ፍኖት

ፍኖት ታማኝ እና ደረጃውን የጠበቀ የመረጃ ምንጭ ለመሆን እንተጋለን።

 ኢትዮ ቴሌኮም በበጀት ዓመቱ መንፈቅ ዓመት 33.8 ቢሊዮን ብር ገቢ ማግኘቱን ገልጿል።ኢትዮ ቴሌኮም አዲስ “ሊድ” የተሰኘ የሦስት ዓመት አዲስ የእድገት ስትራቴጂውን በ2015 በጀት ዓመት መ...
12/01/2023



ኢትዮ ቴሌኮም በበጀት ዓመቱ መንፈቅ ዓመት 33.8 ቢሊዮን ብር ገቢ ማግኘቱን ገልጿል።

ኢትዮ ቴሌኮም አዲስ “ሊድ” የተሰኘ የሦስት ዓመት አዲስ የእድገት ስትራቴጂውን በ2015 በጀት ዓመት መጀመሪያ ካስተዋወቀ በኋላ የመጀመሪያ ግማሽ ዓመት ሪፖርቱን ዛሬ አቅርቧል።

የኢትዮ ቴሌኮም ዋና ስራ አስፈታሚ ወ/ሪት ፍሬህይወት ታምሩ ዛሬ ለጋዜጠኞች በሰጡት መግለጫ ኢትዮ ቴሌኮም በ2015 በጀት ዓመት አጋማሽ 33.8 ቢሊዮን ብር ገቢ ማግኘቱን ገልጿል። ኩባንያንያው ይህም የእቅዱን 96% ማሳካቱን ነው የገለጸው።

የተገኘው የገቢ ድርሻ በአገልግሎት አይነት ሲታይ ፦

- የድምጽ አገልግሎት 47.4% ድርሻ ሲኖረው

- ዳታና ኢንተርኔት 28%፣

- ዓለም አቀፍ ገቢ 8.4%፣

- እሴት የሚጨምሩ አገልግሎቶች የ6.5%፣

- እቃ ሽያጭ( Device) 4.3%

- የመሰረተ ልማት ማጋራት Infra.Sharing (2.2)

- ሌሎች አገልግሎቶች 3.2% ድርሻ አላቸው ተብሏል።

የውጭ ምንዛሪ ከሚያስገኙ አገልግሎቶች 64.8 ሚሊዮን የአሜሪካን ዶላር የተገኘ ሲሆን ይህም የእቅዱን 90% ያሳካ ነው ተብላል።

ኩባንያው የደንበኞቹ ቁጥር 70 ሚሊዮን መድረሱንም ወ/ሮ ፍሬህይወት ገልጸዋል ፦

- የድምጽ አገልግሎት 67.7 ሚሊዮን

- ዳታና ኢንተርኔት 31.3 ሚሊዮን

- መደበኛ የብሮድባንድ 566.2 ሺ ተጠቃሚዎች

- መደበኛ የስልክ 862.2 ሺ ተጠቃሚዎች መድረሱን አስታውቀዋል።

በዚህም በበጀት አመቱ ግማሽ አመት 15.1 እድገት ያሳየ ሲሆን 9.2 ተጨማሪ ደንበኞችን ማግኘቱን አስታውቀዋል።

ዋና ስራ አስፈጻሚዋ በውድድር ገቢያ ውስጥ ሆነን ደንበኞችን የማቆየትና አዳዲስ ደንበኞችን በማፍራት አመርቂ አፈጻጸም ያስመዘገብንበት ነው ሲሉ ገልጸዋል።

#ቲክቫህ #ኢትዮጵያ

የ20/80 እና 40/60 ውል እንዴት እየሄደ ነው ?" በሁለቱም የቤት ልማት ፕሮግራሞች 7,051 ሰዎች ተመዝግበው ቅፅ 09ን  መውሰድ ችለዋል " - የአዲስ አበባ ቤቶች ልማት ኮርፖሬሽንየ2...
12/01/2023

የ20/80 እና 40/60 ውል እንዴት እየሄደ ነው ?

