የአብነት መንደር /Abinet Vellage

የአብነት መንደር  /Abinet Vellage የተሻለ ሃሳብ ለወደፊቱ ህይወት!!

✴✅ አስተማሪ ታሪክ ✅✴✳ አይጧ የግድግዳውን ቀዳዳ በመጠቀም የቤቱ ባለቤት በታሸገ ካርቶን እቃ ይዞ ሲገባ ትመለከታለች፡፡ አይጧ “ዛሬ ደግሞ ምን አይነት ምግብ ይዞ መጣ!?” ብላ ተደስታለች...
29/10/2022

✴✅ አስተማሪ ታሪክ ✅✴

✳ አይጧ የግድግዳውን ቀዳዳ በመጠቀም የቤቱ ባለቤት በታሸገ ካርቶን እቃ ይዞ ሲገባ ትመለከታለች፡፡ አይጧ “ዛሬ ደግሞ ምን አይነት ምግብ ይዞ መጣ!?” ብላ ተደስታለች፤ ነገር ግን ሰውዬው ለባለቤቱ ሊያሳያት የታሸገውን ካርቶን ሲከፍተው ወጥመድ ነው፡፡ አይጧ ደነገጠች፤ ወዲያውኑ ወደ እርሻው ተመለሰችና ጮክ ብላ “በዚህ እርሻ ውስጥ የምትገኙ እንስሳቶች ሆይ! የአይጥ ወጥመድ እየተጠመደላችሁ ነው፤ ወጥመድ! መጥመድ!!” በማለት ትናዘዛለች፡፡

ይህን ድምፅ በንቃት የሰማችው ዶሮ ካጎነበሰችበት ቀና በማለት “አይጦ ላንቺ ምን ያህል እንደሚያስጨንቅሽ ይገባኛል፤ ነገር ግን እኔን አይመለከትም እዛው ጣጣሽን ቻይ” ትላታለች፡፡ መከራ የበዛበት አይጥ የቤቱ በግ ወደሚገኝበት ቦታ ትሄድና የቤቱ ባለቤት የአይጥ ወጥመድ ገዝቶ እንደመጣ ትነግረዋለች፡፡

በጉ በንቀት አይን እየተመለከታት “ይቅርታ አድርጊልኝ አይጦ ምንም ልረዳሽ አልችልም” ይላታል፡፡ እቤት ውስጥ ከሚኖሩት እንስሳቶች የቀረው አንድ በሬ ነበር፤ አይጦ እርሱንም እርዳታ ለመጠየቅ ወዳለበት ትሄዳለች፡፡ “ወጥመድ ወጥመድ የአይጥ ወጥመድ ይዘው መጡ” ትለዋለች፤ በሬው ምንም ሳይመስለው እየሳቀ “አይጦ ምን ነክቶሽ ነው! እኔ እንደሆን ቆዳዬን እንኳ አይጎዳውም፤ ጣጣሽን ቻይ” በማለት ያባርራታል፡፡

አይጧ በጣም ተበሳጭታ አንገቷን አቀርቅራ የገበሬውን ወጥመድ ብቻዋን ልትጋፈጥ ወደ ቤቷ ትመለሳለች፡፡ በዛው ቀን ምሽት ሰው ሁሉ በተኛበት ወጥመዱ ከፍተኛ ድምፅ አሰማ፡፡

የገበሬው ሚስት አስቸጋሪዋ አይጥ ተያዘችልኝ በሚል ሀሳብ ወጥመዱ ወዳለበት ስፍራ ታቀናለች፡፡ ጨለማ ነበርና ምን እንደተያዘም ሳታውቅ የአይጧ ጭራ መስሏት በወጥመዱ የተያዘውን አደገኛ እባብ አፉን ነበር የያዘችው፡፡ እባቡ ነከሳት ነደፋትም፡፡ ገበሬው በፍጥነት ወደ ሆስፒታል ይወስዳታል፤ ከታከመች በሗላ ወደ ቤት ይመልሳታል ነገር ግን አደገኛ ራስ ምታቱ አለቀቃትም፡፡

