Ethio Daliy News

Ethio Daliy News Contact information, map and directions, contact form, opening hours, services, ratings, photos, videos and announcements from Ethio Daliy News, Broadcasting & media production company, Addis Ababa.

አቶ ጌታቸው ረዳ በዛሬው የአዲስ አበባ መግለጫቸው ምን አሉ; ግጭት በሚፈልጉ ሀይሎች ትግራይ መስቀለኛ መንገድ ውስጥ ገብታለችማህተም እየቀሙ እኛ ነን አስተዳዳሪ እኛ ነን ከፌዴራል መንግስት ...
13/03/2025

አቶ ጌታቸው ረዳ በዛሬው የአዲስ አበባ መግለጫቸው ምን አሉ;

ግጭት በሚፈልጉ ሀይሎች ትግራይ መስቀለኛ መንገድ ውስጥ ገብታለች

ማህተም እየቀሙ እኛ ነን አስተዳዳሪ እኛ ነን ከፌዴራል መንግስት ጋር የምንደራደረው የሚሉ አሉ

የትግራይ ህዝብ ጦርነት ሰልችቶታል። የተገኘውን ትንሽ ሰላም ለማድፍረስ የሚንቀሳቀሱ ሀይሎችን የፌዴራል መንግስት ሊያስቆማቸው ይገባል።

#ትግራይ

12/03/2025

ሰበር‼️

የፌደራል መንግሥቱ ጣልቃ እንዲገባ ጠየቀ።

ከጥር 15 ቀን 2017 ጀምሮ አንዳንድ የትግራይ ሰራዊት ከፍተኛ አዛዦች የጠባቦችን የስልጣን ጥማት ለማርካት ግልጽ የሆነ መፈንቅለ መንግስት ለማድረግ ሲንቀሳቀሱ እንደነበር ይታወቃል። በተመሳሳይ የሰሜን ምስራቅ እና ደቡብ ግንባር አዛዦች የሚመሩ ህገወጥ ድርጊቶች በዚህ ሳምንት ተጠናክረው ቀጥለዋል። ይህንን አደገኛ መንገድ ለመግታት እና ህገ-ወጥ ድርጊቶችን ሁሉ ለማስቆም የካቲት 26 ቀን 2007 ዓ.ም ለትግራይ ጦር ዋና አዛዥ የተጻፈ ትዕዛዝ ቢሰጥም የጥፋት ድርጊቱ ለሰዓታት ቀጥሏል። ሁኔታው እልባት ባለማግኘቱ የግንባሩ አዛዦች በመንግስት እገዳ ተጥሎባቸዋል። የጸጥታው ቢሮ ኃላፊም ከኃላፊነታቸው ተነስተዋል። ሆኖም በሰላማዊ ዜጎች ላይ ያነጣጠሩ ጥቃቶች አሁንም ቀጥለዋል። መንግስትን ከላይ እስከታች የማፍረስ ስራው ተጠናክሮ ቀጥሏል። የትግራይ ሰራዊት ከፍተኛ አዛዦች የኋለኛውን ቡድን ፍላጎት ለማስፈጸም መንግስትን በመበተን እና የፕሪቶሪያን ስምምነት በይፋ በመጣስ የትግራይን ህዝብ ወደ ሌላ ጥፋት እያመጡ ነው። ያለፉትን
ስህተቶች ከማረም ይልቅ ከትናንት ጀምሮ የግዚያዊ አስተዳደር አመራሮችን እያደኑ፣ እያፈኑ እና እያሰሩ ነው። ይህም በማኅተም ስም መንግሥትን ለመጣል የሚያደርጉትን እንቅስቃሴ የበለጠ ያጠናክራል። ይህ ኋላ ቀርና ወንጀለኛ ቡድን ዕድሉን ካገኘ ማፈንና ማሰር ብቻ ሳይሆን የጊዚያዊ አስተዳደር አመራርን ለሶስተኛ ወገን እንደሚያስረክቡ መረዳት ያስፈልጋል። በሰራዊቱ አዛዦች ስም የሚካሄደው ዘመቻ ሁኔታውን ከጊዚያዊ አስተዳደር ቁጥጥር ውጪ የሚያደርግ እና እንደ ህዝብ ራሳችንን እንድንዋጋ የሚያደርግ ሃላፊነት የጎደለው እና ተቀባይነት የሌለው ተግባር ነው።

