Ethiopian Daily News

Ethiopian Daily News We provide updated news and information daily!

01/03/2021

የዓረና ፓርቲ መግለጫ ፦

ዛሬ ዓረና ትግራይ ለዴሞክራሲና ሉአላዊነት- ዓረና ፓርቲ ባወጣው መግለጫ ከዚህ ቀደም በትግራይ እና በፌዴራል መንግስት መካከል የነበረው ፍጥጫ በድርድር መፈታት እንዳለበት ሲያሳስብ መቆየቱን አስታውሷል።

ዓረና ሃሳቤ ሰሚ አጥቶ በትግራይ ከማዕከላይ መንግስቱና ከብሄራዊ ምርጫ ቦርድ እውቅና ውጭ ምርጫ ሲካሄድ የጦርነቱ ጅማሬ ዋዜማ እንደነበር ተገንዝቤያለሁ ብሏል።

ጥቅምት 24/2013 ዓ.ም በሀገር መከላከያ ሰሜን ዕዝ ላይ ጥቃት ሲፈፀም የተፈራው ደርሶ የእልቂት አስከፊ ጦርነት ይፋ ሆነ ፤ ወደ ጦርነቱ ሲገባ ህዝቡ ተነጋግሮበት እና መክሮበት የተደረገ አልነበረም፤ እንኳንስ ህዝቡ የትግራይ ክልል ምክር ቤትም ሳይመክርበት የተካሄደ ነበር ሲል ዓረና ፓርቲ ሁኔታውን አስታውሷል።

ዓረና ፓርቲ ፥ ጦርነት ያህል የሚሊዮኖችን ህይወት የሚያናጋ አጥፊ ተግባር በተወሰኑ የፓርቲ አመራሮች እና ሊሂቃን ሲወሰን ጦሱ በንፁሃን ዜጎች ላይ እንደሚሆን ሳይታለም የተፈታ ነበር ብሏል።

ዓረና በትግራይ በአጭር ጊዜ በየመን፣ በሶርያ፣ ሊቢያ እና ኢራቅ የተከሰተው ዓይነት ውድመት ደርሷል ሲል ገልጿል።

ዓረና ፥ አሁንም በትግራይ የፀጥታ ስጋት፣ በየአካባቢው ተኩስ እና ግድያ አለ ያለ ሲሆን በተለይ በውጊያ ሂደት እና ከውጊያ ውጭ በንፁሃን ወገኖች ላይ እየደረሰ ያለው ግድያ አሁንም ድረስ ቀጥሏል ብሏል።

ይህ ሁኔታ በአስቸኳይ መፍትሄ ካልተበጀለት ውድመቱ አሁን ካለው የከፋ ሊሆን ይችላል ሲል አስጠንቅቋል።

ዓረና ፓርቲ አሁንም የትግራይን ህዝብ እንዳይረጋጋ የሚያደርጉ ምክንያቶችን የዘረዘረ ሲሆን መፍትሄ ያላቸውን ሃሳቦችም ባወጣው መግለጫ ላይ በዝርዝር አስቀምጧል።

  12"...በፈተናው ዙሪያ ችግር ለመፍጠር የሚንቀሳቀስ ማንኛውንም አካል አንታገስም" - የአማራ ክልል ፖሊስ ኮሚሽን ኮሚሽነር አበረ አዳሙ የአማራ ክልል ፖሊስ ኮሚሽን ኮሚሽነር አበረ አዳሙ...
26/02/2021

12

"...በፈተናው ዙሪያ ችግር ለመፍጠር የሚንቀሳቀስ ማንኛውንም አካል አንታገስም" - የአማራ ክልል ፖሊስ ኮሚሽን ኮሚሽነር አበረ አዳሙ

የአማራ ክልል ፖሊስ ኮሚሽን ኮሚሽነር አበረ አዳሙ የካቲት 29/2013 በሚጀምረው የ12ኛ ክፍል ፈተና ዙሪያ በክልሉ ችግር ለመፍጠር የሚንቀሳቀስ ማንኛውንም አካል አንታገስም አሉ።

ኮሚሽነር አበረ አዳሙ ይህን ያሉት ዛሬ በባህርዳር በነበረ የ12ኛ ክፍል ብሄራዊ ፈተና ላይ ትኩረት ያደረገ የምክክር መድረክ ላይ ነው።

