የስኬት መርሆዎች

የስኬት መርሆዎች ከታላላቅ ሰዎች የህይወት ተሞክሮ!!!

26/10/2025

ማህበረሰብ ግቡ ሰው ማፍራት ነው ፤ አካላዊ እና ህሊናዊ ጤንነቱ የተሟላ ደስተኛ ግለሰብ ፤ የሚያስብ ግለሰብ ። እንዲህ አይነት ሰው ማፍራት የቻለ ማህበረሰብ በተራው ፖለቲካዊ እና ማህበረ-ባህላዊ ጤንነቱ ይጠበቃል ፤ ህልውናው ፈተና ላይ አይወድቅም ። ግለሰብ የማያፈራ ማህብረሰብ ማህበራዊ መሰረቱ እንደተጠበቀ ሊቀጥል ያዳግተዋል ይፈራርሳል ።



ሰውን ያላፈራ ማህበረሰብ የሚጠበቅበትን ሀላፊነት ሊወጣ አይችልም ። ማህበራዊ ሀላፊነቶች የግለሰብ ተግባራት ናቸው ። "ህዝቡ እንዴት ዝም ይላል?" "ህዝቡ እንዴት አያምጽም?" ...እያልን የምናላዝነው ፣ እንደማህበረሰብ መንፈሳዊ እና አካላዊ ጤንነቱ የተጠበቀ ፣ ሀላፊነቱን የሚያውቅ ፣ ግዴታውን የሚወጣ ሰው ስላላፈራን ነው ። የሚናገር ሰው ያላፈራ ማኅበረሰብ አይናገርም ። ግፍን የሚጸየፍ ሰው ያላፈራ ማኅበረሰብ አያምጽም ። አበበች ጎበናን ያላፈራ ማህበረሰብ ህፃናቱን ሰብሳቢ አያገኝም ። ቢንያም በለጠን ያላፈራ ማህበረሰብ አዛውንቱን ጎዳና ይበትናል ።



ማህበረሰብ መጽሐፍ ነው ፣ እያንዳንዱ ግለሰብ ደግሞ የመጽሐፉ አንድ ገጽ ። የማህበረሰብን መጽሐፍ ስታነብ የምታነብበው እያንዳንዱን ግለሰብ ነው ። የእያንዳንዱ ገጽ ጽሑፍ አንድ አይደለም ፤ ርኩስ እና ቅዱስ _ ፍቅር እና ጥላቻ _ ድብልቅ ነው ። ማህበረሰቡ አድምቆ የፃፈው፣ ጎልቶ እንዲነበብ የፈቀደለት መልኩን እንዲመስልለት የመረጠው የትኛው ገጽ ነው? የሚለው ነው ዋናው ። ርኩሱ ወይስ ቅዱሱ? ጥላቻው ወይስ ፍቅሩ? ስስቱ ወይስ ቸርነቱ? የሂትለርን ገጽ ያደመቀ ማህበረሰብ "ናዚ ጀርመንን" ሆኖ ተነብቧል ። በተቃራኒው እነ አብረሀም ሊንከን ፣ ማርቲን ሉተር ኪንግ ፣ ማህተማ ጋንዲ....የኖሩበትን ማህበረሰብ በበጎ ያስነበቡ አንዳንድ ገጾች ናቸው ።



የማህበረሰብ ልእልና የሚጻፈው በግለሰቦች ላይ ነው ። ደርግ "ታሪክ ሰሪው ሰፊው ህዝብ ነው!"ን እየፎከረ ፣ ህወሀት "ብሔር ብሔረሰብ"ን እየዘመረ ሰው ሳያፈሩ ቀሩ ። የማህበረሰቡ ልእልና የሚፃፍበት ገጽ አጣ ። አብዛኛው የማህበረሰባችን ገጽ የውድቀታችን እና የሽንፈታችን መጻፊያ ሆነ ። ሰው ያላፈራ ማህበረሰብ ሀሳብ ሊኖረው አይችልም ...መዝሙር እና መፈክር እንጂ! ማሰብም ሆነ ማብሰልሰል የሰው እንጂ የማህበረሰብ ሀብት አይደለም ። አሳቢ ሰው ያፈራ ማህበረሰብ ያስባል ፤ ብሔርብሄረሰብ ያፈራ ማህበረሰብ ብዙ መዝሙር እና መፈክር ይኖረዋል ፤ የሚያሳዝነው መዝሙሮቹ እና መፈክሮቹም ሀሳብ የላቸውም ፤ ሰው የሌለው ማህበረሰብ ሀሳብ ከየት ያመጣል ። አንድ ማህበረሰብ ሀላፊነቱን እንዲወጣ አሳቢ ሰው ያስፈልገዋል ።


