ሚዛን ሚዲያ Mizan Media

ሚዛን ሚዲያ Mizan Media ተአማኒ ግልፅ እና እዉነተኛ መረጃ በማቅረብ ንቁ ማህበረሰብ ለመፍጠር እንተጋለን ።
Accuracy,Clarity and brevity is our Media principle.

‎ከሚዲያ ራሴን ስለማግለሌ ዕና የመጨረሻ ጉዞዬ ስለማሳወቅ !‎        ‎እኔ ጁሃር ሳዲቅ እንደሚታወቀዉ ላለፉት አምስት አመታት በሚዛን ሚዲያ እንዲሁም የሱፍያዉን የሚዲያዉን ዘርፍ ሳግዝ ...
18/07/2025

‎ከሚዲያ ራሴን ስለማግለሌ ዕና የመጨረሻ ጉዞዬ ስለማሳወቅ !

‎እኔ ጁሃር ሳዲቅ እንደሚታወቀዉ ላለፉት አምስት አመታት በሚዛን ሚዲያ እንዲሁም የሱፍያዉን የሚዲያዉን ዘርፍ ሳግዝ ቆይቻለሁ ። በመጣንባቸዉ አመታ የአህለሱናዉ አካባቢ ሲታይ የነበረዉ የሚዲያዉን ክፍተት ለመሙላት በተቻለኝ አቅሜ በፈቀደልኝ መጠን ሰርቼ እዚህ አድርሻለሁ ብዬ አስባለሁ ።

‎ነገር ግን በዚሁ በሚዛን ሚዲያ ከፍተኛ የሚዲያ ሽፋን ሰጥቼ በተቻለኝ መጠን ከህዝብ ጋር እንዲተዋወቅ ህዝብን እንዲያገለግል ሳልሰለች የሰራሁለት ታስክ ፎርስ (ግብረሀይል) ዉስጥ ያሉ ጥቂት መጅሊስ የሚገቡ ተደራረዳሪ ግለሰቦች ፣ ሙስሊሙን ማህበረሰብ የታስክ ፎርሱ (የተደራዳሪዉን) ሂደት እንደ ሚዲያ ለሚዲያችን ሲቀርብ ቆይቷል በተደጋጋሚም ህዝቡ የሚያነሳዉን ጥያቄ አቅርቤያለሁ ለጥያቄዎች ቀጥታ ይሄ ነዉ የሚል ምላሽ ካለ መገኘቱ አልፎ አትጠይቁን አትችልምም ተብያለሁ ፣ቅሬታዎች ከመዘገብ ብሎም መጅሊስንና ሀጂ ኢብራሂም ቱፋ አትንኩ ህገ_ወጥ መጅሊስ አትበሉ በሚል ጭምር ተደጋጋሚ በመጡ ጫናዎች እንዳቆም ተነግሮኛል ።

‎ከዚህ በሗላ ታስክ ፎርሱ ዉስጥ የማከብራቸዉ ለመስመሩ የቆሙ ሰዎች መኖራቸዉ በአክብሮት እየገለፅኩ ሂደቱ ወደ ጥቂት ሰዎች የዞረና በጥቂት ግለሰቦች የሚዘወር በመሆኑ ከተነሳሁለት አላማ ጋር ታስክ ፎርሱም በዉስን ሰዎች ካልዘወርነዉ የሚል ከተቋቋመበት አላማ ዉጪ እየሄደ ነዉ የሚል እምነት ያለኝ ሲሆን የሚያደርገዉ የትኛዉም እንቅስቃሴ የማይመለከተኝና የማይወክለኝ መሆኑንና በሚቀጥሉት ግዜያት ከሚዛን ሚዲያ ራሴን ያገለልኩ መሆኑ ለማሳወቅ እወዳለሁ ።

