Abay Tube

Abay Tube I invite you to SUBSCRIBE me 💜 I'm starting my own You Tube channel, Facebook and Instagram accounts to create an honest and approachable conversation.

I’m starting a new journey across YouTube, Facebook, TikTok, and Instagram, and this space is all about real conversations and practical creativity
https://www.tiktok.com/?r=1&t=ZN-92NqaZhXOtT
https://www.instagram.com/abayentertainment Thank You !!!

👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇

https://www.youtube.com/channel/UCSIvgnvTSV-OLuRhDuOhuyA
•Facebook:- https://www.facebook.com/AbayOnYoutube/
•Instagra

m:- https://www.instagram.com/abayentertainment
•Telegram: - https://t.me/AbayonYouTube
•YouTube: - https://www.youtube.com/c/AbayTube_Know

ቮሎዲሚር ዘለንስኪ ከቭላድሚር ፑቲን ጋር በአካል ለመወያየት ጥሪ አቀረቡ  | ዩክሬንና ሩሲያ በቀጥታ በመገናኘት ጦርነቱን እንዲያቆሙ የዩክሬኑ ፕሬዚዳንት ቮሎዲሚር ዘለንስኪ (ቪዲዮ) ለሩሲያው...
05/06/2026

ቮሎዲሚር ዘለንስኪ ከቭላድሚር ፑቲን ጋር በአካል ለመወያየት ጥሪ አቀረቡ

| ዩክሬንና ሩሲያ በቀጥታ በመገናኘት ጦርነቱን እንዲያቆሙ የዩክሬኑ ፕሬዚዳንት ቮሎዲሚር ዘለንስኪ (ቪዲዮ) ለሩሲያው ፕሬዚዳንት ቭላድሚር ፑቲን በጻፉት ግልጽ ደብዳቤ በአካል ለመገናኘት ጥሪ ማቅረባቸው ተሰማ።

የአሜሪካ ትኩረት ሙሉ በሙሉ ወደ ኢራን ጉዳይ በዞረበት በዚህ ወቅት፣ ጦርነቱ እንደገና የአሜሪካ ቀዳሚ አጀንዳ እስኪሆን ድረስ ዝም ብሎ መጠበቅ ስህተት መሆኑን እና ሰላም ሊመጣ የሚችለው በሁለቱ አገራት ቀጥተኛ ንግግር ብቻ መሆኑን ፕሬዚዳንቱ ገልጸዋል።

ቮሎዲሚር ዘለንስኪ ለሚካሄደው ድርድር እንዲረዳ ሙሉ የተኩስ አቁም እንዲታወጅ የጠየቁ ቢሆንም፣ ቭላድሚር ፑቲን ግን ከዚህ ቀደም የተኩስ አቁም ጥያቄውን ውድቅ አድርገውታል።

የክሬምሊን ቤተ መንግሥት ደብዳቤው እንደደረሰውና ለፑቲን ገለጻ እንደሚደረግላቸው ያረጋገጠ ሲሆን፣ ከዚህ ቀደም ሩሲያ ዘለንስኪ ወደ ሞስኮ መጥተው መወያየት እንደሚችሉ ገልጻ ነበር።

ቭላድሚር ፑቲን ስምምነት ለማድረግ ፈቃደኛ መሆናቸውን ቢናገሩም፣ ዩክሬን ዶኔትስክ፣ ሉሃንስክ፣ ኬርሰን እና ዛፖሪዢያ ከተባሉ አራት ክልሎች እንድትወጣ እና የኔቶ አባል የመሆን ጥረቷን እንድታቆም የሚሉትን ጠንካራ ቅድመ ሁኔታዎችን አስቀምጠዋል፡፡

ዩክሬን ግን ይህንን ግዛቶቿን አሳልፋ መስጠት የሩሲያን ዳግም ወረራ የሚያበረታታ መሆኑን በመግለጽ የሩሲያን ቅድመ ሁኔታዎች ሙሉ በሙሉ ውድቅ አድርጋለች።

በሌላ በኩል የአሜሪካው ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ የሁለቱ መሪዎች መገናኘት "በጣም ጥሩ ነገር ነው" ሲሉ ድጋፋቸውን ሰጥተዋል።

ተጨማሪ መረጃዎችን ለማግኘት፡-

•ፌስቡክ፡-https://web.facebook.com/HabeshaTech
• ፌስቡክ፡-https://www.facebook.com/AbayTubeEt

• ቴሌግራም፦https://t.me/HabeshaTechHubs
• ቴሌግራም፦https://t.me/HabeshaUpdate

#ጋዜጣ+

ወቅታዊ ጉዳዮችን አስመልክቶ የተሰጠ መግለጫ   | ​ግንቦት 24 ቀን 2018 ዓ.ም. ማለዳ ላይ፤ የመጀመሪያው የወገግታ ጭላንጭል በከፍታማዎቹ የኢትዮጵያ ተራሮች ላይ ፈንጥቆ ጨለማውን ሳይቀድ...
05/06/2026

ወቅታዊ ጉዳዮችን አስመልክቶ የተሰጠ መግለጫ

| ​ግንቦት 24 ቀን 2018 ዓ.ም. ማለዳ ላይ፤ የመጀመሪያው የወገግታ ጭላንጭል በከፍታማዎቹ የኢትዮጵያ ተራሮች ላይ ፈንጥቆ ጨለማውን ሳይቀድ በፊት ኢትዮጵያውያን ረጃጅም ሰልፍ ተሰልፈዋል። በጅማ፣ በድሬዳዋ፣ በሐዋሳ፣ በባሕር ዳር እንዲሁም ስማቸው በዓለም አቀፍ የዜና ጋዜጣዎች ላይ ፈጽሞ ሊወጣ በማይችሉ ከተሞችና መንደሮች ውስጥ ያሉ ወንዶችና ሴቶች፤ ወሳኝ ተግባር ለመፈጸም በሰልፍ ቆሙ። ድምፅ ሰጡ! ይህንን ታሪካዊ ኃላፊነት ለመወጣት ከሃምሳ አራት ሚልዮን በላይ የሚሆኑ ዜጎች ተመዝግበው ነበር። ይህ ቁጥር ከአንዳንድ ሀገሮች አጠቃላይ ሕዝብ ቁጥር በላይ ነው። ይህ ምርጫ እውነተኛ ስለመሆኑ ጥያቄ ለሚያነሣ ለማንኛውም አካል ግልጽ እና የማያሻማ ምላሽ ሰጥቷል!