ኮሚሽነሩ የክልሉን ሰላም የማይፈልጉ አካላት ፈተናውን እንዳያደናቅፉ በቅንጅትና በልዩ ትኩረት ይሰራልም ብለዋል።

በተጨማሪ ተማሪዎች የረጅም አመት ውጤታቸውን የሚያዩበት ጊዜ በመሆኑ የፀጥታ መዋቅሩ በልዩ ትኩረት ይሰራል ሲሉ ተናግረዋል።

በተለይም የጸጥታ ችግር ባለባቸው አካባቢዎች ልዩ የፀጥታ ሀይል ስምሪት ይደረጋል ያሉ ሲሆን የፀጥታ ተቋሙ ችግሮች ሲፈጠሩ ፈጣን ውሳኔዎችን መስጠት ይገባል ብለዋል፡፡

ፈተናውን የሚያውኩ ማንኛውም መረጃ ፈጥኖ ለፖሊስ አካላት መስጠት ከህብረተሰቡ የሚጠበቅ ተግባር መሆኑን ገልፀዋል፡፡

በዛሬው የምክክር መድረክ ተማሪዎች በማህበራዊ ሚዲያ የሚናፈሱና ትክክለኛ ምንጫቸው ከማይታወቁ መረጃዎች ራሳቸውን በመጠበቅ የተዘጋጁበትን ፈተና እንዲፈተኑ ጥሪ ቀርቧል።

በ2012 ዓ.ም በኮሮና ቫይረስ (ኮቪድ-19) ወረርሽኝ ምክንያት ሳይሰጥ የቀረው የ2012 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ብሄራዊ ፈተና ሊሰጥ 10 ቀናት ብቻ ቀርቶታል።

25/02/2021

በፋይዘር እና ባዩንቴክ የተሰራው የኮቪድ-19 ክትባት ፣ እየተከተቡ ባሉ ሰዎች ላይ ቀደም ብሎ በሙከራው ወቅት ያስመዘገበውን ዓይነት ውጤታማነት እያሳየ መሆኑን አንድ አዲስ ጥናት አመለከተ።

የእስራኤል "ክሌሊት የምርምር ተቋም" ተመራማሪዎች ባካሄዱት አንድ ነጥብ ሁለት ሚሊዮን ሰዎች ያሳተፈ ጥናት እንደገለጠው ሁለት ጊዜ የሚሰጠው የፋይዘር ክትባት በማናቸውም የዕድሜ ክልል ውስጥ ያሉ ክትባቱን የወሰዱ ሰዎች በቫይረሱ የህመም ስሜት በሚያመጣ ደረጃ እንዳይጠቁ በማድረግ ረገድ 94 ከመቶ ውጤታማነት አሳይቷል።

አንዷን ብቻ ክትባት ለወሰዱ ሰዎች፤ 57 ከመቶ ቫይረሱን የመከላከል ዓቅም ሰጥቷቸዋል።

በአቻ ተመራማሪዎች ተገምግሞ 'በኒው ኢንግላንድ የህክምና መጽሄት' ላይ የወጣው ይህ የእስራኤሉ ጥናት በሃገር አቀፍ የኮቪድ19 ክትባት መርሃ ግብር ላይ ያተኮረ ግምገማ ሲካሄድ የመጀመሪያ መሆኑን ቪኦኤ በድረገፁ አስነብቧል።

ኢትዮጵያ እንቁላል ከዩክሬን ልታስገባ ነው ?ዩኬሬን ኢንፎርም የተባለ ድረገፅ ኢትዮጵያ ከዩክሬን እንቁላል ልታስገባ ነው ለዚህም የኢትዮጵያ መንግስት ከዩክሬን አቅራቢዎች ጋር ስምምነት ላይ ደ...
25/02/2021

ኢትዮጵያ እንቁላል ከዩክሬን ልታስገባ ነው ?