‎በምርጫዉ ሂደትም ይሁን በመጅሊሱ በሱፍያዉ ላይ ለሚፈፀሙ ቀጣይ ዙልሞች እነዚሁ ሚዲያዉ መቆም አለበት ያሉ ተደራዳሪ ነን የሚሉ ጥቂት ግለሰቦች ሀላፊነት የሚወስዱ ይሆናል ። ‎

በቀጣይ አስፈላጊ ሆኖ ከተገኘ የመጅሊስ የሱፍያዉ አመጣጥ ፣መጅሊስ የገባዉ ተደራዳሪዉ አካል ባጠቃላይ እየተሄደበት ያለዉ መንገድ በቪዲዮ ማብራራዉ ይሆናል ።

በተረፈ አልሀምዱሊላህ ‎አምስት አመቱ ቀላል አልነበረም ዉጣ ዉረዶቹ ተግዳሮቶቹ ለአላህ መንገድ (ለአህለሱናዉ መንገድ) የተከፈለ የተሰራ ስለሆነ አላህ እንዲቀበለኝ ዱዓ አርጉልኝ ።

‎ለመላዉ ዉድ የመሻኢኽ ልጆች እህቶች ወንድሞች ፣አባቶች ስላገለገልኳችሁ አእናንተን መስመሩንም በማገልገሌ ክብር ይሰማኛል ከጎኔ ለነበራችሁም አመሠግናለሁ ።

‎ማስታወሻ :- ምናልባት የግል ህይወቴን መስመር ካስያዝኩ በቀጣይ አቅም ካገኘሁ የፃፍኳቸዉ "The mother of right movement " በጣም የምወደው እና " የሰዓድ ኢብን አቢ ወቃስ የዝህድና እና የጀግንነት ታሪክ " በተሸኙ ያለቁ መፅሀፎቼ እንገናኝ ይሆናል የሚል ተስፋ አለኝ ኢንሻአላህ ።

‎አላህ ለአህለሱና ወልጀማአ (ሱፍያ) ሙስሊም ማህበረሰብ ድልን ያጎናፅፍ ዘንድ ምኞቴ ነዉ ።

ወንድማችሁ ጁሃር ሳዲቅ

18/07/2025

በተገለበጠ ኮሮጆ የመጅሊስ ምርጫ ህዝበ ሙስሊሙን መናቅ ነዉ

ምርጫ ሲባል ሰዎች በነፃነት ካርድ ወስደዉ ይመራኛል ያሉትት ያመኑበትን በድምፃቸዉ የሚመርጡበት ስርአት ነዉ ።ምርጫ
ባደጉት ሀገራት Absolute ነዉ ባይባልም 70/80% በመቶ በነፃ አሳታፊ መልኩ ይከናወናል የማጆሪቲ ድምፅ ይከበራል የማይኖሪቲዉ መብት ደግሞ ይጠበቃል ።

ባላደጉት አፍሪካ በመሳሰሉ አህጉር ሚደረጉ ምርጫዎች እንተዋቸዉ ምርጫ ሊመስል የሚችል ይደረጋል ።የመጅሊስ ምርጫ ካየነዉ ምርጫ ሊመስል የሚችል አንድ ሂደት አፈፃፀም የለዉም ።

ከሸሪዓ ዉጪ ያለዉ የአዉሮጳ ምርጫ እንዲህ ከሆነ የበለጠ ዴሞክራቲክ ፣ተአማኒ ፣ነፃ ፣ገለልተኛ ፣አሳታፊ ፣አካታች በመሆን ይበልጥ ራሱን ለማጥራት መስራት ሲገባዉ የመጅሊስ ምርጫ ምርጫዉ ሳይጀምረዉ ኮሮጆ ገልብጦ የጀመረዉ የአንባገነኖች ምርጫን እንኳ ደረጃ ያልደረሰ ምርጫ ነዉ ።

ይቀጥላል............