​የኢትዮጵያ ሕዝብ ፍላጎት

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ከ52,000 ምርጫ ጣቢያዎች መካከል ከ50,188 በላይ የሚሆኑት በሰዓቱ ተከፍተው ቀኑን ሙሉ መራጮችን ሲያስተናግዱ እንደነበር አረጋግጧል። ከ42 የፖለቲካ ፓርቲዎች የተወጣጡ ከ10,438 በላይ ዕጩዎች እና 80 የግል እጩዎች በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት እና የክልል ምክር ቤት ወንበሮችን ለማሸነፍ ተወዳድረዋል። ይህ በማንኛውም ሊለካ በሚችል መሥፈርት በኢትዮጵያ ታሪክ ትልቁ እና በውሳኔ አሰጣጥም ሆነ በአስተዳደራዊ ረገድ እጅግ በረቀቀ ሁኔታ ተግባራዊ የተደረገ ዴሞክራሲያዊ ተሳትፎ የታየበት ኩነት ነበር።

​የቀድሞው የኬንያ ፕሬዚዳንት ክቡር ኡሁሩ ኬንያታ የሚመሩትና ከ37 የአፍሪካ ሀገሮች የተወጣጡ 83 ታዛቢዎችን ያቀፈው የአፍሪካ ኅብረት የምርጫ ታዛቢ ቡድን ምርጫውን “ዲሞክራሲያዊ አስተዳደርን በሰፊው በሚደግፍ ሕጋዊና ተቋማዊ ማዕቀፍ ውስጥ የተካሄደ” ሲል ገምግሞታል።

በቀድሞዋ የኡጋንዳ ምክትል ፕሬዚዳንት ክቡር ዶክተር ስፔሲዮዛ ዋንዲራ ካዚብዌ የሚመራው የኢጋድ የምርጫ ታዛቢ ቡድን ባወጣው የመጀመሪያ ደረጃ ሪፖርት፤ በታዘቡባቸው ጣቢያዎች ሁሉ የምርጫ ሳጥኖች በትክክል የታሸጉ መሆናቸውን፣ የፓርቲ ወኪሎች በሂደቱ በሙሉ መገኘታቸውን እንዲሁም ምርጫው አስደናቂ ተቋማዊ፣ አስተዳደራዊና የቴክኖሎጂ ዕድገትን ያሳየ መሆናቸውን አረጋግጧል። የኢጋድ የምርጫ ታዛቢ ልዑክ ይህንን ምርጫ “የበርካታ አዳዲስ ምዕራፎች ምርጫ” ሲል ሰይሞታል።

የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽን በድምፅ መስጠት ሂደት ውስጥ ምንም ዓይነት የሰብዓዊ መብት ጥሰት እንዳልተመለከተ አረጋግጧል። የሲቪክ ማኅበረሰብ ታዛቢዎች ጥምረት በምርጫ ቦርድ ዕውቅና ከተሰጧቸው 55 ድርጅቶች 65,299 ታዛቢዎችን በመላ ሀገሪቱ ያሠማራ ሲሆን፤ 99 በመቶ የምርጫ ጣቢያዎች ላይ ያለምንም ዕንቅፋት የመታዘብ ዕድል ማግኘቱን አረጋግጧል። እነዚህ ተዓማኒነት ያላቸው ሀገራዊ እና አኅጉራዊ ተቋማት ያደረጓቸው ግምገማዎችና የሰጧቸው እውነተኛ ፍርዶች ናቸው። እነዚህ ለአፍሪካ ጥላቻ ካላቸው ወይም የአፍሪካን ዴሞክራሲ በውጫዊ መሥፈርቶች ከሚለኩ ተቋማት የተደመጡ ድምፆች አይደሉም።

​አንዳንድ ዓለም አቀፍ ተንታኞች ይህንን ምርጫ እንደ ንግሥና በዓል አድርገው ያቆሸሹት ሲሆን ውጤቱም አስቀድሞ የተወሰነ ድራማ እንደነበር አድርገው ሊያቀርቡት ሞክረዋል። እነዚህን መግለጫዎች ከአውነታው የራቁ፣ በጥናትና ትንተና ላይ ያልተመሠረቱ እንዲሁም ነፃና የታሰበበት ዲሞክራሲያዊ ምርጫቸውን በኩራት ላደረጉ በሚሊዮን የሚቆጠሩ ኢትዮጵያውያን ክብር የማይሰጡ በመሆናቸው የጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት ሙሉ በሙሉ የማይቀበላቸው መሆኑን ያረግጣል። አስቀድሞ የተወሰነ ውጤት ቢኖር ኖሮ፤ ከ37 የአፍሪካ ሀገሮች የተወጣጡ 83 ገለልተኛ ታዛቢዎችን፣ 65,299 የሀገር ውስጥ የሲቪል ማኅበረሰብ ታዛቢዎችን ወይም 1,100 ዕውቅና የተሰጣቸውን የዓለም አቀፍ ጋዜጠኞችን መጋበዝ ባላስፈለገ ነበር።

​ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ በዚህ ሀገራዊ ምርጫ ለተሳተፉ የኢትዮጵያ ዜጎች፤ ለብሔራዊ ምርጫ ቦርድ እና ላሠማራቸው ከ350,000 በላይ ኃላፊዎች፤ ሂደቱን ለመጠበቅ የጸጥታ ኃይሎች እንዲሁም ኢትዮጵያ ለዲሞክራሲ ግንባታ መጎልበት እና ለሂደቱ መሳካት ያላትን ቁርጠኝነት ላረጋገጡት የአፍሪካ እና ቀጠናዊ የታዛቢ ቡድኖች ምስጋናቸውን ያቀርባሉ።

​ስለ ኢትዮጵያ ልማት

ኢትዮጵያውያን ግንቦት 24 2018 ዓ.ም ውሳኔያቸውን ሲያስቀምጡ፤ ሀገራቸውን በፍጹም የዲሞክራሲ ባህል ውስጥ ለማንበር ነው። በሌላ በኩል ኢትዮጵያ ባላት ጸጋ ልክ የሚያስፈልጋትን ሁለንተናዊ ልማት በፍጥነት እውን የማድረግ ባህል እንዲቀጥል ሕዝባችን ተናግሯል።

​ባለፉት ዓመታት የታየው እውነት እንደሚያሳየን የኢ.ፌ.ዲ.ሪ መንግሥት የተስፋ ቃል መንግሥት አልነበረም፤ ይልቁንም በተጨባጭ የሚታዩ ውጤቶች የተመዘገቡበት ውጤት ተኮር መንግሥት ሲሆን፤ እነዚህም ውጤቶች በግልጽ የሚታዩ ናቸው።

