Photo sisay guzay ፎቶ ሲሳይ ጉዛይ

Photo sisay guzay ፎቶ ሲሳይ ጉዛይ This page belongs to photographer Sisay Guzay who is well known by his funny, historical and and ent

እውቋ ዓለም አቀፍ የፊልም ተዋናይአንጀሊና ጆሊ  ኢትዮጵያ  ነችአንጀሊና ጆሊ የቅዱስ ጴጥሮስ ሆስፒታልን ጎበኙዝነኛዋ አሜሪካዊት ተዋናይት ፣ የፊልም ባለሙያ እና የሰብአዊ ድጋፍ አቅራቢ የሆኑ...
11/08/2025

እውቋ ዓለም አቀፍ የፊልም ተዋናይ
አንጀሊና ጆሊ ኢትዮጵያ ነች

አንጀሊና ጆሊ የቅዱስ ጴጥሮስ ሆስፒታልን ጎበኙ

ዝነኛዋ አሜሪካዊት ተዋናይት ፣ የፊልም ባለሙያ እና የሰብአዊ ድጋፍ አቅራቢ የሆኑት አንጀሊና ጆሊ በዛሬው ዕለት የቅዱስ ጴጥሮስ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታልን ጎብኝተዋል።

ተዋናይቷ ያደረጉት ጉብኝት በዋነኝነት ሆስፒታሉ እየሰጠ በሚገኘው መድሃኒቱን የተላመደ ቲቢ (ኤም.ዲ.አር ቲቢ) ህክምና ዙሪያ እየተከናወኑ ያሉ እንቅስቃሴዎችን ፣ የሚታዩ ለውጦችን እንዲሁም ድጋፍ የሚያስፈልጋቸውን ቦታዎች መለየት ላይ ትኩረት ያደረገ ነበር።

በጉብኝቱ ላይ አንጀሊና የሆስፒታሉን የቲቢና መድሃኒቱን የተላመደ ቲቢ (ኤም.ዲ.አር ቲቢ) ህክምና አገልግሎት መስጫ ዋርድ ፣ ላብራቶሪ እንዲሁም ታካሚዎችን ተዘዋውረው ተመልክተዋል።

አንጀሊና ወደ ሆስፒታሉ ከረጅም ጊዜያት በፊት መጥተው እንደነበር ያስታወሱ ሲሆን በአሁኑ ጉብኝታቸው ላይ ሆስፒታሉ ዘርፈ ብዙ ለውጦች አምጥቶ በመመልከታቸው እጅግ ደስተኛ መሆናቸውን ተናግረዋል።

አክለውም ሆስፒታሉ ድጋፍ ቢደረግለት በቀጣይ የተሻለ
አገልግሎት ለታካሚዎች መስጠት በሚያስችለው አስተማማኝ ደረጃ ላይ እንዳለ በጉብኝቱ ላይ መገንዘባቸውን ገልፀዋል።

በተጨማሪም በሆስፒታሉ በቲቢ ህክምና አገልግሎት አሰጣጥ ላይ የተገኘው እድገት በእጅጉ የሚደነቅ እና የሚያስተማምን ስለሆነ በቀጣይ በጂ.ኤች.ሲ (Global Health Committee (GHC)) በኩል ድጋፍ እናደርጋለን ብለዋል።

የሆስፒታሉ ዋና ስራ አስፈፃሚ ዶ/ር አብርሃም እሸቱ በበኩላቸው ቲቢን ለማጥፋት በሚደረገው ጥረት ውስጥ ተዋናይቱ ላሳዩት ዘላቂ ቁርጠኝነት ፣ ልግስና እና በቀጣይ ለሚያደርጉት ድጋፍ ከፍተኛ ምስጋናቸውን አቅርበዋል።

አንጀሊና ጆሊ ከፊልም ስራ ባሻገር በአለምዓቀፍ ደረጃ ለስደተኞች እና ለሰብአዊ መብቶች ጥብቅና በመቆም በ UNHCR (United Nations High Commissioner for Refugees) የበጎ ፈቃድ አምባሳደር እንዲሁም ልዩ መልዕክተኛ በመሆን ከ20 ዓመታት በላይ በማገልገል በሰሩት ሰፊ የሰብዓዊነት ስራ ይታወቃሉ።

/ቅዱስ ጴጥሮስ ሆስፒታል /

ማዕድ የኢትዮጵያ ተጓዥ ኤክስፖ በመጪው 2018 ከመስከረም 29 እስከ ጥቅምት 1 በአምስተርዳም ይካሄዳልፍቅር ያሸንፋል የበጎ አድራጎት ማህበር የሚያዘጋጀው የመጀመሪያው ማዕድ የኢትዮጵያ ተጓዥ...
11/08/2025

