Photo sisay guzay ፎቶ ሲሳይ ጉዛይ

Photo sisay guzay ፎቶ ሲሳይ ጉዛይ This page belongs to photographer Sisay Guzay who is well known by his funny, historical and and ent

በውብ እፅዋት፣ በአረንጓዴው ስፍራ፣ በተለያዩ ለአይን በሚማረኩ የዱር አራዊት ትዕይንት ተከበው፣በአዕዋፋት፣ በዛፎች ዝማሬ ታጅበው፣በሰማያት ጀምበር ደምቀው ልዩ ደስታ ስሜት  ፣የትዝታ ትዝታ ...
31/12/2025

በውብ እፅዋት፣ በአረንጓዴው ስፍራ፣ በተለያዩ ለአይን በሚማረኩ የዱር አራዊት ትዕይንት ተከበው፣በአዕዋፋት፣ በዛፎች ዝማሬ ታጅበው፣በሰማያት ጀምበር ደምቀው ልዩ ደስታ ስሜት ፣የትዝታ ትዝታ የሚፈጥሩበት፤ ልዩ የተፈጥሮ ውበት በህይወትዎ በፍፁም ይህንን ደስ የሚል ከዚህ ደስ ከማይል ጩህት፣ ከስራ፣ ከኑሮ ገለል ብለን ከአዳዲስ ጓደኞች ፣ከቤተሰበዎ፣ ከልጅዎ ጋር አሪፍ ጊዜ የሚያሳልፍበት የሚያጣጥሙበት ከልብ የምንስቅበት የምንድሰትበት ፣ ውብ ዕይታ በልዩ ልዩ ተሞክሮች የሚያደርጉበት አስደሳች ጊዜ የሚያሳልፍበት ሊያመልጥዎ የማይገባ የአመቱ ምርጡ ጉዞ ሁነት
‎ ሁሉ ሙሉ ቡፌያችን አዘጋጅተን የጠበቅነዎ እንዴ አስከ አሁን እዚህ ነህ የዚህ ጉዞ አባል ሁኑ
‎እንዳያመልጥዎ ያለን ቦታ ውስን ስለሆነ እንዳያመልጥዎ!!!

‎በሳምንቱ መጨረሻ የዕረፍት ቀናት የጉዞ ዕቅዳችሁ ከዚህ ስፍራ ውጪ መሆን የለበትም!
‎🌄Camping Trip to yerer mountain and bishoftu lakes 🏞

‎🚐የአዳር ጉዞ ወደ የረር ተራራ እና ቢሾፍቱ ሀይቅ

‎📆የጉዞ ቀን: ታህሳስ 25-26

‎⌚️ የቆይታ ጊዜ: 2 ቀናት እና 1 ምሽት

‎አሁኑን ይመዝገቡ

‎🦶መነሻ ቦታ፡ stadium Ghion hotel

‎🕛መገናኛ ሰዓት 12:00

‎ 🕕መነሻ ሰዓት 12:30


‎ የጉዞው ወጪ የሚያካትተው


‎🚌ትራንስፖርት ቱሪስት ስታንዳርድ (ኮስተር ባስ)

‎🍕🥘🍱ቁርስ(2)

‎ 🍽️ምሳ (2)

‎🍽️ እራት (1)

‎🥠🥟 🍪ኩኪስ

‎ 🥾የ ጫካ ውስጥ እግር ጉዞ ወደ የረር ተራራ


‎ 🥾የእግር ጉዞ ሀሮ መገሪሳ (በተለምዶ አረንጓዴው ባህር)

‎ 🥾 የእግር ጉዞ ወደ ሃሮ ሀይቅ ቢሾፍቱ


‎🦓🐘ብርቅዪ የዱር እንስሳት ምልከት ዕይታ


‎ 🦢🦩ብርቅዪ እንዲሁም የተለያዩ አዕዋፍ ዝርያ በዜማቸው የምናስብበት

‎🔥🐐የካንፋየር ምሽት (የእሳት ዳር ጨዋታ )

‎ 🚣‍♂️ የሀይቅ ዳር ጨዋታዎች

‎💧የታሸገ ውሃ

‎⛺️🛖ድንኳን ለአንድ ምሽት(shared)

‎ (Room ለምትፈልጉ በልዩ ፓኬጅ አመቻችተናል)

