታገኛለህ። ይሄ ደግሞ ሃሳብህን ገንዘብ ወደሚያመጣ ነገር እንድትቀይር ያስችልሃል። ገንዘብ ለማግኘት ብቻ ሳይሆን፣ የተረጋጋ እና ደስተኛ ህይወት ለመኖርም ይረዳሃል።

2. የምትገኝባቸውን ቦታዎች አስተውል፡-

የምትሄድባቸው ቦታዎች የሃሳብህን እና የአቅምህን ወሰን ይወስናሉ። ርካሽ ቤቶች ውስጥ የምታገኛቸው ሰዎች ብዙ ጊዜ ችግራቸውን የሚያወሩ እና ገንዘብ የሚቸገሩ ናቸው። ይሄ የአንተንም አስተሳሰብ ሊቀይረው ይችላል። ይልቁንም ትልልቅ ንግድ የሚሰሩ፣ ኢንቨስትመንት የሚያወሩ ሰዎች በሚሰባሰቡባቸው ቦታዎች (ለምሳሌ የስራ ኮንፈረንሶች፣ ስልጠናዎች) ላይ ተገኝ። እዚያ የምታገኛቸው ግንኙነቶች እና የምትማራቸው ነገሮች የአስተሳሰብ አድማስህን ያሰፋሉ።

3. የስንፍናን አስተሳሰብ አስወግድ፡-

"ስንፍና የድህነት መጀመሪያ ነው" የሚባል የድሮ ብሂል አለ። የስነ-ልቦና ጥናቶች እንደሚያሳዩት ስንፍና ከፍርሃት እና ከተነሳሽነት ማጣት ይመነጫል። በቀን ውስጥ አብዛኛውን ጊዜህን በእንቅልፍ ወይም በማይጠቅሙ ነገሮች የምታሳልፍ ከሆነ፣ ለስራ የምትሰጠው ጊዜ ይቀንሳል። ይህ ደግሞ በራስ የመተማመን ስሜትህን ይጎዳል። ድህነት የገጠመው ሰው ሌላን አካል መውቀስ ይቀናዋል። ነገር ግን ለውጥ የሚመጣው ከራስህ ስትጀምር ነው። የምትሰራውን ነገር መውደድ እና ለውጤት መስራት የስንፍናን ስነ-ልቦና ይሰብራል።

4. ጠቃሚ እውቀትን አግኝ፡-

አእምሮህ የምትመግበው ነገር ነጸብራቅ ነው። የስነ-ልቦና ባለሙያዎች "የምትፈልገውን ታገኛለህ" ይላሉ። ብዙ ወንዶች ስለ ሴቶች፣ ስለ ስፖርት፣ ስለ ዝነኞች እና ስለ ሌላ ነገር ማውራት ይወዳሉ። ይህ መጥፎ አይደለም፣ ነገር ግን አብዛኛውን ጊዜህን ከወሰደብህ፣ ለአእምሮህ እድገት የሚጠቅም ነገር አይኖርህም። ኢንቨስትመንት፣ ንግድ፣ አዳዲስ ፈጠራዎች ላይ ማተኮር የአስተሳሰብ አድማስህን ያሰፋል። ቢያንስ አንድ ጠቃሚ ክህሎት (skill) መማር በራስ የመተማመን ስሜትህን ከፍ ያደርገዋል፣ የገቢ ምንጭም ይፈጥርልሃል። ኮሌጅ መግባት ባትችልም እንኳን ራስህን ለማስተማር ብዙ መንገዶች አሉ።

5. ከአንተ የተሻሉ ሰዎችን አማክር፡-

ስነ-ልቦናው "የምትኖርበት አካባቢ አንተን ይቀርጽሃል" ይላል። ብዙ ወንዶች ስኬታማ ሰዎች ከአጠገባችን የሉም በማለት ያማርራሉ። ነገር ግን ልክ በድሮ ጊዜ አባት ወደ ጫካ ሄዶ ልጁን አደን እንደሚያስተምረው ሁሉ፣ ዛሬም ትልልቅ ስኬት ያስመዘገቡ ሰዎችን ወጣ ብለህ መፈለግ አለብህ። ከእነሱ ጋር ጊዜ አሳልፍ፣ ሃሳባቸውን አዳምጥ፣ እና ከልምዳቸው ተማር። ከአንተ በተሻሉ ሰዎች ስትከበብ፣ የአንተ አስተሳሰብም ያድጋል። ጥሩ አማካሪዎች የህይወትህን አቅጣጫ ሊቀይሩት ይችላሉ።

6. የተግባር ሰው ሁን፡-

ብዙ ሰዎች ብዙ ነገርን ሰበብ አድርገው ከመስራት ይሸሻሉ። "የእግዚአብሔር በረከት በእጅህ ስራ ላይ ነው" የሚለው አባባል፣ መጸለይ ብቻውን በቂ አለመሆኑን ይነግረናል። ስነ-ልቦናውም እንዲህ ይላል፦ ተግባራዊ መሆን ሃሳቦችን ወደ እውነታ ለመቀየር ቁልፍ ነው። ስትሰራ፣ አዲስ ነገር ስትሞክር፣ ስትሳሳት እና ስትማር፣ አዳዲስ እድሎችን ትፈጥራለህ። ሃሳብህ ባዶ ሆኖ፣ ኪስህም ባዶ ከሆነ፣ ለውጥ ማምጣት ከባድ ነው። ጠንክሮ መስራት የራስህን እምቅ አቅም እንድታገኝ ያደርግሃል።