" በሁለቱም የቤት ልማት ፕሮግራሞች 7,051 ሰዎች ተመዝግበው ቅፅ 09ን መውሰድ ችለዋል " - የአዲስ አበባ ቤቶች ልማት ኮርፖሬሽን

የ20/80 14ኛ ዙር እና የ40/ 60 3ኛ ዙር የቤት ባለ እድለኞች ውል የማዋዋል ስራ " በጥሩ ሁኔታ " እየተካሄደ ይገኛል ሲል የአዲስ አበባ ቤቶች ልማት ኮርፖሬሽን አስታወቀ።

ኮርፓሬሽኑ በ20/80 14ኛ ዙር እና በ40/60 3ኛ ዙር የቤት ባለ እድለኞች ውል የማዋዋል ስራ ከጥር 1/2015 ዓ.ም. ጀምሮ እየተካሄደ መሆኑን ገልጿል።

" ውል ከጀመረበት ቀን ጀምሮ 7,051 ሰዎች ተመዝግበው ቅፅ 09ን በሁለቱም የቤት ልማት ኘሮግራሞች መውሰድ ችለዋል " ብሏል።

ተቋሙ ፤ " ባለ እድለኞች እንዳይጉላሉ በቂ ቦታ እና የሰው ሃይል መድቤ በማስተናገድ ላይ ነኝ " ያለ ሲሆን ውሉ ከተጀመረ ጀምሮ ለተከታታይ 60 የስራ ቀናት ብቻ ይቆያል ሲል አስታውሷል።

#ቲክቫህ #ኢትዮጵያ

 የጥምቀት በዓል እጅግ በድምቀት የሚከበርባት ጎንደር ከተማ ዝግጅቷ በማጠናቀው እንግዶቿን እየተጠባበቀች ነው።በታሪካዊቷ ጎንደር ከተማ የሚገኙ አገልግሎት ሰጪዎች ለበዓሉ የሚመጡ እንግዶችን ለ...
12/01/2023



የጥምቀት በዓል እጅግ በድምቀት የሚከበርባት ጎንደር ከተማ ዝግጅቷ በማጠናቀው እንግዶቿን እየተጠባበቀች ነው።

በታሪካዊቷ ጎንደር ከተማ የሚገኙ አገልግሎት ሰጪዎች ለበዓሉ የሚመጡ እንግዶችን ለመቀበል እና በክብር ለማስተናገድ ዝግጅታችንን ሁሉ አጠናቀናል ብለዋል።

ዘንድሮ እጅግ ከፍተኛ ቁጥር ያለው ሰው የጥምቀት በዓልን ለማክበር ጎንደር ይገባል ተብሎ ይጠበቃል።

የከተማ አስተዳደሩ " የጥምቀት በዓልን የጥበብ መፍለቂያና የፍቅር ከተማ በሆነችው በጎንደር ኑ አብረን እናክብር " ሲል ጥሪ አቅርቧል።

" ጎንደር የሃይማኖት፣ የፍቅር ፣ የጥበብ መፍለቂያ፣ የቱሪስት ምስእብ ፣ የኩሩ ህዝብ ባለቤት ከተማ ናት " ያለው አስተዳደሩ ፤ የጎንደር ህዝብ እንግዳ ተቀባይ፣ ሰው አክባሪ ህዝብ ነው ፤ ኑ የጥምቀት በዓል በጋራ እናክብር ብሏል።

#ቲክቫህ #ኢትዮጵያ

 " በአዲስ አበባ ከተማ ከኦሮምያ ክልል ለአፋን ኦሮሞ ቋንቋ ማስተማርያነት  #በውሰት ተወስዶ ተግባራዊ ሲደረግ የነበረው ስርአተ ትምህርት  #በአዲሱ ስርዐት ትምህርት የሚተካ ይሆናል። " -...
12/01/2023



" በአዲስ አበባ ከተማ ከኦሮምያ ክልል ለአፋን ኦሮሞ ቋንቋ ማስተማርያነት #በውሰት ተወስዶ ተግባራዊ ሲደረግ የነበረው ስርአተ ትምህርት #በአዲሱ ስርዐት ትምህርት የሚተካ ይሆናል። " - የአዲስ አበባ ከተማ ካቢኔ

#ቲክቫህ #ኢትዮጵያ

12/01/2023



የአዲስ አበባ አስተዳደር ካቢኔ ባካሄደው በ2ኛ ዓመት 8ኛ መደበኛ ስብሰባው ከብዝሃ ቋንቋ ካሪኩለም ጋር በተያያዘ ውሳኔዎችን አሳልፏል፡፡

