Agelgl Media

Agelgl Media Agelgle Media is a private media platform, based in Ethiopia.

Established on May 3, 2021 /May 25, 2013 E.c

We brings to you latest news from Ethiopia and around the world as it happens.

የኢራኑ መሪ አያቶላሕ አሊ ኻሚኒ በአሜሪካ እና እስራኤል ጥምር ጥቃት ተገደሉከአያቶላሕ በተጨማሪ የእስላማዊ ኢራን አቢዮታዊ ዘብ አዛዥ ሜጀር ጄነራል መሐመድ ፓክፑር እና ከፍተኛ የደህንነት አ...
01/03/2026

የኢራኑ መሪ አያቶላሕ አሊ ኻሚኒ በአሜሪካ እና እስራኤል ጥምር ጥቃት ተገደሉ

ከአያቶላሕ በተጨማሪ የእስላማዊ ኢራን አቢዮታዊ ዘብ አዛዥ ሜጀር ጄነራል መሐመድ ፓክፑር እና ከፍተኛ የደህንነት አማካሪው ዓሊ ሻምኻኒም እንደተገደሉ የኢራን የመንግሥት ሚዲያ ይፋ አድርጓል።

ሮይተርስ በዘገባው የእስራኤል ከፍተኛ ባለሥልጣን የመሪው መገደል እንዳረጋገጠለት ዘግቧል።

ከመሪዎቹ በተጨማሪ 201 ሰዎች መገደላቸውን እና 747 ሰዎች መጎዳታቸውን ቀይ ጨረቃ ይፋ አድርጓል። ከተገደሉት ውስጥ በትንሹ 100 ያህሉ ተማሪዎች ናቸው።

ይህን ተከትሎ ኢራን የ40 ቀናት ብሔራዊ ሐዘን እና የሰባት ቀናት በዓል አውጃለች።

የተባበሩት መንግሥታት ድንገተኛ ጉባኤ አድርጓል።

የመሪውን መገደል ይፋ ያደረጉት እና ግድያው 'ኢራናውያን ሃገራቸውን ወደ ቀድሞ ለመመለስ ታላቅ እድል ነው' ያሉት የአሜሪካው ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ በኮንግረስ ያልፀደቀ ጦርነት መጀመራቸውን ተከትሎ ህገወጥ ድርጊት የሚል ትችት ቀርቦባቸዋል።

እስራኤል እና አሜሪካ በጥምረት በኢራን ላይ የፈፀሙትን ድንገተኛ ወታደራዊ እርምጃን ተከትሎ፡ ኢራን በእስራኤል ላይ እና በመካከለኛው ምስራቅ የአሜሪካ የጦር ካምፕ ባላቸው አገሮች ላይ አፃፋዊ እርምጃዎችን ወስዳለች።

ኢራን እና ኳታር የአየር በረራዎችን ሙሉ በሙሉ አቁመዋል።
ቀጣዩ የኢራን መሪ ማን ይሆን የሚለው ጉዳይ አነጋጋሪ ሆኗል።

ከትላንት በስቲያ ሰኞ 100 ሺህ ብር ዋስትና በማስያዝ ከእስር እንዲፈቱ በፍርድ ቤት የተበየነላቸው ዶ/ር ሲሳይ አውግቼው፤ ዛሬ ከቂሊንጦ ማረሚያ ቤት በመውጣት ላይ እንዳሉ “በር ላይ ሲጠብቋ...
26/02/2026

ከትላንት በስቲያ ሰኞ 100 ሺህ ብር ዋስትና በማስያዝ ከእስር እንዲፈቱ በፍርድ ቤት የተበየነላቸው ዶ/ር ሲሳይ አውግቼው፤ ዛሬ ከቂሊንጦ ማረሚያ ቤት በመውጣት ላይ እንዳሉ “በር ላይ ሲጠብቋቸው በነበሩ ፖሊሶች ተይዘው መወሰዳቸውን” ጠበቃቸው ተናገሩ።

ተከሳሹ “ወደ ፌደራል ፖሊስ” እየተወሰዱ መሆኑን፤ ሊቀበሏቸው ሲጠብቋቸው ለነበሩ ቤተሰቦቻቸው አሳውቀዋል ተብሏል።

ዶ/ር ሲሳይ በአማራ ክልል ከሚንቀሳቀሰው የፋኖ ታጣቂ ቡድን ጋራ በመሆን “የአማራ ክልልን ከፍተኛ የመንግስት ባለስልጣናት በመግደል የክልሉን ቀጥሎም የፌዴራሉን መንግሥት ስልጣን በኃይል ለመቆጣጠር በማሰብ የሽብር ድርጊት ፈጽመዋል” በሚል ክስ ከቀረበባቸው 51 ተከሳሾች ውስጥ አንዱ ናቸው።