እነዚህን የስነ-ልቦና መርሆች በህይወትህ ውስጥ ተግባራዊ ካደረግክ፣ ከድህነት ለመውጣት ብቻ ሳይሆን፣ ደስተኛ እና የተሳካ ህይወት ለመኖርም ትችላለህ።

ምን ይመስልሃል? ከእነዚህ ውስጥ አንተ የትኛውን ነው መጀመሪያ የምትሞክረው?
@ Psych addis

የህይወት ፍልስፍና

1. ምኞት ስኬታማ ሰው ግልጽ የሆኑ ግቦች አሉት። “ሀብታም መሆን” እንደሚለው አይነት  ግልጽ ያልሆነ ግብ  ይልቅ ፣  “በሚቀጥሉት ሁለት ዓመታት ውስጥ ያለኝን አንድ ሱቅ ወደ ሶስት ሱቆች ...
09/07/2025

1. ምኞት
ስኬታማ ሰው ግልጽ የሆኑ ግቦች አሉት። “ሀብታም መሆን” እንደሚለው አይነት ግልጽ ያልሆነ ግብ ይልቅ ፣ “በሚቀጥሉት ሁለት ዓመታት ውስጥ ያለኝን አንድ ሱቅ ወደ ሶስት ሱቆች ማስፋፋት የሚል አይነት ውስን ግብ ያስቀምጣል።

2. ተነሳሽነት
ስኬታማ ሰዎች በጣም ከሚገለጹበት ባህሪያት አንዱ ተነሳሽነት ነው። ስኬታማ ሰዎች ግባቸውን ለማሳካት ጠንካራ ተነሳሽነት ሊኖራቸው ይገባል። ጠንካራ የተነሳሽነት ስሜት ያለው ስኬታማ ሰው፥ በችሎታው ስለሚተማመንና ግቡን ለማሳካት ስለሚፈልግ ያለ ድካም መስራት ይችላል።

3. ለመማር ፈቃደኛነት
ስኬታማ ሰው ሁሉን አውቃለሁ አይልም። ከሁሉም ሰውና ከሚያጋጥሙት ሁኔታዎች ሁሉ ለመማር የተከፈተ አእምሮ አለው። እያንዳንዱ ተሞክሮ ለማደግ አጋጣሚ እንደሚፈጥር ይረዳል። የማያውቀው ነገር እንዳለ ያምናል፥ አዲስ ነገር ለመማር ቦታ እንዳለው ሲገነዘብም እውቀቱን ለማሻሻል ይነሳሳል።

4. ታጋሽነት
ስኬታማ መሆን የምትፈልግ ከሆነ ትዕግስት ሊኖርህ ይገባል። ነገሮች ምንም ያህል አሁን እንዲሆኑ ብትፈልግ ሊደረስበት ዋጋ ያለውን ማንኛውም ነገር መጠበቅ ደግሞ ዋጋ አለው።

5. ስርዓት
ስኬት ወጥነት ይፈልጋል፥ ወጥነት እንዲኖር ደግሞ ስርዓት ሊኖር ይገባል። ብዙ ስኬታማ ሰዎች ህልማቸውን እውን ለማድረግና በጥረታቸው ውስጥ ወጥነት ያላቸው እንዲሆኑ የዕለት ተዕለት ተግባር ላይ መመስረት አንዱ ቁልፍ እንደሆነ ተገንዝበዋል።

ወጥነት ያለውና ሥርዓታማ በመሆንና ለማደግ ራስህን በመስጠት፣ በስራና በህይወት ውስጥ ብዙ ሽልማቶች እንድታገኝ ያደርግሃል። ይህ ሰዎች በሙያቸው ስኬትን ብቻ ሳይሆን ረጅም ዘመን ኖሯቸው እንዲደሰቱ የሚያስችል ቁልፍ ባህሪ ነው።


የስኬት መርሆዎች-Principles for Success

የስኬት መርሆዎች

09/07/2025

ከራስ በፊት ሌሎችን ለመለወጥ መሞከር ከንቱ ድካም...!

አንድ ጀርመናዊ ግለሰብ ነበር አሉ፡፡ ይህ ግለሰብ ዓለምን ለመለወጥ ፅኑ እምነት ነበረው። ምድርን ተለውጣ፣ የተሻለች ሆና ማየት ይመኝ ነበር፡፡ ቀበቶውን ጠበቅ አድርጎ ዓለምን ለመለወጥ በፅኑ ተነሳ። ለዓመታት ደፋ ቀና አለ። ረፍት የለሽ ስራ ውስጥ ገባ። በአታካች እንቅስቃሴ ተወጠረ። ነገር ግን ጠብ ያለ ነገር የለም።

“ምናልባትም ከዓለም በፊት አውሮፓን ለመለወጥ መነሳት ነበረብኝ!” አለና አውሮፓን ለመለወጥ ተነሳ። ዓመታት ቢማስንም ድካሙ የውሃ ሽታ ሆነ።