ዶሮ ደግሞ ለእንደዚህ አይነት ራስ ምታት ፍቱን መድሃኒት መሆኑ የምናውቀው ጉዳይ ነውና ገበሬው ቤት ውስጥ የምትገኘውን ዶሮ “ለመድሀኒትነት” አረዳት፡፡ ነገር ግን የገበሬው ሚስት ከህመሟ ልታገግም አልቻለችም፤ ህመሟ እየበረታ ሄደ፡፡ የአካባቢው ሰው ሊጠይቃት ይጎርፍ ጀመር፤ ገበሬው እነዚህን እንግዳ ያስተናግድበት ዘንድ በጉን አረደው፡፡ የገበሬው ሚስት ህመሟ በርትቶ ሆስፒታል ስትታከም ከቆየች በሗላ ትሞታለች፡፡ ታዲያ ህዝብ ሁሉ ሊያስቀብራት መጣ፤ አስቀበራትም፡፡ ከቀብር ሲመለሱ ገበሬው ለቀባሪዎች በሬውን አረደው፡፡

አይጧ ይህንን ድርጊት በሙሉ በዛቺ ግድግዳ ቀዳዳ እንደ ፊልም ትመለከት ነበር፡፡ በድርጊቱ በጣም አዘነች፡፡
ይህ አጭር ታሪክ ትልቅ ትምህር አለው፡፡ ለሌላ ጊዜ አንድ ሰው ችግር ላይ ነው ሲባል ሰምተን የኔ ችግር አይደለም በምንልበት ጊዜ አስታውሱ አንዱ ተጨቆነ ማለት ሁላችንም መጨቆናችን አይቀርም፡፡

ሁላችንም ህይወት በምትባል ጉዞ ላይ ተሳታፊዎች ነን፡፡ ታዲያ መንገዱ ላይ ዞር ዞር ብሎ በመቃኘት እርስ በርስ ልንረዳዳ ይገባል፤ አይመለከተንም ብለን ብናስብ እርዳታ ከመስጠት ወደ ሗላ ማለት የለብንም፡፡

ከሁሉም በላይ አዛኙን ፈጣሪም እናስብ ለሰው ልጅ ስታዝን ያዝንልሀል ስትረዳ ይረዳሀል ፈጣሪ በእዝነቱ ይመልከተን ለነዚህ ሰዎች ይህን መልዕክት እናስተላልፍ; በህይወታችን ለረዱን በሙሉ እርዳታቸው እንደጠቀመን ይወቁልን እዚህ አለም ላይ አጥብቀህ ልትይዘው የሚገባ ምርጥ ባህሪ-“ቅን አስተሳሰብ” ነውና፡፡


ሼርርርር

  ~~~1.ከተጋቡ በኅላ አንድ አካል ናቸው። (ማቴ 19:4-62.መፋታት ክልክል ነው። (ሚል2:14)3.አንድ ወንድ ለአንድ ሴት ። 1ኛ ቆሮ 7:24.የሚገባቸውን ሁሉ ማድረግ።5.ባልም ለሚስት...
12/10/2022

~~~

1.ከተጋቡ በኅላ አንድ አካል ናቸው። (ማቴ 19:4-6
2.መፋታት ክልክል ነው። (ሚል2:14)
3.አንድ ወንድ ለአንድ ሴት ። 1ኛ ቆሮ 7:2
4.የሚገባቸውን ሁሉ ማድረግ።
5.ባልም ለሚስትም በራሳቸሁ ሥልጣን የላቸሁም። 1ኛ ቆሮ 7:4
6.ኃላፊነትን መወጣት። ኤፌ5:20-23 ቆላ 3:18
7.ለጾምና ለጸሎት ካልሆነ አለመለያየት 1ኛ ቆሮ7:5
8.ሥጋዊ ጌጥ አለማብዛት ።1ኛ ጴጥ 3:1-4
9.ድንገተኛ ግጭት ቢከሰት ወዲያው መታረቅ።1ኛ ቆሮ 7:10-11
10.በሞት ካልሆነ አለመለያየት።1ኛ ቆሮ 7:39 እናሮሜ 7:2-3
ከሥጋዊ መንፈሳዊ የጋብቻ ዘመድ አለማግባት።ዘሌ 18:6-20 ዘሌ20:16-21፣ማር 6:17።