ካቢኔውም በመደበኛው ስብሰባ የብዝሃ የቋንቋ ስርዓተ ትምህርትን አስመልክቶ የኮተቤ ትምህርት ዩንቨርሲቲ ሲያስጠናው የቆየውን አዲሱን ካሪኩለም አስመልክቶ ተወያይቷል።

በዚህም ፤ ዩንቨርሲቲው ባስጠናው ጥናት ዙርያ ሰፋ ያለ የተለያዩ የሕዝብ ( ) ምክክሮችና ውይይቶች ሲካሄዱበት ቆይቶ በዛሬው ዕለት በጥናቱ በቀረቡት ምክረ ሃሳቦች ዙርያ ውሳኔውን ማሳለፉን የከተማ አስተዳደሩ አስታውቋል፡፡

በዚህም መሰረት፡-

1ኛ:- በአዲሱ ስርዐተ ትምህርት ጥናት መሰረት በአፋን ኦሮሞ የአፍ መፍቻ ቋንቋቸው ለሚማሩ ተማሪዎች አማርኛ እንደ ተጨማሪ (ሁለተኛ ) ቋንቋ እንዲሰጥ፤

2ኛ:- በአማርኛ የአፍ መፍቻ ቋንቋቸው ለሚማሩ ተማሪዎች ደግሞ አፋን ኦሮሞ እንደ ተጨማሪ (ሁለተኛ) ቋንቋ እንዲሰጥ፤

3ኛ:- ከ7ኛ ክፍል ጀምሮ በሁሉም የከተማው ትምህርት ቤቶች የአገር ውስጥ ቋንቋ መማራቸው እንደተጠበቀ ሆኖ ሁሉንም የትምህርት አይነቶችን በእንግሊዘኛ መማር እንዲችሉ እንዲደረግ፤

4ኛ:- ለ9ኛ እና 10ኛ ክፍል ተማሪዎች #አረብኛና #ፈረንሳይኛ በሃይስኩል ደረጃ አማራጭ ትምህርት ሆኖ እንዲቀጥል፤

5ኛ:- የቅድመ አንደኛ ደረጃ የትምህርት መጀመሪያ እድሜ ከ4 ዓመት እንዲሆን፤

6ኛ:- በአዲሱ የስርዓተ-ትምህርት ማዕቀፍ መሰረት 11ኛ እና 12ኛ ክፍል የሥራ እና ቴክኒክ ትምህርት በተለያዩ አመራጮች እንደሚማሩ በሚያስቀምጠዉ መስረትና ከፍተኛ ሀብት የሚፈልግ በመሆኑ ከቴክኒክና ሞያ ኮሌጆች በክላሰተር በቅንጅት እንዲሰጥና በተጠናው ጥናት መሰርት ወደ ግንባታ እንዲገባ እንዲደረግ፤

7ኛ:- የግል ትምህርይ ቤቶችን የመፅሐፍት እጥረት ለመቅረፍ በሽያጭ ለማቅረብ ለመጽሓፍት ህትመት የተዘዋዋሪ ፈንድ 250 ሚሊየን ብር ተጨማሪ በጀት እንዲፈቀድ ውሳኔ አሳልፏል፡፡

በዚህም መሰረት፤ በአዲስ አበባ ከተማ ከኦሮምያ ክልል ለኦሮምኛ ቋንቋ ማስተማርያነት በውሰት ተወስዶ ተግባራዊ ሲደረግ የነበረው ስርአተ ትምህርት በአዲሱ ስርዐት ትምህርት የሚተካ ይሆናል ተብሏል።

ምንጭ፦ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር

#ቲክቫህ #ኢትዮጵያ

ፎቶ ፦ ዛሬ ረቡዕ የአፍሪካ የበሽታዎች መከላከልና መቆጣጠር ማዕከል የመጀመሪያ ምዕራፍ ግንባታ በቻይናው የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ቺን ጋንግ እና በአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀመንበር ሙሳ ፋኪ ተ...
12/01/2023

ፎቶ ፦ ዛሬ ረቡዕ የአፍሪካ የበሽታዎች መከላከልና መቆጣጠር ማዕከል የመጀመሪያ ምዕራፍ ግንባታ በቻይናው የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ቺን ጋንግ እና በአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀመንበር ሙሳ ፋኪ ተመርቋል።

ስለ ማዕከሉ ምን ይታወቃል ?