ዩኬሬን ኢንፎርም የተባለ ድረገፅ ኢትዮጵያ ከዩክሬን እንቁላል ልታስገባ ነው ለዚህም የኢትዮጵያ መንግስት ከዩክሬን አቅራቢዎች ጋር ስምምነት ላይ ደርሰዋል ሲል አስነብቧል።

በግብርና ሚኒስቴር ወደ ውጭ ሀገራት የሚላኩ እና ከውጭ የሚገቡ እንስሳት ደህንነት በተመለከተ የተቋቋመው ዳይሬክተር ኃላፊ ዶ/ር ወንድማገኝ ደጀኔ ፥ ኢትዮጵያ ከዩክሬን እንቁላል ልታስገባ ተስማምታለች ስለመባሉ ግብርና ሚኒስቴር የሚያውቀው ነገር የለም ብለዋል።

ዶክተር ወንድማገኝ ደጀኔ ፥ ከዚህ ቀደም ከዩክሬን የዶሮ ስጋ ለማስገባት እንቅስቃሴ ነበር ይህም ኢትዮጵያ ያሉ ሆቴሎች ፍላጎት ስላሳደሩ ነበር ብለዋል። በወቅቱ የዩክሬን መንግስት የማስገቢያ መስፈርቶችን ጠይቆ እንደነበርም አስታውሰዋል። ነገር ግን ከዛ በኃላ ምንም የተከናወነ ነገር በኢትዮጵያ መንግስት በኩልንም የተፈቀደ ነገር የለም ብለዋል።

ዶ/ር ወንድማገኝ አክለው፥ "...ምናልባት የሚያጠራጥረኝ ምግብ በሚል ስም በጤና ሚኒስቴር በኩል እየሄዱበት ያለው ነገር ካለ እርግጠኛ አይደለሁም እንደ ግብርና ሚኒስቴር ግን ከዩክሬን ጋር የተገናኘ ምንም መረጃ የለንም" ሲሉ ተናግረዋል።

የኢትዮጵያ የዶሮ አርቢዎች እና አቀናባሪዎች ማህበር ስራ አስኪያጅ አቶ ብርሃኑ ሚሊዮን በበኩላቸው በጉዳዩ ዙሪያ ምንም የሚያውቁት ነገር እንደሌለ/እንዳላረጋገጡ ተናግረዋል።

19/12/2020

የደረግ ባለስልጣናቱ እንዴት ጣልያን ኤምባሲ ገቡ?

©

ነገሩ እንዲህ ነው ኢትዮጵያን ለ7 ቀናት ያስተዳደሩት ሌ/ጀነራል ተስፋዬ ገ/ኪዳን ወይም 'የተስፋዬዎች መንግስት' ሀገሪቷን መቆጣጠር ሲሳነው ይሸሻል።

ኢ.ህ.አ.ዴ.ግ ሀገሪቷን በተቆጣጠረበት እለት አንዳንዱ የደርግ ባለስልጣን ከሀገር ይወጣል ወደ 13 የሚጠጉ ባለስልጣናት ደግሞ የጣልያንን በር ያንኳኳሉ ጣልያንም አላሳፈረቻቸውም ኑ ግቡ ትላቸዋለች።

ከገቡት መካካል አንዳንዱ ወዲያው ወጣ ሌላውም ጥቂት ቀናትን ቆይቶ ወጣ። ካልወጡት መካከል ግን ድፍን 26 ዓመት (ይህ ፅሁፍ በወቅቱ ሲፃፍ 2017 ነበር) ሙሉ በኤምባሲው ውስጥ እየኖሩ የሚገኙት 2 ባለስልጣናት ይገኛሉ።

ሁለቱም ባለስልጣናት የሞት ፍርድ የተፈረደባቸው ሲሆኑ የጣልያን ህገ መንግስት የሞት ፍርድን ስለማያስፈፅም ሁለቱን የደርግ ባለስልጣናት ለኢትዮጵያ መንግስት አሳልፎ አልሰጠም።

የጣልያን ኤምባሲ ሰዎቹን ገፍቶ ማስወጣትም አይፈልግም።

የጣልያን መንግስትም ሰዎቹን እንደ በጎ ፍቃድ ታሳሪዎች ነው የሚቆጥራቸው።

የቀድሞ ባለስልጣናቱን 'ከሰብአዊ መብት አያያዝ' ጋር በተገናኘ የተለያዩ የሰብዓዊ መብት ጠበቃዎች እንዲሁም መንግስታዊ ያልሆኑ ተቋማት ይጎበኟቸዋል።