በአጠቃላይ የትግራይ ህዝብ ከውስጥም ከውጪም; የትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር የትግራይ ወጣቶችና የትግራይ ሰራዊት ይህንን ሁኔታ በመረዳት አካባቢያቸውን እንዲጠብቁና በእነዚህ የሁለቱም ግንባሮች አዛዦች ላይ እንዲነሱ ጥሪውን ያቀርባል። የትግራይ ወጣቶች ባንተና በህዝባችሁ ላይ እየደረሰ ያለውን አደጋ ለመታገል በተደራጀ መልኩ አካባቢያችሁን ጠብቁ። የትግራይ ሰራዊትም እንዲሁ የጥፋት ስርዓቱን አጥብቆ በመቃወም ህዝቦቻችሁን ከፊት ካለው ከባድ አደጋ መታደግ አለበት።

የፌደራል መንግስትም በጸጥታ ሃይሎች ስም የሚንቀሳቀሱት ኋላ ቀር እና ወንጀለኛ ቡድን ተላላኪ እንጂ የትግራይን ህዝብና ጊዜያዊ አስተዳደር የማይወክሉ መሆናቸውን ሊረዳ ይገባል። የፕሪቶሪያ ስምምነት በዚህ መንገድ መፍረስ የለበትም የትግራይ ህዝብም ዝም አይልም።

ዓለም አቀፉ ማህበረሰብ በዚህ ቡድን እና አጋሮቹ ላይ ወንጀላቸውን ለመከላከል የፕሪቶሪያ ስምምነትን እየጣሱ በመሆኑ አስፈላጊውን ሁሉ ጫና እንዲያደርግ እንጠይቃለን።

ይህ ካልተደረገ የትግራይ ህዝብ ማምለጥ ወደማይችልበት ሌላ የጥፋት ዙር ውስጥ ይገባል።
መጋቢት 3/2017 ዓ.ም



#በትግራይ

የኢትዮጵያ አየር መንገድ ወደ መቀሌ እና አክሱም  ሲያደርግ የነበረው በረራ አቆመ ።የትጋራይ ፀጥታ ሀይሎች የመቀሌን ከተማ ተቆጣጥረዋል።ጌታቸው ረዳ ከመቀሌ ወጥቷል። የጊዜያዊ መስተዳደር ሰራ...
12/03/2025

የኢትዮጵያ አየር መንገድ ወደ መቀሌ እና አክሱም ሲያደርግ የነበረው በረራ አቆመ ።

የትጋራይ ፀጥታ ሀይሎች የመቀሌን ከተማ ተቆጣጥረዋል።

ጌታቸው ረዳ ከመቀሌ ወጥቷል።

የጊዜያዊ መስተዳደር ሰራተኞች ከነደብሪፂኦን የህወሓት አንጃ ጋር ተፋጠዋል።

በወልደያ ከተማ የሚገኙት የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ እና ዳሽን ባንክ ዛሬ ለሊት ተዘርፈው አድረዋል።
12/03/2025

በወልደያ ከተማ የሚገኙት የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ እና ዳሽን ባንክ ዛሬ ለሊት ተዘርፈው አድረዋል።

የትግራዩ ውጥረት እንደቀጠለ ነውአቶ ጌታቸው ረዳ የክልሉን የሰላም እና ጸጥታ ቢሮ ሃላፊን ማሰናበታቸውን አስታወቁ፣ ቢሮው የጊዜያዊ አስተዳደሩን መዋቅር በማፍረስ ተጠምዷል ሲሉ ተችተዋልየትግራ...
12/03/2025