.. እንደ ማህበረሰብ ለመቀጠል ሰው ያስፈልገናል ።

✍ በድሉ ዋቅጅራ (ዶ/ር) የህይወት ፍልስፍና የህይወት ፍልስፍና

የስኬት መርሆዎች
26/10/2025

የስኬት መርሆዎች

   #ከታላቁ የአለማችን_ስኬታማ_ሰው  1.  #ለተሳካ ሕይወት ምስጢር ዓላማችንን መፈለግ እና ከዚያ ማድረግ ነው።2.  #አንድ ሰው ሊያደርጋቸው ከሚችላቸው ታላላቅ ግኝቶች ውስጥ አንዱ በጣም...
25/10/2025

#ከታላቁ የአለማችን_ስኬታማ_ሰው

1. #ለተሳካ ሕይወት ምስጢር ዓላማችንን መፈለግ እና ከዚያ ማድረግ ነው።

2. #አንድ ሰው ሊያደርጋቸው ከሚችላቸው ታላላቅ ግኝቶች ውስጥ አንዱ በጣም ከሚደነቅባቸው ነገሮች መካከል እሱ ማድረግ የማይችለውን የፈራውን ነገር ማድረግ መቻሉ ነው።

3. #አንድ ሃሳባዊ ሰው ሌሎች እንዲበለፅጉ የሚረዳ ሰው ነው።

4. #አለመሳካቱ እንደገና ለመጀመር አዲስ አጋጣሚ ነው ፣ በዚህ ጊዜ የበለጠ ብልህነት ይኖራል።

5. #ውድቀት አንዳንድ ጊዜ ከስኬት የበለጠ ፍሬያማ ነው፡፡

6. #በሚቀጥለው ዓመት ዓለም ምን እንደሚያደርግ በትምህርት ቤት ውስጥ መማር አትችልም።

7. #የእኔ ምርጥ ጓደኛዬ በውስጤ ምርጡን የሚያወጣው እሱ ነው።

8. #ብቸኛው እውነተኛ ስህተት እኛ ምንም የማንማርበት ስህተት ነው።

9. #እኔ አዲስ ነገር አልፈጠርኩም። እኔ በቀላሉ ለዘመናት የሠሩትን የሌሎች ሰዎች ግኝቶችን ሰብስቤያለሁ ፡፡

10. #መካከለኛነት የብልጽግና በጣም መጥፎ ጠላት ነው ፡፡

11. #በሕይወት ውስጥ ወደፊት ስንራመድ የአቅማችንን ወሰን እንማራለን።

12. #የሚቻለውን እና የማይቻለውን በትክክል ለመናገር በቂ እውቀት ያለው ሰው ላገኝ አልችልም።

13. #ብዙ ሰዎች ችግሮችን ከመፍታት ይልቅ በችግሮች ላይ ሲያንዣብቡ ብዙ ጊዜ እና ጉልበት ያጠፋሉ።

14. #መማርን የሚያቆም ሁሉ ዕድሜው በሃያም ይሁን በሰማንያ ነው። መማርን የቀጠለ ሁሉ ወጣት ሆኖ ይቀራል ፡፡

15. #በሐቀኝነት ውድቀቶች ውስጥ እፍረት አይኖርም፣ውድቀትን በመፍራት ግን እፍረት አለ ፡፡

16. #ትልቅ ችግሮች የሉም ፣ በጣም ብዙ ትናንሽ ችግሮች ብቻ ናቸው።

17. #አንድን ነገር በአዕምሮ ውስጥ በግልፅ ለማየት ፣ ቅርፅ መያዝን እንዲጀምር አድርግ።

18. #ነገ በጭራሽ አይመጣም ብለን ባሰብን ጊዜ ቀድሞ ትናንት ሆኗል ፡፡

19. #ወግ አንፈልግም ፡፡ በአሁኑ ጊዜ መኖር እንፈልጋለን እናም ዋጋ ያለው ብቸኛው ታሪክ ዛሬ የምንሰራው ታሪክ ነው ፡፡