- ማዕከሉ የኢትዮጵያ መንግሥት ኃይሌ ጋርመንት ተብሎ በሚጠራው አካባቢ ከሊዝ ነፃ ባቀረበው በ90 ሺሕ ሜትር ስኩዌር መሬት ስፋት ያለው መሬት ላይ የተገነባ ነው።

- የህንፃው ግንባታ ብቻ በ40 ሺሕ ሜትር ስኩዌር ላይ ያረፈ ነው፡፡

- የቻይና መንግሥት 80 ሚሊዮን ዶላር በማውጣት የግንባታውን ሙሉ ወጪ ሸፍኗል።

- የመጀመሪያው ምዕራፍ ግንባታ 25 ወራትን ፈጅቷል።

- ማዕከሉ የድንገተኛ አደጋ ኦፕሬሽን፣ የመረጃ፣ የላብራቶሪ፣ የስልጠና ፣ የኮንፈረንስ ማዕከል ፣ ቢሮዎች እና አፓርትመንቶች አሉት።

- የማዕከሉ ሁለተኛ ምዕራፍ ግንባታ (አገልግሎት ለማስጀመር የሚያስችሉ የማጠቃለያ ሥራዎች) እየተካሄደ ነው።

- ማዕከሉ በቅርቡ ሙሉ ስራው ተጠናቆ ወደ ሥራ ይገባል።

- በግንባታው ላይ #ቻይናውያንና #ኢትዮጵያውያን የህንፃ ባለሞያዎች እየተሳተፉበት ነው።

Info : ENA
Photo Credit : Tesfaye Wube (Tikvah Family)

#ቲክቫህ #ኢትዮጵያ

የ17 ዓመት ፅኑ እስራት ተፈርዶበታል !የአራት አመቷን ህጻን አስገድዶ የደፈረው ግለሰብ በ17 ዓመት ጽኑ እስራት ተቀጣ።በአማራ ክልል ፤ በምስራቅ ጎጃም ዞን ጎንቻ ሲሶ እነሴ ወረዳ 018 ቀ...
12/01/2023

የ17 ዓመት ፅኑ እስራት ተፈርዶበታል !

የአራት አመቷን ህጻን አስገድዶ የደፈረው ግለሰብ በ17 ዓመት ጽኑ እስራት ተቀጣ።

በአማራ ክልል ፤ በምስራቅ ጎጃም ዞን ጎንቻ ሲሶ እነሴ ወረዳ 018 ቀበሌ ንዋሪ የሆነው ክንድየ ግዛቸው የተባለ ግለሰብ ታህሳስ 19 ቀን 2015 ዓ/ም የዚሁ ቀበሌ ንዋሪ የሆነች የ4 ዓመት ህጻን ከምትጫወትበት ቦታ አታሎ ወደ ጫካ ውስጥ ካስገባት በኋላ ደፍሯት ለመሰወር ይሞክራል።

ምንም እንኳን ግለሰቡ ለመሰወር ቢሞክርም የአካባቢው ማህበረሰብ በሰጠው ጥቆማ መሰረት በፀጥታ ኃይል በቁጥጥር ስር ውሎ ምርመራ ተጣርቶበት መዝገቡ ለሚመለከተው የፍትህ አካል ይላካል።

ጉዳዩን የተመለከተው የጎንቻ ወረዳ ፍርድ ቤት ግለሰቡ ጥፋተኛ መሆኑን በሰው እና በሰነድ ማስረጃ በማረጋገጡ ዛሬ ጥር 3 ቀን 2015 ዓ/ም በዋለው ችሎት ተከሳሽ ክንድየ ግዛቸው በ17 ዓመት ጽኑ እስራት እንዲቀጣ ወስኖበታል።

የተደፈረችው ህጻን ከፍተኛ የሆነ ጉዳት የደረሰባት በመሆኑ በአሁኑ ሰዓት በባህር ዳር ሆስፒታል የህክምና ክትትል እየተደረገላት እንደሚገኝ ታውቋል።

