የስኬት መርሆዎች

የስኬት መርሆዎች ከታላላቅ ሰዎች የህይወት ተሞክሮ!!!

27/09/2025

1. የሰው ልጆች በመጀመሪያ በውልደት ወደዚህ አለም ሲመጡ የመጀመሪያው አንድ ደቂቃ ከሚቀጥሉት አርባ አመታት በላይ የበለጠ ፋይዳ አለው። ምክንያቱም የመጀመሪያው አንድ ደቂቃ ከመሞት በፊት ያለው ትልቁ የህይወት ለውጥ ነው።

2. ፍርሃት የፈሪም የጀግናም መነሻ ነው። ፍርሃት ለፈሪ ጭንቀቱ ሲሆን፤ ለጀግና ደግሞ ጀብዱው ነው።

3. መማር ባለሙያ ያደርጋል፤ መኖር ደግሞ አዋቂ ያደርጋል።

4. ሰው የሆነውን የሚሆነው በአጋጣሚ አይደለም።አዋቂው ሰው ህፃኑ ልጅ በልጅ አዕምሮው የፃፈውን ተውኔት የሚተውን ተዋናይ ነው። የልጅ ጭንቅላት የተባለውን ይይዛል፤ አዋቂ ደግሞ የያዘውን ይተገብራል። አዋቂው ሲያለቅስ ወይም ሲያዝን እንደህፃን አባብይው።

5. ተስፋ የመኖር ምክንያት ነው።ሰውን እንዲኖር የሚያደርገው መለወጥ አለመለወጡ ሳይሆን የመለወጥ ተስፋው ነው። ቢሆንም ግን ህይወት ተከታታይ መሆኗን መገንዘብ ይጠቅማል። ዛሬ የምንኖረው በትላንት ምክንያት ነው።

6. ሰው መሆን ማለት ራቁታችንን ከተወለድን በኋላ፤ ከልብስ ጀምሮ አካላችንን ከሚሸፍኑት ሽፋኖች መላቀቅ ነው። ሰው ሰውነቱን የሚያጣው ራቁቱን ከእናቱ ማህፀን ሰው ሆኖ ተወልዶ በማህበረሰብ፣ በልብስ፣ በትምህርት፣ ሃይማኖት፣ በብሔር የመሰሉ ግዑዛን አልባሳትን በመደረብ ነው።

7. እውነተኛ ለውጥ የማይኖረው ሰው ስላልጣረና ስላልሞከረ ሳይሆን ለውጥ ሂደት እንጂ መድረሻ ስላልሆነ ነው።

8. ጎዳና ላይ የሚያድር ሰው ብርዱን ይለምዳል፣ ፀሃዩን ይታገሳል፣ አውሬ ያስለምዳል፤ ሰውን ግን ይፈራል። ቀኑን ሙሉ ብርድ ሳንፈራ ደረታችንን ገልጠን ራቁታችንን የምንውል ሰዎች፤ ልክ ሲመሽ የውጪ በር ቆልፈን፣ከዛ የሳሎን በር ቆልፈን፣ የጓዳ በር ቆልፈን፣ አልጋችን ውስጥ ገብተን ብርድልብስ ለብሰን፣ ብርድ ልብሱ እንዳይኮሰኩሰን አንሶላ ደርበን፣ አንሶላው እንዳይቀዘቅዘን የለሊት ልብስ ለብሰን ...በነዚህ ነገሮች ሁሉ ተከልለን እንተኛለን። ይህን እንዲሆን ደግሞ ያደረገው ፍርሃታችን ነው።

9. በታሪክ ውስጥ ትልቁ አምባገነን ታሪክ ራሱ ነው።ሁላችንም የታሪክ ተገዢዎች ነን።

10. የማታሸንፈውን ሰው ተጠያቂ ማድረግ የፈሪነት መፍትሔ ነው።

11. እውነት እኮ የጊዜና የቦታ ድምር ውጤት ነው። የራስን ሃሳብ ሌላው እንዲገባው ማድረግ ማለት ፤ የራሱን ሃሳብ ድንበር አልፈን የሃሳብና አስተሳሰብ ወረራ አካሄድን ማለት ነው።

