Horn Agora Review

Horn Agora Review We promote Democracy and integrated development in Horn of Africa

ስለዚህ ለሌላ ወገኗ፣ solidarity በማሳየቷ ፣መደነቅ ይገባታል። የራሷን ቋንቋ አልተቃወመችም።
22/08/2026

ስለዚህ ለሌላ ወገኗ፣ solidarity በማሳየቷ ፣መደነቅ ይገባታል። የራሷን ቋንቋ አልተቃወመችም።

የዎላይታ ተወካዮች ወላይትኛ 6ኛው የፌዴራል የስራ ቋንቋ እንዲሆን ያነሱት ጥያቄ ተከትሉ የሲዳማ ክልል ተወካይ "ወላይትኛ ቋንቋ በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል፣ በማከላዊ ኢትዮጵያ ክልል፣ በደቡብ ምእራብ ኢትዮጵያ ክልልና በሲዳማ ክልል በስፋት ከመነገሩም በላይ በመላ ሀገሪቱ የብሔሩ ተወላጆች ከመበተኑ ጋር ተያይዞ ተጨማሪ የፌዴራል የስራ ቋንቋ ከመሆኑም በላይ ለደቡብ አካባቢ የጋራ መግባቢያ ነው" ማለታቸው በሲዳማ ተወካዮች መካከል መከፋፈል መፍጠሩ ተገለጸ።

በርቱ ፣ ጀግኖች!
22/08/2026

በርቱ ፣ ጀግኖች!

22/08/2026
22/08/2026

H.E. Sahle-Work Zewde, former President of Ethiopia and the country’s first woman head of state, has long emphasized the importance of confidence, possibility, and equal opportunity for women and girls.

Her message is a reminder that leadership expands what the next generation believes is possible.

22/08/2026

ይሄን አይተን እናልቅስ😥 ፣ ወይስ እንሳቅ😂?

21/08/2026

#ዜና: በትግራይ የመምህራን መኖሪያ ቤቶች ላይ በተፈጸመ የአየር ጥቃት 14 ሰዎች መቁሰላቸውን የክልሉ ትምህርት ቢሮ አስታወቀ

መቐለ— የ #ትግራይ ክልል ትምህርት ቢሮ ነሐሴ 14 ቀን 2018 ዓ.ም. #መቐለ ከተማ በሚገኙ “የመምህራን መኖሪያ ቤቶች ላይ በፌደራል መንግሥት” የተፈጸመውን የአየር ጥቃት እንደሚያወግዝ በዛሬው ዕለት ባወጣው መግለጫ አስታወቀ።
በጥቃቱ ሳቢያ “14 መምህራንና የቤተሰቦቻቸው አባላት አካላዊ ጉዳት የደረሰባቸው ሲሆን፣ በከፍተኛ ጥረትና ድካም ባፈሩት ንብረት ላይም ከፍተኛ ውድመት” መድረሱን ቢሮው ገልጿል።

“በትግራይ ህዝብ ላይ እየተፈጸመ ያለውን በደልና ውድመት” የሚቃወመው የትግራይ ትምህርት ቢሮ መግለጫ፣ ጉዳት ለደረሰባቸው መምህራንና የቤተሰብ አባላት ፈጣን ምህረትና ጤንነትን ተመኝቷል። በተጨማሪም በትምህርት ዘርፍ ላይ የሚሰሩ የተለያዩ ሀገር በቀልና ዓለም አቀፍ ድርጅቶች ይህንን ድርጊት እንዲያወግዙና ለተጎዱት መምህራንና ቤተሰቦቻቸው አስፈላጊውን ድጋፍ እንዲያደርጉ ጥሪ አቅርቧል።

ትላንት ነሐሴ 14 ቀን 2018 ዓ.ም. በመቐለ ከተማ ሁለት የተለያዩ ቦታዎች ላይ የአውሮፕላን ጥቃቶች ተፈጽመዋል።

የመጀመሪያው ጥቃት በሐወልቲ ክፍለ ከተማ “ዳ ማርያም” ቤተክርስቲያን አቅራቢያ የሚገኙ የመኖሪያ ቤቶችን ላይ ሲሆን፣ ሁለተኛው ጥቃት ደግሞ በኲሓ አካባቢ ተመዝግቧል።