ማዕድ የኢትዮጵያ ተጓዥ ኤክስፖ በመጪው 2018 ከመስከረም 29 እስከ ጥቅምት 1 በአምስተርዳም ይካሄዳል

ፍቅር ያሸንፋል የበጎ አድራጎት ማህበር የሚያዘጋጀው የመጀመሪያው ማዕድ የኢትዮጵያ ተጓዥ ኤክስፖ በመጪው 2018 ከመስከረም 29 እስከ ጥቅምት 1 ድረስ በአምስተርዳም እንደሚካሄድ አዘጋጆቹ በዛሬው እለት በስጡት መግለጫ አስታውቀዋል።

ማዕድ የኢትዮጵያ ተጓዥ ኤክስፖ ኢትዮጵያዊያንና ትውልደ ኢትዮጵያዊያን ወገኖች ባሉበት የአለም ክፍል በመንቀሳቀስ ከፍተኛ ቅድመ ዝግጅት የተደረገበትን ኢትዮጵያንና ኢትዮጵያዊነትን ብቻ የሚያከብር፤ የሚያስተዋውቅ በአንድ ቦታ በርካታ ዝግጅቶች የሚቀርብበት መነሻውን በሆላንድ አምስተርዳም በማድረግ በተለያዩ ሀገራት ኤክስፖ፤ የፌስቲቫል እና ሌሎች የመዝናኛ ዝግጅቶች የሚቀርቡበት እንደሆነ ተገልጿል።

የኢትዮጵያዊነት ባህላችንን መሰረት ያደረገው ማዕድ ተጓዥ ኤክስፖ ላይ የመጀመርያው ዙር በሆላንድ አምስተርዳም ከተለያየ ቦታ የሚሰባሰቡ ኢትዮጵያዊያንና የሌሎች ሀገራት ዜጎችን በአንድ ማዕድ(ቦታ) አንዲሰባሰቡ በማድረግ አንዲዝናኑ፤ አንዲገበያዩ፧ አንዲወያዩ የሚደረግ ሲሆን በቀጣይም በሌሎች ሀገራት የሚከናወን ይሆናል ተብሏል፡፡

የዝግጅቱ ዓላማ አትዮጵያውያንና የሌሎች ሀገራት ዜጎችንም በማሳተፍ ማዕድ ተጓዝ ኤክስፖ በተሰኘው የፌስቲቫል ዝግጅት አማካኝነት በአንድ ቦታ የገበያ ትስስር መፍጠርና የመዝናኛ ዝግጅቶችን ማቅረብ እንደሆነ በመግለጫው ተነግሯል፡፡

ኤክስፖው የኢትዮጵያን ጨምሮ የተለያዩ ሀገራት ምርትና አገልግሎሎቶች የሚቀርቡበት ታላቅ ኤክስፖ ሲሆን በተለያየ ዘርፍ በአሰመጪና ላኪነት ላይ እንዲሁም በባንክና ሪልስቴት ዘርፍ ላይ የተሰማሩ ተቋማት ይሳተፋሉ፡፡

በኤክስፖ ላይ ለሚሳተፉ ተሳታፊዎች የተሳትፎ ሰርተፍኬት እንደሚሰጥ የተገለፀ ሲሆን ተሳታፊዎች በአዲስ አበባ በፍቅር ያሸንፋል በጎ አድራጎት ቢሮ መመዝገብ ይችላሉ ።

ፍቅር ያሸንፋል የበጎ አድራጎት ማሀበር ከመንግስት ሀጋዊ የስራ ፈቃድ ካገኘ ጊዜ ጀምሮ በርካታ የግንዛቤ ማስጨበጫ እና የበጎ አድራጎት ስራዎችን ሲሰራ ቆይቷል።

ታዳጊዋቹን እንኳን ደስ ያላችሁ በልዋቸው አቦ                         ❤❤❤ህፃናቶች ወደ ኮሪያ ሄደው መማር የሚያስችላቸውን ሙሉ ስኮላር ሺፕ አገኙበማርሻል አርት፣ በጂጂቲየፍ ቴ...
11/08/2025

ታዳጊዋቹን እንኳን ደስ ያላችሁ በልዋቸው አቦ
❤❤❤
ህፃናቶች ወደ ኮሪያ ሄደው መማር የሚያስችላቸውን ሙሉ ስኮላር ሺፕ አገኙ

በማርሻል አርት፣ በጂጂቲየፍ ቴኳንዶና ተያያዥ ስፖርቶች ኢትዮጵያን የሚወክሉ ተወዳዳሪዎች ብቁ ለማድረግ እየሰራ የሚገኘው ሌጀንድ በትላንትናው እለት 250 በላይ ሰልጣኞችን በብቃት አሰልጥኖ አስመርቋል።

አገራችንን በመወከል ከ193 የዓለም አገራት ከተውጣጡ ግራንድ ማስተሮች ሲሰጥ የነበረው የጂቲቲኤፍ ስልጠ እና የብቃት ማረጋገጫ እና ውድድር ብሎም የጂጂትየፍ የዳን ፈተና በእለቱ ደኑን ከግራንድ ማስተረቹ ተቀብለዋል::