12. የሚጠፋ ነገር ዐይንህ ስር ተቀምጦ ያለማየትን የመሰለ ዕውርነት የለም። አንዳንዴ ከሞት በኋላ ስለሚኖር መኖር እየጓጓን የውሸት ማመን የለብንም። ስለፀሎታችንን ምንነት በአንክሮ መፈተሽ ያስፈልጋል

13. ሰው የምታውቀው ፍጡር አይደለም። ሁልጊዜ ሰውን የምናውቀው ይመስለናል። እኔ ሐኪም ስከሆንኩና የአንድ ሰው አካል ቀድጄ ልቡን ስላየሁት ሰውን ያወኩት ይመስለኛል። ነገር ግን ሰው በየትኛውም ደረጃ የሚታወቅ ፍጡር አይደለም።

በደረቁ ሳይንስ አጥንተህ ሰው ውስጥ ያለውን ፕሮቲን እንዴት እንደሚሰራ ስላወቅህ ሰውን አውቃለሁ ማለት አይቻልም።

የመማር አንደኛው ችግር (በተለይ እኛ ሐገር) ቶሎ መታበይና የምናውቀው እውቀት እኛ ያመጣነው ሳይሆን ቀድሞ በሌሎች የተፈጠረ መሆኑን የመርሳት ችግር አለብን። እኛ ያወቅነው ከእኛ በፊት የመጡት የፈጠሩትን ነው። ይህንን እንረሳና እኔ ተምሬ ሳውቅ ራሴን አዋቂና ሐሳቡን እኔ የፈጠርኩት የመምሰል ችግር አለብን።

14. እያወቅክ ስትሔድ ትልቅልነትህን ሳይሆን ትንሽነትህን ነው የምትረዳው "

ብዙ ነገር ለመማር መሞከር እይታህን ያሰፋል። የእይታህ አድማስ ሲሰፋ ደግሞ አንተ እያነስክ ነው የምትሄደው። ሰፊ ከሆነው ዓለም ውስጥ አንተ ምን ያህል ኢምንት እንደሆንክ ትረዳለህ። እያወቅክ ስትሄድ ትልቅነትህን ሳይሆን ትንሽነትህን ነው የምትረዳው።

የህይወት ፍልስፍና

የትኞቹን ሃሳቦች ወደዳችኋቸው? አድርጉልን

ጋዜጠኛዋ ቢሊኒየሩን ቃለመጠይቅ እያደረገችለት ነው...  #ጋዜጠኛዋ:- የስኬትህ ሚስጥር ምንድነው? #ቢሊየነሩ:-  ባዶ ቼክ ለጋዜጠኛዋ አቀበላትና የፈለግሽውንያህል ገንዘብ ፃፊበት አላት!ጋዜ...
21/09/2025

ጋዜጠኛዋ ቢሊኒየሩን ቃለመጠይቅ እያደረገችለት ነው...

#ጋዜጠኛዋ:- የስኬትህ ሚስጥር ምንድነው?

#ቢሊየነሩ:- ባዶ ቼክ ለጋዜጠኛዋ አቀበላትና የፈለግሽውን
ያህል ገንዘብ ፃፊበት አላት!

ጋዜጣኛዋ በእንቢታ ቼኩን እየመለሰች ‹‹አይ እኔ እንደሱ
አይነት ነገር ፈልጌ አይደለም:: የስኬት ሚስጥርዎን መጠየቅ ፈለጌ እንጂ›› አለች።

ቢሊየነሩ ድጋሚ ቼኩን መልሶ ሰጣትና
‹‹የፈለግሽውን ያህል ገንዘብ ፃፊ›› አላት።

ጋዜጠኛዋ እንቢ አሻፈረኝ አለች።

ቢሊየነሩ ቼኩን እያሳያት እንዲህ አላት:-

‹‹የስኬቴ ሚስጥር አሁን አንቺ ያጋጠመሽን አይነት እድል አሳልፌ አለመስጠቴ ነው... የስኬቴ ሚስጥር ያገኘሁትን እድል ሁሉ መጠቀሜ ነው፡፡

አሁን አንቺ እድልሽን ተጠቅመሽ ቢሆን ኖሮ የአለማችን ሃብታሟ ጋዜጠኛ ትሆኚ ነበር...
እኔ ሁለቴ እድል እንደሰጠሁሽ አለም ሁለት እድል አትሰጥሽም። አንዴ ያጋጠመሽን እድል መጠቀም የስኬት ሚስጥር
ነው።››
የስኬት መርሆዎች