በዶ/ር ወንድወሰን አሰፋ መዝገብ ስር የሚገኙት እነዚህ ተከሳሾች “የሽብር ክስ” የቀረበባቸው በሰኔ 2015 ዓ.ም ነበር።

አምስት የመገናኛ ብዙሃን ባለሙያዎች በተካተቱበት በዚህ ክስ ስር ካሉ ተከሳሾች ውስጥ በቅርቡ “የሰላም አማራጭ መቀበላቸውን” ያሳወቁትን ኮሎኔል ፋንታሁን ሙሃባውን ጨምሮ የሃያ ስምንቱ ጉዳይ ሲታይ የቆየው በሌሉበት ነበር።

የተከሳሾቹን ጉዳይ ሲመለከት የቆየው፤ የፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ ህገ መንግስታዊ እና የሽብር ጉዳዮች ወንጀል ችሎት ነው።

ዶ/ር ሲሳይ የ100 ሺህ ብር ዋስትና በማስያዝ ከእስር እንዲለቀቁ፤ ከትላንት በስቲያ ሰኞ የካቲት 16፤ 2018 በዋለው ችሎት ብይን መሰጠቱን ጠበቃው አስረድተዋል።

ለዋስትና የተጠየቀውን ገንዘብ የተከሳሽ ቤተሰቦች በዚያኑ ቀን ረፋድ ላይ መክፈላቸውን የገለጹት አቶ ሰለሞን መግለፃቸውን ኢትዮጵያ ኢንሳይደር አስነብቧል።

https://t.me/agelglmedia

የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙኃን ባለሥልጣን የአዲስ ስታንዳርድ የበየነ-መረብ መገናኛ ብዙኃን የምዝገባ የምስክር ወረቀትን ሰረዘየሚዲያው ዋና አዘጋጅ የቀረቡትን ክሶች ውድቅ አድርገዋልየአዲስ ስታንዳ...
24/02/2026

የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙኃን ባለሥልጣን የአዲስ ስታንዳርድ የበየነ-መረብ መገናኛ ብዙኃን የምዝገባ የምስክር ወረቀትን ሰረዘ

የሚዲያው ዋና አዘጋጅ የቀረቡትን ክሶች ውድቅ አድርገዋል

የአዲስ ስታንዳርድ የበየነ-መረብ መገናኛ ብዙኃን ምዝገባ ምስክር ወረቀት ከዛሬ የካቲት 17 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ መሰረዙን የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙኃን ባለሥልጣን ይፋ አድርጓል፡፡

ባለሥልጣኑ ዛሬ ምሽት ባወጣው መግለጫ “አዲስ ስታንዳርድ የበየነ-መረብ መገናኛ ብዙኃን የሚዲያ ስነ ምግባርን፣ የኢትዮጵያ ሕጎች እና የሀገርንና የሕዝብን ብሔራዊ ጥቅም አደጋ ላይ የሚጥሉ ዘገባዎችን በተደጋጋሚ በማሰራጨት ላይ ይገኛል” ብሏል፡፡

“ባለሥልጣኑ ይህንኑ ድርጊት በመመርመር አዲስ ስታንዳርድ የበይነ መረብ መገናኛ ብዙኃን እንዲታረም” እና “ከአጥፊ አካሄዱ እንዲቆጠብ በተደጋጋሚ ምክር ሲሰጥ ቢቆይም ለመታረም ፈቃደኛ ሳይሆን ቀርቷል” ሲል መግለጫው ገልጿል፡፡

የኢትዮጵያ ሚዲያ ባለስልጣን የሰጠውን መግለጫ በተመለከተ፣ የ ዋና አዘጋጅ ዮናስ ከድር ባለስልጣኑ ያቀረበውን ክስ ውድቅ አድርገዋል። ዋና አዘጋጁ እንደገለጹት፤ ተቋሙ እስካሁን ድረስ ምንም ዓይነት መደበኛ የሕግ ጥሰት እንደፈፀመ የሚያመለከት ማስጠንቀቂያ ደርሶት አያውቅም።

