Agelgl Media

Agelgl Media Agelgle Media is a private media platform, based in Ethiopia.

Established on May 3, 2021 /May 25, 2013 E.c

We brings to you latest news from Ethiopia and around the world as it happens.

በሀገሪቱ አብዛኛው ቦታ የኤሌክትሪክ ኃይል ተቋረጠ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የተቋረጠውን ኃይል ወደነበረበት ለመመለስ እየተሰራ ነው ብሏል ዛሬ ማምሻውን በሲስተም አለመረጋጋት በተፈጠረ ችግ...
07/12/2024

በሀገሪቱ አብዛኛው ቦታ የኤሌክትሪክ ኃይል ተቋረጠ

የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የተቋረጠውን ኃይል ወደነበረበት ለመመለስ እየተሰራ ነው ብሏል

ዛሬ ማምሻውን በሲስተም አለመረጋጋት በተፈጠረ ችግር የተነሳ በመላው ሀገሪቱ የኃይል መቋረጥ አጋጥሟል ሲል የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል አስታውቋል።

ችግሩን በመፍታት የተቋረጠውን ኃይል ወደነበረበት ለመመለስ በኃይል ማመንጫዎች እና በማከፋፈያ ጣቢያዎች ከፍተኛ ርብርብ እየተደረገ ነው ብሏል።

የተፈጠረው ችግር እስኪፈታ ድረስ ደንበኞች በትዕግስት እንዲጠባበቁ ጠይቆ፤ ያሉትን መረጃዎች በፍጥነት የሚያሳውቅ መሆኑንም ገልጿል።

በሴቶች ብልት ውስጥ ዘጠኝ ኪሎ ግራም ወርቅ ተገኘ  በስድስት ሴቶች ብልት ውስጥ ተሰፍቶ ሊያልፍ የነበረ  ከዘጠኝ ኪሎ ግራም በላይ ወርቅ በኡዝቤክ ተወላጆች ወደ ቱርክ በድብቅ ሊገባ ሲል መያ...
13/11/2024

በሴቶች ብልት ውስጥ ዘጠኝ ኪሎ ግራም ወርቅ ተገኘ



በስድስት ሴቶች ብልት ውስጥ ተሰፍቶ ሊያልፍ የነበረ ከዘጠኝ ኪሎ ግራም በላይ ወርቅ በኡዝቤክ ተወላጆች ወደ ቱርክ በድብቅ ሊገባ ሲል መያዙን የቱርክ መንግሥት አሳወቀ።

የቱርክ የጸጥታ አካላት ስለ ህገወጥ የወርቅ ዝውውሩ አስቀድሞ የሚያውቁ ሲሆን ከሳምንት በፊት ከአረብ ኤምሬትስ የመጡ 6 ሴቶችን እና ሊቀበላቸው የመጣውን ሹፌር መያዝቸዉን ገልፀዋል::

በፍተሻውም እያንዳንዳቸው 110 ግራም የያዙ 82 የወርቅ ባርዶች፣ 18 የፕሌይስ ስቴሽን ኮንሶሎች እና 3 ስማርት ስልኮች ተይዘዋል። ተጨማሪ ምርመራ እንደሚያሳየው ተጨማሪ 84 የወርቅ ባርዶች በሴቶች ብልት ውስጥ ተሰፍተዉ ተገኝተዋል::

የቱርክ ፍርድ ቤት ቀዶ ጥገናን የፈቀደ ሲሆን በድምሩ ከ9 ኪሎ ግራም ከሴቶቹ ብልት ውስጥ ተገኝቷል::

የሙከራ ስርጭታችንን ያድምጡ
13/11/2024

የሙከራ ስርጭታችንን ያድምጡ

Listen to Agelgl Radio internet radio online. Access the free radio live stream and discover more online radio and radio fm stations at a glance.