21/09/2025

🌟 መስከረም 12 ኢትዮጵያ የጠበቀችው ድንቅ ዕለት🌟

💥 መስከረም 12 ለፕላኔታችን መሬት በሙላ ታላቅ ዕለት ናት፤ ይኽነን ጥበብ በዘመን ቀመሯና በፊደሏ የያዘችውና የምትምሰክረው ንግሥተ ጥበብ ኢትዮጵያ ናት፤ በእኛ በኢትዮጵያ አቈጣጠር መስከረም 12 በሌላው ዓለም አቈጣጠር ደግሞ እንደ ኹኔታው መስከረም (September) 21 ወይም 21 አንዳንዴም 22 ይኾናል።
🌟 በዚኽ ቀን ፀሓይ ልክ የምድር ወገብ ላይ ኾና ቀኑና ሌሊቱ በመላው ዓለም እኩል የሚኾንበት ወቅት “ዕሪና መዓልት ወዕሪና ሌሊት ዘመፀው" (የመፀው እኩሌ (Autumnal /fall equinox) ይባላል፡፡
🌟 ይኽ ዕለት ፀሐይ የሰማያዊውን ሉል ወገብ አቋርጣ ወደ ደቡብ አግጣጫ የምትኼድበት ጊዜ ሲኾን በሰሜናዊው ንፍቀ ክበብ መፀው የሚዠምርበት ዕለት ነው፡፡ በዚኽ ጊዜ ፀሓይ ልክ በምሥራቅ ትክክለኛ አቅጣጫ ላይ ወጥታ በምዕራብ ትክክለኛ አግጣጫ ላይ ትጠልቃለች፡፡


🌟 በዚኽች ቀንና ሌሊቷ እኩል በሚኾንበት ሰኞ መስከረም 12 በ2018 ዓ.ም ሮሽ ሀሻናህ רֹאשׁ הַשָּׁנָה የቀንደ መለከት በዓል ይኾናል፡፡ “ሮሽ ማለት እራስ “ሀሻናህ” (ዐውደ ዓመት) ማለት ነው፡፡

💥 መስከረም 11/1/2018 (2+0+1+8 = 11) 11/1/11 ቀመር ከተከናወነው ቀለበታማ የፀሓይ ግርዶሽ በሰንቡላ (ቪርጎ) ከታየ በኋላ፤ መላው ዓለም ቀንና ሌሊቱ እኩለ በሚኾንበት መስከረም 12 ዕለት .... በዓለማችን ታላቅ ጉዳይና አንድ ታላቅ የትንቢት ቀጠሮ ጊዜ በጊዜያችን እንደተቃረበ አመላካች ሊኾን ይችላልና በጣም ብዙ ያልተጠበቁ ክንውኖች በዜናም ይኹን በሌላ ልናይ እንደምንችል በመረዳት ኅሊናችንን ሰብሰብ ማረግ ጥሩ ነው፡፡
✍️ በመጋቤ ሐዲስ ዶክተር ሮዳስ ታደሰ
11/1/2018 ዓ.ም. (2+0+1+8 = 11) 11/1/11 ተጻፈ

21/09/2025

በዓለማቀፍ የሞዴሊንግ ኢንደስትሪ ውስጥ አዲስ ስም ተጨምሯል። ይህ ስም ሳሙኤል ባይሳ ይባላል።

ከባይሳ ቱፋ አብራክ ተከፍሏል። ወላጅ እናቱ ደግሞ ጆፋ በሪ ይሰኛሉ። ሳሙኤል ከዚህ የስኬት ጉዞ በፊት በብዙ ውጣ ውረድ ውስጥ አልፏል።

አንዳንድ ጊዜ ህይወት በድንቅ ገጠመኞች የተሞላች ናት። እነዚያ ገጠመኞች ሰውን ለህይወትም ይሁን ለሞት ጋባዥ ናቸው። ሰው እስኪሞት ድረስ መች በልኩ እንደሚኖር አይታወቅም።