ተስፋ ሳይቆርጥ ቅድሚያ ሀገሩን ጀርመንን ለመለወጥ ወሰነ። በጣምም ደከመ። በሀገሪቱ ላይ ያመጣው ግን ምንም ለውጥ የለም። ግራ ተጋባ።

ከአካባቢዩ መጀመር አለብኝ ብሎ ወሰነ። እንዳሰበው አልሆነለትም። አይደለም የአካባቢው ማህበረሰብ በደሞዙ የሚያስተዳድራቸው ቤተሰቦቹ እንኳን ለውጥ ማሳየት አልቻሉም።

አንድ ችግር እንዳለ ተረዳ። ከራስ በፊት ሌሉችን ለመለወጥ መሞከር ከንቱ ድካም መሆኑን ተገነዘበ። በመስታወት ከሚያየው የግል ምስሉ ለመጀመር ወሰነ።...ራሱን ለመለወጥ ራሱ ላይ መድከሙን (ኢንቨስት ማድረጉን) ተያያዘው።

ምንጭ፦ ‘የሕይወት ግብህን ቅረጽ’ መጽሐፍ
ዝግጅት በኡስታዝ ያሲን ኑሩ

ታሪኩን አስተማሪ ሆኖ ካገኛችሁት ሌሎችም ይማሩበት ዘንድ ማድረግን አትርሱ 🙏

ከተመረጡ መፃሕፍት የምናገኛቸውን አስተማሪ ሃሳቦች የምናጋራበት ይህን 👉 ከምርጥ መፃሕፍት ገፆች የፌስቡክ ገፃችንን ብታደርጉት ታተርፋላችሁ።

"እናቴ በብዙ ርህሩህ ነበረች፤ ነገር ግን በድንገት ሳይታሰብ ታመመች" ይላል ለእናቱ ፈውስ ለመፈለግ አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ገብቶ ዘንድሮ የተመረቀው ወጣት ቅዱስ ኤፍሬም። እናቱ በድንገት ሰ...
08/07/2025

"እናቴ በብዙ ርህሩህ ነበረች፤ ነገር ግን በድንገት ሳይታሰብ ታመመች" ይላል ለእናቱ ፈውስ ለመፈለግ አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ገብቶ ዘንድሮ የተመረቀው ወጣት ቅዱስ ኤፍሬም።

እናቱ በድንገት ሰውነታቸው ፓራላይዝድ በመሆኑ እጃቸውም አልሠራ እንዳላቸው እና መናገርም እንደተሳናቸው ይገልጻል።

“ያም ሆኖ እያነከሰችም ቢሆን፣ እኔን ለማሳደግ ብዙ ውጣ ውረዶችን አልፋለች" ይላል ቅዱስ።

እኚህ በብዙ ውጣ ውረድ ውስጥ አልፈው ያሳደጉት እናቱ ታዲያ አንድ ቀን ሲያለቅሱ ያገኛቸዋል።

ምክንያቱ ደግሞ በአንድ የምርቃት ፕሮግራም ላይ በታደሙበት ወቅት በዙሪያቸው ያሉ ሰዎች ሲያናግሯቸው መልስ መመለስ ባለመቻላቸው ነበር።

“በወቅቱ እያነባች እንደምንም በዲፕሎማ ወደ ተመረቀችው ልጅ በመጠቆም ለማስረዳት ሞከረች” ይላል።

ነገሩ የገባው ልጅም ቁጭቱን በልቡ አድርጎ ለዚህ ሕመሟ መፍትሔ ለማግኘት እና እናቱን ለማስደሰት ቆረጠ።

“ከስምንት ዓመት በላይ በስትሮክ ሕመም የተጎዳችው እናቴን ለማስደሰት እና ለመርዳት ስል በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ትምህርቴን ለመማር ወሰንኩ” ሲል ቅዱስ ተናግሯል።

ቅዱስ ኤፍሬም የእናቱን ዕንባ ለማበስ በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የኢንዱስትሪያል ዲዛይን ትምህርት ክፍልን ተቀላቀለ።

ለአራት ዓመታት ዓላማውን ለማሳካት ፈተናዎችን ተቋቁሞ በመማር ለእናቱ በአጠቃላይም ለስትሮክ ታማሚዎች መፍትሔ የሚሰጥ ለእጅ እንቅስቃሴ የሚረዳ መሣሪያ ‘rehabilitation glove’ ሠርቷል።

የመመረቂያ ዲዛይን ፕሮጀክቱን ለእናቱ መፍትሔ ለመስጠት እና ለማኅበረሰቡ ለመድረስ የሠራው ሲሆን፤ "የቤቴን ችግር ለመቅረፍ የተማርኩት ትምህርት ለኢትዮጵያውያን ብቻ ሳይሆን ለአፍሪካም ጉልህ ሚና እንዳለው በተለያዩ ኩባንያዎች አስተያየት እየተሰጠኝ ነው" ብሏል።

የስትሮክ ታማሚ እናቱን በማሰብ መሣሪያውን የሠራው ቅዱስ፣ እጃቸው ፓራላይዝድ የሆነ ሰዎች ሰውነታቸው መሥራት እንዲችል የሚረዳ መፍትሔ ሠርቶ ተመርቋል።