ዶክተር ሙን ከኮሪያ ፣ የዓለም የጂጂቲየፍ ቴኳንዶ መስራች የሆኑት ግራንድ ማስተር ጁሊ ፣ ከአገራችን ዶ/ር ግራንድ ማስተር ሔኖክ ግርማ የጂጂትየፍ ምክትል ፕሬዝደት እንዲሁም ግራንድ ማስተር ሲን የተሳተፉበት ይህ ስልጠና ከኢትዮጵያ ከሁሉም ክልልሎች እንዲሁም ከጎረቤት ሀገራት ጅቡቲ እና ሶማሊያ የተውጣጡ ሰልጣኞችን አሰልጥኗል።

የስልጠናው ዋና ይዘት ትውልዱ በአካል በአእምሮ በስነ ምግባር በመንፈስ ጠንካራ እና አምራች ዜጋ እዲሆን የሚያስችል ከመሆኑም ባሻገር የፍልሚያ አሸናፊ ሳይሆን በህይወት ፈተና በብቃት ማሸነፍ የሚያስችል መሆኑ ተነግሮለታል።

በዚህ ውድድር አሸናፊ ለሆኑት የወርቅ፣ የብር፣ የነሀስ ሜዳሊያ እንዲሁም ከሁሉም አሸናፊው የገንዘብ ሽልማት ተበርክቷል።

"በዓለም መድረክ ኢትዮጵያን ወካይ ስፖርተኞች ብቁ እናደርጋለን።" ብሎ የተነሳው ጂጂቲኤፍ ከ250 በላይ ሰልጣኞችና አሰልጣኞች በኪንግስ ሆቴል ራት ግብዣ በማድረግ ለሁለት ተማሪዎች ኮሪያ ሄደው እንዲሰለጥኑ እድል አመቻችቷል።

በተያያዘም ሀገራችን ኢትዮጵያ በዓለም ዓቀፍ መድረክ ስሟ ያልተጠራበትን ይህንኑ ዘርፍ ብቁ ተወዳዳሪዎችን ለማ
ፍራት እንደሚሰራ በዶክተር ግራንድ ማስተር ሄኖክ ተገልጿል:::

በእኔም በልጆቼም ፆታዊ ጥቃት አድርሶብኛል በማለት በተለያዩ ማህበራዊ ሚዲያዎች አቤቱታ ስታሰማ የነበረችው በሷ ጉዳይም ፖሊስ ከአንድም ሁለት ጊዜ መግለጫ የሰጠ ሲሆን  ወ/ሮ ሰርካለም አስራት...
10/08/2025

በእኔም በልጆቼም ፆታዊ ጥቃት አድርሶብኛል በማለት በተለያዩ ማህበራዊ ሚዲያዎች አቤቱታ ስታሰማ የነበረችው በሷ ጉዳይም ፖሊስ ከአንድም ሁለት ጊዜ መግለጫ የሰጠ ሲሆን ወ/ሮ ሰርካለም አስራት ከዚህ ተግባራቸው ባለመቆጠባቸው የአዲስ አበባ ሴቶች፣ህፃናት እና ማህበራዊ ጉዳይ ቢሮ ከህፃናት መብትና ደህንነት አንፃር ጉዳዩ እንደሚመለከተው ተቋም ይህን ነገር በቅርበት ሲሰሩበት ከነበሩ የቅን ልቦች ድርጅት ጋር በጋራ በመሆን ወ/ሮ ሰርካለም አስራት ከነ ልጆቻቸው እና በጉዳዩ የሚያሟቸው አቶ ተወልደ ከበደን በአዲስ አበባ ሴቶች፣ ህፃናት እና ማህበራዊ ጉዳይ ቢሮ በመጥራት ፊት ለፊት እንዲነጋገሩ ተደርጎ ከዚህ ሀምሌ 30/2017 ዓ.ም ጀምሮ በእንደዚህ አይነት ነገር በማህበራዊ ሚዲያ እንዳይመጡ ተነግሮአቸው ሀለቱም ግለሰቦች በፊርማቸው አረጋግጠዋል።
ወ/ሮ ሰርካለም አስራት ፍቃደኛ ከሆኑ ሶስቱንም ልጆቻቸውን የአዲስ አበባ ሴቶች፣ህፃናትና ማህበራዊ ጉዳይ ቢሮ ተረክቦ ሊያሳድግ ዝግጁ መሆኑን የቢሮው ሀላፊ ወ/ሮ ቆንጂት ደበላ አሳውቀዋል።

ውሸት ነው Fake News የሀሰተኛ መረጃ ማስጠንቀቂያ 🚨ባለፉት ቀናት ውስጥ በማህበራዊ ሚዲያ ላይ አንድ ያልተለመደ ወሬ እየተሰራጨ ነው።“ጄሲካ የምትባል ሴት በዶልፊን ተበላች።” ይህ ታሪክ...
10/08/2025

ውሸት ነው Fake News

የሀሰተኛ መረጃ ማስጠንቀቂያ 🚨

ባለፉት ቀናት ውስጥ በማህበራዊ ሚዲያ ላይ አንድ ያልተለመደ ወሬ እየተሰራጨ ነው።

“ጄሲካ የምትባል ሴት በዶልፊን ተበላች።”
ይህ ታሪክ ፈጽሞ ሐሰት መሆኑን በግልጽ እንገልጻለን።

ከየትኛውም ይፋዊ የዜና ምንጭ ያልተዘገበ።

ከባለስልጣናት ምንም አይነት መግለጫ ያልተሰጠበት።

ምንም አይነት ማስረጃ፣ ፎቶ፣ ወይም ቪዲዮ ከታማኝ ምንጭ ያልቀረበለት።

እውነታው ምንድን ነው?