በጥቃቱ የቆሰሉ በርካታ ሰዎች፣ ህፃናትን ጨምሮ፣ ወደ ዓይደር አጠቃላይ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል ድንገተኛ ህክምና ክፍል ተወስደው አስፈላጊው ህክምና እየተደረገላቸው ይገኛል። ይህ ድርጊት የተፈጸመው በፌደራል መንግሥትና በህወሓት ባለስልጣናት መካከል ያለው አጠቃላይ ውጥረት በድጋሚ እያየለ በመጣበትና የሰላም ስምምነቱ አፈጻጸም ስጋት ላይ በወደቀበት ወቅት ነው።

21/08/2026
21/08/2026

“ትዕግስቱም ወሰን ያለው በመሆኑ”

#ህወሓት መራሹ የትግራይ ክልላዊ መንግሥት ለዓለም አቀፉ ማኅበረሰብ አስቸኳይ የዲፕሎማሲያዊ ጣልቃ ገብነት ጥሪ አቀረበ

መቐለ: በትግራይ እንደ አዲስ የተጋጋጠውን ውጥረትና በቅርቡ የተፈጸሙ ጥቃቶችን አስመልክቶ ህወሓት-መራሹ የትግራይ ክልላዊ መንግሥት ለዓለም አቀፉ ማኅበረሰብ አስቸኳይ የዲፕሎማሲያዊ ጣልቃ ገብነት ጥሪ አቀረበ። #ትግራይ ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ቢሮ ነሐሴ 15 ቀን 2018 ዓ.ም በመቐለ ባወጣው መግለጫ፣ የፌደራል መንግሥት እየወሰዳቸው ያሉ እርምጃዎች ቀጣናውን ወደ አዲስ አጥፊ ጦርነት ከማስገባታቸው በፊት ዓለም አቀፉ ማኅበረሰብ ዝምታውን ሰብሮ ጥቃቶቹን በግልጽ እንዲያወግዝ ጠይቋል።

በመግለጫው መሠረት፣ የፕሬቶሪያው የሰላም ስምምነት አፈጻጸም መስተጓጎሉን ተከተሎ የፌደራል መንግሥት “በራያ፣ #እንትጮ፣ #ሽራሮ” እና በሌሎች አካባቢዎች የድሮን ጥቃቶችንና የወታደራዊ ኃይል እንቅስቃሴዎችን አጠናክሯል። በተለይም ነሐሴ 1 ቀን 2018 ዓ.ም በምዕራብ ትግራይ ሸረሪና በተባለ ቦታ የተፈጸመው ጥቃት፣ ነሐሴ 4 ቀን በደቡባዊ ትግራይ #መረዋ ወረዳ በሚገኝ ትምህርት ቤት ላይ የተካሄደው የድሮን ድብደባ፣ እንዲሁም በዋጃ ቲሙጋ ወረዳ ማርያም ኩቢ መንደር የተፈጸሙ የከባድ መሣሪያ ጥቃቶች በሰላማዊ ሰዎችና በንብረት ላይ ከፍተኛ ጉዳት ማድረሳቸው ተገልጿል።

በተጨማሪም ነሐሴ 12 ቀን በ #መቐለ አቅራቢያ በሚገኘው #ዳንደራ መንደር እንዲሁም በቅርቡ በመቀሌ ከተማ ሐወልቲ ክፍለ ከተማ ሞሞና ሰፈር በሚገኙ የመምህራን መኖሪያ ቤቶች ላይ በተፈጸሙ የአየር ጥቃቶች ሕፃናትን ጨምሮ ቢያንስ 13 ሰዎች መቁሰላቸውና መኖሪያ ቤቶች መደመሰሳቸው በመግለጫው ተጠቅሷል። እነዚህ ጥቃቶች የሰዎችን ሕይወት ከመቀጠፋቸው ባለፈ፣ በሕዝቡ ላይ ከፍተኛ ፍርሃት የፈጠሩና የሴቶችና ልጃገረዶች ባህላዊ ቅርሶች መግለጫ የሆነውን የእሸንደ በዓል አከባበር ሆን ብለው ለማስተጓጎል የተደረጉ ናቸው ሲል የህወሓት አስተዳደር ከሷል።