20. #ትልቁ የካፒታል አጠቃቀም ብዙ ገንዘብ ለማግኘት መስራት ሳይሆን ገንዘብን ሕይወት ለማሻሻል የበለጠ እንዲሠራ ማድረግ ነው፡፡

21. #አስፈላጊነቱ ካልተሰማው ማንም አይለወጥም።

22. #ተፈላጊ እና ትክክለኛ የሆነው ፈጽሞ የማይቻል ብለን የምናስበው ሃሳብ ነው።

የትኞቹ አባባሎች ተመቿችሁ? አድርጉልን

አስተማሪ ሆነው ካገኛችኃቸው ሌሎችም ይማሩባቸው ዘንድ እያደረጋችሁ🙏

የስኬት መርሆዎች

የስኬት መርሆዎች

1. ደስታህን በእምነትህ እንጂ በገንዘብህ ለማግኘት አትሞክር። እምነት ሲኖር ሁሉን ማግኘት ይቻላልና።2. ንግግርህን አሳንሰህ ተግባርና ምልከታህን አብዛ — እውነተኛ ኃይል ዝምታ ውስጥና ስራ...
25/10/2025

1. ደስታህን በእምነትህ እንጂ በገንዘብህ ለማግኘት አትሞክር። እምነት ሲኖር ሁሉን ማግኘት ይቻላልና።

2. ንግግርህን አሳንሰህ ተግባርና ምልከታህን አብዛ — እውነተኛ ኃይል ዝምታ ውስጥና ስራ ላይ ነውና።

3. የወዳጆችህን ክበብ ትንሽ አድርግ፣ ምስጢሮችህን ደግሞ ከዛም በላይ ጥብቅ አድርግ።

4. በሁሉ ነገር አትከራከር — ውጤቶችህ ብቻ ይናገሩ።

5. ንዴትህን ተቆጣጠር — የጠላትህ ምርጥ ሰላይ እሱ ነውና።

6. እነሱ የሚከተሉት ጥሩ ሰው ሁን እንጂ በፍጹም አታሳድድ ።

7. ደግና ጠንካራ ሁን ነገር ግን በፍጹም ልፍስፍስ አትሁን።

8. ትኩረትህን እንደ ገንዘብ በልክ ስጥ — ሁሉም ሰው ሊገዛው አይችልምና።

9. በጣም አስከፊ ቀናትህ ላይ እንኳ እንደ ስኬታማ ሰው ተላበስ።

10. ቦታው ያንተ ባይሆንም እንኳ ፈገግታህን ቀንሰህ ግርማ ሞገስህን ጨምረህ የራስህ እንደሆነ አስመስለህ ተራመድ።

11. ሳይጠበቁህ ብቅ በል — ከዚያም በበለጠ ፍጥነት ከእይታ ስወር በል በእዚያ ቅፅበት ብዙ ነገር ታገኛለህና።

12. በዝምታ ራስህን ገንባ — ድምፅህን ከፍ አድርገህ የምትፎክረው አንድ ጊዜ ብቻ ይሁን።

13. ግድ ቢሰጥም ባይሰጥም እንዲገምቱ አድርጋቸው። ከግምታቸው ብዙ ጠቃሚ ፍንጭ ትማራለህና::

14. ያደረግኸውን ፈጽሞ አታብራራ — አድራጊዎች ብዙ አይናገሩም።

15. ፈጣን ምላሽ አትስጥ — ነገሥታት እኮ እነሱ እንዲጠብቋቸው ያደርጋሉና።

16. በጩኸት ሳይሆን በዝምታህ አደገኛ ሁን።

17. እንደ እሳት ተወዳጅና ተፈሪ ገፅታ ይኑርህ፣ እንደአስፈላጊነቱ በአንዱ ገፅታህ ተገልጠህ ለሚወዱህ ማብሰያ፣ ለሚጠሉህ ማቃጠያ ትሆናለህና።