* ዶልፊኖች ሰዎችን የሚያጠቁ ወይም የሚበሉ አዳኞች አይደሉም። እነሱ እጅግ በጣም ብልህ የባህር እንስሳት ናቸው።

* ምንም እንኳን የዱር ዶልፊኖች አልፎ አልፎ ጠበኛ ባህሪ ሊያሳዩ ቢችሉም፣ እስካሁን ድረስ ዶልፊን ሰውን ገድሎ የበላበት የተመዘገበ ክስተት የለም።

* አንዴ የሐሰት መረጃ ከተሰራጨ በኋላ ማስተካከል ከባድ ነው። ስለዚህ ከመጀመሪያውኑ እናስቆመው።

💡 ኃላፊነት የሚሰማው የማህበራዊ ሚዲያ ተጠቃሚ ይሁኑ!

* ማንኛውንም ታሪክ ከማጋራትዎ በፊት ከታማኝ የዜና ምንጮች መሸፈኑን ያረጋግጡ።

* ከማጋራትዎ በፊት መረጃውን
ከይፋዊ ምንጮች ያጣሩ።

ውሸት አይሰራጩ
ጉርሻ ፔጅ

ስፖርቱ ለዋንጫ ሳይሆን ህይወትን የሚለውጥ ነው አገራችንን በመወከል ከ13 የዓለም አገራት ከተውጣጡ ግራንድ ማስተሮች ሲሰጥ የነበረው የጂቲቲኤፍ ስልጠና ውድድር በነገው እለት እንደሚጠናቀቅ ታ...
09/08/2025

ስፖርቱ ለዋንጫ ሳይሆን ህይወትን የሚለውጥ ነው

አገራችንን በመወከል ከ13 የዓለም አገራት ከተውጣጡ ግራንድ ማስተሮች ሲሰጥ የነበረው የጂቲቲኤፍ ስልጠና ውድድር በነገው እለት እንደሚጠናቀቅ ታወቀ።

ዶክተር ሙን ከኮሪያ ፣ የዓለም ቴኳንዶ መስራች የሆኑት ግራንድ ማስተር ጁሊ ፣ ከአገራችን ዶ/ር ግራንድ ማስተር ሔኖክ ግርማ እንዲሁም ግራንድ ማስተር ሲን የተሳተፉበት ይህ ስልጠና ከኢትዮጵያ ከሁሉም ክልልሎች እንዲሁም ከጅቡቲ እና ከሶማሊያ የተውጣጡ ሰልጣኞችን አሰልጥኗል።

የስልጠናው ዋና ይዘት ትውልዱ በአካል በአእምሮ በስነ ምግባር በመንፈስ ጠንካራ እና አምራች ዜጋ እዲሆን የሚያስችል ከመሆኑም ባሻገር የፍልሚያ አሸናፊ ሳይሆን በህይወት ፈተና በብቃት ማሸነፍ የሚያስችል መሆኑ ተነግሮለታል።

በዚህ ውድድር አሸናፊ ለሆኑት የወርቅ፣ የብር፣ የነሀስ ሜዳሊያ እንዲሁም ከሁሉም አሸናፊው የገንዘብ ሽልማት ይበረከታል ተብሎ ይታሰባል።

ፍላይ አዲስ ትራቭል ሶሉሽን ጋዜጠኛና ፕሮሞተር አብርሃም ግዛውን የድርጅቱ ብራንድ አምባሳደር አድረጎ ለአንድ ዓመት በአንድ ሚሊዮን አምስት መቶ ሺህ ብር (1,500.000.00 )ብር ሾመ።  ...
09/08/2025