ሳሙኤል ባይሳም ህይወት የትና እንዴት የሌላት በተአምር የተሞላች መሆኗን እማኝ ነው። ባለታሪኩ የእትብቱ መቀበሪያ አቡና ግንደበረት ነበር። አንድም ከፊደል ሀ ሌላም ከህይወት ዋ ብሎ ተምሯል።

ህይወት ለሳሙኤል ፈርጣማ ክንዷን የምታሳየው ጠበኛው ነበረች። ለበረታበት ሸክም ያልተረታው ሳሙኤል የተሻለ ነገር ፍለጋ ወደ ቡራዩ ከተማ መጣ። በቡራዩም ቢሆን የህይወት ፈተናና ሳሙኤል የልብ ወዳጆች ነበሩ።

ለኑሮ ሸክም ተሸንፎ ትከሻውን አላጎበጠም ነበር። ስራ ሳይንቅ በመስራት ይታገል ነበር። ከህይወት በገመጠው ግብግብ በእርሱ ያልተሠራ ስራ አልነበረም። ጫማ ጠራጊ ሳለ ከቀዬው በእጆቹ ያላማሩ ጫማዎች አልነበሩም። የታክሲ ወረፋ አስከባሪነት እና ሌሎች የጎዳና ላይ ስራዎችም በእርሱ ተከውነዋል።

የበዛው ፈተና በትምህርቱ ላይ አላሰነፈውም ነበር። የሁለተኛ ደረጃ እና የመሰናዶ ትምህርቱን በጥሩ ውጤት አጠናቆ ለዩኒቨርሲቲ ደረሰ። ያላሰነፈው ብርቱነቱ ግን ትምህርቱን ለመጨረስ በቂ አልነበረም። የቤተሰቡን የኢኮኖሚ ጫና መቋቋም አቃተው። ብዙ ያየበትን ትምህርቱን ለማቋረጥ ተገደደ።

የህይወቱን ቋጠሮ ለመፍታት ወደ ዱባይ አቀና። ዱባይ ደግሞ ሌላ የፈተና ድሯን አድርታ ጠበቀችው። ኮንስትራክሽን ስራ ቦታ የዕለት ተቀጣሪ ሠራተኛ ሆኖ ተቀጠረ። የበረሃው ሙቀትና የሥራው ድካም ትግሉን ከፍ አደረገው።

ከእለታት አንድ ቀን እድል በእጅ በእግር ብላ ሳሙኤልን ፈልጋ አገኘችው። የህይወቱን መልክ እስከወዲያኛው የሚቀይር ነገር ተከሰተ። ከፊለፊቱ አንድ ውድ መኪና ተመለከተ። መኪናውን ላይ ተደግፎ እየተመለከተው ሳለ፣ የመኪናው ሾፌር ሳሙኤልን አይቶ ተደነቀ።

ወዲያውኑም ወደ መኪናው ውስጥ ጋበዘው። ሳሙኤል በደስታ ተሞላ። ወደ መኪናው ውስጠኛ ክፍልም ከነ ኮንስትራክሽን ልብሱ ገባና ተቀመጠ። ሾፌሩም የሳሙኤልን ደስታ ቪዲዮ ቀርፆ በማህበራዊ ሚዲያ ለቀቀው። ቪዲዮው በአጭር ጊዜ ውስጥ በዓለም ዙሪያ ተሰራጨ።

በዚሁ ቪዲዮ ሰበብ የሳሙኤል ታሪክ ተነገረ። ካሜሩናዊው ሞዴል ኤሪክም በሳሙኤል ታሪክ ልቡ ተነካ። የራሱን ያለፈ ህይወት አስታወሰው።

ኤሪክም ወደ ሳሙኤል ስራ ቦታ ሄዶ አነጋገረው። አብረው አጫጭር ቪዲዮዎችን ሰሩ። እነዚህም ቪዲዮዎች ታላላቅ የሚዲያ ተቋማትን ትኩረት ሳቡ። የሳሙኤልን ታሪክም ለብዙኃን አዳረሱ።

ዛሬ ለሳሙኤል እንደ ትናንት ከባድ አይደለም። በመኪና በር ኩል እድል በሯን ከፍታለታለች። የቀደመ ልፋቱን ፍሬ በእድል አጋዥነት እየበላ ነው።