የኢትዮጵያ ኢኮኖሚ በ2017 በጀት ዓመት የ9.2 በመቶ ዕድገት ያስመዘገበ ሲሆን፤ ይህም በዓለም ላይ ፈጣን ዕድገት ካስመዘገቡ ኢኮኖሚዎች አንዱ ያደርገዋል። ዕድገቱ መነቃቃትን መሠረት በማድረግ በ2018 በጀት ዓመት የኢኮኖሚ ዕድገቱ 10.2 በመቶ ይደርሳል ተብሎ ይጠበቃል። ዕድገቱ ግብርናን፣ ኢንዱስትሪንና የአገልግሎት ዘርፎችን በከፍተኛ ደረጃ ያካተተ ሰፊ መሠረት ያለው ቢሆንም፤ ከጊዜ ወደ ጊዜ ግን ኢንዱስትሪው ለዕድገቱ ዋነኛ አንቀሳቃሽ ኃይል ሆኖ እየመጣ ይገኛል። ይህም መንግሥት ለማኑፋክቸሪንግ፣ ለኢንዱስትሪ ልማት፣ ለዕሴት ጭማሪና ለውጭ ገበያ ተኮር ምርቶች የሰጠውን ቀጣይነት ያለው ትኩረት ያሳያል።

​እነዚህ ውጤቶች እንዲሁ ግምቶች ብቻ ሳይሆኑ፤ በጠቅላይ ሚኒስትሩ የ100 ቀናት የሥራ አፈጻጸም ግምገማ ሥርዓት አማካኝነት ክትትል የሚደረግባቸው የተጠያቂነትና የታቀደ አመራር ፍሬዎች ናቸው። አጠቃላይ የወጪ ንግድ ገቢ 20 ቢሊዮን የአሜሪካ ዶላር ይደርሳል ተብሎ የሚጠበቅ ሲሆን፤ ይህም ከ2016 ዓ.ም. ወዲህ የ100 በመቶ ገደማ ጭማሪ አሳይቷል።

የዋጋ ግሽበትም ወደ ታች ማሽቆልቆሉን በመቀጠል አሁን ላይ ወደ አንድ አሐዝ ደረጃ እየተቃረበ ይገኛል፤ ይህም በቅርብ ዓመታት ውስጥ በቤተሰቦችና በንግዶች ላይ ከባድ ጫና ፈጥሮ ከነበረው ባለ ሁለት አሐዝ የዋጋ ግሽበት አንጻር ትልቅ መሻሻል ነው። ይህ ስኬት የተመዘገበው ዓለም አቀፍ የኃይል አቅርቦትና ሌሎች ስትራቴጂካዊ ቁሳቁሶችን ገበያ ያናጋው የመካከለኛው ምስራቅ ወቅታዊ ጂኦፖለቲካዊ ውጥረት ጨምሮ፤ ውጫዊ ጫናዎች በነበሩበት ወቅት ነው።

​የሀገር በቀል ኢኮኖሚ ማሻሻያ አጀንዳ ከተጀመረ ወዲህ መንግሥት ከውጭ ምንጮች ምንም ዓይነት አዲስ የንግድ ብድር ስምምነት ያላደረገ ሲሆን፤ ይህም የሀገሪቱን የብድር ዕዳ ጫና በከፍተኛ ሁኔታ አቅልሎታል። ከእነዚህ ቁጥሮች በስተጀርባ ኢትዮጵያውያን በዓይናቸው የሚያዩትና በእጃቸው የሚዳስሱት ተጨባጭ ለውጥ አለ። ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ለመኖሪያ ቤቶች፣ ለንግድ ተቋማትና ለጎረቤት ሀገራት የኤሌክትሪክ ኃይል እያመነጨ ይገኛል። ይህ ግድብ በራሳቸው በኢትዮጵያውያን የተደገፈ፣ በኢትዮጵያውያን መሐንዲሶች የተገነባ እና ቀጣይነት የነበረውን ውጫዊ

ጫናዎችን ተቋቁሞ የተጠናቀቀ ነው። ከሃይድሮ ፓወር ጎን ለጎን፤ በኢትዮጵያ ሶማሌ ክልል የሚገኘውን የአይሻ ሁለት የንፋስ ኃይል ማመንጫ እና በአርሲ ዞን የሚገኘውን የአሰላ የንፋስ ኃይል ማመንጫ ፕሮጀክቶች፤ በመሳሰሉ ሥራዎች ታዳሽ ኃይል አቅርቦቷን እያሰፋች ሲሆን፤ ይህም የቀጣናዊ ኢነርጂ ትብብርን እያሳደገ የብሔራዊ ኃይል አቅርቦት መረቡን የመቋቋም ዐቅም ያጠናክራል። በአፍሪካ አህጉር ታሪክ ውስጥ ትልቁ የመሠረተ ልማት ኢንቨስትመንት አንዱ የሆነው የቢሾፍቱ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ፕሮጀክት የመሠረት ድንጋይ ተጥሎ ግንባታው ተጀምሯል። እነዚህ ምኞቶች አይደሉም፤ ተጨባጭ ሐቆች ናቸው።

​ግብርና፣ አምራች ኢንዱስትሪና ቴክኖሎጂ

በግብርናው ዘርፍ፤ የመንግሥት የምግብ ሉዓላዊነት አጀንዳ ወቅታዊ ለውጦችን ሳይሆን መዋቅራዊ ውጤቶችን እያስገኘ ቀጥሏል። በሶማሌ ክልል የጎዴ ዩሪያ ማዳበሪያ ፋብሪካን ለመገንባት ከአሊኮ ዳንጎቴ ግሩፕ ጋር የተፈረመው አጋርነት የዘመኑ ጉልህ የኢንዱስትሪ ኢንቨስትመንቶች አንዱ ማረጋገጫ ነው። ፋብሪካው በዓመት 3 ሚሊዮን ሜትሪክ ቶን ዩሪያ የማምረት አቅም እንዲኖረው ታቅዶ እየተገነባ ሲሆን፤ ይህም ኢትዮጵያን በዓለም ትላልቅ ማዳበሪያ አምራች ሀገራት ተርታ ያሰልፋታል።

ጠቅላይ ሚኒስትሩ ግንቦት 9 ቀን 2018 ዓ.ም. የፕሮጀክቱን የግንባታ ሂደት በጎበኙበት ወቅት እንደገለጹት፤ “ይህ ፕሮጀክት በግብርና ትራንስፎርሜሽን፣ በምግብ ዋስትና፣ በኢንዱስትሪ ዕድገትና በኢኮኖሚ ራስን መቻል ላይ የተደረገ ስትራቴጂካዊ ኢንቨስትመንት ነው” ብለዋል። አስተማማኝ ባልሆነና ውድ በሆነ የማዳበሪያ አቅርቦት ለረጅም ጊዜ ለተገደቡት ኢትዮጵያውያን አምራቾች የዚህ ፕሮጀክት ፋይዳ ፈጣንና ተጨባጭ ነው።
​ከዚህ ምርጫ ጥቂት ቀናት ቀደም ብሎ ጠቅላይ ሚኒስትሩ ግንቦት 19 ቀን 2018 ዓ.ም. በነገሌ ቦረና ገዳ አውሮፕላን ማረፊያ ምርቃት ላይ ሲገኑ የታየው ተምሳሌትነት ለቦረና ሕዝብ ትልቅ ትርጉም ነበረው። ይህ ዞን በዓለም አቀፍ ደረጃ የሚታወቅበት ስም የሀገርን አንገት ያስደፋ እንደነበር የቅርብ ጊዜ ትውስታ ሲሆን፤ እርሱም ድርቅ ነው።