ፍላይ አዲስ ትራቭል ሶሉሽን ጋዜጠኛና ፕሮሞተር አብርሃም ግዛውን የድርጅቱ ብራንድ አምባሳደር አድረጎ ለአንድ ዓመት በአንድ ሚሊዮን አምስት መቶ ሺህ ብር (1,500.000.00 )ብር ሾመ።
***
ፍላይ አዲስ ትራቭል ሶሉሽን ባለፉት አራት ዓመታት አውሮፓ ፖላንድ ቱርክ ጣሊያን ካናዳ ሩሲያ እና ሌሌሎች በርካታ የአለም ሀገራት ለትምህርት ለስራና ለህክምና እንዲሁም ለጎብኝት ጉዞ ለሚያደርጉ ዜጎች የጉዞ እና አጠቃላይ ሂደቱችን የማማከር አግልግሎቶችን በመስጠት ታዋቂና ተመራጭ ለመሆን የቻለ ድርጅት ሲሆን ይህንኑ ስራውን ይበልጥ ወደ ህብረተሰቡ እንዲደርስ እና እንዲተዋወቅ ለማድረግ በተለያዩ የጋዜጠኝነት ወይም የሚዲያ ሥራዎች የፕሮሞሽን የተለያዩ ሁነቶች (ኢቨንቶችን)በማዘጋጀት በማስተባበርና በመምራት የሚታወቀውን ጋዜጠኛና ፕሮሞተር አብርሃም ግዛውን የድርጅቱ ብራንድ አምባሳደር አድረጎ በዛሬው ዕለት ቦሌ በሚገኘው ጎልደን ቱሊፕ ኢንተርናሽናል ሆቴል ተፈራርመዋል ።
በዚህ የፊርማ ስነ-ሥርዓት በርካታ የክብር እንግዶች የተገኙ ሲሆን ይህ የብራንድ አምባሳደር ስምምነት ለቀጣይ ሁለት አመታት ድርጅቱን ለማስተዋወቅ የተደረገ ስምምነት እንደሆን በፊርማ ስነ-ስርዓቱ ወቅት ተገልጿል ።

አስገጅ ህጉ ሊተገበር 2 ወራት ቀርተውታል         አሽከርካሪ ልብ በል በግዜቲቢኤ(TBK) ትሬዲንግ ኃላፊነቱ/የተ/የግል ማህበር  ( PLC ) ግሪን ቴክ የነዳጅ ቆጣቢና የካርቦን ልቀትን...
08/08/2025

አስገጅ ህጉ ሊተገበር 2 ወራት ቀርተውታል
አሽከርካሪ ልብ በል በግዜ
ቲቢኤ(TBK) ትሬዲንግ ኃላፊነቱ/የተ/የግል ማህበር ( PLC ) ግሪን ቴክ የነዳጅ ቆጣቢና የካርቦን ልቀትን የሚቀንስ መሳሪያ አዲስ ቴክኞሎጂ ወደ ሀገር ዉስጥ አስገብቶ በስራ ላይ ይገኛል ይህ በእንዲህ እንዳለ የትራንስፖርትና ሎጅስቲክስ ሚኒስቴር ከካርቦን ልቀት ጋር ያወጣውን አስገዳጅ መመሪያ ዛሬ በስካይላይት ሆቴል አብራርቷል::
አርቲስት ዬአዳን አፍሬም የ GREENTECH Africa አምባሳደር ሆኖ ለረዥም ዓመት እያገለገለች ትገኛለች

በኢትዮጵያ "አዲስ የገበያ ማዕከል ይዘን መጥተናል" ላክስ አዲስ ፕሮፐርቲስከሚንበር ቲቪበኢትዮጵያ “ግብይትን ከተፈጥሮና ሰው ሠራሽ መዝናኛ ጋር ያጣመረ ግዙፍና ዘመናዊ ሞል” በካቮድ ሪል እስ...
08/08/2025

በኢትዮጵያ "አዲስ የገበያ ማዕከል ይዘን መጥተናል" ላክስ አዲስ ፕሮፐርቲስ
ከሚንበር ቲቪ

በኢትዮጵያ “ግብይትን ከተፈጥሮና ሰው ሠራሽ መዝናኛ ጋር ያጣመረ ግዙፍና ዘመናዊ ሞል” በካቮድ ሪል እስቴት እየተገነባ መሆኑን ላክስ አዲስ ፕሮፐርቲስ (LUXADDIS PROPERTIES) የተሠኘ ድርጅት አስታወቀ፡፡ የድርጅቱ ሥራ አስኪያጅ አቶ ሙሐመድ ሰዒድ፤ ዛሬ ጁመዐ ነሐሴ 2/2017 በስካይ ላይት ሆቴል በተሰጠ ጋዜጣዊ መግለጫ ይህንኑ ተናግረዋል፡፡

በዚህ መግለጫ ላይ የአፍሪካ መዲና እና የዲፕሎማሲ ማዕከል የሆነችው አዲስ አበባ፤ “ስጦታ ሞል” የተሠኘ ፕሮጀክት በከተማዋ እምብርት ላይ የመገንባት ሥራው እንደተጀመረ ይፋ አድርገዋል፡፡

የፕሮጀክቱ ባለቤት ካቮድ ኮሜርሺያል እና በስጦታ ሞል ብቸኛ የሽያጭ ወኪል ላክስ አዲስ ፕሮፐርቲስ በጋራ በተሰጠው ጋዜጣዊ መግለጫ፤ “ስጦታ ሞል የተለያዩ የስጦታ ግብዓቶችና ተዛማጅ አገልግሎቶች በአንድ ጣሪያ ሥር በተመቻቸ ሁኔታ የሚሰበሰቡበት መሆኑን እንዲሁም የከተማችን አዲስ መልክና የግብይት ባህልን ወደ ላቀ ደረጃ እንደሚያሸጋግር” የላክስ አዲስ ፕሮፐርቲስ ሕዝብ ግንኙነት ዳይሬክተር ጋዜጠኛ ሙሐመድ ፈረጅ አስረድተዋል፡፡