ጣልያን ኤምባሲ ከገቡት እንዲሁም ገብተው ከወጡት መካከል ሜጀር ጀነራል ስዩም መኮንን (በማረፊያ ቤት ህይወታቸው አልፏል) ፣ ወሌ ቸኮል ፣ ፍሲካ ሲደልል ፣ ሽመልስ ማዘንጊያ ፣ ዶ/ር አለሙ አበበ ፣ ሸዋንዳኝ በለጠ ይገኙበታል።

በአሁን ሰዓት ጣልያን ኤምባሲ ውስጥ የሚኖሩት ሁለቱ (2) ባለስልጣናት አንዱ የቀድሞ የውጭ ጉዳይ ሚንስትር የነበሩት ብርሀኑ ባየህ እንዲሁም በደርግ ስርዓት ከፍተኛ ተሰሚነት የነበራቸው ሌተናል ጀነራል ሀዲስ ተድላ (የጦር ሀይሎች ጠቅላይ ኢታማጆር ሹም) ናቸው።

ሀይሉ ይመንህ ራሳቸውን አጥፍተዋል።

ሌፍተናንት ጀነራል ተስፋዬ ገብረኪዳን የኢትዮጵያ የአንድ ሳምንት ፕሬዘደንት በብርሀኑ ባየህ እንደተገደሉ ይነገራል።

ወሮ ኬሪያ ኢብራሂም (የ ሕወሀት Maria Carey) ለመንግስት እጅ ሰጡ !
01/12/2020

ወሮ ኬሪያ ኢብራሂም (የ ሕወሀት Maria Carey) ለመንግስት እጅ ሰጡ !

የትግራይ ሕዝብ ከስግብግቡ ጁንታ ጋር እንዳልሆነ በተግባር አስመስክሯል። የመከላከያ ሠራዊት በድል በገሠገሠባቸው የትግራይ አካባቢዎች ሁሉ የትግራይ ሕዝብ  ለሀገሩ ያለውን ፍቅርና ለመከላከያ ...
28/11/2020

የትግራይ ሕዝብ ከስግብግቡ ጁንታ ጋር እንዳልሆነ በተግባር አስመስክሯል።

የመከላከያ ሠራዊት በድል በገሠገሠባቸው የትግራይ አካባቢዎች ሁሉ የትግራይ ሕዝብ ለሀገሩ ያለውን ፍቅርና ለመከላከያ ሠራዊቱ ያለውን ክብር አሳይቷል። ጁንታው ካስታጠቃቸው ጥቂት የክፋት ኃይሎች ውጭ ያለው የትግራይ ሕዝብ መቀሌ እስኪገባ ድረስ ለመከላከያ ሠራዊቱ የሚጠበቅበትን ድጋፍ ሁሉ አድርጓል። ይህም የሠራዊቱን ድልና የጁንታውን ሽንፈት አፋጥኖታል።

ስግብግቡ ጁንታ በየትኛውም መመዘኛ ለትግራይ ሕዝብ አይመጥነውም። የትግራይ ሕዝብ ከእውነት ጋር በመቆምና የጁንታውን እኩይ ዓላማ በመፃረር ከቀበሌ ቀበሌ፣ ከዞን ዞን መቀሌ እስኪገባ ድረስ ተመሳሳይ ድጋፍ ለሠራዊቱ ሰጥቷል። ለዚህም ከፍ ያለ ምስጋናዬን አቀርባለሁ። ጁንታው በሸሸበት ከተማና አካባቢ ሁሉ የጤና ተቋማትን፣ ተ/ቤቶችን፣ ድልድዮችን፣ መንገዶችን፣ መሥሪያ ቤቶችን እያወደመ ሄዷል። በዚህም የገዛ ወገኑ ጠላት መሆኑን አሳይቷል። ጁንታው እኔ ከሞትኩ ብሎ ያፈረሳቸውን መሠረተ ልማቶች በፍጥነት በመገንባት የትግራይ ሕዝብ ወደ ሰላማዊ ኑሮው እንዲመለስ ለማድረግ የቻልነውን ሁሉ እንደምናደርግ ቃል እገባለሁ።