የኢትዮጵያ አየር መንገድ ወደ አስመራ የሚያደርገውን በረራ አቋረጠየኢትዮጵያ አየር መንገድ ወደ ኤርትራ ዋና ከተማ አስመራ የሚያደርገውን በረራ ከነገ ነሐሴ 28/2016 ጀምሮ እንደማይኖር አስ...
02/09/2024

የኢትዮጵያ አየር መንገድ ወደ አስመራ የሚያደርገውን በረራ አቋረጠ

የኢትዮጵያ አየር መንገድ ወደ ኤርትራ ዋና ከተማ አስመራ የሚያደርገውን በረራ ከነገ ነሐሴ 28/2016 ጀምሮ እንደማይኖር አስታውቋል፡፡

አየር መንገዱ በረራውን ያቋረጠው በኤርትራ ውስጥ አገልግሎቱን ለመስጠት ባጋጠመው ከአቅም በላይ በሆነ የአሰራር ችግር እንደሆነ በማኅበራዊ ትስስር ገጽ ባወጣው መረጃ አመልክቷል፡፡

Heaven Awot was sexually assaulted, mutilated and killed by her mother’s landlord Getnet Baye last August in the north-w...
19/08/2024

Heaven Awot was sexually assaulted, mutilated and killed by her mother’s landlord Getnet Baye last August in the north-western city of Bahir Dar in Amhara region.

Read full story👇

I have lost my Heaven, justis for heaven, r**e, killed. ethiopia, Amhara, Tigray

“የመንግስት መዋቅር በሌቦች ተጠልፏል”- ዶ/ር አብርሃም በርታ፤ የኢዜማ የፓርላማ አባልየህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ዛሬ ሐሙስ ሰኔ 27፤ 2016 እያካሄደ ባለው መደበኛ ስብሰባ፤ የፓርላማ አ...
04/07/2024

“የመንግስት መዋቅር በሌቦች ተጠልፏል”- ዶ/ር አብርሃም በርታ፤ የኢዜማ የፓርላማ አባል

የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ዛሬ ሐሙስ ሰኔ 27፤ 2016 እያካሄደ ባለው መደበኛ ስብሰባ፤ የፓርላማ አባላት ለጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ ጥያቄዎችን አቅርበዋል። የኢትዮጵያ ዜጎች ለማኅበራዊ ፍትህ (ኢዜማ) የፓርላማ ተወካይ የሆኑት ዶ/ር አብርሃም በርታ በመንግስት መስሪያ ቤቶች ይስተዋላል ስላሉት “የሀብት ብክነት” እና “ሙስና” ጠይቀዋል።

ኢትዮጵያ በአሁኑ ወቅት የምትገኝበት የሙስና ችግር “እጅግ አሳሳቢ ደረጃ ደርሷል” ያሉት ዶ/ር አብርሃም፤ ሙስና በሀገሪቱ “ከዓመት ዓመት እየጨመረ መምጣቱን” ዓለም አቀፍ ተቋማት በሚያወጣቸው ሪፖርቶች ጭምር ይፋ መደረጉን አመልክተዋል። የፌደራል ዋና ኦዲተር መስሪያ ቤት በቅርቡ ለፓርላማ ባቀረበው ዓመታዊ ሪፖርትም፤ “ከፍተኛ የሆነ የሃገር ሀብት ብክነት እንዳለ” በዝርዝር በማስረጃ አስደግፎ ማቅረቡንም ጠቅሰዋል።

“በኦዲተር ሪፓርት መሰረት በየመስሪያ ቤቶቹ ከፍተኛ የሆነ የጥሬ ገንዘብ ጉድለት ይታያል። ገንዘብ ያለማስረጃ ወጪ በማድረግ ይጠቀማሉ። ምንም አይነት ማስረጃ ሳያቀርብ በወጪ ይመዘግባሉ። ከፋይናንስ መመሪያና ደንብ ውጪ የገንዘብ ክፍያ ይፈጸማል” ሲሉ የፓርላማ አባሉ ተናግረዋል። መንግስት ሙስናን ለመዋጋት “ይህ ነው የሚባል መፍትሄ እየሰጠ አይደለም” ሲሉም ተችተዋል።