18. ሁልጊዜ ስንፍናህን ወደ ኃይል ለውጥና ታታሪ ሁን።

19. ስምህ ከህልውናህ የበለጠ ክብደት እንዲኖረው አድርግ።

20. ስትሄድ ትዝታን ሳይሆን አሻራን ትተህ እለፍ።

የስኬት መርሆዎች
የስኬት መርሆዎች

24/10/2025

ክረምት ከበድ ሲል ርግብ ዝም ትላለች
በረዶ ሲጨምር ርግብ ትጠፋለች
የተፈጥሮን ሂደት ጠንቅቃ ታውቃለች
ርግብ አስተዋይ ነች ጊዜን ትረዳለች

የነፋሱ ፉጨት
የድምፁ ማዕበል የዝናቡ ፍጥነት
ጋብ እስኪል ወጀቡ የወጨፎው ጉልበት
ርግብ ትጠፋለች
ርግብ አስተዋይ ነች ጊዜን ትረዳለች

ሁሉን የፈጠረ
በቦታዉ ያኖረ
ጊዜን የቀመረ
የጊዜው ባለቤት ሁሉን የሚያዝበት
'ድምፅሽን አሰሚኝ ውዴ ውጪ' እስኪላት
በድንጋዩ ስንጥቅ ባለቱ ንቃቃት
አጮልቃ እያየች ፀሐይ እስክትወጣ
ርግብ ዝም ትላለች ንጋት እስኪመጣ

ሁሉ ውብ ሚሆነው
ሁሉ ልክ ሚሆነው
ሁሉ በጊዜው ነው
ለሁሉ ጊዜ አለው

ርግቤ እህቴ ወዳጄ ዝምታሽ ይሰማል
ዝምታሽ ድምፅ አለው ዝምታሽ ይጮሀል
ዝምታሽ ሀይል አለው ጊዜን ይናገራል

ሀይልን በሚሰጠኝ ብለሽ ያወጅሽለት
ሀይልን ይስጥሽ እና
ጊዜን ይስጥሽ እና
ክረምት ሰማይሽን ቶሎ ይልቀቅና
አበቦች ሲታዩ ዳግም በምድር ላይ ዳግም እንደገና
ድምፅሽን እንስማው ርግቧ እንደገና

✍ገጣሚ- ፍሬዓለም ሺባባው (የእጅግአየሁ ሽባባው ታላቅ እህት)
የህይወት ፍልስፍና

 :- ፍላጎት (Desire) የመጀመሪያው የስኬት መርህ ፍላጎት ነው። ከልብ የመነጨ ፍላጎት። ፍላጎታችንን እንደ ዘር ልናየው እንችላለን። ፍሬ እንደሚያፈራ አምነን የምንዘራው ዘር። ነገር ግን...
24/10/2025

:- ፍላጎት (Desire)

የመጀመሪያው የስኬት መርህ ፍላጎት ነው። ከልብ የመነጨ ፍላጎት። ፍላጎታችንን እንደ ዘር ልናየው እንችላለን። ፍሬ እንደሚያፈራ አምነን የምንዘራው ዘር። ነገር ግን ዛሬ ዘርተነው ዛሬውኑ ፍሬ የሚሰጠን ተክል የለም።

ፍላጎታችንም ልክ እንደ በቆሎ ወይም ማንኛውም ዘር ዛሬ ተዘርቶ በቂ ውሃ፤ በቂ ጸሃይ፤ በቂ እንክብካቤ ፤ካገኘ በኋላ በግዜው የሚያሽት ነው።

የምንፈልገውን ነገር ጥርት ባለ መልኩ ማወቁ ይጠቅመናል። ለመረጥነው ነገር ምን ያህል ፍላጎት እንዳለን ለማወቅ የምናደርጋቸውን ነገሮች መቃኘት ያስፈልገናል። ከምንም በላይ በውስጣችን ያለው የትዕግስት መጠን ፍላጎታችን ምን ያህል እንደሆነ ያስረዳናል።