ለሦስት ተከታታይ ዓመታት የዝናብ መጥፋት በሚሊዮን የሚቆጠሩ ከብቶችን የገደለ፣ ቤተሰቦች ለውኃ ፍለጋ በመቶዎች የሚቆጠሩ ኪሎ ሜትሮችን እንዲጓዙ ያስገደደ፣ እንዲሁም በእነዚህ የግጦሽ መሬቶች ላይ ለዘመናት ራሳቸውን ችለው የኖሩ ማኅበረሰቦችን ለአስቸኳይ የምግብ እርዳታ እጅ እንዲዘረጉ አድርጎ ነበር። ዓለም የሚያውቃት ቦረና እርሷ ነበረች።
​የጠቅላይ ሚኒስትሩ የግንቦት ወር ጉብኝት ግን የተለየ ታሪክ አሳይቷል።

አሁን ላይ ለአርብቶ አደር ማኅበረሰቦችና ለከብቶቻቸው ንጹሕ ውኃ እያቀረቡ ያሉትን የውኃና የመስኖ መሠረተ ልማቶችን የገመገሙ ሲሆን፤ ከጥቂት ዓመታት በፊት አቧራ ብቻ በነበረው መሬት ላይ የክላስተር እርሻዎችን ጎብኝተዋል፤ በያቤሎ የባህል ማዕከል መርቀዋል፤ እንዲሁም በአየር ንብረት ሁኔታዎች ምክንያት ቀድሞ ተገልሎ ለነበረው ቀጣና ዓመቱን ሙሉ ትስስር የሚፈጥር አውሮፕላን ማረፊያ መርቀው ከፍተዋል።

​የአምራች ዘርፉም ተመሳሳይ የለውጥ ታሪክ አለው። በግንቦት 2018 ዓ.ም. በተካሄደው 4ኛው ኢትዮጵያ ታምርት ኤክስፖ ላይ፤ መንግሥት ለአራት ዓመታት የተመዘገበውን ቀጣይነት ያለው የኢንዱስትሪ መስፋፋት ውጤቶች አቅርቧል። የአምራች ዘርፉ የግብአት አቅርቦት በዓመት 9 ሚሊዮን ቶን ወደ 15 ሚሊዮን ቶን አድጓል። የምርት አቅም አጠቃቀም ከ47 በመቶ ወደ 67 በመቶ ከፍ ማለቱን፣ የማኑፋክቸሪንግ ዕድገት ከ4.8 በመቶ ወደ 10.7 በመቶ ማደጉን፣ እንዲሁም ለአነስተኛና መካከለኛ ኢንተርፕራይዞች የሚቀርበው ፋይናንስ ከ8.1 ቢሊዮን ብር ወደ 50 ቢሊዮን ብር ማደጉን ያሳያል።

እነዚህ ስኬቶች በሀገር ውስጥ ምርት ላይ በከፍተኛ ሁኔታ እየተንጸባረቁ ይገኛሉ። ኤክስፖው በተጠናቀቀ በሃያ ቀናት ውስጥ ጠቅላይ ሚኒስትሩ በዘጠኝ ወራት ውስጥ ብቻ ተጠናቆ ከ80 በመቶ በላይ ጥሬ ዕቃውን ከሀገር ውስጥ የሚያገኘውን ግዙፍ የኢንዱስትሪ ኢንቨስትመንት «ግራንዲዩር የሴራሚክ ማኑፋክቸሪንግ» ፋብሪካን በሞጆ ከተማ መርቀዋል። ቀደም ሲል በገቢ የሴራሚክ ምርቶች ላይ ጥገኛ የነበረችው ኢትዮጵያ አሁን ላይ የሴራሚክ ምርቶችን ከውጭ ማስገባት ሙሉ በሙሉ ለማቆምና ለውጭ ገበያ የሚሆን ምርት ለማስፋፋት እየተዘጋጀች ትገኛለች።

​በቴክኖሎጂው ዘርፍም፤ ዘመናዊ ልማት ከጊዜ ወደ ጊዜ በዳታ፣ በፈጠራና በዲጂታል ሥርዓቶች የሚወሰን መሆኑን በመገንዘብ፤ መንግሥት ኢትዮጵያን ሰው ሠራሽ አስተውሎት እና የኢንዱስትሪ 5.0 ማሕቀፎችን ቀድመው ከተገበሩ ሀገራት ተርታ እያሰለፋት ይገኛል።

​የጽንፈኝነትን ፖለቲካ ውድቅ ማድረግ

በኦነግ ሸኔ ዐማጽያን በንጹሐን ዜጎች ላይ በተለይም በሃይማኖት ተቋማት ውስጥ ዒላማ ተደርገው የተፈጸሙ ጥቃቶችን ተከተሎ፤ የቤተሰብ እና የወዳጆቻቸውን ሕይወት ላጡ፣ የአካል ጉዳት ለደረሰባቸው እና የቤት ንብረታቸው ለወደመባቸው በአርሲ ዞን ለሚገኙ ወገኖቻችን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ በኢትዮጵያ መንግሥት ስም የተሰማቸውን ጥልቅ ኀዘን ይገልጻሉ።
​እነዚህ ጥቃቶች የሀገሪቱን ብሔራዊ ዕድገት ለማደናቀፍ ከሚሹ አካላት፣ በአማራ ክልል ከሚንቀሳቀሱ የሀገር ውስጥ አማፂ ቡድኖች እና ለሀገሪቱ ሁለንተናዊ ዕድገት ጥላቻ ካላቸው የውጭ ኃይሎች ጋር በጥምረት የተከናወኑ ሲሆኑ፤ ዓላማቸውም በኢትዮጵያ አለመረጋጋትንና የምርጫ መስተጓጎልን ለመፍጠር ሲደረግ የነበረ የጥፋት ውጥን ተከታይ ነው።

​መንግሥት 7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ያለ አንዳች የፀጥታ ችግር ፍትሐዊና አሳታፊ ሆኖ እንዲጠናቀቅ ከአንድ ዓመት በላይ የዘለቀ ልዩ ትኩረትና ዝግጅት በማድረግ በቁርጠኝነት ሲሠራ ቆይቷል። በሌላ በኩል የጥፋት ኃይሎች ከባዕዳን ጋር 'ፅምዶ' የሚል ቁርኝት በመፍጠር ዕኩይ ዓላማቸውን ለማሳካት ሰፊ የጥፋት ዝግጅት ሲያደርጉ ቆይተዋል፣ ሀገራዊ ምርጫው እንዳይከናወን ሰፊ ርብርብ አድርገዋል። በተጨባጭም በቅድመ ምርጫ እና በምርጫ ወቅት የዜጎችን የመምረጥ መብትና ነጻነት ለመጋፋትና ለማደናቀፍ አለን የሚሉትን የጥፋት እጅ ዘርግተዋል።