እናቱም የድጋፍ መሣሪያውን ተጠቅመው እጃቸውን ማንቀሳቀስ ችለዋል።

የሠራውን የድጋፍ መሣሪያ ያዩ መምህሮቹም "እናትህ ወለደችህ፤ አንተ ደግሞ እናትህን ወለድካት" የሚል አስተያየት ሰጥተውታል።

“ከተሠራ የማይቻል የለም፤ እግዚአብሔር ብዙ አስችሎኛል” የሚለው ቅዱስ ኤፍሬም፣ ከጎኑ በመሆን ለደገፉት ሁሉ ምስጋናውን አቅርቧል።

via

የስኬት መርሆዎች-Principles for Success
የስኬት መርሆዎች

08/07/2025

👉ቶማስ ኤዲሰን ከአራት ወራት በኋላ ከትምህርት ቤት ተባረረ መምህሩ የአእምሮ ጉድለት እንዳለበት ገልጾለታል። በኋላም በታሪክ ውስጥ ከታላላቅ ሰዎች አንዱ ሆነ።

👉ቻርለስ ዳርዊን ህክምናን እንዲተው ጫና ተደረገበት፡ አባቱ በምሬት እንዲህ አለ፡- "አንተ ከቅዠቶች በስተቀር ምንም አታስብም!"በመጨረሻ በዝግመተ ለውጥ ጽንሰ-ሐሳብ ባዮሎጂን የኢቮሉሽን አብዮት አመጣ።

👉ዋልት ዲስኒ "የፈጠራ ክህሎት እጦት የታየበት" በሚል ከጋዜጣ ስራ ተባረረ። ከዚያም በዓለም ዙሪያ በትውልዶች የተወደደ የመዝናኛ ግዛት ገነባ።

👉የቤቴሆቨን የሙዚቃ አስተማሪ ፍፁም ተሰጥኦ የለሽ ብለውታል። በዓለም ላይ እጅግ ጊዜ የማይሽራቸው ድንቅ ስራዎችን ሰርቷል።

👉አልበርት አንስታይን እስከ አራት አመቱ ድረስ መናገር አይችልም ነበር እና መምህሩ የአእምሮ እክል እንዳለበት ገልፆታል።በታሪክ ከታላላቅ የሳይንስ ባለ አዕምሮዎች አንዱ ሆነ።

👉 አውግስጦስ ሮዲን የአርት ትምህርት ቤት መግቢያ ፈተና ሶስት ጊዜ ወድቆ "ደደብ" ተብሎ ተፈርጇል። ሮዲን አሁን ካሉት ታላላቅ ቅርጻ ቅርጾችን ከሚሰሩት ውስጥ የምንጊዜም ቀራጺ አንዱ ሆኖ ይከበራል።

👉ዲሚትሪ ሜንዴሌቭ በኬሚስትሪ አማካኝ ነጥብ ብቻ ቢያገኝም በኋላ ግን ፕሬዲክ ቴብል/predic table ሠርቷል።ሳይንስን በመሠረቱ ለውጦታል።

👉ታዋቂው የፎርድ አውቶሞቢል ፈጣሪ ሄንሪ ፎርድ ከመሰረታዊ እውቀት ጋር ታግሏል እናም እዚህ ከፍታ ላይ ከመድረሱ በፊት ብዙ ጊዜ ኪሳራን አስተናግዷል።

👉ማርኮኒ ሬዲዮን ፈልስፎ በአየር ላይ የሚተላለፉ ቃላትን ሲገልጽ ጓደኞቹ አእምሮው እንደተቃወሰ በማሰብ ወደ የአእምሮ ህክምና ባለሙያ ወሰዱት። ከወራት በኋላ የፈጠረው ፈጠራ በባህር ላይ ስፍር ቁጥር የሌላቸውን ህይወት አድኗል።

*መቼም ቢሆን የሌሎች ፍርድ ያንተን አቅም እንዲገልጽ አትፍቀድ።

ታላቅነት ብዙውን ጊዜ የሚጀምረው ከውድቀት ነው።

በራስህ መተማመንህን ቀጥል!

ሰዎች ያሉትን ይበሉ አንተ ግን እንደንስር ወደላይ ከፍ ማለትህን ቀጥል💡🎯💫

አስተማሪ ሆኖ ካገኛችሁት ሌሎችም ይማሩበት ዘንድ ማድረግን አትርሱ 🙏
—————————————————
አስተማሪ ሃሳቦች የምናጋራባቸውን የማህበራዊ ገፆቻችንን በመከተል ቤተሰብ ሁኑ። ታተርፋላችሁ:-

facebook 👉 የህይወት ፍልስፍና

tiktok 👉 https://www.tiktok.com/?_t=ZM-8xCEKgHbiuT&_r=1

Group 👉 የህይወት ፍልስፍና

08/07/2025

1. የሰው ልጆች በመጀመሪያ በውልደት ወደዚህ አለም ሲመጡ የመጀመሪያው አንድ ደቂቃ ከሚቀጥሉት አርባ አመታት በላይ የበለጠ ፋይዳ አለው። ምክንያቱም የመጀመሪያው አንድ ደቂቃ ከመሞት በፊት ያለው ትልቁ የህይወት ለውጥ ነው።