ላክስ አዲስ ይዞት የመጣው ስጦታ ሞል፤ ከአራት ኪሎ፣ ከፒያሳ፣ ስድስት ኪሎ፣ ከመነንና ከሰሜን ሆቴል በእኩል ርቀት ላይ በሰው ሠራሽ ሐይቅ፣ በሰፊ መናፈሻ እና በአቅሷ መስጂድ የተከበበ መሆኑ ልዩ እንደሚያደርገው በመድረኩ ተገልጿል፡፡ ከዘመናዊ የሱቆች በተጨማሪ ግብይትና መዝናኛን ያጣመረ አገልግሎት ስለሚሰጥ በደንበኞች ዘንድ ተመራጭ ያደርገዋል ተብሏል፡፡

18 ሺሕ ካሬ ሜትር አጠቃላይ ሥፋት የያዘውና በ18 ወራት ግንባታው እንደሚጠናቀቅ በተነገረው በስጦታ ሞል፤ የንግድ ቦታዎችን 50 በመቶ የሚደርስ ከወለድ ነፃ ብድር እንደተመቻቸ በላክስ አዲስ ፕሮፐርቲስ የሥራ ኃላፊዎች ተገልጿል።

በዛሬው እለት ከተሰጠው መግለጫ በኋላ በፕሮጀክቱ ባለቤት ካቮድ ኮሜርሺያል እና በስጦታ ሞል ብቸኛ የሽያጭ ወኪል ላክስ አዲስ ፕሮፐርቲስ ኃላፊዎች የብቸኛ ሽያጭ ወኪልነት የፊርማ ሥነ ሥርዐት አካሔደዋል፡፡ የፊርማ ሥነ ሥርዐቱ የተካሄደው በላክስ አዲስ ፕሮፐርቲስ ዋና ሥራ አስኪያጅ አቶ ሙሐመድ ሰዒድ እና በካቮድ ኮሜርሻል ቺፍ ኦፊሰር አቶ ፍሬው ታምሩ አማካኝነት ነው፡፡ (ሚንበር ቲቪ)

በተጨማሪም

የሃገር ልጆች ድንቅ የእጅ ሥራ ውጤቶች በአንድ ስፍራ የሚከትሙበት ነው የተባለው ስጦታ ሞል፤ ዘላቂና አዋጭ ኢንቨስትመንት ለሚፈልጉ ሁሉ የተለየ ዕድልን ይዞ እንደመጣ የተገለጸ ሲሆን፤ የሱቅ ቦታዎችን በካሬ ከብር 240,000 ጀምሮ መግዛት እንደሚቻልና 50% የሚደርስ ከወለድ ነፃ ብድር እንደተመቻቸ በላክስ አዲስ ፕሮፐርቲስ የሥራ ኃላፊዎች ተገልጿል።

🎉 ህብር የህጻናት ፌስቲቫል | ነሃሴ 2 – 4/2017 🎉📍 በኤግዚቢሽን ማዕከል🕘 ጊዜ፡  ሙሉቀን🔥 3 ቀናት ሙሉ ፍንደቃ እና ደስታ !በሙዚቃ፣ በህጻናት ቴአትር ፣ በፓፔት ትርኢት፣ በተለያዩ...
08/08/2025

🎉 ህብር የህጻናት ፌስቲቫል | ነሃሴ 2 – 4/2017 🎉
📍 በኤግዚቢሽን ማዕከል
🕘 ጊዜ፡ ሙሉቀን

🔥 3 ቀናት ሙሉ ፍንደቃ እና ደስታ !
በሙዚቃ፣ በህጻናት ቴአትር ፣ በፓፔት ትርኢት፣ በተለያዩ ጌሞች በሚደምቀው በዚህ የህጻናት ፌስቲቫል ላይ ለመገኘት ይዘጋጁ የማይረሳ ጊዜን ያሳልፉ 🌞❄️

🎶 በሙሉ ባንድ ሙዚቃ ዝግጅት እና በዲጄ የሚቀርቡ ሙዚቃዎች
🎭 የፓፔት ትርኢቶች እና የህጻናት ቴአትር
🎮 ሁሉንም የእድሜ ክልል ያማከሉ የጌም ጨዋታዎች እና ውድድሮች
🛍 የህጻናት እና ታዳጊዎች ቁሳቁስ መሸጫዎች
🍔 የተለያዩ ጣፋጭ ምግቦች

ለሁላችሁም ወላጆች እና ህፃናት ...