: #አታግባ
የህይወት ምንነት ሳታውቅ አታግባ
የትዳርን ምንነት ሳታውቅ አታግባ
የትዳር አጋርህን ሀቅ (መብት) ሳታዘጋጅ አታግባ
በችግር ሰዓት ህይወትን አብረህ ልትገፋ ምትችል ሴት ሳታገኝ አታግባ
ኃላፊነትህን እንዴት መወጣት እንዳለብህ ሳታቅ አታግባ
ለልጆችህ ተምሳሌት መሆን ሳትችል አታግባ

#ትዳር
ትዳር ማለት 1ወንድ አንድ ሴት
ትዳር ማለት 1እምነት አንድ እውነት
ትዳር ማለት 1እሳት አንድ ውሃ
ትዳር ማለት 1 ሙሉ አንድ ጎዶሎ
ትዳር ማለት 1መጥፎ አንድ ጥሩ
ትዳር ማለት 1 ጉልቻ አንድ ድስጥ
ትዳር ማለት 1ወንዝ አንድ ውሃ የሚቀዳ ቢሆንም
ካልተንከባክበውና ካልተቻቻልንበት ሊደርቅ የሚችል #ወራጅ

#ወንዝ ነው።
ደግ ሴትን ባሏ ያመሰግናታል፤
የሕይወት ዘመኑም እጥፍ ይሆናል።
ቅን ሴት ባሏን ደስ ታሰኘዋለች፤
ዘመኑንም በሰላም ይጨረሳል።
የደግ ሴት ዕድሏ ያማረ ነው፤
እግዚአብሔርን የሚፈራ ሰውንም ወደ
ዕድሉ ታደረሰዋለች
መፀሐፈ ሲራክ 26:1~3

በፍቅር ያማረ ትዳር ሠላም ያለው እውነተኛ ፍቅር ፈጣሪ ይስጠን

በህይወት እያለህ መልካም ስራ-" በምትሞትበት ጊዜ   በመጀመሪያ  ስምህ ይቀየራል  ስምህም ሬሳ ትባላለች" እከሌ/እከሊት ሳይሆን   ሬሳዉ አልወጣም ወይ ትባላለህ ።  የቅርብ ሰዉ እንኳን  ...
10/10/2022

በህይወት እያለህ መልካም ስራ

-" በምትሞትበት ጊዜ በመጀመሪያ ስምህ ይቀየራል ስምህም ሬሳ ትባላለች" እከሌ/እከሊት ሳይሆን ሬሳዉ አልወጣም ወይ ትባላለህ ። የቅርብ ሰዉ እንኳን ቢሆን
ከጎንህ ሊሆን ይፈራል" ወደ መቃብር ስፍራ ወስደዉ አጣድፈዉ ከቀበሩህ በሗላ ብቻህን ጥለዉህ ለመሔድ ይቻኮላሉ።

ላይጠቅምህ አብሬህ ካልሔድኩ እያለ የሚያለቅሱልህ እንኳን ቢኖር ቀብሮህ ተሎ ይሸሻል።ቀብረዉህ እደተመለሱ ንብረት ካለህ ለመከፋፈል ይጣደፋሉ ። ከሳምንት በሗላ ጭራሹኑ ከምድር ያልኖርክ እስኪመስል ድረስ በአብዛኞቹ ትረሳለህ ።

የቅርብ ወዳጆችህ እንኳን ቢሆኑ ሀዘኑ በልባቸዉ ጥቂት ወራት ያክል ቢቆይ ነዉ ።በቃ ምድር ላይ የነበረህ ቆይታ በዚህ መልኩ ይጠናቀቃል ።ፍራሽህ አፈር ትራስህ ደሞ ድንጋይ ይሆናል😌 ይሔዉ ነዉ ።

ያኔ ማንም ምንም አይጠቅምህም መልካም ስራህ ብቻ🙌

በዚች አለም ላይ እድለኛ ሠዉ ማለት በህይወት እያለ ወደ ፈጣሪዉ የተመለሠ ሰዉ ነዉ 🙌"👏
ቪዲዮ ለማየት ሊንኩን ይጫኑ👉https://youtu.be/bNmCPSOU7S0