2. ፍርሃት የፈሪም የጀግናም መነሻ ነው። ፍርሃት ለፈሪ ጭንቀቱ ሲሆን፤ ለጀግና ደግሞ ጀብዱው ነው።

3. መማር ባለሙያ ያደርጋል፤ መኖር ደግሞ አዋቂ ያደርጋል።

4. ሰው የሆነውን የሚሆነው በአጋጣሚ አይደለም።አዋቂው ሰው ህፃኑ ልጅ በልጅ አዕምሮው የፃፈውን ተውኔት የሚተውን ተዋናይ ነው። የልጅ ጭንቅላት የተባለውን ይይዛል፤ አዋቂ ደግሞ የያዘውን ይተገብራል። አዋቂው ሲያለቅስ ወይም ሲያዝን እንደህፃን አባብይው።

5. ተስፋ የመኖር ምክንያት ነው።ሰውን እንዲኖር የሚያደርገው መለወጥ አለመለወጡ ሳይሆን የመለወጥ ተስፋው ነው። ቢሆንም ግን ህይወት ተከታታይ መሆኗን መገንዘብ ይጠቅማል። ዛሬ የምንኖረው በትላንት ምክንያት ነው።

6. ሰው መሆን ማለት ራቁታችንን ከተወለድን በኋላ፤ ከልብስ ጀምሮ አካላችንን ከሚሸፍኑት ሽፋኖች መላቀቅ ነው። ሰው ሰውነቱን የሚያጣው ራቁቱን ከእናቱ ማህፀን ሰው ሆኖ ተወልዶ በማህበረሰብ፣ በልብስ፣ በትምህርት፣ ሃይማኖት፣ በብሔር የመሰሉ ግዑዛን አልባሳትን በመደረብ ነው።

7. እውነተኛ ለውጥ የማይኖረው ሰው ስላልጣረና ስላልሞከረ ሳይሆን ለውጥ ሂደት እንጂ መድረሻ ስላልሆነ ነው።

8. ጎዳና ላይ የሚያድር ሰው ብርዱን ይለምዳል፣ ፀሃዩን ይታገሳል፣ አውሬ ያስለምዳል፤ ሰውን ግን ይፈራል። ቀኑን ሙሉ ብርድ ሳንፈራ ደረታችንን ገልጠን ራቁታችንን የምንውል ሰዎች፤ ልክ ሲመሽ የውጪ በር ቆልፈን፣ከዛ የሳሎን በር ቆልፈን፣ የጓዳ በር ቆልፈን፣ አልጋችን ውስጥ ገብተን ብርድልብስ ለብሰን፣ ብርድ ልብሱ እንዳይኮሰኩሰን አንሶላ ደርበን፣ አንሶላው እንዳይቀዘቅዘን የለሊት ልብስ ለብሰን ...በነዚህ ነገሮች ሁሉ ተከልለን እንተኛለን። ይህን እንዲሆን ደግሞ ያደረገው ፍርሃታችን ነው።

9. በታሪክ ውስጥ ትልቁ አምባገነን ታሪክ ራሱ ነው።ሁላችንም የታሪክ ተገዢዎች ነን።

10. የማታሸንፈውን ሰው ተጠያቂ ማድረግ የፈሪነት መፍትሔ ነው።

11. እውነት እኮ የጊዜና የቦታ ድምር ውጤት ነው። የራስን ሃሳብ ሌላው እንዲገባው ማድረግ ማለት ፤ የራሱን ሃሳብ ድንበር አልፈን የሃሳብና አስተሳሰብ ወረራ አካሄድን ማለት ነው።

12. የሚጠፋ ነገር ዐይንህ ስር ተቀምጦ ያለማየትን የመሰለ ዕውርነት የለም። አንዳንዴ ከሞት በኋላ ስለሚኖር መኖር እየጓጓን የውሸት ማመን የለብንም። ስለፀሎታችንን ምንነት በአንክሮ መፈተሽ ያስፈልጋል

13. ሰው የምታውቀው ፍጡር አይደለም። ሁልጊዜ ሰውን የምናውቀው ይመስለናል። እኔ ሐኪም ስከሆንኩና የአንድ ሰው አካል ቀድጄ ልቡን ስላየሁት ሰውን ያወኩት ይመስለኛል። ነገር ግን ሰው በየትኛውም ደረጃ የሚታወቅ ፍጡር አይደለም።

በደረቁ ሳይንስ አጥንተህ ሰው ውስጥ ያለውን ፕሮቲን እንዴት እንደሚሰራ ስላወቅህ ሰውን አውቃለሁ ማለት አይቻልም።

የመማር አንደኛው ችግር (በተለይ እኛ ሐገር) ቶሎ መታበይና የምናውቀው እውቀት እኛ ያመጣነው ሳይሆን ቀድሞ በሌሎች የተፈጠረ መሆኑን የመርሳት ችግር አለብን። እኛ ያወቅነው ከእኛ በፊት የመጡት የፈጠሩትን ነው። ይህንን እንረሳና እኔ ተምሬ ሳውቅ ራሴን አዋቂና ሐሳቡን እኔ የፈጠርኩት የመምሰል ችግር አለብን።

14. እያወቅክ ስትሔድ ትልቅልነትህን ሳይሆን ትንሽነትህን ነው የምትረዳው "