ለምሳሌ ሰዓሊነት ፍላጎቱ የሆነ ሰው ባይከፈለው እንኳን ስዕል መሳሉን አያቆምም። አላማ ብለን ለመረጥነው ነገር በቀላሉ ሊገደብ የማይችል ፍላጎት ሊኖረን ይገባል። ጥልቅ ፍላጎት ማለት ወደኋላ እንዳናፈገፍግ የመመለሻውን ድልድይ እንደማቃጠል ያህል ነው።

:- እምነት (Faith)

እምነት አላማችን የሚገነባበት መሰረት ነው። የምንፈልገው ነገር ምንም ይሁን ምን እምነት ከሌለን ነዳጅ የሌለው መኪናን ለመንዳት እንደመሞከር ይሆንብናል። ደግነቱ እምነት በመጀመሪያ ባይኖረንም፤ በሂደት ልንገነባው የምንችለው ጥበብ ነው።

ለአእምሮአችን ቀና የሆኑ ነገሮችን በመመገብ እምነትን በሂደት ማዳበር ይቻላል። የምንፈልገውን ነገር ለማግኘት እምነት እጅግ ወሳኝ ነገር መሆኑን መዘንጋት የለብንም። ማርቲን ሉተር ኪንግ ስለ እምነት ደስ የሚል አባባል አለው ” እምነት ማለት ሙሉውን ደረጃ እስከየት እንደሚያደርሰን ባናውቅም እንኳ የመጀመሪያውን ደረጃ መውጣት ነው” ይላል።

:- እራስን ማሳመን (Auto Suggestion-አውቶ ሰጀሽን)

አእምሮአችን እውነት ብሎ የሚቀበለው ነገር ደጋግመን የምንመግበውን ነው። እዚህ ላይ ይህንን በደንብ የሚያስረዳ አንድ ታሪክ ትዝ አለኝ። ታሪኩ እንዲህ ነው

ሁለት ውሾች የነበሩት አንድ ሰው ነበር። አዘውትሮ እኒህን ውሾች አደባባይ እየወሰደ እንዲደባደቡ ያደርግ ነበር። ታዲያ ተመልካቾቹ የትኛው ውሻ በእለቱ እንደሚያሸንፍ ሲጠይቁት “በደንብ የምመግበው ውሻ ነው” ሲል መለሰላቸው። ሁላችንም ውስጥ ሁለት ዉሾች አሉ የመልካም እና የክፋት፤ የልማት እና የጥፋት፤ የእውቀት እና የድንቁርና፤ የውድቀት እና የድል ውሾች። የበላይ ሆኖ የሚመራን ውሻ ዘወትር የምንመግበው ነው።

ለዚህ ነው ናፖሊዮን ሂል “አውቶ ሰጀሽን” ወይም ለራስ መልካም ነገሮችን ደጋግሞ በመንገር አእምሮአችንን ወደፈለግነው መንገድ መምራት እንደምንችል የሚነግረን። መንገር ብቻም ሳይሆን የሚያሳስበን!

:- በአንድ ነገር ላይ እራስን የተካኑ ማድረግ (ስፔሻላይዝድ ኖውሌጅ)-

ልንሰማራበት በመረጥነው ወይም ፍላጎት ባለን ሙያ ላይ የተሰማሩ ሰዎችን መተዋወቁ እና ቅርርብ መፍጠሩ ወሳኝ ነገር ነው። ጊዜያችንን የምናሳልፈው ከነማን ጋር ነው? የምናውቃቸው ሰዎች ወይም ጓደኞቻችን ለምንፈልገው ሙያ የሚያግዙን ናቸው?

ለምሳሌ:- ፕሮፌሰር ለመሆን ፍላጎት ያለው ሰው በተቻለው መጠን ዩንቨርሲቲ አካባቢ ካሉ ሰዎች ጋር ግንኙነቱን ቢያዳብር ይጠቅመዋል። ተዋናይ መሆን የሚመኝ ሰው እራሱን ከቲያትር መድረክ አካባቢ ማራቅ የለበትም። ሁላችንም የምንማረው ቀድመውን ካወቁት ነውና፤ የምንፈልገውን ነገር በቅጡ የሚያውቁ ሰዎችን ማወቁ ይጠቅመናል።