“አዲስ ስታንዳርድ ተደጋጋሚ ማስጠንቀቂያዎች ደርሰውታል የሚለው ክስ ከእውነት የራቀ ነው። የኢትዮጵያ ሚዲያ ባለስልጣን ቀደም ሲል ስለነበሩ የሕግ ጥሰቶችም ሆነ ስለተወሰዱ እርምጃዎች ለአዲስ ስታንዳርድ የዜና ክፍል በይፋ ያሳወቀው ነገር የለም” ብለዋል።

አክለውም የጋዜጣው አሳታሚ የሆነው ጃኬን ፐብሊሺንግ (JAKENN Publishing PLC) መብቱን ለማስከበርና የሕግ የበላይነት መከበሩን ለማረጋገጥ ያሉትን የሕግ አማራጮች እየገመገመ እንደሚገኝ ገልጸዋል።

እንደ ኢትዮጵያ መገናኛ ብዙኃን ባለስልጣን መግለጫ ከሆነ ተቋሙ “በሚዲያ ዘርፉ ላይ የሙያ ስነምግባር እና የሀገርና የህዝብ ብሔራዊ ጥቅም አክብሮ እንዲሰራ ተደጋጋሚ ማሳሰቢያ እና ማስጠንቀቂያ ቢሰጠውም ለመታረም ፈቃደኛ አልሆነም”፡፡

በዚህም የአዲስ ስታንዳርድ የበየነ-መረብ መገናኛ ብዙኃን የምዝገባ ምስክር ወረቀት “በመገናኛ ብዙኃን አዋጁ መሰረት” ከዛሬ የካቲት 17 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ መሰረዙን የተቋሙ መግለጫ አመልክቷል፡፡

መንግሥት በተለይ በቅርቡ በሚዲያዎች ላይ ተመሳሳይ እርምጃዎችን ወስዷል። በሮይተርስ፣ በጀርመን ድምፅ ራዲዮ (ዶይቸ ቨለ) እና በዋዜማ ራዲዮ ላይ ያደረገው ክልከላ ተጠቃሽ ነው።

ለተጨማሪ መረጃዎች የቴሌግራም ገፃችንን ይጎብኙ👇

https://t.me/agelglmedia

https://t.me/agelglmedia

በመከላከያ ሠራዊት እና በትግራይ ኃይሎች መካከል ግጭት መካሄዱን ዲፕሎማቲክ ምንጮች ተናገሩበኢትዮጵያ መንግሥት እና በትግራይ ኃይሎች መካከል ግጭት መካሄዱን የፈረንሳይ ዜና ወኪል ኤኤፍፒ እና...
29/01/2026

በመከላከያ ሠራዊት እና በትግራይ ኃይሎች መካከል ግጭት መካሄዱን ዲፕሎማቲክ ምንጮች ተናገሩ

በኢትዮጵያ መንግሥት እና በትግራይ ኃይሎች መካከል ግጭት መካሄዱን የፈረንሳይ ዜና ወኪል ኤኤፍፒ እና ሮይተርስ የደኅንነት እና የዲፕሎማቲክ ምንጮችን ጠቅሰው ዘግበዋል።

በሰሜን ኢትዮጵያ የአማራ እና ትግራይ ክልል አዋሳኝ አካባቢዎች ከዚህ ሳምንት መጀመሪያ አንስቶ ግጭቶች እየተካሄዱ መሆናቸውን የሚያመለክቱ ዜናዎች እየተሰሙ ቢሆንም ተጨባጭ መረጃ ማግኘት አዳጋች ሆኖ ቆይቷል።

ግጭቶች የተቀሰቀሱት ጸለምት በሚባለው የአማራ እና የትግራይ ክልሎች በይገባኛል በሚወዛገቡበት እና በአማራ ክልል ቁጥጥር ሥር በሚገኛው አካበቢ መሆኑን ያመለከተው የዜና ወኪሉ፤ አንድ የደኅንነት ምንጭ "ሁኔታው እየተባባሰ እየሄደ ነው" ሲሉ እንደነገሩት ገልጿል።

በተጨማሪም ስማቸው እንዳይጠቀስ የጠየቁ ዲፕሎማሲያዊ ምንጭ ለኤኤፍፒ እደንተናገሩት የትግራይ ኃይሎች "ከኢትዮጵያ ሠራዊት እና ከአማራ ሚሊሻዎች" ጋር እየተዋጉ ነው።

ምንጩ አክለውም "ባለፉት ቀናት ግጭቶች እንደነበሩ የተረጋገጠ ነው፤ ነገር ግን ዛሬ [ሐሙስ] ስላለው ሁኔታ የምናውቀው ነገር የለም" ብለዋል።

የጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ የምሥራቅ አፍሪካ ጉዳዮች አማካሪ አቶ ጌታቸው ረዳ ረቡዕ ዕለት በማኅበራዊ ሚዲያ ገጻቸው ላይ "ህወሓት ውስጥ የሚገኙ የሥልጣን ጥም ያለባቸው ግለሰቦች…ትግራይን ወደ ሌላ ዙር ጦርነት ሊያስገቧት እንቅስቃሴ እያደረጉ ይገኛሉ" በማለት በትግርኛ ጽፈዋል።

የቀድሞው የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር ፕሬዝዳንት አቶ ጌታቸው፤ ግጭት መካሄዱን በሚያመለክት ሁኔታ የህወሓት መሪዎች ወጣቶችን ለጉዳት የሚዳርግ የጦር ስልት መከተላቸውን ጠቅሰው "...ከእንግዲህ አጉል መስዋዕትነት አልከፍልም ብለህ ተቃውሞህን አሰማ" በማለት ጥሪ አቅርበዋል።

አንድ ስማቸው ያልተጠቀሰ የአካባቢው ነዋሪ ግጭቶች መካሄዳቸውን አረጋግጠዋል። ነገር ግን ኤኤፍፒ ለፌደራል መንግሥቱ ሠራዊት እና ለህወሓት ጥያቄ አቅርቦ ምላሽ እየጠበቀ ነው።

በተመሳሳይ ሮይተርስ የዜና ወኪል አንድ ዲፕሎማቲክ ምንጭን ጠቅሶ "በዚህ ሳምንት በምዕራብ ትግራይ ለአጭር ጊዜ የቆየ ግጭት" በመከላከያ ሠራዊት እና በትግራይ ኃይሎች መካከል መካሄዱን ዘግቧል።

ግጭቱን በተመለከተ የፌደራል መንግሥቱም ሆነ የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር እስካሁን ያሉት ነገር የለም።

መረጃዎችን ለማግኘት👇

https://t.me/agelglmedia

የኢትዮጵያ አየር መንገድ ወደ ትግራይ ክልል የሚያደርጋቸው በረራዎች ተሰረዙ ለዛሬ ጥር 21/2018 ዓ.ም ተይዘው በነበሩ በረራዎች ወደ አዲስ አበባ ለመጓዝ ትኬት ቆርጠው የነበሩ መንገደኞች ...
29/01/2026

የኢትዮጵያ አየር መንገድ ወደ ትግራይ ክልል የሚያደርጋቸው በረራዎች ተሰረዙ

ለዛሬ ጥር 21/2018 ዓ.ም ተይዘው በነበሩ በረራዎች ወደ አዲስ አበባ ለመጓዝ ትኬት ቆርጠው የነበሩ መንገደኞች ጉዟቸው እንደተሰረዘ የሚገልፅ አጭር የጽሁፍ መልዕክት እንደደረሳቸው ተናግረዋል።

በመልዕክቱ ላይ "ከዕቅድ ውጪ በመሆነ ምክንያት" በረራው መሰረዙን እና መንገደኞች የኢትዮጵያ አየር መንገድን ወይም የጉዞ ወኪላቸውን እንዲያገኙ መክሯል።

ነገር ግን የኢትዮጵያ አየር መንገድ የበረራዎቹን መቋረጥን በተለመከተ እስካሁን የሰጠው ይፋዊ ምክንያትም ሆነ መግለጫ የለም።

ስለ በረራዎች መሰረዝ የተጠየቁት የክልሉ ትራንስፖርት ኃላፊ አቶ ታደለ መንግሥቱ ምክንያቱን ባያውቁም በረራዎች መቋረጣቸውን አረጋግጠው።

አንድ ስማቸው እንዲጠቀስ ያልፈቀዱ የአየር መንገዱ ኃላፊ ወደ ትግራይ የሚደረጉ በረራዎች መቋረጣቸውን አረጋግጠዋል።

እኚሁ የአየር መንገዱ ባልደረባ እንደገለጹት "በረራዎች ለዛሬ [ሐሙስ ጥር 21 ቀን 2018] ብቻ ነው የተሰረዙት፤ ነገር ግን የቀጣይ ቀናት በረራዎች በሚኖረው ሁኔታ የሚወሰን ይሆናል" በማለት ለውሳኔው ምክንያቱ ምን እንደሆነ ከመግለጽ ተቆጥበዋል።