ብዙ ነገር ለመማር መሞከር እይታህን ያሰፋል። የእይታህ አድማስ ሲሰፋ ደግሞ አንተ እያነስክ ነው የምትሄደው። ሰፊ ከሆነው ዓለም ውስጥ አንተ ምን ያህል ኢምንት እንደሆንክ ትረዳለህ። እያወቅክ ስትሄድ ትልቅነትህን ሳይሆን ትንሽነትህን ነው የምትረዳው።

የትኞቹን ሃሳቦች ወደዳችኋቸው? አድርጉልን

አስተማሪ ሆኖ ካገኛችሁት ሌሎችም ይማሩበት ዘንድ ማድረግን አትርሱ 🙏
—————————————————
አስተማሪ ሃሳቦች የምናጋራባቸውን የማህበራዊ ገፆቻችንን በመከተል ቤተሰብ ሁኑ። ታተርፋላችሁ:-

facebook 👉 የህይወት ፍልስፍና

tiktok 👉 https://www.tiktok.com/?_t=ZM-8xCEKgHbiuT&_r=1

Group 👉 የህይወት ፍልስፍና

07/07/2025

አርቲስት ሸዊት ከበደ በሰይፉ ፋንታሁን ሾው ላይ ስለ ትዳር የሰጠችው አስተያየት ከብዙዎች ልብ የገባ ነው! 👏 '

ወንዶችን በማክበር መከበር አለ ብዬ አምናለሁ' ያለችው ሸዊት፣ በትዳር ውስጥ ወንድን ማክበር የግድ እንደሆነና እሱም ምላሹ ክብር መሆኑን አጥብቃ ትናገራለች።

ባል የቤቱ ራስ ተደርጎ መታየት እንዳለበት በማመን፣ ከመጠን በላይ ከመናገርና ከመደፋፈር መራቅ እንዳለብን ታሳስባለች።

በመጨረሻም የትዳር መሰረት
መከባበር መሆኑን አሳስባለች።

እናንተስ በእሷ ሀሳብ ትስማማላችሁ?
ሀሳባችሁን አካፍሉን

ምን ትላላችሁ?

የህይወት ፍልስፍና

05/07/2025

የኃይሌን የህይወት ፍልስፍና የሚዳስስ
መጽሐፍ 😮

የአትሌት ኃይሌ ገብረስላሴን የሚዳስሰው አዲስ መጽሐፍ በቅርቡ ለንባብ ይበቃል።

'የኃይሌ ኃይሎች' (Dissecting Haile) የተሰኘው ይህ መጽሐፍ የተጻፈው በልጁ ሜላት ኃይሌ ነው። በነሐሴ ወር መጨረሻ ላይም ለአንባብያን ይደርሳል!

:

* ጸሐፊ ✍️: ሜላት ኃይሌ
* የገፅ ብዛት: 247
ይህ መጽሐፍ በአትሌት ኃይሌ ገብረስላሴ የሕይወት ፍልስፍና ላይ የሚያተኩሩ 12 ምዕራፎች አሉት።

* #በአማርኛ፣ #በእንግሊዝኛ፣ እና #በብሬይል ቅርጸት የተዘጋጀ ነው።

ልጁ #ሜላት መጽሐፉን ለመጻፍ አንድ ዓመት እንደፈጀባት ገልጻ፣ የአባቷን ለወጣቱ ትውልድ ማስተማሪያ እንዲሆን ታስቦ እንደተዘጋጀ ተናግራለች።

: አትሌት ኃይሌ ገብረስላሴ በልጁ ሥራ እጅግ መኩራቱን ገልጾ፣ መጽሐፉ የእሱን ጉዞ ብቻ ሳይሆን ከጀርባው የነበሩትን ኃይሎች ጭምር የሚያሳይ መሆኑን ተናግሯል።

via Arada Fm

የህይወት ፍልስፍና [Philosophy of Life]

ትርጉም ያለው ኑሮ በመኖር በሥራና ኑሮህ ደስተኛ ለመሆን ከሁሉ አስቀድሞ ለህይወትህ ዓላማ አበጅለት። ዓላማ ሲኖርህ በየቦታው ለዓላማህ መዳረሻ የሚሆኑ፣ ጉዞህን አቅጣጫ የሚያሲዙ እና ፍጥነትህ...
05/07/2025

ትርጉም ያለው ኑሮ በመኖር በሥራና ኑሮህ ደስተኛ ለመሆን ከሁሉ አስቀድሞ ለህይወትህ ዓላማ አበጅለት።

ዓላማ ሲኖርህ በየቦታው ለዓላማህ መዳረሻ የሚሆኑ፣ ጉዞህን አቅጣጫ የሚያሲዙ እና ፍጥነትህን ለማስተካከል የሚረዱ ግብ እና ምዕራፎች ይኖሩሃል።

ዓላማ ያለው ህይወት እቅድና ግብ ሊኖሩት ያስፈልጋል። ዓላማ ያለው ህይወት እንዲሳካ ሥራ ይፈልጋል። ዓላማ ያለው ህይወት የሚሳካው በእቅድ ሲሠራ እንጂ የተገኘውን ሁሉ በመሥራት አይደለምና ሥራን አቅደህ ሥራ።

ማቀድ ትልቅ የሃሳብ ውጤት ነው። ሳያቅዱ በዘፈቀደ ህይወትን እንደአመጣጡ የሚኖሩ አሉ። ሳያቅዱ በምኞት የሚኖሩ አሉ። አቅደው የሚኖሩ አሉ። እቅዳቸውን በጽሁፍ አስቀምጠው በዝርዝር እየተከታተሉ የሚኖሩ አሉ። አንተ ከየትኛው ነህ?