የትግራዩ ውጥረት እንደቀጠለ ነው

አቶ ጌታቸው ረዳ የክልሉን የሰላም እና ጸጥታ ቢሮ ሃላፊን ማሰናበታቸውን አስታወቁ፣ ቢሮው የጊዜያዊ አስተዳደሩን መዋቅር በማፍረስ ተጠምዷል ሲሉ ተችተዋል

የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር ፕሬዝዳንት አቶ ጌታቸው ረዳ የክልሉን የሰላም እና ጸጥታ ቢሮ ሃላፊ የሆኑትን ሌተናል ጄነራል ፍስሃ ኪዳኑን ከሃላፊነት ማንሳታቸውን ትላንት መጋቢት 2 ቀን 2017 ዓ.ም በጻፉት ደብዳቤ አስታወቁ፤ “የቢሮው ሃላፊ ወገንተኝነታቸው የማን እንደሆነ በግልጽ አሳይተዋል” ሲል ተችተዋል።

የጸጥታ ቢሮው “የመንግስትን ትዕዛዝ ከማክበር ይልቅ የመንግስትን መዋቅር ማፍረስ ላይ ተጠምዷል፣ ይህንንም የህግ ማስከበር ስራ አስመስሎ እያቀረበ ይገኛል” ሲሉ ኮንነዋል፤ “የቢሮው ሃላፊ ወገንተኝነታቸው የማን እንደሆነ በግልጽ ያሳያል” ሲሉ ባወጡት መግለጫ ተችተዋል።

በሌላ ዜና በክልሉ ደቡብ ምስራቅ ዞን በምትገኘው አዲጉዱም ከተማ በጸጥታ ሀይሎች እና በከተማዋ የጊዜያዊ አስተዳደሩን ተሿሚዎች በሚደግፉ ነዋሪዎች መካከል በተፈጠረ ግጭት አምስት ሰዎች በጥይት ተመትተው መቁሰላቸውን መቀለ ኤፍኤም 104 ሬድዮ በዘገባው አስታውቋል፤ ከቆሰሉት መካከል ሁለቱ ወደ መቀለ አይደር ሪፈራል ሆስፒታል መላካቸውን ጠቁሟል።
#በትግራይ

😎😎😎* የኢትዮጵያ ጠቅላይ ሚኒስቴር * ከምክትል ጠቅላይ ሚኒስቴር ጋር📷📷📷
09/03/2025

😎😎😎

* የኢትዮጵያ ጠቅላይ ሚኒስቴር * ከምክትል ጠቅላይ ሚኒስቴር ጋር

📷📷📷

የአምስት ሰዎች ህይወትን የቀጠፈ ጥቃት ደረሰበትግራይ ክልል ማንነታቸው ያልታወቁ ታጣቂዎች በሰላማውያን ሰዎች ላይ ጥቃት አድርሰዋል ሲል የትግራይ ኮሚኒኬሽን ጉዳዮች ፅህፈት ቤት አስታውቀል። ...
08/03/2025

የአምስት ሰዎች ህይወትን የቀጠፈ ጥቃት ደረሰ

በትግራይ ክልል ማንነታቸው ያልታወቁ ታጣቂዎች በሰላማውያን ሰዎች ላይ ጥቃት አድርሰዋል ሲል የትግራይ ኮሚኒኬሽን ጉዳዮች ፅህፈት ቤት አስታውቀል።

ፅህፈት ቤቱ ከደቂቃዎች በፊት ያጋራውን መረጃ መሰረት ትላንት የካቲት 28 ቀን 2017 ዓ/ም በራያ አላማጣ ወረዳ ጥሙጋ ላይ ማንነታቸው ባልታወቁ ታጣቂዎች በተፈፀመ ጥቃት የአምስት ሰዎች ህይወት ሲያልፍ ሁለት ሰዎች በከባድ መቁሰላቸው ገልፆል።