‎🧾 የመግቢያ ዋጋ

‎🚶የአስጎብኝ ክፍያ

‎⛺የድንኳን ክፍያ

‎🍶 💉Safety and first aid kit

‎ 👫 Networking and team story telling challenge game

‎🚶‍♀️የፓርክ ጠባቂ

‎🏊‍♀️ውሃ ዋና

‎ 🧘‍♀️ Nature retreated and meditations

‎ 📸 የፎቶግራፍ ባለሙያ

‎🎻🎸 acoustic music sky experience on Mount yerer and lake bishoftu's

‎🎨🧑‍🎨 live painting at the mountain top drawing beyond on nature

‎🧉☕ ባህላዊ የቡና ስነሰስርአት እና ሻይ


‎🛶⚓ጀልባ ጉዞ

‎ 💦 የታሸገ ዉሃ 1/2


‎⚽️🏐🤽‍♂🏅🏆የተለያዩ አስገራሚ ጌሞችና ሽልማቶች


‎የምንጎበኛቸው መስዕብ ቦታዎች

‎-የረር ተራራ

‎-hora መገሪሳ,አዶ (አረንጓዴው ባህር)

‎- የቢሾፍቱ ከተማ ጉብኝት

‎-ሆራ ቢሾፍቱ ሀይቅ

‎- stunning amazing rich vibrant nature landscape view spot

‎ breathtaking view and sunrise ,sunset view

‎-Any guest to perform talent

‎ የጥቅል ዋጋ በሰው :-9999

‎ቀደም ብሎ ለሚከፍሉ :-9100

‎ ዘግይተው ለሚከፍሉ :- 9600

‎ለፍቅረኛሞች -10% off

‎ለተማሪዎች 6+ - 10%off

‎ለቤተሰብ (5+)- 8%

‎ የመጀመሪያዎች ሶስት በግሩፕ ሁነው ለሚመጡ 5+- 7%off

‎ለውጭ ሀገር ዜጎች :-125$

‎ማስታወሻ :-


‎~ያሉን ቦታዎች ጥቂት ብቻ ስለሆኑ👇
‎አሁኑኑ ይመዝገቡ

‎~Account for deposit;

‎ 100041223043 commercial bank of Ethiopia ergibe wondimu

‎19606392 boa Ergibe wondimu

‎+251-901087694 tellbirr

‎~ማሳሰቢያ

‎👉የመመዝገቢያ ቀን ከአሁን ጀምሮ ጥቂት ቦታ እስከሚሞላ ብቻ ይሆናል

‎👉ለመመዝገብ ከላይ በተገለፁት የባንክ ቁጥሮች ገቢ በማድረግ ደረሰኙን መላክ ይኖርባችኋል ላይ ባለው ስልክ ቁጥር

‎ 👉ወዲያው የከፈላችሁበት ደረሰኝ በላካችሁ የማረጋገጫ መለያ code,ልትይዟችሁ የሚገቡ ጉዞ ላይ ሲመጡ ፣ የጉዞዎን ሙሉ መርሃግብር ፣package የሚያጠቃልሉ እና የማያጠቃልሉ ነገሮች ይላክሎታል በስልክዎ ቁጥር ።

‎ 👉መሄድ /መጓዝ ለምትፈልጉ ብቻ ልትይዟችሁ የሚገቡ አስፈላጊ ነገሮች በቁጥርዎ እናደረሳለን፣

‎👉በተጠቀሰው ሰዓት እና ቦታ ይገኙልን(ሰዓት ለራስ ስለሆነ ሰዓት ይከበር )


‎👉እኛን መርጠው በልዪነት ስለሚጓዙ እናመሰግናለን !!!


‎ for more info and registration
‎👇👇👇👇
‎ book now !!! all are invited
‎contact us
‎+251-901087694
‎+251-937603056
‎ Follow us on social media
‎ Please don't hesitate to contact us
https://gigavel.iambiruk.com/Ergibayehabesha
‎Have enjoyed the trip and unforegttable memory with us!!!

Please !!!Please !!!please!!!share your friends,copylink ,gift your familes and couple

ጋሽ ሰለሞን መኪናቸውን በክብር ዛሬ ተረክበዋል!!ለአንጋፋው አርቲስት ጋሽ ሰለሞን ተካ በወጣቱ ቲክቶከር አዶናይ አማካኝነት በማህበራዊ ሚዲያ በተጀመረው የ"መኪና ቻሌንጅ" (Car Challen...
31/12/2025

ጋሽ ሰለሞን መኪናቸውን በክብር ዛሬ ተረክበዋል!!