ለሰላምና ለቀጣናው ረጋታ ሲሉ እስካሁን ከፍተኛ ትዕግስት ማሳየታቸውን የጠቀሰው ቢሮው፣ ይህ ትዕግስት ግን እንደ ድክመት ወይም ሕዝብንና ግዛትን የመጠበቅ አቅም እንደሌለው ተደርጎ መወሰድ እንደሌለበት አሳስቧል። የትግራይ አስተዳደር ለሰላማዊ ውይይት ያለው ቁርጠኝነት የጸና ቢሆንም ትዕግስቱም ወሰን ያለው በመሆኑ፣ ዓለም አቀፉ ማኅበረሰብ አሁኑኑ ወሳኝ ዲፕሎማሲያዊ እርምጃ እንዲወስድ ጥሪውን አስተላልፏል።

21/08/2026

#ኢትዮጵያ በ180 ሺህ ኪሎ ሜትር የመንገድ ሽፋን በአፍሪካ ሦስተኛ ደረጃን መያዟን ግሎባል ፋየር ፓወር አስታወቀ

​ኢትዮጵያ በአጠቃላይ 180 ሺህ ኪሎ ሜትር የመንገድ ሽፋን በመዘርጋት በአፍሪካ ሦስተኛ፣ በዓለም አቀፍ ደረጃ ደግሞ 30ኛ ደረጃን መያዟን መቀመጫውን #አሜሪካ ያደረገው «ግሎባል ፋየር ፓወር» የተሰኘው የመከላከያ መረጃ ተቋም አስታወቀ።

​የ2026 መረጃውን ይፋ ያደረገው ተቋሙ፤ ኢትዮጵያ በ750 ሺህ ኪሎ ሜትር የአፍሪካን ትልቁን የመንገድ ሽፋን በመያዝ የመሪነት ደረጃ ላይ ከምትገኘው እና በ195 ሺህ ኪሎ ሜትር ሁለተኛ ደረጃን ከያዘችው #ናይጄሪያ ቀጥላ የምትገኝ ሲሆን፣ #ኬንያ በ161 ሺህ 452 ኪሎ ሜትር ከአህጉሪቱ አራተኛ፣ በዓለም ደግሞ 32ኛ ደረጃ ላይ ተቀምጣለች።

​ኢትዮጵያ በዚሁ የመንገድ ሽፋን ኬንያን በ18 ሺህ 548 ኪሎ ሜትር የምትበልጥ ሲሆን፣ በአፍሪካ ቀንድ ከሚገኙ በርካታ ጎረቤቶቿም በእጅጉ የላቀ የመንገድ ሽፋን እንዳላት ተመላክቷል።

በዓለም አቀፍ ደረጃ ሱዳን በ31 ሺህ ኪሎ ሜትር የመንገድ ሽፋን 100ኛ ደረጃን ስትይዝ፣ ኤርትራ በ16 ሺህ ኪሎ ሜትር 118ኛ፣ እንዲሁም ሶማሊያ በ15 ሺህ ኪሎ ሜትር ገደማ 121ኛ ደረጃ ላይ ይገኛሉ።

​ግሎባል ፋየር ፓወር ዓመታዊ የሀገራት ደረጃ ምዘናው ጥቅም ላይ የሚውለውን እና አገልግሎት የሚሰጠውን አጠቃላይ የመንገድ ሽፋን የሚለካ መሆኑን ገልጿል። ይህም የመንገድ መሠረተ ልማት የሀገራትን የመሠረተ ልማት ዕድገት ደረጃ፣ እንዲሁም ወደ ኢንዱስትሪ ዘርፎች፣ ተርሚናሎችና ወደቦች ለመድረስ የሚያስችል ቁልፍ መስፈርት እንደሆነ አብራርቷል።

​አክሎም የመንገድ መረብን ከሰዎችና ከቁሳቁስ እንቅስቃሴ ጋር በማያያዝ፣ የትራንስፖርት መሠረተ ልማት ለሀገራዊ ንቅናቄና ለደኅንነት ወሳኝ እንደሆነ ገልጿል።

​በዓለም አቀፍ ደረጃ አሜሪካ ትልቁ የመንገድ ሽፋን ያላት ሀገር ስትሆን፣ ሕንድ፣ ቻይና፣ ብራዚል እና ሩሲያ በቅደም ተከተል ይከተላሉ።

Address

4 Kilo
Addis Ababa

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Horn Agora Review posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Shortcuts

Share