በዚህም ምክንያት ከአዲስ አበባ ወደ መቐለ እና ወደ ሌሎች የትግራይ ክልል ከተሞች ሐሙስ ዕለት የሚደረጉ በረራዎች እንዲሁም ወደ አዲስ አበባ የሚደረጉ በረራዎች መሰረዛቸው ተሰምቷል።

ከአዲስ አበባ ወደ ትግራይ ክልል ከተሞች የሚደረጉ በረራዎች መሰረዛቸውን በከተማዋ ከሚገኘው የኢትዮጵያ አየር መንገድ የቲኬት ቢሮ ገልጿል።

በተጨማሪም መቐለ የሚገኙ የኢትዮጵያ አየር መንገድ ሠራተኞች ዛሬ ወደ ቢሮ እንዳይገቡ እንደተናገራቸው ቢቢሲ አረጋግጫለሁ ብሏል።

የበረራዎቹን መቋረጥ በተለመከተ እስካሁን ከትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር እና ከኢትዮጵያ መንግሥት የተሰጠ አስተያየት የለም።

በመቐለ አሉላ አባነጋ አየር ማረፊያ የተለመደው የተጓዦች እንቅስቃሴ እንደሌለ እና ከአየር ማረፊያው የጥበቃ አባላት ውጪ የሌሎች እንቅስቃሴ እንደሌለ ቢቢሲ በስፍራው ተገኝቶ ማረጋገጡን ዘግቧል።

ተጨማሪ መረጃዎችን ለማግኘት https://t.me/agelglmedia

ዓርብ ጥር 8 ቀን 2018 ዓ.ም ከዚህ ዓለም በሞት የተለየው የተወዳጁና ሁለገቡ አርቲስት ነፃነት ወርቅነህ ስርዓተ ቀብር ነገ እሁድ ጥር 10 ቀን 2018 ዓ/ም ይፈጸማል።በተወዳጅ ፊልሞቹ፣ ...
17/01/2026

ዓርብ ጥር 8 ቀን 2018 ዓ.ም ከዚህ ዓለም በሞት የተለየው የተወዳጁና ሁለገቡ አርቲስት ነፃነት ወርቅነህ ስርዓተ ቀብር ነገ እሁድ ጥር 10 ቀን 2018 ዓ/ም ይፈጸማል።

በተወዳጅ ፊልሞቹ፣ በቴሌቪዥን ፕሮግራሞቹ እና በቅርብ ሰዎቹ በደግነቱ የሚታወቀው ነፃነት ወርቅነህ ህልፈተ ህይወቱ የታወቀው በድንገት ነበር።

ኢቢኤስ ቴሌቪዥን ባወጣው መረጃ መሰረት ከጠዋቱ 2፡30 ጀምሮ በ4 ኪሎ መንበረ ጸባኦት ቅድስት ስላሴ ካቴድራል የሽኝት መርሃ ግብር ይደረጋል።

ከሽኝት መርሃ ግብሩ በኋላ ከቀኑ 6:00 ሰዓት ላይ የመጨረሻው የቀበርሥነ-ሥርዓት ይፈፀማል።

ለወዳጅ ዘመዶቹ በሙሉ መፅናናትን እንመኛለን።

ተወዳጅ ቤተሰቦችምርጥ ምርጡን ለእናንተ የሚያቀርበው አገልግል ሬድዮ ለጆሮ የሚጥሙ ተወዳጅ ሙዚቃዎችን እና የመዝናኛ ዝግጅቶችን ያለ ጊዜ ገደብ ይዞላችሁ ቀርቧል።በ24/7 ስርጭታችን ሁል ጊዜ ...
17/01/2026

ተወዳጅ ቤተሰቦች
ምርጥ ምርጡን ለእናንተ የሚያቀርበው አገልግል ሬድዮ ለጆሮ የሚጥሙ ተወዳጅ ሙዚቃዎችን እና የመዝናኛ ዝግጅቶችን ያለ ጊዜ ገደብ ይዞላችሁ ቀርቧል።

በ24/7 ስርጭታችን ሁል ጊዜ አብረናችሁ አለን። አብራችሁን ሁኑ።
👇
በዚህ ማስፈንጠሪያ አድምጡን።

Listen to Agelgl Radio - Live Streaming

አርቲስት ነጻነት ወርቅነህ ከዚህ ዓለም በሞት ተለየበበርካታ ፊልሞች እና በኢቢኤስ የቤተሰብ ጨዋታ ፕሮግራም የሚታወቀው አርቲስት ነጻነት ወርቅነህ ባደረበት ህመም በድንገት ከዚህ ዓለም በሞት ...
16/01/2026