ለአንጋፋው አርቲስት ጋሽ ሰለሞን ተካ በወጣቱ ቲክቶከር አዶናይ አማካኝነት በማህበራዊ ሚዲያ በተጀመረው የ"መኪና ቻሌንጅ" (Car Challenge) ስኬታማ በሆነ መልኩ መጠናቀቁ ይታወቃል።

በዚህም መሰረት ዛሬ ጋሽ ሰለሞን የመኪና ቁልፋቸውን ተቀብለዋል።

እኛም ለብሩክ ሪል ስቴት እና ለቲክቶከር አዶናይ ምስጋና ይገባቸዋል።

ለጋሽ ሰለሞን ደግሞ እንኳን ደስ አለዎት እንላለን! ዜና 24

2ኛው የአዋጭ የአባላት የገና ባዛር ተከፈተአዋጭ የገንዘብ ቁጠባና ብድር ኃላፊነቱ የተወሰነ መሰረታዊ ኅብረት ሥራ ማህበር ያዘጋጀው የዘንድሮውና 2ኛው የአዋጭ የአባላት የገና ባዛር  በዛሬው ...
30/12/2025

2ኛው የአዋጭ የአባላት የገና ባዛር ተከፈተ

አዋጭ የገንዘብ ቁጠባና ብድር ኃላፊነቱ የተወሰነ መሰረታዊ ኅብረት ሥራ ማህበር ያዘጋጀው የዘንድሮውና 2ኛው የአዋጭ የአባላት የገና ባዛር በዛሬው እለት በይፋ ተከፍቷል

ለ8 ቀናት በሚቆየው በዚህ ባዛር የመክፈቻ መርሀገብር የኅብረት ስራ ማህበሩ ከፍተኛ አመራሮች ፣የኢትዮጵያ ኅብረት ስራ ኮሚሽን አመራሮች እና ሌሎች ጥሪ ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል

ተቋሙ የአዋጭ የአባላት የገና ባዛርን በንግዱ ዘርፍ የተሰማሩ አባላቱን ተጠቃሚ ለማድረግ እና በገበያው ውስጥ የሚስተዋለውን የኑሮ ውድነት በተመለከተ የራሱን አስተዋፆ ለማበርከት አስቦ በመሰረታዊ የኅብረት ስራው ዘርፍ ሁለተኛ የሆነውን የአባላት የገና ባዛር "ለአባላት የገበያ ትስስር በመፍጥር ዘላቂ እድገት ማስቀጠል" በሚል መሪ ቃል ከዛሬ ከታህሳስ 21 እስከ 28 / 2017 ዓ.ም ድረስ የተዘጋጀ እንደሆነ ተገልጿል

በተጨማሪም ባዛሩ ለአዋጭ የንግድ ወይንም የመደበኛ ብድር ተበዳሪ ለሆኑ ነጋዴ አባላት እንደተዘጋጀ ተገልጾ ተቋሙ የአባላቱን ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥና በተለይም ተበዳሪ አበላቱን ለማበረታታትና ለማገዝ ያስችለው ዘንድ ይህ ለ8 ቀናት የሚቆይ የገና በዓል ባዛር ተከፍቷል ተብሏል።

ባዛሩ ለተሳታፊ አባላቱ የነጻ አገልግሎት ለመስጠት የተዘጋጀ እንደሆነም ተጠቁሟል

በባዛሩ ተሳታፊ የሆኑ በቁጥር ከ80 በላይ የአዋጭ አባላት ያለምንም ክፍያ በሾላ ገበያ አካባቢ በሚገኘው የኅብረት ስራ ማህበሩ የግል ይዞታ ላይ የገበያ ትስስር ተፈጥሮላቸው ምርት እና አገልግሎታቸውን ቀጥታ ለሸማቹ ሕብረተሰብ ተደራሽ ማድረግ እንዲችሉ ታስቦ መዘጋጀቱ ተነግሯል

የባዛሩ ተሳታፊ አባላት በብዛት የራሳቸውን ምርትና እንዲሁም ሌሎች ግብዓቶችን ይዘው በመቅረብ በተመጣጣኝ ዋጋ ለሸማቹ ሕብረተሰብ ተደራሽ እንደሚያደርጉ የተጠቆመ ሲሆን ከምርቶቹም መካከል የባልትና ውጤቶች፣ የሀገር ባህል ልብሶች፣ የቤት ዕቃዎች፣ የቆዳ ውጤቶችና የመሳሰሉት ለበዓል የሚሆኑ ግበዓቶች ይገኙበታል፡፡

አዋጭ የገንዘብ ቁጠባና ብድር ኃላፊነቱ የተወሰነ መሰረታዊ ኅብረት ሥራ ማህበር የማህበረሰቡን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ችግር ለመፍታት በአባላት ፍላጎት በ1999 ዓ.ም የተቋቋመ እና በአሁኑ ወቅት ከ163,000 በላይ አባላትን በማፍራት የሀብት መጠኑን h16 ቢሊዮን ብር በላይ ማድረስ የቻለ ተቋም ነው፡፡