ምንጭ፦ የምስራቅ ጎጃም ዞን ፖሊስ

#ቲክቫህ #ኢትዮጵያ

 #ነዳጅ  ወደ ትግራይ ክልል  #ነዳጅ መግባት መጀመሩን የክልሉ የንግድ ውድድርና ሸማቾች ጥበቃ ቢሮ አስታውቋል።ቢሮው ፤ ወደ መቐለ 10 ቦቴ ነዳጅ መግባቱን ያመለከተ ሲሆን ወደ ኩዊኃ እና ...
11/01/2023

#ነዳጅ

ወደ ትግራይ ክልል #ነዳጅ መግባት መጀመሩን የክልሉ የንግድ ውድድርና ሸማቾች ጥበቃ ቢሮ አስታውቋል።

ቢሮው ፤ ወደ መቐለ 10 ቦቴ ነዳጅ መግባቱን ያመለከተ ሲሆን ወደ ኩዊኃ እና ዓጉላም ነዳጅ መግባት መጀመሩን ጠቁሟል።

ከፌዴራል መንግስት ጋር ጥሩ ትብብር እየተደረገ ነው ያለው ቢሮ " እናተ ጋር ካለው ችግር አንፃር ቅድሚያ እንሰጣለን " ተብለናል ሲል ገልጿል።

ጦርነት ለመፈጠሩ በፊት በወር 12 ሚሊዮን ሊትር ናፍጣ ይገባ እንደነበር የገለፀው ቢሮው አሁን እየገባ ያለው ነዳጅ ከሚፈለገው አንፃር እጅግ በጣም ትንሽ ነው ብሏል።

መቐለ ውስጥ ካሉት 15 ማደያዎች ነዳጅ የገባው በ4ቱ ላይ ብቻ እንደሆነ ተገልጿል።

ነዳጅ ለማግኘት እነማን ቅድሚያ አላቸው ?

አሁን እየገባ ያለው ነዳጅ በተወሰነ መልኩ ስለሆነ ፦

- አምቡላንስ
- እሳት አደጋ
- ውሃ አቅራቢ ቦቴዎች
- የመንግስት ተሽከርካሪዎች
- የእርዳታ አከፋፋይ አካላት
- ባንክ፣ ቴሌ፣ መብራት ኃይል
- በትራንስፖርት ቢሮ ታሪፍ የወጣላቸው ለህብረተሰቡ የትራንስፖርት አገልግሎት የሚሰጡ ቅድሚያ እንደሚያገኙ ተመላክቷል።

የፋይናንስ እጥረት በበቂ ሁኔታ ነዳጅ እንዳይገባ እንቅፋት መሆኑን ያሳወቀው ቢሮው ችግሩን ለማፍታት ከባንክ ጋር ንግግር እየተደረገ መሆኑን ገልጿል።

ቤንዚን እና ናፍጣ ስንት እየተሸጠ ነው ?

የነዳጅ ምርቶች የችርቻሮ መሸጫ ዋጋ ከፌዴራል መንግስት ለክልሉ እንደተላከ ለመረዳት ተችሏል።

በመቐለ #ቤንዚን በሊትር 60 ብር ከ57 ሳንቲም እየተሸጠ ሲሆን #ናፍጣ 66 ብር ከ58 ሳንቲም እየተሸጠ መሆኑን ከክልሉ ቴሌቪዥን ያገኘነው መረጃ ያሳያል።

Photo Credit : Tigrai Television

#ቲክቫህ #ኢትዮጵያ

ፎቶ ፦ የፌዴራል መንግስት እና ህወሃት በስምምነቱ መሰረት የከባድ መሳሪያዎችን  መረካከብ ጀምረዋል።በፌዴራል መንግስት እና በህወሃት አመራሮች መካከል በደቡብ አፍሪካ እና በኬኒያ የተደረሰዉን...
11/01/2023

ፎቶ ፦ የፌዴራል መንግስት እና ህወሃት በስምምነቱ መሰረት የከባድ መሳሪያዎችን መረካከብ ጀምረዋል።

በፌዴራል መንግስት እና በህወሃት አመራሮች መካከል በደቡብ አፍሪካ እና በኬኒያ የተደረሰዉን ስምምነት ተከትሎ በትላንትናዉ ዕለት የመጀመሪያ ዙር ከባድ መሳሪያ ርክክብ መደረጉ ተገልጿል።