:- ነገሮችን በህሊናችን መሳል- (Imagination)
ሁሉም ነገር ሃሳብ ነበር። ምንም ነገር እውን ሆኖ ከማየታችን በፊት በአንድ ሰው አይምሮ ውስጥ የተጠነሰሰ ሃሳብ ነበር። የምንፈልገውን ነገር እውን ሆኖ ከማየታችን በፊት በህሊናችን መሳል ትልቁ የስኬት ሚስጥር እንደሆነ ብዙዎች የተስማሙበት ነው። አላማችን ቁልጭ ብሉ በህሊናችን ከታየን ለጉዟችን ትልቅ ጉልበት አገኘን ማለት ነው። ምክንያቱም የጊዜ ጉዳይ ነው እንጂ እንደሚሳካ አእምሮአችን እየነገረን ነው።

:- እቅድ ማውጣት- (Organized planning)

እቅድ ማውጣት ጊዜን በአግባቡ እንድንጠቀም ከማድረጉም በላይ፤ በአንድ ጊዜ አንድ ደረጃ እየወጣን ጉዟችን አድካሚ እንዳይሆን ያደርግልናል። እቅድ ስናውጣ ነገሮች ሳይደራረቡብን ቀስ በቀስ ወደ ግባችን እንደርሳለን።

እቅድ ስናወጣ ግን እራሳችንን በሚያጨናንቅ እና ካልፈጸምነው የጥፋተኝነት ስሜት እንዲሰማን በሚያደርግ ሁኔታ ሳይሆን፤ ከጊዜያችን ፤ ከባህሪያችን እንዲሁም ከማንነታችን ጋር የሚስማማ እቅድ ነው ማውጣት አለብን። ምክንያቱም ሌላው ያቀደበት መንገድ ለኛ ላይስማማ እና ከግባችን ላያደርሰን ስለሚችል ነው።

:- ውሳኔ (Decision)

የሰው ልጅ ውድቀት አንደኛው መንስዔ የውሳኔ ማጣት ነው። አንድ ሰው ምንም ያህል እምቅ እውቀት ቢኖረው፤ ምንም ያህል የሚያስደንቅ ሃሳቦችን ማመንጨት ቢችልም ውሳኔ መወሰን ካልቻለ ግን አቅሙ ሁሉ ከውስጡ አይወጣም።

ውሳኔ በማጣት የተነሳ ብዙ ሙዚቃዎች ሳይሰሙ፤ ብዙ መጽሐፎች ሳይጻፉ፤ ብዙ ግኝቶች ሳይገኙ፤ ወደ መቃብር ይወርዳሉ።.በሁላችንም ውስጥ ለኛ ብቻ የተሰጠ ስጦታ አለ፤ ይህን ስጦታ ግን አውጠን ሌሎች እንዲያዩት ማድረግ የምንችለው ውሳኔ መወሰን ስንችል ብቻ ነው። የምንወስነው ምንድን ነው ካላችሁ፤ መልሱ የምንወስነው መሆን የምንፈልገውን ነው።

:- ጽናት (Persistence)

ውሳኔ ብቻውን አቅም የለውም። ውሳኔያችን ባህሩን አቋርጦ ከአላማችን ዳርቻ እንዲደርስ የሚያደርገው ሃይል ጽናት ነው። ብዙዎቻችን የተለያዩ ውሳኔዎችን እዚህና እዚህ እንወስናለን ነገር ግን ጽናት ኖሮን አንገፋበትም።

ለዚህ ነው ናፖሊዮን ሂል የውድቀት እና የስኬት ዋናው መለያ ጽናት ነው ያለው። ለምሳሌ ከመጠጥ ሱስ መላቀቅ የሚፈልግ ሰው መቶ ጊዜ ለማቆም ቢወስንም ከውሳኔው ጋር ጽናት ካልተደመረበት በቀር ውሳኔው ብቻውን ምንም ዋጋ የለውም። ስለዚህ በውስጣችን ያለውን የጽናት መጠን መፈተሹ እጅግ ወሳኝ ነገር ነው።

:- ጥምር ሃይል (Power of the master mind)