ሰበር ዜናሐዋሳ ገብርአል ላይ ውሸት መሆኑ ተረጋገጠ ሰሞኑን በሀገር ውስጥ እና በውጪ ሀገር ያሉ አንዳንድ የማኅበራዊ ሚዲያ አንቂ ነን የሚሉ ግለሰቦች በሎዛ ኹነቶች አዘጋጅ ፣ በዩቱበሮች፣ በ...
28/12/2025

ሰበር ዜና
ሐዋሳ ገብርአል ላይ ውሸት መሆኑ ተረጋገጠ

ሰሞኑን በሀገር ውስጥ እና በውጪ ሀገር ያሉ አንዳንድ የማኅበራዊ ሚዲያ አንቂ ነን የሚሉ ግለሰቦች በሎዛ ኹነቶች አዘጋጅ ፣ በዩቱበሮች፣ በቲክቶከሮች፣ በአገልጋዮች፣ በአርቲስቶች እና በዐቢያተክርስቲያናት ላይ የሐሰት ፕሮፓጋንዳ ዘመቻ መክፈታቸው ይታወቃል።

የክሣቸው ጭብጥም ከዚኽ በታች በምስሉ ላይ ያስቀመጥንላችኹ ምንጩ ያልተረጋገጠን ወረቀት በማዘዋወር ሎዛ ኢቨንትን እና አጋሮቹን በፐርሰንት እየሠሩ ቤተክርስቲያን ዘርፈዋል በሚል በሐሰት ሲወነጀሉ ቆይቷል። ይኹንና ዛሬ ሐዋሳ ገብርኤል ታቦት ወጥቶ ብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት፣ ጥሪ የተደረገላቸው የመንግሥት ባለሥልጣናት፣ ምእመናን በተሰበሰቡበት የሀገረስብከቱ ዋና ሥራ አስኪያጂ የሲዳማ ሀገረስብከት መጋቤ ጥበባት ቀሲስ ሞላልኝ መርጊያ፣ ሐገረ ስብከቱ እና አድባራቱ የማያውቁት በውሸት የተሠራጨ መረጃ እና አድራሻው የማይታወቅ ወረቀት መሆኑን ለተሰበሰበው ምእመናን ተናግረዋል።

ሎዛ ኹነቶች አዘጋጅ በዚኽ ሀገረ ስብከቱ በማያውቀው እና ከሣሺ በሌለው ወረቀት ምክንያት ስሙ በመጥፎ እየተነሣ ነበር። ይኽም የውሸት አጀንዳ በዛሬው ዕለት ሐሰት መሆኑ ተረጋግጧል።

ሁለተኛ ሎዛ ላይ ሲነሣ የነበረው ክሥ በፐርሰንት ይሠራል የሚል ነበር። እርሱም ተቋሙ ከቀናት በፊት ባወጣው መግለጫ በፐርሰንት ወይም በኮሚሺ ሠርቶ እንደማያውቅ፤ የሚሠሩም ካሉ አጥብቆ እንደሚጸየፍ የተናገረ ሲሆን በፐርሰንት ይሠራል የሚሉ ካሉም ሕጋዊ መረጃ ይዘው መክሠሥ እንደሚችሉ አሳስቧል።

በሦስተኛ የተከሠሠው የዋልድባ ገዳም አባቶች ቢሮው ድረስ ሂደው አዘጋጅልን ብለው ቢጠይቁት ኢቨንቱን አስተባብርልን ብለው ቢጠይቁት ለራሱ በሚሊዬን የሚቆጠር ብር ክፈሉኝ አላቸው የሚል ነበር። ይኽንንም ክሥ የአርአያ ሚዲያ ባለቤት ጋዜጠኛ አርአያ መካሻ ባደረገው የምርመራ ዘገባ ለገዳሙ አበመኔት ለቆሞስ አባ አምደ ሥላሴ እና ለኮሚቴው በመደወል ሎዛን አስተባብርልን ብለው እንዳልጠየቁ በሚዲያው ምስከርነት ሰጥተው የማኅበራዊ ሚዲያ ክሡ በአባቶች ምስክርነት ውድቅ ሆኗል።

በሎዛ ኹነቶች ላይ በዚህ መጠን የሐሰት ስም ማጥፋት ዘመቻ ላይ መገባቱ ለምን እንዳስፈለገ? ብዙዎቹን ግራ አጋብቷል።

በደራሲ ካህሳይ አብርሃ ብስራት (አማኑኤል ማንጁስ) የተፃፈው «ያልተመለሱ ዳናዎች» የተሰኘው መጽሐፉ ተመረቀከዚህ ቀደም "የአሲምባ ፍቅር"በሚለው ተወዳጅ መፅሐፍ የሚታወቁት አቶ ካህሳይ አብር...
28/12/2025