​እነዚህ የጠላት ኃይሎች በመደጋገፍና በመናበብ ዐመፅና ሁከት ለማነሳሳት፣ ከተሞችን በሽብር ጥቃት ለማወክ፣ በመንገዶች የደፈጣ ጥቃት በመፈጸም እንቅስቃሴ ለመገደብ እና በተወሰኑ አካባቢዎች ዒላማ አድርገው ነጥሎ ለማጥቃት ተንቀሳቅሰዋል። እንደ ማሳያ የጦር መሣሪያ፣ ተተኳሾችንና ሌሎች ሎጀስቲክሶችን በድጋፍ በማቅረብ በደቡባዊ ትግራይ በሚገኙ አዋሳኝ የአማራ ክልል አንዳንድ ቦታዎች ላይ ትንኮሳ ፈጽመዋል፣ በአማራ ክልል ባሕር ዳር፣ ጎንደር፣ ደብረ ብርሃን እና ወልድያ ከተሞችን ጨምሮ በክልሉ ዋና ዋና ከተሞች እና ሲቪሎች ላይ ዒላማ በማድረግ ያካሄደው የሽብር እንቅስቃሴና ዝግጅት፣ በአዲስ አበባ ከተማ ባደራጃቸው የኅቡዕ ሴሎች አማካኝነት በተመረጡ አከባቢዎች ላይ ጥቃት እንዲፈጸም ተንቀሳቅሰው የነበረ ቢሆንም ይሄን የጥፋት ሴራ እና ድርጊት እንዲከሽፍ ማድረግ ተችሏል።

​በተመሳሳይ በኦሮሚያ ክልል የሸኔ ሽብር ቡድን ከጽንፈኛው ፋኖ ታጣቂ ቡድን ጋር በመናበብ በአንዳንድ አካባቢዎች መንገዶችን በመዝጋት እንቅስቃሴ ለማስቆምና ለማስተጓጎል ፍላጎት የተንቀሳቀሰ ቢሆንም በጸጥታ ኃይሉ በተወሰደበት የተጠናከረ እርምጃ ፍላጎቱን ማሳካት አልቻለም። ቡድኑ በፀጥታ ኃይሉ የተወሰደበትን ርምጃ መቋቋም ባለመቻሉ እና ፍላጎቱን ማሳካት ባለመቻሉ ስስ ዒላማዎች ላይ ያተኮረ ርምጃ በመውሰድ የሃይማኖት እና የብሔር ግጭት ለመቀስቀስ በማለም በአርሲ ዞን አሰኮ እና አካባቢው ጥቃት በመፈጸም ሁሉን አይነት የጥፋት ርብርብ ያደረገ ቢሆንም ሁኔታውን በመቆጣጠር ፀጥታ ኃይላችን በእነዚህ ኃይሎች ላይ የተቀናጀ ርምጃ እየወሰደ ይገኛል።

​መንግሥት መሰል ሥጋቶችን በንቃት በመከታተል ላይ ሲሆን፣ በምርጫው ወቅትም በብዙ የሀገሪቱ አካባቢዎች የተቀነባበሩ ተመሳሳይ ዕቅዶችን በስኬት ማክሸፍ ችሏል። በንጹሐን ዜጎች ላይ የሚፈጸሙ ጥቃቶችን፤ ፍርሃትና ክፍፍልን ከሚያጎሉ የሚዲያ ዘመቻዎች ጋር በማስተሣሠር የተቀነባበረው ይህ እኩይ ተግባር፤ በመንግሥት የደኅንነት መዋቅርና ኦፕሬሽኖች አማካኝነት በከፍተኛ ሁኔታ እንዲስተጓጎል ተደርጓል። ብሔራዊ እና ሃይማኖታዊ ክፍፍልን ለመዝራት የኃይል ጥቃትን እና ውድመትን እንደ መሣሪያ የሚጠቀሙ አካላት በሁሉም ኢትዮጵያውያን ዘንድ በግልጽ ሊወገዙ ይገባል። መሰል ተግባሮች በኢትዮጵያ ውስጥ ምንም ዓይነት የወደፊት ዕድል እንደሌላቸው ለማሳየት የተቀናጀ ብሔራዊ ምላሽ በመስጠት ወሳኝ ርምጃዎችን ይቀጥላል።

​በንጹሐን ዜጎች ላይ ጥቃት የሚፈጸሙ አካላት፣ ድርጊታቸውን ምክንያታዊ ለማስመሰል ምንም ዓይነት የፖለቲካ ንግግር ቢጠቀሙ፤ ወሳኝ ዓላማን እያሳኩ ሳይሆን ወንጀል እየፈጸሙ ነው። የፖለቲካ ቅሬታዎች በኢትዮጵያ ሕገ መንግሥታዊ ሥርዓት፣ በብሔራዊ ምክክር ሂደት እና በዴሞክራሲያዊ ተቋማት አማካኝነት መፍትሔ ሊያገኙ የሚችሉ እና ሊያገኙ የሚገባቸው ናቸው።

​ጽንፈኝነት ግን በኢትዮጵያ ምድር ፈጽሞ ቦታ የለውም::

​የጠቅላይ ሚኒስትር ጽ/ቤት

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ልዑካን ቡድን በምሥራቅ አርሲ የተፈጸመውን ጥቃት አስመልክቶ ከመንግሥት አካላት ጋር ተወያየ።በምሥራቅ አርሲ ዞን በአሰኮ፣ በሺርካ እና በሆንቆሎ ዋ...
05/06/2026

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ልዑካን ቡድን በምሥራቅ አርሲ የተፈጸመውን ጥቃት አስመልክቶ ከመንግሥት አካላት ጋር ተወያየ።

በምሥራቅ አርሲ ዞን በአሰኮ፣ በሺርካ እና በሆንቆሎ ዋቤ ወረዳዎች በኦርቶዶክሳውያን ወገኖቻችን ላይ የደረሰውን ጥቃትና የቤተክርስቲያን መቃጠል ተከትሎ፣ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ከፍተኛ ልዑካን ቡድን ከሰላም ሚኒስቴር እና ከኦሮሚያ ክልል መንግሥት ከፍተኛ ኃላፊዎች ጋር የውይይት መድረክ አካሂዷል።