ኖር❗ለምን እንላለን❓ ፣  በእግዜር❗ለምን እንባላለን❓    እንግዳ ወይም የምናውቀው ይኹን የማናውቀው ሰው ሲገባ ሲወጣ ፣ እኛ ቁጭ ብለን እርሱ ቆሞ ከኾነ ፣ ከመቀመጫችን ጥቂት ከፍ ከወገባ...
09/10/2022

ኖር❗ለምን እንላለን❓ ፣ በእግዜር❗ለምን እንባላለን❓

እንግዳ ወይም የምናውቀው ይኹን የማናውቀው ሰው ሲገባ ሲወጣ ፣ እኛ ቁጭ ብለን እርሱ ቆሞ ከኾነ ፣ ከመቀመጫችን ጥቂት ከፍ ከወገባችን እና አንገታችን ዝቅ ብለን "ኖር❗" እንለዋለን።
እርሱም እንደዛው በክብር ዝቅ ብሎ ፣ "በእግዜር" ብሎ ይመልስልናል።

ግን ለምን? ምንስ ማለት ነው?

በድሮ ጊዜ ኢትዮጵያ ሃገራችን ውስጥ እጅግ አስከፊ ቤተሰብ ከቤተሰብ የበታተነ ፣ ዘመድ ከአዝማድ የነጣጠለ ድርቅ ተከሰተ ።

የዛን ጊዜ ክፉ ዘመን ሰዎች እንደቅጠል ረገፉ ፣ መላእከ ሞት እስኪሰለቸው ነፍሳትን ነጠቀ ፣ በሕይወት የተረፉት በየፊናቸው ድርቁን ቸነፈሩን በዚኽም የሚመጣውን ሞት ሽሽት እግራቸው ወዳመራቸው ቀያቸውን ትተው ተሰደዱ።

ስዓታት ተቆጠሩ ፣ መሸም ነጋም ቀናት ተቆጠሩ ፣ ሳምንታት አልፈው ፣ ወራት እና አመታት እንደዘበት ነጎዱ ፣ ጊዜ ያልፋልና መልካሙ ቀን መጣ ከዚያ ክፉ ቀን የሸሹ ኹሉ ወደ ቀያቸው ሰፈራቸው መንደራቸው እና ቤታቸው ተመለሱ ፣

የሞተ ሞተ የተረፈ በየቤቱ "እንዴት አሳለፋችኹ?" ሊባባል በየቤቱ ሰፈር መንደሩ መጠያየቅ ጀመረ ፣

ሰው ኹሉ ሲገናኝ ፣ በአካለ ሥጋ ሲተያይ "በሕይወት አላችኹ❓" ተባብሎ መጠያየቅ ልማድ ሆነ።

ተጠያቂውም ሲመልስ " ኖርነ❗" ይላል፣
ይኽውም መትረፉን መኖሩን ለመናገር
"ኖርን ፣ ኖርነ❗" ይላል ። መላሹም "በእግዜር❗" ይላል ፣

"መኖራችን በእርሱ በኋያሉ በእግዚ"አብ"ሔር ባይኾን ፣ ሞተን ነበር ይመስገን " እንደማለት ነው።
"ኖርነ! በማን? በእግዜር!" የሚል አንድምታ አለው።

ይኽም ቆይቶ አኹን አኹን "ኖር❗" ሲባል ልጆች ያለው "በልጆቻችን!" ይላል ደመወዙ የሚያኖረው "ኖር!" ሲባል ፣ "በደመወዛችን!" ይላል፣ ጉልበተኛውም "ኖር!" ሲባል "በጉልበታችን!" ብሎ ጉራውን ይነዛል።

እናንተ ግን ተወዳጆች "ኖር❗" በሉ "

በቱካ ማቲዎስ

👉ፀፀት! ዶክተሩ በድንገት ተደውሎለት ለአስቸኳይ የቀዶ ህክምና በጥድፊያ ወደ ሆስፒታሉ እየገባ ነው። በተቻለው አቅም የስልክ ጥሪውን በአግባቡ አስተናግዷል። የህክምና ልብሱን በአስቸኳይ ቀይሮ...
06/10/2022

👉ፀፀት!