ሼር በማድረግ ያዳርሱ


ሙሉ ቪዲዮ ለመመልከት
https://youtu.be/h2tljeU2F60?si=GxcN7h0JmPjQ4Fq0

ሚዛን ሚዲያ Mizan Media

17/07/2025

ክፍል 3 ምርጫ ህገወጥ ተቋም ህጋዊ ለማድረግ

ምርጫ ቦርዱ በተጠና መንገድ ሆን ተብሎ በህገወጥ መንገድ ሀምሌ 11 መጅሊስ የተቆጣጠረዉ አካል በምርጫ በሚል ስም ማጭበርበር ህጋዊ ለማድረግ ነዉ ።

ምርጫዉ ህዝበ ሙስሊሙ ባሳተፈ መልኩ አካታች ፍትሃዊ ፣ተአማኒ ፣ግልፀኝነት ያልተከተለ በመሆኑ ድምፅ በመሰረቅ መጅሊስ ቢመሠረት ህጋዊነቱን አያፀናም ።

ሙሉ ቪዲዮ ይመልከቱ ሼር በማድረግ ያዳርሱ
https://youtu.be/QFj9S5ravWE?si=saVF_1y3oy3QR3Jl
ሚዛን ሚዲያ Mizan Media

መጅሊስ ከበስተጀርባ የሚዘዉረዉ የምርጫ ቦርድ !በመጅሊስ ምርጫ የተሰሩ ቪዲዮዎች በሚቀጥሉት ሁለት ወይም ሶስት ቀናት እናጠናቅቃለን ።
17/07/2025

መጅሊስ ከበስተጀርባ የሚዘዉረዉ የምርጫ ቦርድ !

በመጅሊስ ምርጫ የተሰሩ ቪዲዮዎች በሚቀጥሉት ሁለት ወይም ሶስት ቀናት እናጠናቅቃለን ።

ሰበር :- የምርጫው ሂደት ባለመስተካከሉ የአቃቂ ክፍለ ከተማ ሱፊዮች በምርጫዉ ተስፋ መቁረጣቸዉ አስታዉቀዋል በአቃቂ ቃሊቲ የሚገኘዉ የአህለሱና ወልጀማአ ማህበረሰብ በክፍለከተማዉ ባሉ በአምስ...
17/07/2025

ሰበር :- የምርጫው ሂደት ባለመስተካከሉ የአቃቂ ክፍለ ከተማ ሱፊዮች በምርጫዉ ተስፋ መቁረጣቸዉ አስታዉቀዋል

በአቃቂ ቃሊቲ የሚገኘዉ የአህለሱና ወልጀማአ ማህበረሰብ በክፍለከተማዉ ባሉ በአምስት ወረዳዎች በሚገኙ መስጂዶች በምርጫዉ ዙሪያ ከካርድ ምዝገባ ጀምሮ የምርጫዉ ሂደት ላይ በመጅሊሱ እየተዘወረ ተገለናል እንዳንሳተፍ ተደርገናል ሲሉ ቅሬታቸዉ ሲገልፁ መቆየታቸዉ ገልፀዋል ።

ይሁንጂ ለጥያቄያቸዉ ምላሽ የሚሠጥ አካል አለማግኘታቸዉም ይገልፃሉ ። በተያዘው በጀት ዓመት መጨረሻ ላይ ሀገር አቀፉ የመጅሊስ ምርጫ ይካሄዳል ሲባል ሀገር አቀፍ የሱፊያ ቅሬታ አቅራቢ ግብረ-ሃይል ለሰላም ሚኒስተር ባለፉት 3 ዓመታት ውስጥ በሀገሪቱ ሁሉም ክፍሎች ሱፍያው ማህበረሰብ ላይ የደረሰውን ዘርፈ ብዙ ጭቆና በዝርዘር ጠቅሶ ያቀረበው በመሪ ተቋም ውስጥ በሚገባ ልክ የመወከል ጥያቄ ለአንዴ እና ለመጨረሻ ጊዜ እልባት አግኝቶ ሁሉም ወገን ይሆነኛል የሚለውን መሪ በመምረጥ የአስትምህሮት ልዩነቱ ተጠብቆ፤ ለየትኛውም ወገንም ሆነ ለሀገር ከማይበጀው የገመድ ጉተታ በመላቀቅ ህዝበ ሙስሊሙ ጊዜውን ፣ ገንዘቡን፣ ጉልበቱን እና ዕውቀቱን ከብክነት ታድጎ ሙሉ ቡሙሉ ትኩረቱን ልማት ላይ በማድረግ ለቀጣይ ትውልድ ምቹ እና አኩሪ ሀገርን ለማስረከብ የሚያስችል ሰፊ ምህዳር ለመፍጠር ያግዛል በሚል በታላቅ ደስታ ነበር የምርጫውን ሂደት የተቀላቀልነው ሲሉ ገልፀዋል ።