ጥቃቱ ምሽት 4:00 ገደማ መፈፁሙን የገለፀው ፅህፈት ቤቱ የጥቃቱ ሰለባዎች ደግሞ በቤተክርስትያን ውስጥ የፀሎት ስነስርዓት ሲፈፅሙ የነበሩ ስቪሎች ናቸው ብሏል።

የትግራይ ኮሚኒኬሽን ጉዳዮች ፅህፈት ቤት ጥቃቱን ጭካኔ የተሞላበት ጭፍጨፋ ሲል የገለፀው ሲሆን የክልሉ መንግስት ከሚመለከታቸው የፀጥታ አካላት ጋር በመሆን የድርጊቱ ፈፃሚዎች በቁጥጥር ስር ለማዋል ክትትል እያደረገ መሆኑን አክሏል።

አካዳሚው ዕጩ መኮንኖችን እያስመረቀ ነውአዲስ አበባ፣ የካቲት 29፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) የኢትዮጵያ ወታደራዊ አካዳሚ የ70ኛ ዙር ቃኘው ኮርስ ዕጩ መኮንኖችን እያስመረቀ ነው፡፡በምረቃ ሥነ...
08/03/2025

አካዳሚው ዕጩ መኮንኖችን እያስመረቀ ነው

አዲስ አበባ፣ የካቲት 29፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) የኢትዮጵያ ወታደራዊ አካዳሚ የ70ኛ ዙር ቃኘው ኮርስ ዕጩ መኮንኖችን እያስመረቀ ነው፡፡

በምረቃ ሥነ-ሥርዓቱ ላይ የጦር ኃይሎች ጠቅላይ ኤታማዦር ሹም ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላን ጨምሮ ጄኔራል መኮንኖች፣ የመንግሥት የሥራ ኃላፊዎች፣ የተለያዩ ሀገራት አምባሳደሮችና ወታደራዊ አታሼዎች እንዲሁም ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል።

ተመራቂ ዕጩ መኮንኖቹ የሚጠበቅባቸውን ሥልጠና ወስደው ያጠናቀቁ መሆናቸው ተገልጿል፡፡

"ከዩክሬን ጋር መደራደር ከባድ ነዉ" ትራምፕየአሜሪካዉ ፕሬዝዳንን ዶናልድ ትራምፕ በሩሲያና ዩክሬን መካከል ሰላም ለመፍጠር በሚደረገው ጥረት ከሩሲያ ይልቅ ከዩክሬን ጋር መገናኘቱ “ይበልጥ አ...
08/03/2025

"ከዩክሬን ጋር መደራደር ከባድ ነዉ" ትራምፕ

የአሜሪካዉ ፕሬዝዳንን ዶናልድ ትራምፕ በሩሲያና ዩክሬን መካከል ሰላም ለመፍጠር በሚደረገው ጥረት ከሩሲያ ይልቅ ከዩክሬን ጋር መገናኘቱ “ይበልጥ አስቸጋሪ ሆኖ አግኝቼዋለሁ” አሉ።

ትራምፕ በኦቫል ኦፊስ ለጋዜጠኞች በሰጡት ማብራሪያ አሜሪካ ከሩሲያ ጋር ጥሩ እየሰራች ነው ያሉ ሲሆን ከኬቭ ይልቅ ከሞስኮ ጋር መገናኘት ቀላል ነዉ ሲሉ ተናግረዋል።

ይህ በእንዲህ እንዳለ አሜሪካ ለኬቭ ወተደራዊ እርዳታዋን ካቆመች በኋላ ዩክሬን የሳተላይት ምስሎችን የማግኘት እድል እንዳይኖራት ማገዷን የጠፈር ቴክኖሎጂ ኩባንያዉ ማክስር ለቢቢሲ ገልጿል።