“የህዝብና የመንግስት ሃብት በዘረፉ ሙሰኛ ባለስልጣናት ላይ መቀጣጫ የሚሆን እርምጃን ከመውሰድ ይልቅ ተጨማሪ ሹመትና የቦታ ዝውውር በመስጠት መንግስት ሙሰኞችን አብሮ አቅፎ ይኖራል ማለት ይቻላል። ከዚም የተነሳ የመንግስት መዋቅር በሌቦች ተጠልፏል” ሲሉ ዶ/ር አብርሃም ወንጅለዋል።

Listen

https://onlineradiobox.com/et/agelgl/playlist/

https://zeno.fm/player/agelgl-radio

https://liveonlineradio.net/agelgl-radio

https://radio.menu/stations/agelgl-blogspot-com-agelgl-radio/

https://liveonlineradio.net/agelgl-radio

https://radiofy.online/en/et/agelgl

https://liveradiostations.net/station/agelgl-radio/

24 ሰዓት ያለ ማቋረጥ ጥርት ባለ ድምፅ ለጆሮ የሚቀርበው የራዲዮ ስርጭታችንን በሚከተሉት አማራጮች ያድምጡ!🥰https://onlineradiobox.com/et/agelgl/playlist/https...
21/04/2024

24 ሰዓት ያለ ማቋረጥ ጥርት ባለ ድምፅ ለጆሮ የሚቀርበው የራዲዮ ስርጭታችንን በሚከተሉት አማራጮች ያድምጡ!🥰

https://onlineradiobox.com/et/agelgl/playlist/

https://zeno.fm/player/agelgl-radio

https://liveonlineradio.net/agelgl-radio

https://radio.menu/stations/agelgl-blogspot-com-agelgl-radio/

https://liveonlineradio.net/agelgl-radio

https://radiofy.online/en/et/agelgl

https://liveradiostations.net/station/agelgl-radio/

Listen to Agelgl Radio online

" ' በኃይል ይዣለሁ ፣ ይዣለሁ ማለቱ ፍጹም ሰላም አያመጣም " - ሌ/ጄነራል ታደሰ ወረደየትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር ምክትል ፕሬዜዳንት የሆኑት ሌተናል ጄነራል ታደሰ ወረደ ፥ " በወረራ "...
18/04/2024

" ' በኃይል ይዣለሁ ፣ ይዣለሁ ማለቱ ፍጹም ሰላም አያመጣም " - ሌ/ጄነራል ታደሰ ወረደ

የትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር ምክትል ፕሬዜዳንት የሆኑት ሌተናል ጄነራል ታደሰ ወረደ ፥ " በወረራ " ተይዘዋል ያሏቸውን የትግራይ ክልል ግዛቶችን በሰላም ስምምነቱ መሰረት ነጻ እንዲወጡ እና የአካባቢዎቹ ሰላምና ደህንነት ተረጋግጦ ተፈናቃዮች ወደ ቀድሞ ቄያቸው እንዲመለሱ የማድረግ ኃላፊነት የኢትዮጵያ መከላከያ ሰራዊት እና የፌዴራል ፖሊስ ወስደው እንዲሰሩ ከፌዴራል መንግሥት ጋር መግባባት ላይ መድረሱን ተናግረዋል።

ከዚህ ውጭ የክልሉ ጸጥታ ኃይል ምንም አይነት የኃይል እርምጃ ለመውሰድ እንዳልተንቀሳቀሱ ከሰላም ስምምነቱ ጋር የሚጣረስ አንድም ነገር ላለመፈጸም በከፍተኛ ጥንቃቄ ላይ እንደሚገኙ ተናግረዋል።

ጄነራሉ የፕሪቶሪያ ሰላም ስምምነቱን ለመገምገም በአፍሪካ ህብረት በተመራው የስትራቴጂክ ግምገማ ወቅት እስካሁን ድረስ ስላልተሰሩ ጉዳዮች ተነስቶ እንደነበር እና እንዲሰራባቸው አቅጣጫ መቀመጡን አስታውሰዋል።

ከስትራቴጂክ ግምገማው በኃላም ለውጦች መታየታቸውን አመልክተዋል።

መሰረታዊ ከሚባሉት የስምምነቱ ክፍሎች እና ካልተፈጸሙት አንዱ ተፈናቃዮችን ወደ ቄያቸው መመለስ ነው ያሉት ጄነራሉ " ተፈናቃዮች እንዲመለሱ የትግራይ ግዛት መከበር አለበት ብለዋል።