በውይይቱ ላይ የጠቅላይ ቤተ ክህነት ዋና ሥራ አስኪያጅ ብፁዕ አቡነ ሳዊሮስ እና የቅዱስ ሲኖዶስ ዋና ጸሐፊ ብፁዕ አቡነ ዲዮስቆሮስ የተመሩት አባቶች፤ በምዕመናን ላይ የደረሰው ሕልፈተ ሕይወት እጅግ አሳዛኝ መሆኑን ገልጸዋል። መንግሥት የችግሩን ሥር መሰረት በማጥናት ለዜጎች አስተማማኝ ሰላም እንዲያረጋግጥ አጥብቀው አሳስበዋል።

የልዑካን ቡድኑ ያቀረባቸው ዋና ዋና ጥያቄዎች፡-

1. ከቀያቸው የተፈናቀሉ ወገኖች ወደ ቀድሞ ቦታቸው የሚመለሱበትና የሚቋቋሙበት ዘላቂ መፍትሔ እንዲመቻች፣

2. ጥቃቱን የፈጸሙ አካላት በሕግ አደባባይ ቀርበው ተገቢውን ቅጣት እንዲያገኙ፣

3. በቀጣይ መሰል አሳዛኝ ድርጊቶች እንዳይደገሙ መንግሥት የደኅንነት ሥራውን እንዲያጠናክር፣

የምሥራቅ አርሲና የጅግጅጋ አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ብፁዕ አቡነ ኤልሳዕ፣ በሥፍራው የደረሰውን ጉዳት በቁጥር በተደገፈ መረጃ ለውይይቱ ተሳታፊዎች አቅርበዋል።

በተመሳሳይ፣ የሰላም ሚኒስትሩ አቶ መሐመድ እድሪስ በበኩላቸው፤ መንግሥት ጉዳዩን በቅርበት እየተከታተለ መሆኑን በመግለጽ፣ አስቸኳይ አጣሪ ቡድን ወደ ስፍራው መላኩን እና አጣሪው በሚያቀርበው ሪፖርት መሠረት ሕጋዊ እርምጃዎች እንደሚወሰዱ አረጋግጠዋል።

ከኦሮሚያ ክልል መንግሥትና ከብልጽግና ፓርቲ አመራሮች ጋር በተደረገው ውይይትም፣ የክልሉ አመራሮች በስፍራው የተከሰተውን ግጭት ለመቆጣጠር ከፍተኛ ተጋድሎ ማድረጋቸውን ጠቁመዋል። መንግሥት ለተጎጂዎች የሚደረገውን ድጋፍ እንደሚያግዝም ቃል ገብተዋል።

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ቋሚ ሲኖዶስ በበኩሉ፣ የተጎዱትን ወገኖች ለመደገፍ፣ አብያተ ክርስቲያናትን መልሶ ለመገንባት እና የሰላም ስራዎችን ለማጠናከር አስፈላጊውን ሁሉ እንደሚያደርግ በውይይቱ ወቅት ተመላክቷል።

መረጃው፡ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን የሕዝብ ግንኙነት መምሪያ ነው።

ተጨማሪ መረጃዎችን ለማግኘት፡-

•ፌስቡክ፡-https://web.facebook.com/HabeshaTech
• ፌስቡክ፡-https://www.facebook.com/AbayTubeEt

• ቴሌግራም፦https://t.me/HabeshaTechHubs
• ቴሌግራም፦https://t.me/HabeshaUpdate

ገና ስንት ሰው መሞት አለበት?" — አርቲስት ማራማዊት በወቅታዊው ቀውስ ላይ ዝምታዋን ሰበረች፤ ለሰላም ጥሪ አቀረበችታዋቂዋ አርቲስት ማራማዊት በንፁሃን ተጎጂዎች ስም ፍትህና ሰላም እንዲሰፍ...
05/06/2026

ገና ስንት ሰው መሞት አለበት?" — አርቲስት ማራማዊት በወቅታዊው ቀውስ ላይ ዝምታዋን ሰበረች፤ ለሰላም ጥሪ አቀረበች

ታዋቂዋ አርቲስት ማራማዊት በንፁሃን ተጎጂዎች ስም ፍትህና ሰላም እንዲሰፍን ጠይቃለች።

ድምፅ አልባ ለሆኑት በመቆም የተሰማትን ጥልቅ ሀዘን እንዲህ ስትል ገልጻለች፦

ዛሬ በከባድ ሀዘን ተሞልቼ፣ የህዝባችንን ስቃይ ችላ ማለት እንደማይችል አንድ የሰው ልጅ ከፊታችሁ ቆሜያለሁ።

ገና ስንት ሰው መሞት አለበት? ገና ስንት አብያተ ክርስቲያናት መቃጠል አለባቸው? ይህ የታሪካችን፣ የእምነታችን እና የህዝባችን መጥፋት ነው።

እኔ የምናገረው ለንጹሃኑ ነው። የምናገረው ለጠፉት ወገኖቻችን ነው። ለተቀጠፈው ህይወት ሁሉ፣ ለፈረሰው ቤተሰብ ሁሉ እናገራለሁ።

ድምፅ ለሌላቸው፣ ለተጎጂዎች፣ እንዲሁም በፍርሃት ለሚኖረው ማህበረሰብ ድምፄን አሰማለሁ።

መናገር ለማይችሉት ድምፄን ከፍ አደርጋለሁ። ዝም ማለት አንችልም። ሰላም፣ ፍትህ እና ሰብአዊነት እንዲሰፍን በአንድነት መጠየቅ አለብን።"

Please፣ ቤተክርስቲያኖቻችንን አትንኩብን።

* ማረፊያዎቻችን ናቸው፣
* መደበቂያዎቻችን ናቸው፣
* ሰላም ማግኛዎቻችን ናቸው።

እባካችሁ ቤተክርስቲያኖቻችንን ተዉልን፣ ልጆቻችንን አትንኩብን።."

©️ማራማዊት

ተጨማሪ መረጃዎችን ለማግኘት፡-

•ፌስቡክ፡-https://web.facebook.com/HabeshaTech
• ፌስቡክ፡-https://www.facebook.com/AbayTubeEt

• ቴሌግራም፦https://t.me/HabeshaTechHubs
• ቴሌግራም፦https://t.me/HabeshaUpdate

ተሰርዟል........አርቲስት ሄኖክ ድንቁ (ድንቁ) በአርሰናል ደጋፊዎች ታቅዶ የነበረውን የምስጋናና የሽልማት መርሐ-ግብር መሰረዙን አሳወቀ::ታዋቂው አርቲስትና የአርሰናል እግርኳስ ክለብ ደ...
05/06/2026

ተሰርዟል........