ሳሙኤል ሞዴል ሆኖ ማስታወቂያዎች በመስራት ላይ ነው። በቲክቶክ፣ በኢንስታግራም እና በፌስቡክ በመቶ ሺዎች የሚቆጠሩ ተከታዮችን አግኝቷል።

የአትዮጵያ ሪልስቴቶችን ጨምሮ በርካታ አካላት ለስራ እንደሚያገኙት ኢትዮጵያ ኦብዘርቨር ዘግቧል። ሳሙኤልም ሌሎች በህይወት ሸክም የደከሙ ሰዎችንም ተስፋ እንዳይቆርጡ ያበረታታል።

@ጋዜጣ ፕላስ
የህይወት ፍልስፍና

20/09/2025

ከ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና ጋር ተያይዞ 5 ጉዳዮች በጣም አሳሳቢ ሆነዋል።

1ኛ፣ 2ኛ እና 3ኛ ደረጃ ጠቅልሎ የሚይዘው ፈተናውን ያላለፉ ተማሪዎች ጉዳይ ነው። በዚህ ዙሪያ አገራዊ ምክክር ማድረግ እና መፍትሔ ማምጣት ይጠበቅብናል። ይሄ ትኩስ ኃይል ወደ ትምህርት/ሥልጠና የሚሄድበትን መንገድ ማሰብ አለብን። የአጫጭር እና የመካከለኛ ጊዜ የሙያ ሥልጠናዎች በሌሎች ሀገራት ከፍተኛ ለውጥ አምጥተዋል። በመንግሥት እና የግሉ ሴክተር ትብብር የግብርና እና አግሮ ፕሮሰሲንግ ትምህርት፣ ሥልጠና እና ሥራዎች ላይ ያተኮረ ሥራዎች መሥራት ይቻላል። መሬት በመንግሥት እጅ ነው፤ የታክስ ፖሊሲ ጉዳዮች በመንግሥት ቁጥጥር የሚከናወን ነው፤ አንዳንድ ትላልቅ ባንኮች ለግብርና የሚመድቡት ብድር በከፍተኛ መጠን አድጓል ወዘተ. እነዚህን እንደ ጥሩ አጋጣሚ በመጠቀም እንደ ምሣሌ በዚህ ዙሪያ የሚያሰለጥኑ (ወይም አዲስ የሚቋቋሙ) የግል የቴክኒክ እና ሙያ ሥልጠና ተቋማትን ዘለግ ላለ ጊዜ ከታክስ ነፃ በማድረግ እንዲሁም በዝቅተኛ ወለድ በማበደር መደገፍ ይቻላል። በሌሎች ዘርፎችም መሥራት ይቻላል። ''መፍትሔዎችን እንመካከር'' እያሉ ይገኛሉ ወዳጆቼ ዶ/ር Erssido Lendebo እና ኢ/ር Kefe Hailu ። ከሰሞኑ መድረክ ልናዘጋጅ አስበናል።

2ኛ. ሕክምና የመማር ፍላጎት በጣም መቀነስ አሳይቷል። የጥናት ውጤት እጄ ላይ ባይኖርም በሚዲያ ከምናየው እንዲሁም በዙሪያችን ጥሩ ውጤት አምጥተው ፍላጎታቸውን ከሚገልጹ ተማሪዎች እንደተረዳነው ''ሕክምና መማር እፈልጋለሁ'' የሚል ተማሪ ቁጥር መቀነስ በጣም ሊያሳስበን ይገባል። አንደኛው መፍትሔ አሁን ያሉንን ሐኪሞች በእንክብካቤ መያዝ እና ጥያቄዎቻቸውን በአግባቡ መመለስ ነው። ፕሮፌሽኑ እንደተከበረ ማቆየት ካልቻልን ''የጤናው ሴክተር is at risk'' is loading ...