ሆኖም ግን የምርጫውን ሁነት በበላይነት የሚመራው የምርጫ አስፈፃሚ ኮሚቴ ከሁሉም ወገን ግልፅ እና ፍትሐዊ በሆነ መንገድ ይሰባጠራል ብለን ስንጠብቅም ፍፁም አግላይ እና በዳይ አደላደል በክፍለ ከተማችን ምርጫ ከሚከናወንባቸው 29 መሳጂዶች ውስጥ ከ10 በላይ መስጂዶች ጋር ሲደርስ የማግለል መጠኑ ጣራ ነክቶ 100% የመስጂድ ምርጫ አስፈፃሚ ቦርድ ፣ ግብረ-ሃይል እና ታዛቢ ከአንድ ቡድን ብቻ ተደርጓል ብለዋል ።

በወረዳ 1 ዑመር መስጂድ ፣ በወረዳ 5(ኢብራሒም ፣ ኹዘይፋ እና ቁባእ) መስጂዶች ፣ ወረዳ 7 (ሀምዛ ፣ ጃሚዑልኸይራት እና አብሬት) መስጂዶች ፣ ወረዳ 8 (ቢላል ሰርጢ እና ሃሩን ረሺድ መስጂድ) እንዲሁም ወረዳ 6 የሚገኙ 3 መስጂዶች ላይ ከላይ ያስቀመጥነው አስነዋሪ ተግባር ተፈፅሟል ሲሉ ገልፀዋል ።

የምርጫ አሳላጮች በዚህ መልክ የተዋቀሩበት የይስሙላ ምርጫ ባለፉት 3 ዓመታት ውስጥ ሱፊያው ላይ እጅግ ከፍተኛ በደል ሲፈፅም ለከረመው መጅሊስ ዕውቅና ለማሰጠት እና አጠናክሮ ለማስቀጠል ካልሆነ በቀር የሚያመጣው አንዳች አዎንታዊ ለውጥ ባለመኖሩ አብዛኛው ማህበረሰባችን ተሰፋ በመቁረጥ ከምዝገባ እየራቀ ይገኛል ብለዋል ።



ሚዛን ሚዲያ Mizan Media

ሰበር :- በነገዉ እለት የሚከናወነዉ ህገወጥ የመጅሊስ ጉባኤ እልደማይታደሙ የአህለሱና ወልጀማአ አባቶች ገለፁይህ የዛሬ ሶስት አመት ያሠማነዉ የአባቶቻችን ወኔ አቋማዊ የዉሳኔ ከፍተኛ የሞራል...
17/07/2025

ሰበር :- በነገዉ እለት የሚከናወነዉ ህገወጥ የመጅሊስ ጉባኤ እልደማይታደሙ የአህለሱና ወልጀማአ አባቶች ገለፁ

ይህ የዛሬ ሶስት አመት ያሠማነዉ የአባቶቻችን ወኔ አቋማዊ የዉሳኔ ከፍተኛ የሞራል ልእልና የታከለበት ዉሳኔ ዜና ነበር ።

በክቡር ዶ/ር ተቀዳሚ ሀጂ ሙፍቲ ሀጂ ዑመር እድረስ መጅሊሱ ህገ_ወጥነት አንቀበልም ብለዉ ጀግኖች አባቶቻችን ታሪካዊ ዉሳኔ ዛሬ ሀምሌ 10 ሶስት አመቱ ደፎኗል ።