አርቲስት ነጻነት ወርቅነህ ከዚህ ዓለም በሞት ተለየ

በበርካታ ፊልሞች እና በኢቢኤስ የቤተሰብ ጨዋታ ፕሮግራም የሚታወቀው አርቲስት ነጻነት ወርቅነህ ባደረበት ህመም በድንገት ከዚህ ዓለም በሞት መለየቱን ኢቢኤስ ቴሌቪዥን ገለጸ።

አርቲስት ነጻነት ወርቅነህ በቴሌቪዥን ፕሮግራም አቅራቢነት፣ በተዋናይነትና በሌሎች የጥበብ ስራዎቹ በኪነ ጥበቡ ቤተሰብ ዘንድ ይታወቃል።

ሁለገቡ አርቲስት ነጻነት ወርቅነህ ለበርካታ ዓመታት በኢቢኤስ ቴሌቪዥን የሚተላለፈውን የቤተሰብ ጨዋታ ፕሮግራም አዘጋጅና አቅራቢ በመሆን እያገለገለ ነበር።

አርቲስት ነጻነት ወርቅነህ በፊልም እና በቴአትር ስራዎቹ እጅግ ተወዳጅ የነበረ ሲሆን፤ ሲቲ ቦይስ፣ ሳልነግራት፣ ያንቺው ሌባ 2፣ ኤፍቢአይ፣ ሚስተር ኤክስ፣ ቾምቤ እና ሌሎችም ድንቅ ብቃቱን ያሳየባቸው ፊልሞች ናቸው።

ፍሬሽ ማን ከህዝብ ጋር ያስተዋወቀው የቴአትር ስራው ነው።

አርቲስት ነጻነት ወርቅነህ ባለትዳርና የ3 ልጆች አባት ነበር።

ከህብረተሰቡ ባህል፣ ሞራልና እሴት ተቃራኒ የሆኑ መልዕክቶችን በማህበራዊ ሚዲያ ሲያሰራጭ የነበረን ግለሰብ በቁጥጥር ስር አዋልኩኝ አለ የአዲስ አበባ ፖሊስ፡ የአዲስ አበባ ፖሊስ በመግለጫው ና...
24/12/2025

ከህብረተሰቡ ባህል፣ ሞራልና እሴት ተቃራኒ የሆኑ መልዕክቶችን በማህበራዊ ሚዲያ ሲያሰራጭ የነበረን ግለሰብ በቁጥጥር ስር አዋልኩኝ አለ የአዲስ አበባ ፖሊስ፡

የአዲስ አበባ ፖሊስ በመግለጫው ናትናኤል ባደግ ገብሬ የተባለን ተጠርጣሪ በቁጥጥር ስር የዋለው የማህበራዊ ሚዲያን (YouTube እና tiktok platform) ን በመጠቀም በንግግር ልቅ ፆታዊ ግንኙነትን የሚያበረታታና የሚያስፋፋ አፀያፊ መልዕክቶችን ሲያሰራጭ በመቆየቱ ነው ብሏል።

ተጠርጣሪው በተለምዶአዊው ንግግር ሊገለፁ የማይችሉ አስፀያፊ ቃላትን በመጠቀም በትውልዱ ላይ አሉታዊ ተፅዕኖ ሲያሳድር እንደነበር እና መሰል ይዘቶችን በተደጋጋሚ ጊዜ በመስራት በማህበራዊ ሚዲያ (YouTube እና tiktok platform) በመጠቀም ሲያሰራጭ እንደነበር ፖሊስ አብራርቷል፡፡

Agelgl Media

የጋምቤላ ክልላዊ መንግሥት፣ ጋምቤላ ከተማን ጨምሮ የጸጥታ ችግር ባለባቸዉ አካባቢዎች ከዛሬ ረቡዕ ከምሽቱ 2:00 ሰዓት ጀምሮ እስከ ንጋቱ 12:00 ሰዓት ድረስ የሚቆይ ሰዓት እላፊ ላልተወሰ...
24/12/2025

የጋምቤላ ክልላዊ መንግሥት፣ ጋምቤላ ከተማን ጨምሮ የጸጥታ ችግር ባለባቸዉ አካባቢዎች ከዛሬ ረቡዕ ከምሽቱ 2:00 ሰዓት ጀምሮ እስከ ንጋቱ 12:00 ሰዓት ድረስ የሚቆይ ሰዓት እላፊ ላልተወሰነ ጊዜ መጣሉን አስታወቀ።