ኑ.... ና ... በ2000 ዓ.ም በሚሊኒየም ዋጋ ደረጃውን የጠበቀ መስተንግዶ ጣዕም ካለዉ ምግብ ጋር

ታላቅ የምግብ ፌስቲቫል
በጉርሻ ማዕድ እና የምግብ አገልግሎት ....
በአያቶች

1. በኤግዚብሽን ማዕከል
ከነሐሴ 02 እስከ ነሐሴ 04 ቀን 2017 ዓ.ም
ከማለት 3.00 እስከ ምሽት 1.00

2. በኢትዮ ኩባ ወዳጅነት አደባባይ
ከነሐሴ 05 እስከ ጳጉሜ 05 ቀን 2017 ዓ.ም
ከማለት 3.00 እስከ ምሽት 1.00

እጅግ ተመጣጣኝ በሆነ ዋጋ

ትኩስ ነገሮች
1. ሻይ ... 10.00
2. የጀበና ቡና ... 20.00
3. የታሸገ ዉሃ ...15.00

ምግቦች
1. ፓስታ ... 50.00
2. ሽሮ ... 100.00
2 ፍርፍር ... 75.00
3. በያይነት ... 100.00
4. የፆም ብፌ .... 150.00
5. ትኩስ ብስኩት እና ሳንቡሳ ... 30.00
5. ችብስ ....50.00
6. አይስ ክሬም ...150.00

መስተንግዶ በታዋቂ አርቲስቶች እና አያቶች ...

በዩቶጱያ ቢዝነስ እና ኮሙኒኬሽን ኃ/የተ/የግ/ማህበር

ለማንኛዉም የድግስ ፍላጎትዎ ይደረግልን
0934 211884. 0983 010211

መስተንግዶ በታዋቂ አርቲስቶች ... በታላቅ ክብር ይደረጋል ...

💥 ተረት በታዋቂ ሰዎች ይቀርባል
💃 ከቤተሰብዎ ጋር ይምጡ በክረምት እጅግ ተወዳጅ በሆነው ኤቨንት ላይ በመገኘት ይዛናኑ!!!🌞❄️ የቴአትር ቤቶች አስተዳደር ድርጅት ከኤግዚቢሽን ማዕከል ጋር በመተባበር






ልዩ የማርሻል ስልጠና እየተካሄደ  ነው''ኢትዮጵያውያን ለማርሻል አርት የሚመች ተክለ ሰውነት አላቸው '':-ግራንድ ማስተር አብሃይ ሲንግ ራቶሬ      ትውልደ ሀገራቸው ህንድ ብትሆንም አሁን...
07/08/2025

ልዩ የማርሻል ስልጠና እየተካሄደ ነው
''ኢትዮጵያውያን ለማርሻል አርት የሚመች ተክለ ሰውነት አላቸው '':-ግራንድ ማስተር አብሃይ ሲንግ ራቶሬ
ትውልደ ሀገራቸው ህንድ ብትሆንም አሁን ግን ዜግታቸውም ሆነ የሚኖሩባት ሀገር አሜሪካ ናት ፤ዋነኛው ሥራቸውም የማርሻል አርት ሥልጠና መስጠት ነው፦ግራንድ ማስተር አብሃይ ራቴሪ
ከእኚህ ሰው ጋር የመተዋወቅ ዕድል ያገኘነው በካፒታል ሆቴል ውስጥ ከሀምሌ 30 እስከ ነሃሴ 4 ድረስ በዚሁ ሆቴል ውስጥ በመካሄድ ላይ ስለሚገኘው የማርሻል ሥልጠናን በሚመለከት ጋዜጣዊ መግለጫ በተሰጠበት ወቅት ነው።
ይህ የማርሻል አርት ሥልጠና በመካሄድ ላይ የሚገኘው በኢትዮጵያ ልጀንድ ኢንተርናሺናል ቴኳንዶ
አሶሲዬሽን እና በጂጂቲኤፍ ትብብር ሲሆን በርካታ ህፃናትና ታዳጊዎች የዚህ ወርቃማ ዕድል ተጠቃሚ በመሆን ላይ ናቸው ።
የዘጠኝ ዳን ጥቁር ቀበቶ ባለቤት የሆኑት ግራንድ ማስተር አብሀይ ሰንግ ራቶሪ ለመጀመሪያ ወደ አዲስአበባ የመጡት በዚሁ ሥልጠና ላይ ሙያቸውን ለማካፈል መሆኑን የገለፁልንም በዚሁ ኩነት ላይ ነበር።
የጂጂቲኤፍ ምክትል ፕሬዝዳንት የሆኑት ግራንድ ማስተር ሲንግ ኢትዮጵያውያንወጣቶችና ታዳጊዎች ለማርሻል አርት የሚመች ተክለ ሰውነት እንዳላቸውና ሀገሪቷንም በፍቅር የተመለከቷትመሆናቸውንም ገልፀዋል ።
''እኛ እዚህ የመጣነው ሰዎችን በተለይም ወጣቶችና ታዳጊዎችን ለመርዳት ነው፣ይህንን ተግባር በተለያዩ ሀገራት ውስጥ ስናከናውን ቆይተናል፣አሁን ደግሞ ተራው የኢትዮጵያውያን ነዉ ''ያሉት ማስተር ሲንግ በአሁኑ ወቅት ሰዎች ማርሻል አርትን የሚያዘወትሩት ለኦሎምፒክ ውድድሮች ሳይሆን ለህይወታቸው እንደሆነም አስምረውበታል ።አያይዘውም ወደ ኢትዮጵያ ከመጡ ገና ሁለት ቀናቸው ቢሆንም ኢትዮጵያውን ትሁትና ፍቅርን የተላበሱ ፣ህፃናቱም መልካም ሥነምግባር ያላቸው መሆኑን መረዳታቸውንም አብራርተዋል።
''ኢትዮጵያውያን ለማርሻል አርት አመቺ ተክለ ሰውነት ያላቸው ቢሆንም ይህንን ጥበብ ለመማርዕድል የሚገጥማቸው ጥቂቶች ናቸው ፤ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ግን በርካቶች ይህንን ስፓርት ለመመር እየሞከሩ መሆናቸውን ተረድቻለሁ ፤ከጥቂት ዓመከታት በኋላ የማርሻል አርት ማዕከል እንደምትሆንም አምናለሁ ።''ብለዋል ማስተር ራቶሪ ።ለአምስት ቀናት ያህል የሚካሄደው ሥልጠናም በስኬት እንደሚጠናቀቅ እርግጠኛ መሆናቸውንም አልሸሸጉም ።