ህገ ወጡ መጅሊስ ዛሬም ቀጥሏል በምርጫ ሰበብም ቀጣይ ግዜያት እቀጥላለሁም እያለ ይገኛል ።




16/07/2025

በመጅሊሱ ምርጫ ቦርድ ከምርጫ ዉጪ የሆነዉ የወሎ አህለሱና ወል ጀማዓ ላይ የተሰራዉ ግፍ የወሎ ምርጫ ቦርድ ተደርገዉ ተሰይመዉ በመጅሊሱና በምርጫ ቦርድ የተሰራባቸዉ ሴራ ይናገራሉ ።

(ይደመጥ.........)

ሚዛን ሚዲያ Mizan Media

16/07/2025

ክፍል 2 :- የመጅሊሱ የ2017 ምርጫ ድራማ

መራጭ መጅሊስ አስመራጭ መጅሊስ ሁሉም ነገር መጅሊስ
የሆነበት ምርጫ ተከትሎ ቪዲዮች ተከታታይ እናጋራለን ።

https://youtu.be/QFj9S5ravWE?si=wjmZCu5mtQkEaG_7

ሚዛን ሚዲያ Mizan Media

ሰበር !  የይርጋጨፌ አህለሱና ወልጀማዓ ማህበረሰብ በምርጫዉ ዙሪያ አካታች ባለመሆኑ ተቃዉሞ መግለፁ ተሰማ ።የይርጋጨፌ አህለሱና ወልጀማዓ ማህበረሰብ በምርጫዉ ዙሪያ አካታች ባለመሆኑ ተቃዉሞ...
16/07/2025

ሰበር ! የይርጋጨፌ አህለሱና ወልጀማዓ ማህበረሰብ በምርጫዉ ዙሪያ አካታች ባለመሆኑ ተቃዉሞ መግለፁ ተሰማ ።

የይርጋጨፌ አህለሱና ወልጀማዓ ማህበረሰብ በምርጫዉ ዙሪያ አካታች ባለመሆኑ ተቃዉሞ መግለፁ ከይርጋጨፌ የሚዛን ምንጮች ገልጸዋል ።

በይርጋ ጨፌ ለመጅሊሱ የመስጂዶችን ዶክመንት ካላስረከባቹ ምርጫ አይደረግም ማለቱን ተከትሎ ድምፃቺን ታፍኖ እስካሁን 5 መስጆዶች አሉን በአምስቱም ምዝገባ አልተጀመረም በማለት ገልፀዋል ።

በዚህም ድምችፃን ይሰማ ፍትህ ለጨፌ ህዝበ ሙስሊም ውርደት የህዝብን ጥያቄ ችላ ያለ መጅሊስ እንዲሁም ምርጫ ቦርድ አይወክለንም ሲሉ ተቃዉሟቸዉ ገልጸዋል ።

ፍትህ ለታፈነው ለጨፌ አህለሱና ሱፍያ ሙስሊም በማለት እየጠየቁ ይገኛል ።

ሚዛን ሚዲያ Mizan Media

መጅሊስን ያመነ ጉም የዘገነ የሆነዉ (የሱፍያዉ) አህለሱና ወልጀማአዉ ወሳኝ ጥያቄዎች !የያዛችሁትን ይዛችሁ😁የትኛዉን ይዘን ? የሼኽ ሀጂ😁 ጠረባ1 አካታችነት * የዑለማዕ ምክር ቤት አካታችነ...
16/07/2025

መጅሊስን ያመነ ጉም የዘገነ የሆነዉ (የሱፍያዉ) አህለሱና ወልጀማአዉ ወሳኝ ጥያቄዎች !