አቅደህ፣ እቅድህን በጽሁፍ አስቀምጠህ፣ ዘወትር የእቅድህን አፈጻጸም እየተከታተልህና ማስተካከያ እያደረግህ የምትኖር ከሆነ አንተ ከዓለማችን 20% ሰዎች አንዱ ነህ።

ማደራጀት የሌለበት እቅድ ረጅም እድሜ የለውም። ሥራህን ለጥሩ አፈጻጸም እንዲመች እና ሥራን እንዲያቀላጥፍ አድርገህ አደራጅ። ሥራን በዘርፍ በዘርፍ፣ በክፍል ክፍል አድርጎ ማደራጀት እና ሁኔታው ሲቀየርም እንደገና አፍርሶ ማደራጀት የአዋቂዎች እና የብልሆች ተግባር ነው። ያቀድከውን ሥራ ለማስፈጸም ሥራህን በአግባቡ ማደራጀት እና እንደ ሁኔታው በተለያየ መልኩ የአደረጃጀት ቅያሪ እያደረግህ መምራትን እወቅበት። ሁኔታዎች ባሉበት አይቀጥሉምና ሁኔታ ሲቀየር አደረጃጀትን ወይም ሰውን መቀየር ቻልበት። ሁኔታዎች ቢቀየሩም የማይቀየረው ግቡ እንጂ የግብ መዳረሻ መንገድ እና አደረጃጀት ወይም በቦታው የተቀመጠው ሰው አይደለም።

ግብህን ለማሳካት እንዲያስችል አድርገህ ሥራህን በትክክል አደራጅ። ባደራጀኸው የሥራ መደብ ላይ ትክክለኛ እና ተገቢ ሰዎችን ማስቀመጥ እና ሁኔታዎች ሲቀያየሩም ያለ ይሉኝታ አደረጃጀትህን ወይም ሰዎችን መቀየር ከቻልህ አንተ ከዓለማችን 10% ሰዎች አንዱ ነህ።

ተግባር የእቅድ ነፍስ መዝሪያ ነው። እቅድን ተከትሎ መተግበር ብዙ ሰው ይቸገራል። መሥራት እና እቅድና የአደረጃጀት መስመርን ተከትሎ መሥራት የተለያዩ ጉዳዮች ናቸው። እቅድና የአደረጃጀት መስመርን ተከትለው ዘወትር ሳይታክቱ በግባቸው ነጥብ ላይ አትኩረው የሚሠሩ ሰዎች ጥቂት ናቸው። ሌላው ሲሄድ ሲመለስ፣ ሲጀምር ሲያቋርጥ፣ ከአንዱ ሥራ ወደ ሌላው ሲቀይርና ሲቀያይር እድሜውን የሚፈጅ ነው።

የጀመሩትን ሳይታክቱ ሠርተው ከሚያጠናቅቁት ውስጥ ለመሆን ትኩረት እና መስመርን መጠበቅ፣ ዘወትር ራስን ማነቃቃትና ማበርታት እና የአእምሮ መዛልና በአዳዲስ ምኞት ከመወሰድ እና ለችግር ከመንበርከክ ራስን መጠበቅ አስፈላጊ ነው። እነዚህ ሰዎች ከዓለማችን 4% ያህል ናቸው። እነዚህ ሰዎች ጎራ ውስጥ ለመገኘት የህይወት ዓላማ፣ ከፍ የለ የግብ እምነት እና ትኩረት፣ የማይናወጥ ዲሲፕሊን እና ብርቱ ጥረት ያስፈልጋል።

የሥራ አቅጣጫን ይዞ መሥራት ብቻውን ለስኬት በቂ አይደለም። አቅጣጫ የሌለው ፍጥነት ከመርበትበትና ትርጉም ከሌለው ዙረት ውስጥ የሚመደብ ነው። አቅጣጫውን ሳታውቅ አትፍጠን። ስትፈጥን በትክክለኛው መስመር ውስጥ ፍጠን። ያለመስመርህ ከምትፈጥን በትክክለኛው መስመር ውስጥ ቀስ ብለህ ብትጓዝ ይሻላል። ሆኖም በትክክለኛው መስመር ውስጥ ቀስ ብሎ መጓዝ ብቻውን በቂ አይደለም። ሁኔታው ተቀይሮ መንገዱ በዝናብ በረዶና ጎርፍ እንዲሁም ናዳ ከመዘጋጋቱ በፊት ፈጥነህ ገና ጠዋት ሳለ በረሃውን አቋርጥ። ትክክለኛ መስመር ውስጥ ከሆንክ ምን ያዘገይሃል? በትኩረት ወደፊት ገስግስ። በትክክለኛ መስመር ውስጥ ከሆንክ ወለም ዘለም ሳትል የጉዞህን ፍጥነት እየለካህ በትክክለኛው ፍጥነት ወደፊት ገስግስ። ዘግይተህ ከሆነ ፍጥነትህን ጨምር። እንዲህ ያሉ የጉዟቸውን ትክክለኛ አቅጣጫ ይዘው ፍጥነታቸውን እየለኩና እያስተካከሉ በግባቸው ላይ አትኩረው የሚጓዙ ሰዎች እጅግ ጥቂት ናቸው። እነዚህ 1% ናቸው። አንተ ከእነዚህ 1% ሰዎች ውስጥ ነህ?