አርቲስት ሄኖክ ድንቁ (ድንቁ) በአርሰናል ደጋፊዎች ታቅዶ የነበረውን የምስጋናና የሽልማት መርሐ-ግብር መሰረዙን አሳወቀ::

ታዋቂው አርቲስትና የአርሰናል እግርኳስ ክለብ ደጋፊ ሄኖክ ድንቁ፣ በእሁድ ዕለት በአራት ኪሎ ዘመን ሲኒማ ሊካሄድ ታቅዶ የነበረውን የክለቡን የዋንጫ ድል ማክበሪያና የማሊያ ስጦታ (Giveaway) መርሐ-ግብር መሰረዙን አስታወቀ።

አርቲስቱ ውሳኔውን ያስተላለፈው፣ በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ላይ በደረሰው የሐዘን ወቅት እና ሀገራዊ ሁኔታን ከግምት በማስገባት ነው። ይህንን አሳዛኝ ክስተት ተከትሎ፣ ከደስታ መግለጫ ይልቅ

ለቤተክርስቲያኒቱና ለተጎጂ ወገኖች አክብሮት ማሳየት ተገቢ መሆኑን በመግለጽ ፕሮግራሙን መሰረዙን ገልጿል።
በዚሁ መሰረት፣ ቀደም ብለው በቴሌብር (Telebir) አማካኝነት ትኬት የቆረጡ ደጋፊዎች፣ የክፍያ ማረጋገጫ (Screenshot) በመያዝ በቴሌግራም (Telegram) አድራሻችን በመላክ ተመላሽ እንዲያደርጉ ጥሪ ቀርቧል።

አርቲስት ሄኖክ ድንቁ፣ ለተፈጠረው መስተጓጎል አክብሮት በመስጠት ሁሉም ደጋፊዎች መረጃውን ለሌሎች እንዲያጋሩ (Share እንዲያደርጉ) ጠይቋል።

⚽️⚽️⚽️

ተጨማሪ መረጃዎችን ለማግኘት፡-

•ፌስቡክ፡-https://web.facebook.com/HabeshaTech
• ፌስቡክ፡-https://www.facebook.com/AbayTubeEt

• ቴሌግራም፦https://t.me/HabeshaTechHubs
• ቴሌግራም፦https://t.me/HabeshaUpdate

''ሰውየውን ማግኘት እፈልጋለሁ''  | የአሜሪካው ፕሬዝደንት ዶናልድ ትራምፕ ከኢራኑ ከፍተኛ መንፈሳዊ መሪ ሞጅታባ ኻሚኒ ጋር ቀጥተኛ ግንኙነት ለመፍጠር ፍላጎት እንዳላቸው የገለጹ ሲሆን፣ የ...
05/06/2026

''ሰውየውን ማግኘት እፈልጋለሁ''

| የአሜሪካው ፕሬዝደንት ዶናልድ ትራምፕ ከኢራኑ ከፍተኛ መንፈሳዊ መሪ ሞጅታባ ኻሚኒ ጋር ቀጥተኛ ግንኙነት ለመፍጠር ፍላጎት እንዳላቸው የገለጹ ሲሆን፣ የውይይቱ መሳካት ግን በሁለቱ ሀገራት መካከል በተጀመሩት ስምምነቶች ውጤት ላይ እንደሚወሰን አስታውቀዋል።

​ፕሬዝደንት ትራምፕ በነጩ ቤተ መንግስት በሰጡት ቃለ ምልልስ፣ የኢራንን ሃይማኖታዊ መሪ ለማግኘት ፍላጎት እንዳላቸውና ስብሰባው ሊካሄድ የሚችለው ዋሽንግተንና ቴህራን በኒውክሌር ፕሮግራም፣ በዩራኒየም ክምችት፣ በክልላዊ ደህንነትና በተኩስ አቁም ጉዳዮች ላይ ስምምነት ላይ መድረስ ሲችሉ ብቻ መሆኑን አስገንዝበዋል።

​ከ1979 የኢራን አብዮት በኋላ በሁለቱ ሀገራት መካከል የነበረውን የረጅም ጊዜ ውጥረት ከግምት ውስጥ በማስገባት፣ ይህ የታሰበው መገናኘት እውን ቢሆን በዓለም አቀፍ ፖለቲካ ላይ ታሪካዊ ለውጥ ሊያመጣ እንደሚችል ተነግሯል።

ተጨማሪ መረጃዎችን ለማግኘት፡-

•ፌስቡክ፡-https://web.facebook.com/HabeshaTech
• ፌስቡክ፡-https://www.facebook.com/AbayTubeEt

• ቴሌግራም፦https://t.me/HabeshaTechHubs
• ቴሌግራም፦https://t.me/HabeshaUpdate

​ #አሜሪካ #ኢራን #ዶናልድትራምፕ #ሞጅታባኻሚኒ #ዓለምአቀፍዲፕሎማሲ #የኒውክሌርውል #ዋሽንግተን #ቴህራን

በጣና ሐይቅ ገዳማት ላይ አደጋ ደረሰ ተብሎ በቲክቶክ የሚናፈሰው ወሬ ፍጹም ሃሰት መሆኑ ተረጋገጠበማህበራዊ ትስስር ገጾች (በተለይም በቲክቶክ) "በሃይቅ ላይ ፍንዳታና ከባድ የእሳት አደጋ ተ...
05/06/2026

በጣና ሐይቅ ገዳማት ላይ አደጋ ደረሰ ተብሎ በቲክቶክ የሚናፈሰው ወሬ ፍጹም ሃሰት መሆኑ ተረጋገጠ

በማህበራዊ ትስስር ገጾች (በተለይም በቲክቶክ) "በሃይቅ ላይ ፍንዳታና ከባድ የእሳት አደጋ ተከሰተ" በሚል እየተሰራጨ ያለው መረጃ መሠረተ ቢስ መሆኑን የገዳማት አባቶችና የአካባቢው ምንጮች አረጋገጡ።

ጉዳዩን አስመልክቶ የተደረገውን ማጣሪያ እና እውነተኛውን መረጃ ጋዜጣዊ ይዘት ባለው መልኩ እንደሚከተለው አቀናጅተነዋል።

የሃሰተኛው መረጃ መነሻና የፈጠረው ስጋት
ሰሞኑን (በተለይም በ27/09/2018 ዓ.ም) በርካታ የቲክቶክ ተጠቃሚዎች አንድ የእሳት ምስል በመጠቀም በጣና ሐይቅ ላይ አደጋ እንደደረሰ የሚያሳይ መረጃ ሲያሰራጩ ቆይተዋል።

ይህ ያልተጣራ ወሬ በሐይቁ ላይ የሚገኙ ታሪካዊ ገዳማት በእሳት እንደነደዱ አድርገው ያሰቡ በርካታ ምዕመናንን ለአላስፈላጊ ስጋትና ጭንቀት የዳረገ ሲሆን፣ ጉዳዩን ለማጣራትም ወደ ስፍራው የሚደውሉ ሰዎች ቁጥር ከፍተኛ ሆኗል።

ተጨባጩ እውነታ ምንድን ነው?