በዚህ ዘመቻችን ንጹሐን ዜጎች ዒላማ ሳይሆኑ፣ ከተሞቻችንና ቅርሶቻችን ሳይጎዱ መቀሌ ለመግባት ተችሏል።
PM Dr Abiy Ahmed

'የሮይተርስ የኢትዮጵያ ዘጋቢ ታገደች'የኢትዮጵያ መንግስት በዓለም አቀፍ ሚዲያዎች ላይ እርምጃ እየወሰደ መሆኑ ተሰማ።እርምጃ እየተወሰደባቸው የሚገኙት ዓለም አቀፍ ሚዲያዎች በኢትዮጵያ ውስጥ ...
20/11/2020

'የሮይተርስ የኢትዮጵያ ዘጋቢ ታገደች'

የኢትዮጵያ መንግስት በዓለም አቀፍ ሚዲያዎች ላይ እርምጃ እየወሰደ መሆኑ ተሰማ።

እርምጃ እየተወሰደባቸው የሚገኙት ዓለም አቀፍ ሚዲያዎች በኢትዮጵያ ውስጥ ያለውን ሁኔታ ዓለም በተሳሳተ መንገድ እንዲያውቀውና በኢትዮጵያ መንግስት ላይ ጫና እንዲበረታ በማድረጋቸው ነው ተብሏል።

የኢትዮጵያ ብሮድካስት ባለስልጣን ለሸገር ኤፍ ኤም 102.1 እንደተናገረው መቀመጫቸውን አዲስ አበባ ያደረጉ ዓለም አቀፍ ሚዲያዎች ወቅታዊውን ሁኔታ በጥንቃቄ እንዲሁም በሞያዊ ስነ ምግባር እንዲዘግቡ ማሳሰቢያ ቢሰጣቸውም በእንቢተኝነት በቀጠሉት ላይ እርምጃ መወሰዱን አሳውቋል።

ዶቼ ቨለ (DW) ፣ BBC ፣ ሮይተርስ የማስጠንቀቂያ ደብዳቤ ከተሰጣቻው መካከል ይገኙበታል።

"ሮይተርስ" ከትላንትና ወዲህ በሀገር ውስጥ ያላቸው ዘጋቢ በኢትዮጵያ ጉዳይ ምንም አይነት እንቅስቃሴ እንዳታደርግ ፣ ዘገባዎችን ፣ ዜናዎችን እንዳትሰራ ሙሉ በሙሉ እንደታገደች የብሮድካስት ባለስልጣን ለሬድዮ ጣቢያው ገልጿል።

ጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝ (የፍትህ ማናጂንግ ዳይሬክተር) ከእስር መፈታቱን ወንድሙ ታሪኩ ደሳለኝ ከደቂቃዎች በፊት አሳውቋል።ከዚህ በተጨማሪ የፍትህ መጽሔት ዋና አዘጋጅ ምስጋን ዝናቤም ከእስር...
15/10/2020

ጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝ (የፍትህ ማናጂንግ ዳይሬክተር) ከእስር መፈታቱን ወንድሙ ታሪኩ ደሳለኝ ከደቂቃዎች በፊት አሳውቋል።

ከዚህ በተጨማሪ የፍትህ መጽሔት ዋና አዘጋጅ ምስጋን ዝናቤም ከእስር መፈታቱ ተሰምቷል።

ችሎት !በአርቲስት ሃጫሉ ሁንዴሳ ግድያ ተጠርጥረው በቁጥጥር ሥር የሚገኙት 4ቱ ተጠርጣሪዎች ፦- ጥላሁን ያሚ፣ - ከበደ ገመቹ፣ - አብዲ አለማየሁ እንዲሁም ላምሮት ከማል እያንዳንዳቸው "ወን...
14/10/2020

ችሎት !