" በዚህ ላይ ' እንደ ራያና ጸለምቲ ቀላል ነው ፤ ምዕራብ ትግራይ ነው ከባዱ ፤ ሌላ ጊዜ ደግሞ ሁሉም ቀላል ነው ሁሉም ከባድ ነው ' እየተባለ ምክንያት ይቀርባል። አንዳንዴ ደግሞ ' አከራካሪ ቦታዎች ' እያሉ ይገልጹታል ሆኖም በህገ መንግሥቱ መሰረት ትግራይ ትግራይ ነው አከራካሪ የሚባል ነገር የለም ጥያቄ ካለ እንኳን በህግ አግባብ ነው መተግበር ያለበት " ሲሉ ተናግረዋል።

" ' በኃይል ይዣለሁ ፣ ይዣለሁ ማለቱ ፍጹም ሰላም አያመጣም " ሲሉ አክለዋል።

ጄነራሉ ጊዜያዊ አስተዳደሩ ችግሮች ዘላቂ ሰላም በሚያመጣ መልኩ እንዲፈቱ እንደሚፈልግ ገልጸው " ለዚህም የመከላከያ ሰራዊት እና ፌዴራል ፖሊስ ኃላፊነት ወስደው እንዲሰሩ እየተደረገ ያለው " ብለዋል።

" በወረራ ተይዟል " ባሉት የትግራይ ክፍል ሁሉም ነገር ያለ አግባብ መቀየሩን አስታውሰው " ሁሉም ፈርሶ ወደነበረበት የትግራይ ቅርጽ እንዲመለስ ፌዴራል መንግሥት በትኩረት እየሰራ ነው " ሲሉ ተናግረዋል።

የትግራይ የጸጥታ ኃይል ስምምነቱን የሚያፈርሱ ተግባራት ላለመፈጸም ከፍተኛ ጥንቃቄ እያደረገ ነው ብለዋል።

" በማህበራዊ ሚዲያ እና በሌሎችም ፦
- በራያ አላማጣ፣
- በኦፍላና ፣
- በኮረም ላይ ትኩረት አድርገው የሚናፈሱት ወሬዎች ከእውነት የራቁ ናቸው። እነሱ እንደሚሉት በኃይል መያዝ የምንፈልገው አካባቢ የለም። በስምምነቱ መሰረት በፌዴራል መንግሥት ጥረት ነጻ እንዲሆንልን ነው የምንፈልገው " ሲሉ ገልጸዋል።

" ዘላቂ ሰላም የሚያረጋግጥና ዳግም ደም አፋሳሽ ጦርነትን የማይቀሰቅስ ተግባር እንዲፈጸም ነው የምንፈልገው በእርግጥ ችግሩን በሰላም ለመፍታት በነበረው ሂደት አለመግባባትና ፍጥጫ ነበር ይህ ለራሳቸው ሆነ ለሀገራችን ስለማይጠቅም ከድርጊታቸው እንዲቆጠቡና የሰላም ተባባሪ እንዲሆኑ እንጥራለን " ብለዋል።

ዛሬ የአማራ ክልል መንግሥት በሰጠው ይፋዊ መግለጫ፤ " ከትናንት ታሪካዊ ስህተቱ መማር የተሳነው ሕዝባዊ ወያኔ ሀርነት ትግራይ (ህወሓት) የፕሪቶሪያውን ስምምነት ሙሉ በሙሉ በመጣስ ለአራተኛ ዙር ሕዝባችን ላይ ወረራ ፈፅሟል " ሲል ከሷል።

እስካሁን ድረስ በጉዳዩ ላይ የፌዴራል መንግሥት የሰጠው አስተያየት የለም።

የግል መገናኛ ብዙሃን የፍትህ ሚኒስትሩ የፓርላማ ሪፖርት እንዳይዘግቡ ተከለከሉየፍትህ ሚኒስቴር ሐሙስ እለት ለፓርላማ ያቀረበውን የግማሽ ዓመት የስራ አፈጻጸም ሪፖርት፤ የግል መገናኛ ብዙሃን ...
01/02/2024