ርክክቡ ከመቐለ ከተማ 36 ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ በሚገኘው አጉላ ካምፕ የተከናወነ ሲሆን በርክክቡ የተለያዩ ሀገራት ወታደራዊ ታዛቢዎች ተገኝተው እንደነበር ተገልጿል።

በቀጠናው የተሰማራው የሰራዊት አመራር ሌተናል ኮሎኔል አለሜ ታደለ ፤ " በመንግስታችንና በህዋሃት አመራሮች መካከል በተደረሰው የሰላም ስምምነት መሰረት የተለያዩ ዓይነት ከባድ መሳሪያዎችን ተረክበናል " ብለዋል።

ህወሃት ለሀገር መከላከያ ሰራዊት ያስረከባቸዉ የመሳሪያ ዓይነቶች፦

- ብረት ለበስ ታንኮች፤
- የተለያዩ ሚሊ ሜትር መድፎች፤
- ሮኬቶች፤
- ዙዎች፤
- ሞርተሮች እና ፐምፐን ያጠቃለለ መሆኑን ሌተናል ኮሎኔል አለሜ ታደለ ተናግረዋል፡፡

የርክክብ ስነ-ስርዓቱን ለመታዘብ የአፍሪካ ህብረት ታዛቢ አረካካቢ ኮሚቴዎች የተገኙ ሲሆን ከአረካካቢዎች መካከል ብርጋዴር ጄኔራል አድዋ ልቡካን ፒተር በሁለቱም ወገኖች በኩል እየተደረገ ያለዉ የከባድ መሳሪያ ርክክብ የተጀመረዉን የሰላም ጉዞ የሚያጠናክር መሆኑን ገልፀዋል፡፡

" በኢትዮጵያ ፌደራላዊ ዲሞክራሲያዊ ሪፐፕሊክ መንግስትና በህወሃት መካከል የተደረሰው ሰላምን የማስፈን ተግባር ዓለምን የሚስደንቅ ስለሆነ ለመላው ህዝብና ስምምነቱን ተግባራዊ እያደረጉ ላሉ አካላት ምስጋናዬን አቀርባለሁ " ብለዋል፡፡

Credit : የሀገር መከላከያ ሰራዊት

#ቲክቫህ #ኢትዮጵያ

 የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን አመራሮች እና የትግራይ ክልል ተወላጅ የሆኑ አትሌቶችን የያዘ የልዑካን ቡድን ነገ ማክሰኞ ጥር 2/ 2015 ዓ/ም ወደ ትግራይ ክልል መዲና ፤ መቐለ እንደሚጓ...
09/01/2023



የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን አመራሮች እና የትግራይ ክልል ተወላጅ የሆኑ አትሌቶችን የያዘ የልዑካን ቡድን ነገ ማክሰኞ ጥር 2/ 2015 ዓ/ም ወደ ትግራይ ክልል መዲና ፤ መቐለ እንደሚጓዝ " ኢትዮጵጵያ ኢንሳይደር " ዘግቧል።

የልዑካን ቡድኑ የሚመራው በኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌደሬሽን ፕሬዝዳንት አትሌት ደራርቱ ቱሉ ሲሆን ወደ መቐለ የሚጓዘው የክልሉ ተወላጅ የሆኑ አትሌቶችን ከቤተሰቦቻቸው ጋር ለማገናኘት መሆኑ ተነግሯል።

ቡድኑ ወደ መቐለ ነገ ረፋድ በአውሮፕላን የሚጓዝ ሲሆን በመቐለ ከተማ የሚኖረው ቆይታ የአንድ ቀን ብቻ መሆኑን በጉዞው ላይ ተሳታፊ የሆነ አንድ አትሌት ተናግሯል።

በኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን የኮሚዩኒኬሽን ባለሙያ የሆኑት አቶ ቴዎድሮስ ለገሰ ለድረገፁ በሰጡት ቃል ፤ የፌዴሬሽኑ አመራሮች እና አባላት በአንድ ቀን ቢመለሱም እዚያው የሚቆዩ አትሌቶች ግን ይኖራሉ ሲሉ አረጋግጠዋል።