በደራሲ ካህሳይ አብርሃ ብስራት (አማኑኤል ማንጁስ) የተፃፈው «ያልተመለሱ ዳናዎች» የተሰኘው መጽሐፉ ተመረቀ

ከዚህ ቀደም "የአሲምባ ፍቅር"በሚለው ተወዳጅ መፅሐፍ የሚታወቁት አቶ ካህሳይ አብርሃ (አማኑኤል ማንጁስ) ሁለተኛ ስራቸው የሆነውን «ያልተመለሱ ዳናዎች» የተሰኘ አዲስ መጽሐፍ በኢትዮጵያ ቤተመዛግብትና ቤተመጻሕፍት አገልግሎት በዛሬው እለት ተመርቆ ለንባብ በቅቷል

በመጽሐፉ ምርቃት ስነ-ስርዓት ላይ ታዋቂ ግለሰቦች፣ የጥበብ ሰዎችና ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ታድመዋል

መጽሀፉ በይዘቱ የሚዳስሰው የቀድሞውን ትውልድ የትግል መስራቾች (29ሰዎች) ታሪክ ቃለመጠይቅ እና የኢሀሰን የትግል ታሪክ ከመጀመርያው እስከ ፍጻሜው እንደሆነ የመጽሐፉ ጸሐፊ አቶ ካህሳይ አብርሃ (አማኑኤል ማንጁስ) ገልጸዋል ።

በምረቃ ስነስርአቱ ላይ እንደተገለጸው መጽሀፉ በ53 ምእራፍ እና 335 ገፅ የያዘ ነው

አቶ ካህሳይ አብርሃ (አማኑኤል ማንጁስ) ከአስርት ዓመታት በፊት በሶስት ቋንቋዎች የተተረጎመውን "የአሲምባ ፍቅር"መፅሐፍ ለንባብ ማብቃቱ ይታወሳል
#ድሬትዩብ

ይህ የሆነው ከርቸሌ ወህኒ  ( ማረምያ ቤት ) ነውበሸገር ማረሚያ ቤት በልብስ ስፌት 100 ታራሚዎች ተመረቁበባውዜር ትሬዲንግ የገንዘብ ድጋፍ የተሰጠው ይህ ስልጠና ለ45 ቀናት የቆየ ሲሆን ...
27/12/2025

ይህ የሆነው ከርቸሌ ወህኒ ( ማረምያ ቤት ) ነው
በሸገር ማረሚያ ቤት በልብስ ስፌት 100 ታራሚዎች ተመረቁ

በባውዜር ትሬዲንግ የገንዘብ ድጋፍ የተሰጠው ይህ ስልጠና ለ45 ቀናት የቆየ ሲሆን 700 ሺ ብር ወጥቶበታል።

የሸገር ማረሚያ ቤት አስተዳዳሪ ረዳት ኮሚሽነር ዋቅጋሪ ጫላ ባደረኩት ንግግር ታራሚዎች ከህብረተሰቡ ጋር ሲቀላቀሉ ብቁ እና ጠቃሚ ዜጋ እንዲሆኑ ብሎም ሀገራቸውና ህዝባቸውን እንዲጠቅሙ የእጅ ስራ ሙያዎችን በማስልጠን ማረሚያ ቤቱ ሀላፊነቱን እየተወጣ መሆኑን ገልፀዋል።

ዛሬ በተካሄደው የምርቃ ስነ ስርዓት የባውዜር ትሬዲንግ ባለቤት አቶ መሀመድ ሰኢድ የማረሚያ ቤቱ ከፍተኛ አመራሮች የመንግስት ስራ ሀላፊዎች ተገኝተዋል።

The new Face of Addis Ababa
27/12/2025

The new Face of Addis Ababa

ያለ መነሻ ካፒታል የንግድ ዕድል የሚፈጥረው "ዳንቴል" የዲጂታል መድረክ ይፋ ተደረገ የኢትዮጵያን የበይነመረብ ንግድ (e-commerce) ዘርፍ ወደ አዲስ ምዕራፍ ያሸጋግራል የተባለለትና "ዳ...
26/12/2025

ያለ መነሻ ካፒታል የንግድ ዕድል የሚፈጥረው "ዳንቴል" የዲጂታል መድረክ ይፋ ተደረገ

የኢትዮጵያን የበይነመረብ ንግድ (e-commerce) ዘርፍ ወደ አዲስ ምዕራፍ ያሸጋግራል የተባለለትና "ዳንቴል" የተሰኘው አዲስ የቴክኖሎጂ መድረክ በይፋ ስራ መጀመሩን የዳንቴል ሶፍትዌር ኃ.የተ.የግ.ማህበር አስታወቀ።