የያዛችሁትን ይዛችሁ😁የትኛዉን ይዘን ? የሼኽ ሀጂ😁 ጠረባ

1 አካታችነት
* የዑለማዕ ምክር ቤት አካታችነት አለም የለም ማለት
አይቻልም ዚግዛጉ ቀጥሏል ።

2 የተወሰዱ መስጂዶች እና ኢማሞች ይመለሱ

*አዲሱ መጅሊስ ሚመሠረት ጠብቁ ስድስት ወር ያኔ ወደቤታችሁ ግቡ እንላችሗለን ጠብቁን ።

3 መጅሊስ የሚመራባቸዉ ሰነዶች በአካታችነት ታይተዉ ይፅደቁ የምርጫ ሂደቱ ቦርዱ አካታች ይሁን

* የዑለማእ መግባቢያ ሰነድ = ምላሽ => በዜሮ
*የመጅሊስ ህገ ደንብ = ምላሽ => በዜሮ
*የመጅሊስ ምርጫ ደንብ = ምላሽ => በዜሮ

አዲስ ምክር ቤት ሊዋቀር ነዉ አለም ያወቀዉ ፀሀይ የሞቀዉ ጉዳይ ነዉ አዲስ መጅሊስ ሊባል ነዉ እዉነታዉ ይኸዉ ነዉ ።

ዝርዝር በተሰሩት ቪዲዮዎቻችን ይለቀቃል ።

ሚዛን ሚዲያ Mizan Media

የትኛዉ ምርጫ መጅሊሱ ራሱ ተወዳድሮ ለራሱ ያመቻቸዉ ምርጫ !!ምርጫዉ በሀገራቀፍ ደረጃ !አዲስ አበባ=> 4 ለ 1 =ሱፍያዉ  0ኦሮሚያ 5 ለ 0 =ሱፍያዉ 0አማራ ክልል 5 ለ 0 = ሱፍያዉ 0...
16/07/2025

የትኛዉ ምርጫ መጅሊሱ ራሱ ተወዳድሮ ለራሱ ያመቻቸዉ ምርጫ !!

ምርጫዉ በሀገራቀፍ ደረጃ !

አዲስ አበባ=> 4 ለ 1 =ሱፍያዉ 0
ኦሮሚያ 5 ለ 0 =ሱፍያዉ 0
አማራ ክልል 5 ለ 0 = ሱፍያዉ 0
አፋር ክልል. 5 ለ 0 = ሱፍያዉ 0
ሶማሌ ክልል 5 ለ 0 = ሱፍያዉ 0
ማእከላዊ ኢትዮጵያ = ዜሮ
ደቡብኢትዮያ = ዜሮ
ጋምቤላ = ዜሮ
ቤንሻንጉል = ዜሮ
ሀረር = ዜሮ
ድሬደዋ = ሱፍያዉ ዜሮ

ይህ ምርጫ ሳይሆን ሌብነት ስርቆት ቅርጫ ነዉ !



መሪ የሌለዉ መሪዉ ሸይጧን ነዉ         የመሪ አስፈላጊነት !ባለፉት በተከታታይ ክፍል ዳሠሣዎቻችን የሀበሻ ጥንታዊ የሀይማኖት መሠረት የእስልምና መሠረት በተለያየ መልኩ ተግዳሮት ተሻግሮ ...
16/07/2025

መሪ የሌለዉ መሪዉ ሸይጧን ነዉ
የመሪ አስፈላጊነት !