የክልሉ መንግሥት ዛሬ ምሽት 11:30 ገደማ ባወጣው መግለጫ፣ ለሥራ ከተመደቡ የጸጥታ ኃይሎች በስተቀር ሰዎችም ኾኑ ተሽከርካሪዎች በሰዓት እላፊው ወቅት እንዳይንቀሳቀሱ ከልክሏል።

ከጸጥታ አካላት ውጪ በማናቸውም ቦታ ጦር መሳሪያ ይዞ መንቀሳቀስ ክልክል መሆኑንም የክልሉ መንግሥት አስታውቋል። የክልሉ መንግሥት የሰዓት እላፊውን ያወጀው፣ በክልሉ በተለይም በጋምቤላ ከተማ እንዲኹም በጋምቤላ እና ኢታንግ ወረዳዎች ከኅዳር 28 ጀምሮ በተከሠቱ ግጭቶች እና የጸጥታ መደፍረስ ሳቢያ የሰዎች ሕይወት መጥፋቱንና የአካል ጉዳት መድረሱን ተከትሎ ነው።

በክልሉ ግጭት የተቀሠቀሠው፣ የጋምቤላ ከተማ ፖሊስ አዛዥ ኡመድ ኡጁሉ በታጠቀ ግለሰብ ከተገደሉ በኋላ ነበር።

የክልሉ መንግሥት በግጭቱ እስካሁን የስንት ሰዎች ሕይወት እንዳለፈ እና ከግጭቱ ጋር በተያያዘ ስንት ተጠርጣሪዎችን በቁጥጥር ሥር እንዳዋለ ይህ ዘገባ እስከተጠናቀረበት ሰዓት ድረስ ይፋ አላደረገም።

በትግራይ ክልል አሰገደ ወረዳ ሕጻጽ የስደተኞች መጠለያ ላይ የሚደረገው የሰብዓዊ ድጋፍ ዓመቱን በሙሉ  ሳይቆራረጥ ተደርጓል አለ የኢትዮጵያ አደጋ ስጋት አመራር ኮሚሽን ኮሚሽኑ በቅርቡ በማህበ...
24/12/2025

በትግራይ ክልል አሰገደ ወረዳ ሕጻጽ የስደተኞች መጠለያ ላይ የሚደረገው የሰብዓዊ ድጋፍ ዓመቱን በሙሉ ሳይቆራረጥ ተደርጓል አለ የኢትዮጵያ አደጋ ስጋት አመራር ኮሚሽን

ኮሚሽኑ በቅርቡ በማህበራዊ ሚዲያ አማካኝነት እየተሰራጨ ያለው መረጃ ሀሰት ነው ሲል አጣጥሏል።

"በሕጻጽ ጊዜያዊ መጠለያ ጣቢያ የሚገኙ ዜጎቻችን አመቱን ሙሉ ተመሳሳይ ድጋፍ ሲደረግላቸው ነበር" ያለው ኮሚሽኑ ከመስከረም ወር 2018 ዓ.ም ጀምሮ እስከ ታህሳስ ወር 2018 ድረስ የተሟላና ያልተቆራረጠ የምግብ ስብአዊ ድጋፍ እየተደረገላቸው ነው ሲል ዛሬ ረቡዕ ታህሳስ 15 ቀን 2018 ዓ.ም በሰጠው መግለጫ ጠቅሷል።

"ባለፉት አራት ወራት ለ14 ሺህ 413 ዜጎች ድጋፍ ሲደረግ ቆይቷል" ያለው ኮሚሽኑ "በተጨማሪም ከአጎራባች መጠለያ ጣቢያ የሚገኙ ዜጎችን ጨምሮ በመስከረም ወር 16 ሺህ 775 በጥቅምት ወር 18 ሺህ 290 በህዳር ወር 17 ሺህ 813 እንዲሁም በታህሳስ ወር የሚያስፈልገው ለ14 ሺህ 413 ዜጎች የሚያስፈልግ ምግብ ተሰራጭቷል" ብሏል።

"በድምሩ 11 ሺህ 406 ኩንታል ምግብ (ስንዴ፣ ማሽላ፣ ጥራጥሬና የምግብ ዘይት) ባለፉት አራት ወራት እንዲዳርሳቸው ተደርጓል፡፡ ይህ ድጋፍ በገንዘብ ሲተመን ከ257 ሚሊየን ብር በላይ ይሆናል።" ነው ያለው።