መተግበሪያው ማህበራዊ ሚዲያን ወደ ገቢ ምንጭነት የሚቀይር አሰራር ይዟል። ተጠቃሚዎች በመድረኩ ላይ ያሉ ምርቶችን በቴሌግራም፣ ፌስቡክ እና ቲክቶክ አማካኝነት ለወዳጅ ተከታዮቻቸው በማጋራትና ሽያጭ እንዲከናወን በማድረግ የኮሚሽን ተጠቃሚ ይሆናሉ።

ይህ አሰራር በተለይ የስራ ፍላጎት እያላቸው በመነሻ ካፒታል እጥረት ለተቸገሩ ወጣቶች ትልቅ ዕድል ይዞ መጥቷል።

​ዳንቴል የንግድ እንቅስቃሴውን ቀልጣፋ ለማድረግ ከኢትዮጵያ ፖስታ አገልግሎት ጋር ስምምነት ላይ ደርሷል። ይህም ደንበኞች ያዘዙት ምርት ባሉበት ቦታ እንዲደርሳቸውና የት ደረጃ ላይ እንደሚገኝ በመተግበሪያው እንዲከታተሉ ያስችላቸዋል።

​በተጨማሪም በዲጂታል ግብይት ላይ የሚታየውን የእምነት ጉድለት ለመቅረፍ፣ ደንበኞች የገዙት ምርት ካልተመቻቸው የመመለስ መብት (Return Policy) እንዲኖራቸው ከአቅራቢዎች ጋር ስምምነት መደረጉ ተጠቁሟል።

የድርጅቱ መስራች አቶ ፊሊጶስ ማርሳይ እንዳሉት፣ "ዳንቴል" በዘመናዊ የንግድ ስርዓትና በማህበራዊ ትስስር መካከል ያለውን ክፍተት በመሙላት፣ ማህበረሰቡን በኢኮኖሚ ለማብቃት ትልቅ ድልድይ እንደሚሆን ያላቸውን እምነት ገልጸዋል።

ይህ ጅምር በኢትዮጵያ የዲጂታል ኢኮኖሚ ግንባታ ላይ የራሱን አሻራ እንደሚያርፍም ይጠበቃል።

ዝግባ የህጻናትና አረጋውያን የበጎ አድራጎት ድርጅት የገና በዓልን አስመልክቶ ድጋፍ አደረገ።ዝግባ የህጻናትና አረጋውያን  የበጎ አድራጎት ድርጅት የገና በአልን ምክንያት በማድረግ ድጋፍ አድር...
26/12/2025

ዝግባ የህጻናትና አረጋውያን የበጎ አድራጎት ድርጅት የገና በዓልን አስመልክቶ ድጋፍ አደረገ።

ዝግባ የህጻናትና አረጋውያን የበጎ አድራጎት ድርጅት የገና በአልን ምክንያት በማድረግ ድጋፍ አድርጓል።

ድርጅቱ ወላጆቻቸዉን በሞት ላጡና ለችግር የተጋለጡ ህፃናት ፣ጧሪ ደጋፊ ለሌላቸዉ አረጋዉያን፣ ለችግረኛ ሴቶች የመዓድ ማጋራት፣ የአልባሳት እና ቁሳቁስ ስጦታ በዛሬዉ እለት አካሂዷል።

ከህፃናትና አረጋውያን እንዲሁም ከችግረኛ ሴቶች መካከል በአዲስ አበባ ድጋፍ የሚደረግላቸውን ከ2ዐዐ በላይ ሰዎች ነዉ በአልን ምክንያት በማድረግ ድጋፉ እንደተደረገ ተጠቁሟል።

ድርጅቱ ከ2 ሺህ 650 በላይ ወላጆቻቸውን በሞት ላጡና ለከፋ ችግር የተጋለጡ ሕፃናት እና ጧሪ ያጡ አረጋዊያን እንዲሁም ችግረኛ ሴቶችን በገቢ ማስገኛ ስራ በማሰማራት የድጋፍና እንክብካቤ አገልግሎት እየሰጠ ያለ አገር በቀል የበጎ አድራጎት ድርጅት ነው፡፡

የድርጅቱ ስራ አስኪያጁ አቶ ስለሺ ጌታቸው አሁን በዝግባ ቅጥር ግቢ ውስጥ እና በውጪ ድጋፍ የሚደረግላቸው ህፃናትና አረጋውን ቁጥር ከ3ሺህ 254 በላይ ናቸው ብለዋል።