ባለፉት በተከታታይ ክፍል ዳሠሣዎቻችን የሀበሻ ጥንታዊ የሀይማኖት መሠረት የእስልምና መሠረት በተለያየ መልኩ ተግዳሮት ተሻግሮ መጥቷል ። ከሁሉም ተግዳሮቶች ከፍተኛዉ ተግዳሮት ከሰላሳ አመት ወዲህ የተረጨዉ ማንነት አልባ ideology ለነባሩ ትልቅ Catastrophe ሆኖ ዘልቋል ።

የአለማቱ ነብይ የሆኑት ነብዩም ሰዐወ መሪ (አሚር)የሌለዉ ስብስብ መሪዉ ሸይጧን ነዉ በማለት የመሪ የአሚር የአመራር አስፈላጊነት አስቀምጠዋል ። ላለፉት ሰላሳ አመታት የሀገሬዉ ነባር ጠንካራዉ የመሻኢሆቹ የአህሉሱና ወልጀማአ እስልምና
ከኦሮሚያ እስከ አማራ አልፎም በደቡቡ ከፍተኛ ተግዳሮት የገጠመው ያንን combat የሚያደርግ የአስተዳደርም ሆነ ወጥ የሆነ በአሚር የሚመራ ስብበስ ባለመኖሩ መሆኑ ልንዘነጋ አይገባም ።

እስከዛሬ የነበረዉ በየአቅጣጫዉ ጥርጊያ መንገዱን ለማመቻቸት የነበረ ሲሆን አሁን ህዝባችን
ያስፈልገዋል wisly ያሉት ተጨባጮች የሚገነዘብ የሚያሳስበዉ ስብስብ /ማህበረሰብ እስካለ ይህንን አለማሠብ ትልቅ mess ነዉ ።

የአመራሩ ሚና ከተባለ የማህበረሰቡ ችግሮች ነቅሶ ማዉጣት ፣በየዘርፉ ማደራጀት ፣ሹራ መምራት ፣ ማስተማር ፣ማንቃት
ማስተሳሰር ፣ማወያየት Decision make ማድረግ (ዉሳኔ ማሳለፍ) ክትትል ማድረግ መተግበር ፣መፈፀም ነዉ ።

Modern organizational beurocracy የተከተለ higher archy ያለዉ (Structure) ያለዉ ግዜዉን ከግንዛቤ በማስገባት ማናበብ ያስፈልጋል ።

በሀገራችን ያለዉ የሙስሊም የተማረዉ ኤሊት ክፍል ይህንን ሃላፊነቱ አልተወጣም ባይ ነን ።ከአንድ ማህበረሰብ የተገኘ ምሁር ኤሊት የተማረዉ የቀራዉ መጀመሪያ ራሱ ሊያዉቅበት ከዛ ማህበረሰቡ ማስተማር ያልቻለበት ከሆነ እንደማይታይ መብራት ይቆጠራል ።

መሻኢኾቻችን ዝም ብለዉ መንፈሳዊዉን አለም ሲመሩ መርተዉም አሳይተዉናል በመሪነታቸዉ Strong Commitment + Effective Decision making አኩርተዉናል ያንን ከፍ የሚያደርግ Strategy ነድፎ የሚመጣ አመራር ሱፍያዉ ያስፈልገዋል ።

የዘመነ መሳፍንታዊ አካሄድ የሚያበቃበት ነዉ ይህም ስንል የተበጣጠሰዉ ስርዓት ከአህለሱናዉ የመምራት ብቃት ያላቸዉ ከታገዙ ሊሠሩ ሚችሉ ሰዎችን ከሗላም ይሁን ከፊት በማምጣት ወደ አንደ ማዕከል አምጥቶ የሃሳብ ልዕልናዎችን አዋህዶ መስመር ማስያዝ አስፈላጊ ነዉ ።

መሪ የሌለዉ መሪዉ ሸይጧን ነዉ እንዳሉት ነብዩ (ሰዐወ) የመሪ አስፈላጊነት ወሳኝ ወቅት ላይ እንገኛለን ።

The time is Now !!

Address

Lideta Subcity
Addis Ababa
VOICEOFTHEOPPRESSED

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when ሚዛን ሚዲያ Mizan Media posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to ሚዛን ሚዲያ Mizan Media:

Share

Category