ይህ የሆነዉ ትራምፕ የዩክሬኑን ፕሬዝዳንት ቮሎዲሚር ዘለንስኪን ለአሜሪካ “አክብሮት የጎደላቸው” በማለት ከወቀሱበት የኋይት ሀውስ ንግግር ከአንድ ሳምንት በኋላ ነው።

የዩክሬኑን ፕሬዝዳንት ቮሎዲሚር ዘለንስኪን ከትራምፕ ጋር በተፈጠረዉ ግጭት እና አሁን ላይ ከአሜሪካ ጋር ባላቸዉ ግንኙነት መፀፀታቸዉን ገልፀዋል።

የእንግሊዝ ባለስልጣናት በበኩላቸዉ 20 የሚሆኑ ሀገራት ዩክሬንን ለመርዳት ፍቃደኛ እንደሆኑና እቅድ በመንደፍ ላይ መሆናቸዉን ገልፀዋል።

በሚቀጥለው ሳምንት የአሜሪካዉ ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ እና አስተዳደራቸዉ ከዩክሬን ጋር ለመምከር ወደ ሳዑዲ አረቢያ ያቀናሉ ተብሎ ይጠበቃል።

Ethiopia :- ለማንኛውም ጦርነት ዝግጁ ነኝ
07/03/2025

Ethiopia :- ለማንኛውም ጦርነት ዝግጁ ነኝ

Welcome to Ethio Media!This YouTube channel delivers daily news and in-depth analysis on current events. Make sure to subscribe to our channel and hit the be...

መረጃ ‼️የኤርትራ ጦር ከሰሜን ምእራብ የነበረዉን ግዙፍ ሃይል ወደ ደቡባዊ የሃገሪቱ ክፍል እያሰፈረ  መሆኑን የኤርትራ ሚዲያዎች ዘገቡ በኤርትራ ከባለፈው ወር ጀምሮ ከፍተኛ የተባለ ወታደራዊ...
07/03/2025

መረጃ ‼️

የኤርትራ ጦር ከሰሜን ምእራብ የነበረዉን ግዙፍ ሃይል ወደ ደቡባዊ የሃገሪቱ ክፍል እያሰፈረ መሆኑን የኤርትራ ሚዲያዎች ዘገቡ

በኤርትራ ከባለፈው ወር ጀምሮ ከፍተኛ የተባለ ወታደራዊ ዝግጅት እየተደረገ ሲሆን ሜከናይዝድ ጦሩም እየተንቀሳቀሰ ይገኛል ፡፡

በሀገሪቱ በተላለፈዉ ወታደራዊ ትእዛዝ መሰረት ከብሄራዊ ጦር ተለይተዉ የነበሩ ተጠባባቂ ወታደሮች በፍጥነት ጦሩን እንዲቀላቀሉ መደረጉ ይታወሳል ፡፡

ወታደራዊ እንቅስቃሴዉ ሃገሪቱ ሰሞኑን ከኢትዮጵያ ጋር በገባቸዉ የቃላት ምልልስ ጋር ተያይዞ ይሁን አይሁን የተባለ ነገር የለም ፡፡

Ethio Daliy News

#በትግራይ

27ኛ ቀን...648 ሚልየን ብር!!መቄዶንያ የአረጋውያንና የአዕምሮ ህሙማን መርጃ ማዕከል በቀጥታ ስርጭት በሚያደርገው የገቢ ማሰባሰቢያ መርሐ-ግብር ብዙዎች እየተሳተፉ ነው::እስከአሁን ከ64...
07/03/2025

27ኛ ቀን...648 ሚልየን ብር!!

መቄዶንያ የአረጋውያንና የአዕምሮ ህሙማን መርጃ ማዕከል በቀጥታ ስርጭት በሚያደርገው የገቢ ማሰባሰቢያ መርሐ-ግብር ብዙዎች እየተሳተፉ ነው::

እስከአሁን ከ648 ሚሊዮን ብር በላይ ተሰብስቧል።

#ሜቄዶንያ

Address

Addis Ababa

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Ethio Daliy News posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to Ethio Daliy News:

Share