ዋረን በፌትን ተመልከት! ዳላይ ላማን ተመልከት! ቢኒያም በለጠን ተመልከት!

እነዚህ 1% ሰዎች ህይወታቸውን ያለ ግርግር እና ጭንቀት የሚመሩ ናቸው።

እነዚህ ሰዎች ግባቸው አንድ ነው። ትኩረታቸውም ግባቸው ላይ ነው።

አትበታተን!

✍️ Get Thoughe Zer

የስኬት መርሆዎች-Principles for Success

የስኬት መርሆዎች

የስኬት መርሆዎች-Principles for Success
05/07/2025

የስኬት መርሆዎች-Principles for Success

04/07/2025

1. ‹‹የዘጠኝ ወር እርጉዝ በማግባት በአንድ ወር የራስህን ልጅ ልትወልድ አትችልም››

2. ‹‹ዛሬ ዛፍ ጥላ ስር የምንቀመጠው የሆነ ጊዜ ላይ የሆነ ሰው ዛፉን ስለተከለው ነው፡፡››

3. ‹‹ዝናህን ለመገንባት ሃያ ዓመት ይወስድብሃል፡፡ ዝናህን ለማበላሸት ግን ሃያ ደቂቃ በቂህ ነው፡፡ ይሄን ጉዳይ ካሰብክ ነገሮችን በተለያየ መንገድ ታከናውናቸዋለህ፡፡››

4. ‹‹ባልገባህ ቢዝነስ ላይ ኢንቨስት አታድርግ››

5. ‹‹ስጋት ወይም ፈተና የሚመጣው የምትሰራውን ባለማወቅ ነው፡፡››

6. ‹‹በአንድ ገቢ ብቻ ጥገኛ አትሁን፡፡ ሁለተኛ የገቢ ምንጭ ፍጠር››

7. ‹‹በአሜሪካ ቢዝነስ ቁጭ ብሎ ማሰብ ያልተለመደ ነው፡፡ እኔ ግን ብዙ ጊዚዬን የማጠፋው ቁጭ ብዬ በማሰብ ነው፡፡

8. ‹‹በጣም አስፈላጊው ኢንቨስትመንት በራስህ ላይ የምታደርገው ነው፡፡››

9. ‹‹የማትፈልገውን የምትገዛ ከሆነ የምትፈልገውን ወዲያው ትሸጣለህ፡፡››

10. ‹‹ከመጥፎ ሰው ጋር ጥሩ ውል ማሰር አትችልም፡፡

11. ‹‹ደስተኛ ሰዎች የሚደሰቱት ምርጥ ነገር ስላላቸው አይደለም፡፡ እነሱ የሚደሰቱት ያላቸውን ነገር አክብረውና ወደው ስለያዙ ነው፡፡

12. ‹‹በመኝታህ ሰዓት ገንዘብ ለማግኘት አስበህ አዲስ መላ ካልፈጠርክ እስክትሞት ትሰራለህ፡፡

13. ‹‹አጥፍተህ የቀረህን አትቆጥብ፡፡ ከቁጠባ በኋላ የተረፈህን አጥፋ፡፡››

14. ‹‹ብዝሃነት ወይም ሁለገብ ዕውቀት ከመሐይምነት ይከላከላል፡፡

15. ‹‹ታማኝነት በጣም ውዱ ስጦታ ነው፡፡ ይሄን ስጦታ ከርካሽ ሰዎች አትጠብቅ፡፡››

16. ‹‹ያልተለመደ ከሆነ ሰዎች ብዙ ጊዜ ትክክለኛውን ነገር ከመስራት ሊያስቆሙህ ይሞክራሉ፡፡

17. ‹‹በዓለም ላይ ሐይል ያለው ምንም ቅድመ ሁኔታ የሌለው ፍቅር ነው፡፡

18. ‹‹ሁልጊዜም ሐብት ማግኛ ምርጡ መንገድ ለራስህ ዋጋ መስጠት ነው፡፡

19. ‹‹አነባለሁ፣ አነባለሁ፣ አነባለሁ! በቀን ውስጥ ከአምስት እስከ ስድስት ሰዓት ድረስ አነባለሁ፡፡››

20. ‹‹ብዙ በተማርክ ቁጥር ብዙ ታገኛለህ። ››

ብዙ ለመማር ዝግጁ ከሆናችሁ አስተማሪ ሃሳቦች የምናጋራባቸውን የማህበራዊ ገፆቻችንን በመከተል ቤተሰብ ሁኑ። ታተርፋላችሁ:-

facebook 👉የህይወት ፍልስፍና

tiktok 👉 https://www.tiktok.com/?_t=ZM-8xCEKgHbiuT&_r=1

Group 👉 የህይወት ፍልስፍና [Philosophy of Life]
------------------------
የትኞቹን አባባሎች ወደዳችኋቸው? አድርጉልን

አስተማሪ ሆኖ ካገኛችሁት ሌሎችም ይማሩበት ዘንድ ማድረግን አትርሱ 🙏

Address

Addis Ababa

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when የስኬት መርሆዎች-Principles for Success posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share