በክልሉ ጊዜያዊ አስተዳደር የተለያዩ የሰብአዊ ድጋፍ ችግሮች መኖራቸውንና ተጨማሪ የፌዴራል ድጋፍ እንደሚያስፈልግ አለመጠየቁን የገለፀው ኮሚሽኑ ለተፈናቃይ ማሕበረሰብ የሚላከው ድጋፍ ለታለመለት አላማ ብቻ መዋሉን የማረጋገጥና ክፍተቶች ቢኖሩም እንዲሟላ የማድረግ ሃላፊነት የክልሉና የአካባቢው ጊዜያዊ አስተዳደር ነው ሲልም ዛሬ በሰጠው መግለጫ አሳውቋል።

በክልሉ ደደቢት አቅራቢያ በሚገኘው ሕጻጽ የመጠለያ ጣቢያ 1,700 ሰዎች ለከፋ ረሀብ መጋለጣቸውንና 350 ገደማ ሰዎች በከባድ ረሀብ ምክንያት ህይወታቸው እንዳለፈ መዘገባችን ይታወሳል።

Agelgl Media

የህንድ ጠቅላይ ሚኒስትር ናሬንድራ ሞዲ አዲስ አበባ ገቡጠቅላይ ሚኒስትሩ ቦሌ ኤርፖርት ሲደርሱ አቻቸው የኢፌዴሪ ጠቅላይ ሚኒስተር ዐቢይ አህመድ አቀባበል አድርገውላቸዋል።ጠቅላይ ሚኒስትር ናሬ...
16/12/2025

የህንድ ጠቅላይ ሚኒስትር ናሬንድራ ሞዲ አዲስ አበባ ገቡ

ጠቅላይ ሚኒስትሩ ቦሌ ኤርፖርት ሲደርሱ አቻቸው የኢፌዴሪ ጠቅላይ ሚኒስተር ዐቢይ አህመድ አቀባበል አድርገውላቸዋል።

ጠቅላይ ሚኒስትር ናሬንድራ ሞዲ አዲስ አበባ መግባታቸውን በተመለከተ በX ገፃቸውን ላይ " ኢትዮጵያ ታላቅ ታሪክ እና የደመቀ ባህል ያላት ሀገር ነች። ህንድ እና ኢትዮጵያ ጥልቅ የሆነ የስልጣኔ ትስስርም አላቸው። በተለያየ ዘርፍ ያለንን አጋርነት የበለጠ ለማጠናከር ከኢትዮጵያ አመራር ጋር ለመወያየት ተዘጋጅቻለሁ " ሲሉ በአማርኛ ጽፈዋል።

የኢፌዴሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐብይ አህመድ ቦሌ ዓለማቀፍ አየር ማረፊያ ተገኝተው ከተቀበሏቸው በኋላ፤ ወደ ሳይንስ ሙዚየም ወስደዋቸዋል።

" ይህ ሙዚየም የተለያዩ የሳይንስና የፈጠራ ስራዎችን እና ለኢትዮጵያ እድገት እንዴት ጥቅም ላይ ሊውሉ እንደሚችሉ ያሳያል " ብለዋል።

የህንድ ጠቅላይ ሚኒስትር በኢትዮጵያ በሚኖራቸው ይፋዊ የስራ ጉብኝት የተለያዩ የሁለትዮሽ ውይይቶችን ያደርጋሉ። ረቡዕ በህዝብ ተወካዮችና በፌዴሬሽን ምክር ቤቶች የጋራ ስብሰባ ላይ ንግግር ያደርጋሉ ተብሎ ይጠበቃል።

ናሬንድራ ሞዲ በዓለም በህዝብ ብዛት ቀዳሚ የሆነቺው የህንድ ጠቅላይ ሚኒስትር ናቸው።

Agelgl Media
አገልግል ሬድዮን በተለያዩ አማራጮች ያድምጡ👇

https://onlineradiobox.com/et/agelgl/playlist/

https://zeno.fm/player/agelgl-radio

https://liveonlineradio.net/agelgl-radio

https://radio.menu/stations/agelgl-blogspot-com-agelgl-radio/

https://liveonlineradio.net/agelgl-radio

https://radiofy.online/en/et/agelgl

https://liveradiostations.net/station/agelgl-radio/

Address

Addis Ababa
1000

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Agelgl Media posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share