01/03/2026
የኢራኑ መሪ አያቶላሕ አሊ ኻሚኒ በአሜሪካ እና እስራኤል ጥምር ጥቃት ተገደሉ
ከአያቶላሕ በተጨማሪ የእስላማዊ ኢራን አቢዮታዊ ዘብ አዛዥ ሜጀር ጄነራል መሐመድ ፓክፑር እና ከፍተኛ የደህንነት አማካሪው ዓሊ ሻምኻኒም እንደተገደሉ የኢራን የመንግሥት ሚዲያ ይፋ አድርጓል።
ሮይተርስ በዘገባው የእስራኤል ከፍተኛ ባለሥልጣን የመሪው መገደል እንዳረጋገጠለት ዘግቧል።
ከመሪዎቹ በተጨማሪ 201 ሰዎች መገደላቸውን እና 747 ሰዎች መጎዳታቸውን ቀይ ጨረቃ ይፋ አድርጓል። ከተገደሉት ውስጥ በትንሹ 100 ያህሉ ተማሪዎች ናቸው።
ይህን ተከትሎ ኢራን የ40 ቀናት ብሔራዊ ሐዘን እና የሰባት ቀናት በዓል አውጃለች።
የተባበሩት መንግሥታት ድንገተኛ ጉባኤ አድርጓል።
የመሪውን መገደል ይፋ ያደረጉት እና ግድያው 'ኢራናውያን ሃገራቸውን ወደ ቀድሞ ለመመለስ ታላቅ እድል ነው' ያሉት የአሜሪካው ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ በኮንግረስ ያልፀደቀ ጦርነት መጀመራቸውን ተከትሎ ህገወጥ ድርጊት የሚል ትችት ቀርቦባቸዋል።
እስራኤል እና አሜሪካ በጥምረት በኢራን ላይ የፈፀሙትን ድንገተኛ ወታደራዊ እርምጃን ተከትሎ፡ ኢራን በእስራኤል ላይ እና በመካከለኛው ምስራቅ የአሜሪካ የጦር ካምፕ ባላቸው አገሮች ላይ አፃፋዊ እርምጃዎችን ወስዳለች።
ኢራን እና ኳታር የአየር በረራዎችን ሙሉ በሙሉ አቁመዋል።
ቀጣዩ የኢራን መሪ ማን ይሆን የሚለው ጉዳይ አነጋጋሪ ሆኗል።