3ኛ. ወደ ክልል ዩኒቨርሲቲዎች (''ምርጥ'' ወደሚባሉትም ሳይቀር) ሔዶ ለመማር ያለ ፍራቻ። የሰላምና ጸጥታጉዳይ ዋነኛው እንደሆነ የምታውቁት ነው። ፖለቲካዊ መፍትሔ የሚፈልግ እንደሆነም እንደዚያው። ሌሎች መፍትሔዎች ከዚያ በኋላ የሚመጡ ናቸው።

ያለ ትምህርት ዕድገትም ሆነ ሥልጣኔ አይታሰብም። አሸዋ ላይ እንደተገነባ ቤት ማለት ነው። ዩኒቨርሲቲ ገብቶ መማር ግዴታ አይደለም፤ ሆኖም ዜጎች በየደረጃው የትምህርት እና ሥልጠና አገልግሎት እንዲያገኙ ማድረግ ቅድሚያ ከሚሰጣቸው የቤት ሥራዎቻችን ውስጥ ነው።

✍ ሀውለት አህመድ (ዶ/ር)

የህይወት ፍልስፍና

19/09/2025

የህይወት ፍልስፍና

1. ምኞት ስኬታማ ሰው ግልጽ የሆኑ ግቦች አሉት። “ሀብታም መሆን” እንደሚለው አይነት  ግልጽ ያልሆነ ግብ  ይልቅ ፣  “በሚቀጥሉት ሁለት ዓመታት ውስጥ ያለኝን አንድ ሱቅ ወደ ሶስት ሱቆች ...
19/09/2025

1. ምኞት
ስኬታማ ሰው ግልጽ የሆኑ ግቦች አሉት። “ሀብታም መሆን” እንደሚለው አይነት ግልጽ ያልሆነ ግብ ይልቅ ፣ “በሚቀጥሉት ሁለት ዓመታት ውስጥ ያለኝን አንድ ሱቅ ወደ ሶስት ሱቆች ማስፋፋት የሚል አይነት ውስን ግብ ያስቀምጣል።

2. ተነሳሽነት
ስኬታማ ሰዎች በጣም ከሚገለጹበት ባህሪያት አንዱ ተነሳሽነት ነው። ስኬታማ ሰዎች ግባቸውን ለማሳካት ጠንካራ ተነሳሽነት ሊኖራቸው ይገባል። ጠንካራ የተነሳሽነት ስሜት ያለው ስኬታማ ሰው፥ በችሎታው ስለሚተማመንና ግቡን ለማሳካት ስለሚፈልግ ያለ ድካም መስራት ይችላል።

3. ለመማር ፈቃደኛነት
ስኬታማ ሰው ሁሉን አውቃለሁ አይልም። ከሁሉም ሰውና ከሚያጋጥሙት ሁኔታዎች ሁሉ ለመማር የተከፈተ አእምሮ አለው። እያንዳንዱ ተሞክሮ ለማደግ አጋጣሚ እንደሚፈጥር ይረዳል። የማያውቀው ነገር እንዳለ ያምናል፥ አዲስ ነገር ለመማር ቦታ እንዳለው ሲገነዘብም እውቀቱን ለማሻሻል ይነሳሳል።

4. ታጋሽነት
ስኬታማ መሆን የምትፈልግ ከሆነ ትዕግስት ሊኖርህ ይገባል። ነገሮች ምንም ያህል አሁን እንዲሆኑ ብትፈልግ ሊደረስበት ዋጋ ያለውን ማንኛውም ነገር መጠበቅ ደግሞ ዋጋ አለው።

5. ስርዓት
ስኬት ወጥነት ይፈልጋል፥ ወጥነት እንዲኖር ደግሞ ስርዓት ሊኖር ይገባል። ብዙ ስኬታማ ሰዎች ህልማቸውን እውን ለማድረግና በጥረታቸው ውስጥ ወጥነት ያላቸው እንዲሆኑ የዕለት ተዕለት ተግባር ላይ መመስረት አንዱ ቁልፍ እንደሆነ ተገንዝበዋል።

ወጥነት ያለውና ሥርዓታማ በመሆንና ለማደግ ራስህን በመስጠት፣ በስራና በህይወት ውስጥ ብዙ ሽልማቶች እንድታገኝ ያደርግሃል። ይህ ሰዎች በሙያቸው ስኬትን ብቻ ሳይሆን ረጅም ዘመን ኖሯቸው እንዲደሰቱ የሚያስችል ቁልፍ ባህሪ ነው።