በዚህ ጉዞ ላይ የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን አመራሮች፣ የስራ አስፈጻሚ ኮሚቴ አባላት እና የተለያዩ የስራ ክፍል አባላት ተሳታፊ እንደሚሆኑ ተገልጿል።

በነገ ጉዞ ከሚሳተፉ የትግራይ ክልል ተወላጅ ከሆኑ አትሌቶች መካከል ፦

- አትሌት ለተሰንበት ግደይ፣
- አትሌት ጎተይቶም ገብረ ስላሴ
- አትሌት ጉዳፍ ጸጋይ እንደሚገኙበት ተናግሯል።

ምንጭ፦ https://ethiopiainsder.com/2023/9310/

#ቲክቫህ #ኢትዮጵያ

 #ጥምቀትጎንደር ከተማ በጥምቀት በዓል ሰሞን በ100 ሺዎች የሚቆጠሩ እንግዶችን ለመቀበል የሚያስችላትን አስፈላጊውን ሁሉ ዝግጅት ማድረጓ አሳውቃለች።የጎንደር ከተማ ባህልና ቱሪዝም መምሪያ ፤...
09/01/2023

#ጥምቀት

ጎንደር ከተማ በጥምቀት በዓል ሰሞን በ100 ሺዎች የሚቆጠሩ እንግዶችን ለመቀበል የሚያስችላትን አስፈላጊውን ሁሉ ዝግጅት ማድረጓ አሳውቃለች።

የጎንደር ከተማ ባህልና ቱሪዝም መምሪያ ፤ በጥምቀት በዓል ሰሞን እስከ 2 ቢሊየን ብር በቱሪዝሙ ምክንያት ኢኮኖሚው ገቢ ያገኛል ተብሎ እንደሚጠበቅም አሳውቋል።

በጥምቀት በዓል ወቅት ከ750 ሺ እስከ 1 ሚሊየን ጎብኚ ወደ ጎንደር እንደሚመጣ ይጠበቃል ያለው መምሪያው ለዚህም ከ400 በላይ ሆቴሎች እና ድንኳን የሚጣልባቸው ሥፍራዎች ዝግጁ መሆናቸውን ገልጿል።

እንደ ሚመጡ እንግዶች አቅም የማረፊያ፣ ምግብን ጨምሮ አስፈላጊ ነገሮችን መሸመቻ አማራጭ መሰናዳቱን መምሪያው አሳውቋል።

በተጨማሪ ከጥር 4 እስከ 9 ቀን 2015 ዓ.ም የባህል ሣምንት የሚከበር ሲሆን በዚህም የአካባቢውን ፣ የክልሉን ባህል፣ ወግና ትውፊት የሚያሳዩ ዝግጅቶች ይቀርባሉት ተብሏል።

እንዲሁም ጥር 6 ቀን 2015 ዓ.ም የአጼ ቴዎድሮስ ልደት ሀገራዊ አንድነትን በሚያፀና ሁኔታ እንደሚከበር መምሪያው መግለፁን ኤፍ ቢ ሲ ዘግቧል።

#ቲክቫህ #ኢትዮጵያ

 ቻይና ከ3 ዓመታት በኋላ ለመጀመርያ ጊዜ ድንበሯን  #ለጎብኚዎች ከፍት አድርጋለች።ቻይና በመጋቢት 2020 ዓ/ም የኮቪድ  19 ወረርሽኝን ተከትሎ ነበር የጉዞ እግድ የጣለችው።ከአሁን በኃላ ...
09/01/2023



ቻይና ከ3 ዓመታት በኋላ ለመጀመርያ ጊዜ ድንበሯን #ለጎብኚዎች ከፍት አድርጋለች።

ቻይና በመጋቢት 2020 ዓ/ም የኮቪድ 19 ወረርሽኝን ተከትሎ ነበር የጉዞ እግድ የጣለችው።

ከአሁን በኃላ ገቢ መንገደኞች ማቆያ ስፍራ መቆየት ሳያስፈልጋቸው በቀጥታ መግባት ይችላሉ። ይሁንና ገቢ መንገደኞች ውስጥ የወሰዱትን የክትባት ማስረጃ ማቅረብ እንደሚጠበቅባቸው ቢቢሲ ፅፏል።

#ቲክቫህ #ኢትዮጵያ

Address

Addis Ababa

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when ፍኖት posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share