ቃጠሎው ከማንኛውም ድንገተኛ አደጋ ወይም ከገዳማቱ ጋር ምንም አይነት ግንኙነት የሌለው ሲሆን፣ የአካባቢው ማህበረሰብ አመታዊ የግብርና ትውፊት አካል ነው።

* ክስተቱ የተመዘገበው በጣና ሐይቅ ዳርቻ በተለምዶ አባ ገሪማ" ተብሎ በሚጠራው አካባቢ ነው።

* የዚህ አካባቢ ነዋሪዎች አመቱን ሙሉ የሐይቁን "ደንገል" በማጨድ ታንኳ የሚሰሩበት እንዲሁም ጨፌ በማዘጋጀትና በመሸጥ የሚተዳደሩበት ስፍራ ነው።

* ደንገል ተክሉን ለስራቸው የሚጠቀሙት የአካባቢው አርሶ አደሮች፣ ለቀጣዩ ዓመት አዲሱ ተክል በጥራትና በደንብ እንዲበቅልላቸው የደረቀውን አሮጌ ተክል ሆን ብለው በእሳት የማቃጠል የተለመደ ተግባር ያከናውናሉ።
ሰሞኑን የታየው እሳትም ይሄው የለመደው ቁጥጥር የሚደረግበት ቃጠሎ ነው።

"በጣና ሐይቅም ሆነ በውስጡ በሚገኙ ጥንታዊ ገዳማት ላይ የተከሰተ ምንም አይነት አደጋ የለም። ማህበረሰቡ በማህበራዊ ሚዲያ ላይ በሚለቀቁ ያልተረጋገጡና ህዝብን ለድንጋጤ በሚዳርጉ የሀሰት ወሬዎች እንዳይታለል እናሳስባለን።"

ስለሆነም ህዝበ ምዕመናን በማህበራዊ ሚዲያ የሚናፈሰውን ይህንን የተሳሳተ ወሬ ወደ ጎን በመተው ሙሉ በሙሉ ሊረጋጋ እንደሚገባ ተገልጿል።

ተጨማሪ መረጃዎችን ለማግኘት፡-

•ፌስቡክ፡-https://web.facebook.com/HabeshaTech
• ፌስቡክ፡-https://www.facebook.com/AbayTubeEt

• ቴሌግራም፦https://t.me/HabeshaTechHubs
• ቴሌግራም፦https://t.me/HabeshaUpdate

04/06/2026
የአለልኝ አዘነ ገዳዮች ተብለው የ16 እና 15 ዓመት እስራት ተፈርዶባቸው የነበሩት ግለሰቦች፣ በይግባኝ ሰሚ ችሎት በነፃ እንዲለቀቁ ተወሰነ።"   |የአለልኝ አዘነ ጉዳይ፡ የይግባኝ ሰሚው ች...
04/06/2026

የአለልኝ አዘነ ገዳዮች ተብለው የ16 እና 15 ዓመት እስራት ተፈርዶባቸው የነበሩት ግለሰቦች፣ በይግባኝ ሰሚ ችሎት በነፃ እንዲለቀቁ ተወሰነ።"

|የአለልኝ አዘነ ጉዳይ፡ የይግባኝ ሰሚው ችሎት ውሳኔ ቤተሰቡን ለከፍተኛ ሀዘን እና ድንጋጤ ዳርጓል

የኢትዮጵያ እግር ኳስ ማህበረሰብን በከፍተኛ ሁኔታ ያሳዘነው እና የብዙ ኢትዮጵያውያንን ልብ ሰርስሮ የገባው የሟች አለልኝ አዘነ የፍትሕ ሂደት፣ አሁን ላይ አሳዛኝ እና አነጋጋሪ ምዕራፍ ላይ ደርሷል።

ባለፈው ጊዜ በግድያ ወንጀል ጥፋተኛ ተብለው በቅደም ተከተል 16 እና 15 ዓመት ፅኑ እስራት ተፈርዶባቸው የነበሩት ወ/ሮ አደይ ጌታቸው እና ሉንጎ ሉቃስ፣ በይግባኝ ሰሚ ችሎት በነፃ እንዲሰናበቱ መወሰኑን የሟች ቤተሰቦች አረጋግጠዋል።

ይህ ውሳኔ ቤተሰቡን ከዚህ ቀደም ከነበሩበት ሀዘን ባሻገር፣ ለከፍተኛ የስነ-ልቦና ቀውስ እና ብስጭት ዳርጓቸዋል። የቤተሰብ አባላት እንደገለጹት፣ ወንጀሉ ተፈጽሞ፣ ጥፋተኞች ተለይተውና በፍርድ ቤት ውሳኔ ተላልፎባቸው የነበረ ቢሆንም፣ በይግባኝ ሰበብ እንዲህ በነፃ መለቀቃቸው ተቀባይነት የሌለው እና የፍትሕ ሥርዓቱን የሚያጠይቅ ሆኖ አግኝተውታል።

በችሎቱ ውሎ ወቅት የነበረው ውጥረት፣ የቤተሰቡ ለቅሶ እና ሰቆቃ፣ እንዲሁም በፍትሕ ሥርዓቱ ላይ የነበራቸው የመጨረሻ ተስፋ መሟጠጡ መላውን የፍትህ ናፋቂ ማህበረሰብ በእጅጉ አሳዝኗል።

ቤተሰቡ እንደገለጸው፣ ድርጊቱ የተፈጸመበት ቦታ እርባምንጭ ሆኖ ሳለ፣ የፍርድ ሂደቱ ወደ ወላይታ ሶዶ ተዛውሮ የወሰደው ቅርፅና ውጤት ለቤተሰቡ ድርብ ስቃይ ሆኗል።

ይህ ውሳኔ በኢትዮጵያ የፍትሕ ታሪክ ውስጥ ትልቅ ክርክር ሊያስነሳ እንደሚችል እየተነገረ ነው። በተለይም የወንጀል ድርጊት ተረጋግጦ በነበረበት መዝገብ ላይ እንዲህ ያለ የይግባኝ ውሳኔ መሰጠቱ፣ በፍትሕ ተቋማት ላይ ያለው የመተማመን ቀውስ እንዲባባስ ማድረጉ አልቀረም።

የሕግ ባለሙያዎች እንደሚናገሩት፣ ጉዳዩ በሰብአዊ መብት እና በሕግ የበላይነት መርህ መሠረት በሰፊው ሊጤን የሚገባው ሆኗል።

የሟች ቤተሰብ አባላት በከፍተኛ ሀዘን ውስጥ ይገኛሉ፤ መላው የኢትዮጵያ ህዝብ ከጎናቸው እንዲቆም እና የፍትሕ ጥያቄውን እንዲያቀናጅ ጥሪ አቅርበዋል።

©️ቤተሰብ

Address

Addis Ababa
Addis Ababa
1983/1110

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Abay Tube posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to Abay Tube:

Share