የስኬት መርሆዎች

18/09/2025

« እናንተ ተማሪዎች ናቸሁ። አርቆና አቅርቦ የሚያይ ዓይን ፣ እያጠለለ የሚሰማ ጆሮ ፣ ያየውንና ያደመጠውን ደግሞ የሚጠይቅ በሚዛናዊነት የሚተነትን የሠለጠነ አእምሮ ያስፈልጋችኋል።

ስኬታማ ሰዎች አእምሯቸውን የመቆጣጠር አቅም ያላቸው ናቸው ። ከአንደበታችሁ ይልቅ ጆሮዎቻቸሁ ክፍት መሆንን መልመድ አለባቸው ።

በሰማችሁት ሳይሆን በተናገራችሁት ነገር ሰው ታስቀይማላችሁ። የልቡና ስፋት ሳይሆን የምላስ መርዘም አገር ያጠፋል። ሁሉም ሲናገር ያን ጊዜ ዝም በሉ ። በጸጥታችሁ ሰላም ይፈጠራል።

ልሰማ ባይ በበዛበት ስፍራ አድማጭ ሁኑ። በዝምታ ውስጥ ያለ ያስተውላል። በልባቸው የምታስቡትን ፣ በአንደበታችሁ ፣ የምታናገሩትን በድርጊታችሁ የምትገልጹትን ለይታችሁ እወቁ ።

በገዛ ጥረታችሁ ከእነዚህ ሦስት ነገሮች የምታገኙት በምክንያታዊ ስሌት ነው አስቡ ።

በጉዟችሁ በስተመጨረሻ የአስተሳሰባችሁን ፣ የአነጋገራችሁን ፣ የድርጊታችሁን በፍሬ ታገኛላችሁ ። »

【Yonas Zewde Kebede 】

የፌስቡክ ገፃችንን በማድረግ ቤተሰብ ይሁኑ
👉 የህይወት ፍልስፍና

ባሻዬ!! ከብዙ ዓመታት በፊት ተስፋዬ የሚባል የኮሌጅ ተማሪ መቅደስ የምትባለውን  ተማሪ ወደዳትና በቴክስት ቡክ ውስጥ እንዲህ የሚል የፍቅር ደብዳቤ ጽፎ ሰጣት፣"መቅዲ! እኔ እወድሻለሁ። አን...
17/09/2025

ባሻዬ!! ከብዙ ዓመታት በፊት ተስፋዬ የሚባል የኮሌጅ ተማሪ መቅደስ የምትባለውን ተማሪ ወደዳትና በቴክስት ቡክ ውስጥ እንዲህ የሚል የፍቅር ደብዳቤ ጽፎ ሰጣት፣

"መቅዲ! እኔ እወድሻለሁ። አንቺም የምትወጂኝ ከሆነ ለምልክት ነገ ቀይ ቀሚስ ለብሰሽ ትምህርት ቤት ነይ "

በቀጣዩ ቀን መቅደስ ቢጫ ቀሚስ ለብሳ ትምህርት ቤት መጣችና ቴክስት ቡኩን መለሰችለት። ተሰፋዬ በሁኔታው በጣም አዘነና መቅደስን ዳግመኛ ላያያት ለራሱ ቃል ገባ።

ዓመታት አለፉ። ልጅቷም ባል አገባች።

አንድ ቀን ተስፋዬ የቤቱን የመፅሐፍ መደርደሪያ ሼልፍ ሲያፀዳ ያ ቴክስት ቡክ መሬት ላይ ተገልብጦ ወደቀና ውስጡ የነበረ ወረቀት ተዘርግቶ ታየ። ልጁ ወረቀቱን አንስቶ ሲያነበው እንዲህ ይላል፣

"ተስፍሽ! እኔም እወድሃለሁ። ቀይ ቀሚስ ስለሌለኝ የምወደውን ቢጫ ቀሚሴን ለብሼው መጣሁ"

ባሻዬ! እባክህ ቴክስት ቡክህን በየጊዜው እየከፈትክ አንብበው። ማትሪክ ሞተ ብለህ ደረትህን እየመታህ አትቀመጥ። አንብብ፣ አንብቢ፣ አንብቡ ፣ እናንብብ!!!

የስኬት መርሆዎች ✍ ተስፋዬ ኃ/ማርያም

Address

Addis Ababa

Telephone

+251904400505

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when የስኬት መርሆዎች posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share