ዶክተሩ በድንገት ተደውሎለት ለአስቸኳይ የቀዶ ህክምና በጥድፊያ ወደ ሆስፒታሉ እየገባ ነው። በተቻለው አቅም የስልክ ጥሪውን በአግባቡ አስተናግዷል። የህክምና ልብሱን በአስቸኳይ ቀይሮ ወደ ቀዶ ጥገና ክፍል እያመራ ሳለ ኮሪደሩ ላይ የዶክተሩን መምጣት እየተንጎራደደ ይጠብቀው የነበረውን ሰው አገኘው።

"እንዴት ለመምጣት ይህን ያህል ግዜ ይፈጅብሀል? የልጄ ህይወት ልትጠፋ አደጋ ላይ እንዳለች አይታይህም? ህሊና የለህም?" ብሎ ዶክተሩ ላይ ጮኸበት።

ዶክተሩም በትንሹ ፈገግ አለና ,,,,
"አዝናለሁ ሆስፒታል ውስጥ አልነበርኩም። የስልኩን ጥሪ ከተቀበልኩ በሗላ በቻልኩት ፍጥነት እዚህ ለመድረስ ጥሬያለሁ አሁን አንተም ብትረጋጋ እኔም ስራዬን ብሰራ መልካም ነው" ብሎ ሊያረጋጋው ሞከረ።

ሰውየው ግን ,,,
"ተረጋጋ ነው ያልከው? ያንተ ልጅ ቢሆንስ አሁን እዚህ ክፍል ውስጥ ሆኖ ትረጋጋ ነበር? ልጅህ ቢሞት ምን ታደርግ ነበር?" አለ አባት በቁጣ።

ዶክተሩ አሁንም በትንሹ ፈገግ አለና እንዲህ መለሰለት
"የአምላክ ፈቃድ ይሁን። ዶክተር ህይወት ሊያራዝም ሊያጠፋም ሊተካም አይችልም ግን የቻልነውን ያህል እንጥራለን። እንደ አምላክ ፍቃድ ልጅህም ይድንልሀል አንተ ብቻ ተረጋጋ" አለው አሁንም ፈገግ እያለ።

ሰውየውም ,,,
" ባልገቡበት ጭንቀት አስተያየትና ምክር መስጠት ቀላል ነው" እያለ አጉረመረመ። ቀዶ ጥገናውም የተወሰነ ሰዓታትን ወስዶ በሰላም ተጠናቀቀ ዶክተሩ በደስታ እየተጣደፈ ከቀዶ ጥገናው ክፍል ውስጥ ወጣ።

ለአባትየውም ,,,,
"ፈጣሪ ይመስገን ልጅህ ተርፏል።" ብሎት የአባትየውን መልስ ሳይጠብቅ "ማንኛውም ጥያቄ ካለህ ሌሎች ረዳት ዶክተሮችን መጠየቅ ትችላህ።" ብሎት ዶክተሩ መንገዱን በሩጫ ቀጠለ።

የልጁም አባት "ለምንድነው ዶክተሩ እንደዚህ ስሜታዊና ችኩል የሆነው? ምናለ አሁን አንድ ደቂቃ ስለ ልጄ ሁኔታ ብጠይቀው?" ሲል ተናገረ።

ይህን የሰማችው ነርስ እንባ በጉንጮቿ እየጎረፈ ,,,,
"ትላንት ነበር የዶክተሩ ልጅ በመኪና አደጋ የሞተው። ለልጅህ ህክምና ስንደውልለት የልጁ ቀብር ላይ ነበር አሁን ያንተን ልጅ ህይወት ታደገ የራሱን ልጅ ደግሞ የቀብር ስርዓት ሊጨርስ በሩጫ ሄደ።" አለችው።

አባት ከሰዓታት በፊት ዶክተሩ ያሳየውን ፈገግታ እያሰበ ተንሰቀሰቀ።

"ቀድሞ መፍረድ ለህሊና ፀፀት ይዳርጋል"
❤ምንጭ facebook

27/09/2022
 #በድጋሚ አንድ ገበሬ በጣም የሚወደው ፈረሱ ይታመምበትና ወደ እንስሳት ሀኪም ጋር ይዞት ይሄዳል። ሀኪሙም ፈረሱ ጉረኖ ድረስ በመሄድ በሚገባ መረመረው።ለገበሬውም - "ተላላፊ በሽታ ስላለበት...
26/09/2022