አሁን ላይ 15 የትራንስፖርት ብቻ ድጋፍ የሚደረግላቸው በጎፈቃዳኞች ሲኖሩ ለ50 ስራተኞች ቋሚ የስራ እድል ፈጥሯል ብለዋል።

አቶ ስለሺ አክለውም ሁሉም ግለሰብ እና ድርጅት ይህን ዘላቂ ድጋፍ ለሚሰጠዉ ድርጅት ድጋፋቸዉን እንዲሰጡ በመግለፅ እስካሁንም አብረዋቸዉ ሲሰሩ የቆዩትን ግለሰቦችና ድርጅቶች አመስግነዋል።

ዝግባ የህጻናትና አረጋውያን መርጃ ድርጅት ኮሜድያን ምትኩ ፈንቴንና አዝመራው ሙሉሰውን የበጎ ፈቃድ አምባሳደር አድርጎ ሾሟል።

ዝግባ የህጻናትና አረጋውያን መርጃ የበጎ አድራጎት ድርጅት ከ3ሺህ 254 በላይ ለከፋ ችግር የተጋለጡ ሕፃናት፣ጧሪ ያጡ አረጋዊያንና በዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ ለሚገኙ ችግረኛ ሴቶችን እየደገፈ ይገኛል።

በአዲስ አበባ በባህርዳር እና እነጅባራ ከተማ የድጋፍና እንክብካቤ አገልግሎት እየሰጠ ያለ ማኅበረሰብ አቀፍ አገር በቀል የበጎ አድራጎት ድርጅት ነው፡፡

ዳሽን ባንክ ከታክስ በፊት 6 ነጥብ 7 ቢሊዮን ብር ማትረፉን አስታወቀ የባንኩ ጠቅላላ ሃብት ከ254 ቢሊዮን ብር በላይ ደርሷልዳሽን ባንክ በበጀት ዓመቱ 6.7 ቢሊዮን ብር አጠቃላይ ትርፍ ያ...
25/12/2025

ዳሽን ባንክ ከታክስ በፊት 6 ነጥብ 7 ቢሊዮን ብር ማትረፉን አስታወቀ

የባንኩ ጠቅላላ ሃብት ከ254 ቢሊዮን ብር በላይ ደርሷል

ዳሽን ባንክ በበጀት ዓመቱ 6.7 ቢሊዮን ብር አጠቃላይ ትርፍ ያስመዘገበ ሲሆን፣ይህም ካለፈው ዓመት ጋር ሲነጻጸር የ5.1% ጭማሪ ማሳየቱ ተገልጿል፡፡

ባንኩ በተጠናቀቀው የበጀት ዓመት (2017) ከፍተኛ የፋይናንስ አፈጻጸም በማስመዝገብ አጠቃላይ ገቢውን ብር 31.4 ቢሊዮን እንዳደረሰ ያስታወቀ ሲሆን፣ ይህም ካለፈው ዓመት ጋር ሲነጻጸር የ34% ከፍተኛ ጭማሪ የታየበት ነው ተብሏል።

ባንኩ በበጀት ዓመቱ ጠቅላላ ሃብቱን ከ254 ቢሊዮን ብር በላይ ያሻገረ ሲሆን፣ ይህም በቀደመው የበጀት ዓመት ከነበረው 183.7 ቢሊዮን ብር ጋር ሲነፃፀር የ38.5 በመቶ ዕድገት የተመዘገበበት ነው፡፡

ከገቢ ዕድገት በተጨማሪ የዳሽን ባንክ የተቀማጭ ገንዘብ መጠን 202.2 ቢሊዮን ብር የደረስ ሲሆን፣ ይህም ከቀደመው ዓመት ጋር ሲነፃፀር የ38.7% ጉልህ ጭማሪ ማሳየቱ ተጠቁሟል::

ከጠቅላላው የባንኩ ተቀማጭ ገንዘብ የዳሸን ባንክ ወለድ ነፃ አገልግሎት (ሽሪክ) የ15.8 ቢሊዮን ብር አስተዋጽኦ ያደረገ ሲሆን፣ ይህም ከባለፈው ዓመት ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲመሳከር የ42.3% ከፍተኛ ዕድገት አሳይቷል:: ባንኩ በውጭ ምንዛሪ ግኝት ረገድም ከፍተኛ አፈፃፀም ያስመዘገበ ሲሆን፣ ከቀደመው ዓመት ጋር ሲነፃፀር የ15.58% ጭማሪ ያለው 1.12 ቢሊዮን የአሜሪካን ዶላር አግኝቷል::