“ሁለት ጭንቅላቶች አንድ ላይ ሲሆኑ ሶስተኛ ጭንቅላት ይወለዳል”። አንድ ሰው የራሱ የሆነ ሃሳብ ወይም ግኝት ሊኖረው ይችላል፤ ከሌሎች ሰዎች ሃሳብ ጋር ሲደመር ደግሞ ይበልጥ ይሰምራል።

“ከአንድ ብርቱ ሁለት መድሐኒቱ” እንዲል የሃገራችን ሰው በጋራ የመስራትን ልምድ ማዳበር መቻል አለብን። አብሮ መስራት መቻል ትልቅ ክህሎትም ጭምር ነው።

:- የምታደርገው ነገር ደስታን ሊስጠህ ይገባል– (Enthusiasm)

ስቲቭ ጆብስ በህይወት በነበረበት ወቅት እንዲህ ብሎ ነበር “የምንሰራውን ነገር የማንወደው ከሆነ እስከመጨረሻው ለመሄድ አንችልም፤ የሚሰራውን የማይወድ ማንኛውም ሰው ተስፋ ቢቆርጥ አይፈረድበትም”።

እውነት ነው የምንወደውን ነገር ስናደርግ በቀላሉ ተስፋ አንቆርጥም። ሙያችን እንዲሆን የምንመርጠው ነገር የምንወደው ነገር ከሆነ በዛ ነገር ላይ እውቀታችንን ለማዳበርም ሆነ ልምድ ለማግኘት ፍላጎት ይኖረናል።

ለምሳሌ ሰውን መርዳት የማይወድ ወይም ለሰው ምንም ግድ የለለው ሰው የህክምና ባለሙያ ቢሆን፤ በሽተኞቹን እንደ ገንዘብ ማግኛ ከመቁጠር በቀር ለጤንነታቸውም ሆነ ለደስታቸው ደንታ አይሰጠውም። ስለዚህ የምንሰራው ነገር ምን ያህል ደስታ ወይም እርካት ይሰጠናል? የሚለው ጥያቄ በተሰማራንበት መስክ ሁሉ እራሳችንን ልንጠይቀው የሚገባ ጥያቄ ነው።

የፌስቡክ ገፃችንን በማድረግ ቤተሰብ ይሁኑ

👉 የስኬት መርሆዎች

የስኬት መርሆዎች

24/10/2025

አንድ ሠው ሶቅራጠስ ወዳረፈበት እልፍኝ ሄዶ እንዲህ አለው፡፡

‹‹ሶቅራጠስ ወዳጄ፣ እገሌ ስለተባለው ወዳጅህ ዛሬ የሠማሁት ነገር ምንም ደስ አይልም›› አለው፡፡

ሶቅራጦስ መከዳው ላይ እንደተደገፈ መልስ ሳይሰጠው ዝም አለ፡፡

ሠውዬውም እንደገና ‹‹ይገርማል ከእርሱ አይጠበቅም፤ በጣም ገርሞኛል›› ሲል ተናገረ፡፡

ሶቅራጦስ፣ ይህ ሠው በቀላሉ እንደማይፋታው ስለተረዳ አንድ መደራደሪያ አቀረበለት፡፡

‹‹ስለ ወዳጄ ልትነግረኝ የፈለከውን እንድሠማህ ከፈለግህ ሶስት ጥያቄዎች አሉኝ፤ እነርሱን በቅድሚያ ልትመልስልኝ ይገባል! ይህ ሲሆን ብቻ ነው የምሰማህ›› አለው፡፡

ሠውዬው ለወሬው ቢቸኩልም አማራጭ ስላልነበረው በሶቅራጠስ ሀሳብ ተስማማ፡፡

‹‹የመጀመሪያው ጥያቄዬ የእውነት ጥያቄ ነው" አለ ሶቅራጠስ።

"ስለወዳጄ የሠማኸው መቶ በመቶ እውነት ነው ወይ?›› ሲል ጠየቀ፡፡

ሠውዬውም፡- ‹‹መቶ በመቶ እንኳን እርግጠኛ መሆን አልችልም›› ሲል እያመነታ መለሰለት፡፡

‹‹በጣም ጥሩ! ልትነግረኝ የፈለግከው እርግጠኛ ያልሆነ ነገር ነው ማለት ነው፡፡ እሺ ሁለተኛው ጥያቄዬ የመልካምነት ነው፡፡ የምትነግረኝ መልካም ነገር ነው ወይ?›› ሲል ሶቅራጠስ አቀረበ ጥያቄውን፡፡