በአርቲስት ሃጫሉ ሁንዴሳ ግድያ ተጠርጥረው በቁጥጥር ሥር የሚገኙት 4ቱ ተጠርጣሪዎች ፦

- ጥላሁን ያሚ፣
- ከበደ ገመቹ፣
- አብዲ አለማየሁ እንዲሁም ላምሮት ከማል እያንዳንዳቸው "ወንጀሉን አልፈጸምንም፤ ጥፋትም የለንም" በማለት ዛሬ ለፍርድ ቤት ተናግረዋል።

ተጠርጣሪዎቹ ይህን ያሉት በፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት የሕግ እና ጸረ ሽብር ችሎት ዛሬ ረቡዕ በቀረቡበት ወቅት ነው።

የተከሳሾች ጠበቃ ተከሳሾቹ የክስ መከላከያ እንደሌላቸው ለፍርድ ቤቱ ተናግረዋል።

ዐቃቤ ሕግ ፖሊስ መስክሮችን እንዲያቀርብ ትዕዛዝ ይሰጠ ሲል ፍርድ ቤቱን ጠይቋል።

ፍርድ ቤቱ ግን ዐቃቤ ሕግ ራሱ መስክሮቹን ፍርድ ቤት እንዲያቀርብ አዟል።

በዚሁ መሠረት ከኅዳር 23 እስከ 25/2013 ዓ.ም ምስክሮቹን ይዞ እንዲቀርብ ፍርድ ቤቱ ተዕዛዝ ሰጥቷል።

Via BBC

ጋዜጠኛ ተመስገን ታስሮ አዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን እንደገባ ወንድሙ ታሪኩ ደሳለኝ አሳውቋል !ታሪኩ ደሳለኝ ተከታዩን ብሏል ፦"ጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝ አዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን መታሰሩን በ...
14/10/2020

ጋዜጠኛ ተመስገን ታስሮ አዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን እንደገባ ወንድሙ ታሪኩ ደሳለኝ አሳውቋል !

ታሪኩ ደሳለኝ ተከታዩን ብሏል ፦

"ጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝ አዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን መታሰሩን በር ላይ ያሉት ፖሊሶች ነግረውናል።

ጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝ ከቢሮ መወሰዱን እንደሰማን ወደ አዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን ያመራን ሲሆን እዛ በር ላይ ያሉት ፖሊሶች ተመስገንና የመፅሔቱ አዘጋጅ ምስጋን ዝናቤ ተይዘው መግባታቸውን ገልፀውልናል።

ከዚያ ውጪ ምንም ዓይነት መረጃን ያላገኘን ሲሆን ምናልባት ምግብና ልብስ ካመጣን ለማስገባት እንደሚተባበሩን ነግረውናል።"

በአርሜኒያ እና አዛርባጃን መካከል ተደርጎ የነበረው የተኩስ አቁም ስምምነት ከአንድ ቀን በላይ መዝለቅ አልቻለም። አዛርባጃን በዛሬው ዕለት እንዳስታወቀችው የተኩስ አቁም ስምምነት ከተደረሰ ከ...
11/10/2020

በአርሜኒያ እና አዛርባጃን መካከል ተደርጎ የነበረው የተኩስ አቁም ስምምነት ከአንድ ቀን በላይ መዝለቅ አልቻለም።

አዛርባጃን በዛሬው ዕለት እንዳስታወቀችው የተኩስ አቁም ስምምነት ከተደረሰ ከአንድ ቀን በኋላ ለዛሬ እሁድ አጥቢያ የአርሜኒያ ኃይሎች በሰነዘሩት ጥቃት 7 ሰዎች ተገድለዋል።

ጥቃቱ የተሰነዘረው በአዛርባጃንዋ የጋንጃ ከተማ የመኖርያ መንደሮች ላይ ነው ተብሏል።

በጥቃቱ ከተገደሉት ውጭ ህጻናትን ጨምሮ ሌሎች 33 ሰዎች መቁሰላቸውን የአዛርባጃን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር በትዊተር ገጻቸው ላይ አስፍረዋል።

ነገር ግን የአርሜኒያ ኃይሎች ውንጀላውን አጣጥለው ይልቁኑ የተኩስ አቁም ስምምነቱን በመጣስ የአዛርባጃን ኃይሎችን ተጠያቂ ማድረጋቸው የፈረንሳይ ዜና ምንጭ ዘግቧል።

በሩስያ አደራዳሪነት በሁለቱ ሀገራት መካከል ተደርጎ የነበረው የተኩስ አቁም ስምምነት ለሁለት ሳምንት የሚቆይ እንደነበር የፈረንሳይ ዜና ምንጭ ዘገባ ያመለክታል።

Address

Addis Ababa

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Ethiopian Daily News posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share