የግል መገናኛ ብዙሃን የፍትህ ሚኒስትሩ የፓርላማ ሪፖርት እንዳይዘግቡ ተከለከሉ

የፍትህ ሚኒስቴር ሐሙስ እለት ለፓርላማ ያቀረበውን የግማሽ ዓመት የስራ አፈጻጸም ሪፖርት፤ የግል መገናኛ ብዙሃን እንዳይዘግቡ ተደረገ።

የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የዛሬውን መደበኛ ስብሰባ እንዲዘግቡ ፍቃድ የሰጠው ለአምስት መገናኛ ብዙሃን ብቻ ነው።

የኢፌዲሪ ሕገ መንግስት፤ የፓርላማ አባላት አሊያም በፌደራል የሕግ አስፈጻሚ የሆነ አካል ስብሰባው በዝግ እንዲደረግ ጥያቄ ካላቀረቡ የምክር ቤቱ ስብሰባዎች በግልጽ እንደሚካሄዱ ይደነግጋል።

በዝግ ስብሰባ እንዲደረግ ጥያቄ በሚቀርብበት ወቅትም ቢሆን፤ ከፓርላማ አባላት ውስጥ “ከግማሽ በላይ” ድጋፍ ማግኘት እንዳለበት በሕገ መንግስቱ ተደንግጓል።

የተወካዮች ምክር ቤት መደበኛም ሆነ ልዩ ስብሰባዎቹን በዚህ አግባብ ከማከናወን አልፎ፤ በማህበራዊ የትስስር ገጾቹ በቀጥታ ስርጭት ሲያቀርብ ቆይቷል።

ከምክር ቤቱ ፍቃድ የተሰጣቸው መገናኛ ብዙሃን እነዚህን ስብሰባዎች ያለ ምንም ገደብ ሽፋን የሚሰጡ ቢሆንም፤ በዛሬው የፓርላማ ስብሰባ የግል መገናኛ ብዙሃን ጋዜጠኞች ፍቃድ ሳያገኙ ቀርተዋል።...
አገልግል ሚዲያን ይወዳጁ

አገልግል ሬድዮን በሚከተሉት አማራጮች ያድምጡ
https://onlineradiobox.com/et/agelgl/playlist/
https://zeno.fm/player/agelgl-radio
https://liveonlineradio.net/agelgl-radio

ደመቀ መኮንን ከመንግስት እና ከገዢው ፓርቲ ከነበራቸው ኃላፊነት ተሰናበቱ11 ዓመታትን ምክትል ጠቅላይ ሆነው ያገለገሉት ደመቀ መኮንን፤ ከመንግስት እና በገዢው ፓርቲ ከነበራቸው ኃላፊነት መሰ...
26/01/2024

ደመቀ መኮንን ከመንግስት እና ከገዢው ፓርቲ ከነበራቸው ኃላፊነት ተሰናበቱ

11 ዓመታትን ምክትል ጠቅላይ ሆነው ያገለገሉት ደመቀ መኮንን፤ ከመንግስት እና በገዢው ፓርቲ ከነበራቸው ኃላፊነት መሰናበታቸውን ኢትዮጵያ ኢንሳይደር ምንጮቹን ጠቅሶ ዘግቧል።

አቶ ደመቀ በብልጽግና ፓርቲ ምክትል ፕሬዝዳንትነት በነበራቸው የኃላፊነት ቦታ ላይ፤ የብሔራዊ መረጃ እና ደህንነት አገልግሎት ዋና ዳይሬክተር አቶ ተመስገን ጥሩነህ መተካታቸውን ምንጮቹ አስታውቀዋል።

ይመሩት የነበረው የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴርን በተመለከተ በዘገባው አልተጠቀሰም።

አገልግል ሬድዮን በሚከተሉት አማራጮች ያድምጡ
https://onlineradiobox.com/et/agelgl/playlist/
https://zeno.fm/player/agelgl-radio
https://liveonlineradio.net/agelgl-radio

Address

Addis Ababa
1000

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Agelgl Media posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share