ሠውዬውም፡- ‹‹እርሱማ መልካም አይደለም›› አለ ቱግ ብሎ፡፡
የሶቅራጠስ ጥያቄዎች ለማውራት የቋመጠለትን ወሬ እንዳያወራ እንቅፋት መስለው ታዩት።

ሶቅራጦስም ‹‹እውነትነቱ ያልተረጋገጠና መልካም ያልሆነ ነገር ልትነግረኝ ፈልገሃል፡፡ እሺ ሶስተኛውና የመጨረሻው ጥያቄዬን ልጠይቅህ?›› አለው፡፡

ሠውዬውም ጥያቄውን ለመስማት ፈጥኖ ‹‹እሺ›› አለ፡፡

ሶቅራጦስ ጠየቀ፤ ‹‹የምትነግረኝ ነገር ለእኔ የሚጠቅመኝ ነገር አለው ወይ?››

‹‹የለም! የለም! መጥቀም እንኳን አይጠቅምህም። ብቻ ብትሰማኝ...›› ብሎ ሰውዬው መቅለስለስ ጀመረ።

ይሄን ጊዜ ሶቅራጦስ ‹‹ታዲያ እንደምን አድርጌ እውነትነቱ ያልተረጋገጠ፤ መልካም ያልሆነ እና ለእኔ ምንም ጥቅም የሌለው ነገር ልንገርህ ስትለኝ እንዴት እሰማሃለሁ። ዞር በል ካጠገቤ አልሰማህም!!›› አለው ይባላል፡፡

ስንቶቻችን ነን ሰው የሚነግረን ነገር እውነት፣ መልካምና ጠቃሚ መሆኑን አጣርተን የምንሰማው?

ስንቶቻችን ነን ለሰው ቁምነገር ብለን ልንናገር ስንል ከሶስቱ አንዱን ማሟላቱን የምናረጋገጠው?

አሁን እኮ ሰው ዝም ብሎ የተነገረውን ስለሚሰማ በቀላሉ እንደ እንስሳ የሚነዳ ሆኗል፡፡ በየሶሻል ሚዲያው ላይ ፖስት የሚደረጉት ብዙዎቹ መረጃዎች እውነት ያልሆኑ፣ መልካምነት የሌላቸው እና ለእኛ ምንም ጥቅም የማይሰጡ ናቸው፡፡ በተቃራኒው የውሸት መረጃዎች ሆነው ስንቱን ያጭበረበሩ፣ ሰይጣናዊ ርምጃ ለመውሰድ የሚገፋፉ ሆነው ሳለ ያለማቅማማት እንሰማቸዋለን፡፡

አሁን አሁን እውነት ከሚናገሩት ሰዎች በላይ በመርዝ የተለወሰ ውሸት የሚናገሩ ሰዎች የተሻለ ብዙ ተከታይ አላቸው፡፡ መልካም መልካሙን ከሚሰብኩ ሰዎች ይልቅ የጥፋት ሰባኪዎች ብዙ ደጋፊ አላቸው፡፡ የጀገኑት ፍለጠው/ቁረጠው ባዮች ናቸው፡፡

እነሱን ማስቆም አይቻል ይሆናል፤ ነገር ግን እነሱን አለመስማት/አለመከተል ቀላል ነው፡፡ እነዚህን የሶቅራጠስ 3ቱ ጥያቄዎችን እንደ ወንፊት ተጠቅመን ማጣራት ብቻ በቂ ነው፡፡

‹ፅሁፉን› እውነት፣ መልካም እና ጠቃሚ ሆኖ ካገኛችሁት ሼር አድርጉት፡፡

(የጽሑፉ አዘጋጅ፦ መሳፍንት ተፈራ)

ይህን ገፅ በማድረግ ይከተሉን! ያተርፉበታል!

የህይወት ፍልስፍና

Address

Addis Ababa

Telephone

+251904400505

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when የስኬት መርሆዎች posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share