#በድጋሚ



አንድ ገበሬ በጣም የሚወደው ፈረሱ ይታመምበትና ወደ እንስሳት ሀኪም ጋር ይዞት ይሄዳል። ሀኪሙም ፈረሱ ጉረኖ ድረስ በመሄድ በሚገባ መረመረው።

ለገበሬውም - "ተላላፊ በሽታ ስላለበት ለሶስት ቀን መድሀኒት እንስጠውና ካልተሻለው ወደሌሎቹ ፈረሶች እንዳይዛመት እንገለዋለን" ብሎት ሄደ።

ይሄንን ሲያወሩ ፍየል ተደብቃ ሰምታቸው ኖሯል ለፈረሱ እያለቀሰች ያወሩትን ነገረችውና "እንደምንም ብለህ ተነስ! ያለበዛ ይገሉሀል" እያለች ተንሰቀሰቀች። የመጀመርያው ቀንሀኪሙ መጥቶ መድሀኒቱን ሰጥቶት ወጣ።
ወድያው ፍየል ለምለም ሳርና አተላ ይዛለት መጣች ና "እንደምንም ተነስ!" ብላ ተማፀነችው።
በሁለተኛውም ቀን ሀኪሙ ሲመጣ ፈረሱ ምንም ለውጥ አላመጣም መድሀኒቱን ወግቶት እስከ ቀጣዩ ቀን ጠብቆት ካልተሻለው እንደሚገለው ለገበሬው ነግሮት ሄደ።

ይሄን ግዜ ፍየል ለምለም ሳር ፈልጋ ለፈረሱ በማምጣት አፅናናችው። የመጨረሻ ቀን ሀኪሙ ሲመጣ አሁንም ፈረሱ ምንም ለውጥ አላመጣም ይሄን ጊዜ ከገበሬው ጋር ቢገሉት
እንደሚሻል በር ላይ ቆመው ሲያወሩ ፍየል ቀስ ብላ ተደብቃ ፈረሱ ጋር ገብታ እየተንሰቀሰቀች-
"በናትህ አኔንም ጓደኛ አታሳጣኝ ካልተነሳህ ይገሉሀል" ብላ አለቀሰች። ፈረሱ በፍየሏ ግፊት ቀስ ብሎ ተነሳ። ፍየል ደስ አላት።

"ጎበዝ አስኪ እሩጥ" እያለች አበረታችው። ፈረሱ በወኔ በፊት ከሚሮጥበት ፍጥነት በላይ ሮጠ። ይሄን ጊዜ ፍየል በደስታ ጮሇች። ገበሬውና ሀኪሙ የምን ጩሇት ነው ብለው ሲያዩ
ያዩትን ማመነን አቃታቸው።ፈረሱ በሓይል አየሮጠ ነው።ገበሬው በደስታ ብዛት ሀኪሙን አንቆ ሳመው። እረኛውን ጠርቶት "ዛሬ እኔ ቤት ትልቅ ድግስ አለ! ስለዚህ ቶሎ በሉ ፍየሏን እረዱልኝ! ምሳ እዚህ ነው" አለ።
------------------------------------------------------------------------------
አንዱ የሌላው መሰላል ነው። ለአንዱ ህይወት ለሌላው ሞት ነው። ለሀብታም ህይወት የደሀው ችግር ግድ ነው። ለአንዱ ማለፍ የሌላው ውድቀት ወሳኝ ነው። ይህ የአለም ህግ ነው።
የምትመራበት ህግ!
አንብበው ሲጨርሱ ሼር
ማድርጉን አይርሱ


ውድ የአብነት መንደር ቤተሰቦች እንኳን ለአዲሱ ዓመት አደረሳቹህ!! መጭው ጊዜ የሰላምና የፍቅር የበጎነት ያድርግልን!!
11/09/2022

ውድ የአብነት መንደር ቤተሰቦች እንኳን ለአዲሱ ዓመት አደረሳቹህ!! መጭው ጊዜ የሰላምና የፍቅር የበጎነት ያድርግልን!!

08/09/2022
08/09/2022
08/09/2022

መልካምነት ይከፍላል።

Address

Addis Ababa

Telephone

+251967149855

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when የአብነት መንደር /Abinet Vellage posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share