One pack for One Child አንድ እሽግ ለአንድ ልጅ ዘመቻ በይፋ ተጀመረ።---------------------------------" በትምህርት ቁሳቁስ ምክንያት አንድም ተማሪ እቤቱ መቅ...
07/08/2025

One pack for One Child አንድ እሽግ ለአንድ ልጅ ዘመቻ በይፋ ተጀመረ።
---------------------------------

" በትምህርት ቁሳቁስ ምክንያት አንድም ተማሪ እቤቱ መቅረት የለበትም " ! በሚል መርህ ለአዲስ አመት 2016 ዓ.ም እንደ አለፉት አመታት በኢትዮጵያ ውስጥ በተለያዩ ቦታዎች አቅም ለሌላቸው ህጻናት ልጆች የትምህርት ቀሳቁስ በመስጠት ወደ ትምህርት ቤት እንዲሄዱ ያድርጉ በማለት በNew Dawuro Media ዘመቻ እና ገቢ የማሰባሰብ መረሀ ግብር የሁለተኛ ዙር በይፋ ተጀምሯል።

ይህን ዘመቻ ከተለያዩ አከባቢዎች ግለሰቦች እና ድርጅቶች ተቀላቅላችሁ የበኩላችሁን አስተዋጽኦ እንድታበረክቱ ጥሪ እናቀርባለን።

እንደ ሀገር ትምህርት የሚጀምርበት ቀን መስከረም በመሆኑ ፤ ከተለያዩ በጎ ሰዎች እና ግለሰቦች ያምናሰባስበው ደብተር እና ስክሪብቶ ለተፈለገለት ዓላማ ለማዋል አንድ ወር ብቻ ስለቀረን ፤ የአንድ እሽግ ለአንድ ልጅ ዘመቻ ሁላችሁም እንድትቀላቀሉ ጥሪ እናቀርባለን።

ውድ የNew Dawuro Media ቤተሰቦች ከዛሬ ጀምሮ ለተከታታዬ 45 ቀናት ለሚደረገው ዘመቻ የበኩላችሁን አስተዋጽኦ እንድታበረክቱ ስንል ጥሪ እናቀርባለን።
-------------------------------------------------
አንድ እሽግ ለአንድ ልጅ
12 ደብተር
2 እስኪርቢቶ
2 እርሳስ
2 መቅረጫ
2 ላጲስ

የአንድ እሽግ ዋጋ 1000 ብር ሲሆን ፤ እርሶ እንደ አቅሞ የቻሉትን በመለገስ የአንድ እሽግ ለአንድ ልጅ ዘመቻ እንድትቀላቀሉ በትህትና እንጠይቃለን!! 🙏🙏

የOne Pack For one Child (የአንድ እሽግ ለአንድ ልጅ) ዘመቻ በመቀላቀል ይህንን መልካም ዓላማችንን ይደግፉ። በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ በተከፈተው አካውንት 1000563357798 አቅሞ የፈቀደው በመላክ እና የባንክ ስሊፕ በ0917411711 በቴሌግራም ይላኩሉን ፤ ይደውሉልን። በቅርብ ይላችሁ ከላይ የተጠቀሱ የትምህርት ቁሳቁሶችን ለመስጠት ሲፈልጉ ፤ በ0917411711 ይደውሉሉን!





Address

Addis Ababa

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Photo sisay guzay ፎቶ ሲሳይ ጉዛይ posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share