የወለድ ነፃ የባንክ አገልግሎትን ጨምሮ የባንኩ አጠቃላይ የብድር ክምችት መጠን በሂሳብ ዓመቱ መጨረሻ 134 ቢሊዮን ብር የደረሰ ሲሆን፣ ይህም ከቀደመው ዓመት ጋር ሲመሳከር የ17.3% ዕድገት ታይቶበታል፡፡ በሌላ በኩል የባንኩ ካፒታል ባለፈው የበጀት ዓመት መጨረሻ የ2.3 ቢሊዮን ብር ዕድገት በማሳየት 14.3 ቢሊዮን ብር ደርሷል፡፡

የዳሽን ባንክ የዳይሬክተሮች ቦርድ ሊቀመንበር አቶ ዱላ መኮንን፣ ዓመቱ በዓለም አቀፍ ደረጃ የተለያየ ተለዋዋጭ የኢኮኖሚ እንቅስቃሴ የተመዘገበበት እንደነበር አስታውሰው፣ ይሁን እንጂ ዳሽን ባንክ በኢትዮጵያ ዲጂታል ትራንስፎርሜሽን ጉዞ ውስጥ መሪነቱን ያስመሰከረበትን የዳሽን ሱፐር አፕ መተግበሪያ ለመጀመሪያ ጊዜ ለባንክ ኢንዱስትሪው ያበረከተበት ዓመት እንደነበር ተናግረዋል፡፡

የዳሸን ባንክ ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ አስፋው አለሙ በበኩላቸው፣ በበጀት ዓመቱ የባንኩ ባለአክሲዮኖች ላሳዩት ያልተቋረጠ ድጋፍ፣ ደንበኞች ለጣሉት እምነት፣ እንዲሁም የባንኩ ሰራተኞች የላቀ አገልግሎት በመስጠት ላሳዩት ቁርጠኝነት ምስጋናቸውን አቅርበዋል፡፡

ዳሸን ባንከ በተጠናቀቀው የበጀት ዓመት የደንበኞቹን ቁጥር በ17.4% በማሳደግ በጠቅላላው 7.88 ሚሊዮን ያደረሰ ሲሆን፣ በሌላ በኩል የቅርንጫፎቹን ቁጥር በዓመቱ መጨረሻ 906 አድርሷል፡፡ ባንኩ የማህበራዊ ኃላፊነት ተግባራትን ለመወጣት ካለው ቁርጠኝነት ጋር በሚስማማ መልኩ በበበጀት ዓመቱ ለማህበረሰብ ተኮር ስራዎች እንዲሁም ለአካባቢ ጥበቃ ፕሮግራሞች በድምሩ 108.6 ሚሊዮን ብር ድጋፍ አድርጓል፡፡

ጊፍት ሪል ስቴት የገና በዓልን ምክንያት በማድረግ 1000 ቤቶችን በልዩ ሁኔታ ሊሸጥ ነው!ቀዳሚ እንደሆነ የሚመሰከርለት ጊፍት ሪል እስቴት በ2 በመቶ(2%) ቅድመ ክፍያ እስከ 20% ልዩ ቅና...
24/12/2025

ጊፍት ሪል ስቴት የገና በዓልን ምክንያት በማድረግ 1000 ቤቶችን በልዩ ሁኔታ ሊሸጥ ነው!

ቀዳሚ እንደሆነ የሚመሰከርለት ጊፍት ሪል እስቴት በ2 በመቶ(2%) ቅድመ ክፍያ እስከ 20% ልዩ ቅናሽ በማድረግ የአፓርትመንት እና የንግድ ሱቆችን ሽያጭ መጀመሩ ይታወሳል።

በዛሬው እለት ለገሀር አካባቢ በሚገኘው መንደሩ ከዛሬ ጀምሮ ለ14 ቀናት የሚቆይ የገና በዓል የቤቶች የሽያጭ ኤክስፖ ማካሄድ መጀመሩንም ገልጿል።

ሪል እስቴቱ የገና በዓልን ምክንያት በማድረግ “መኖር በጊፍት መንደር!" በሚል መሪ ቃል ነው ሽያጩን የጀመረው።

የጊፍት ሪል እስቴት ካደረጋቸው ኤክስፖዎች የዛሬውን ለየት የሚያደርገው በተሻለ ዋጋ፣ በ2% ቅድመ ክፍያ እስከ 20% ቅናሽ ብቻ የመኖሪያና የንግድ ቤት ባለቤት የማድረግ አጋጣሚን ለሚቀጥሉት ሁለት ሳምንታት መፍጠሩ መሆኑ ተገልጧል።

በ2017 በተዘጋጀው የሽያጭ ኤክስፖ ከ2500 ቤቶች በላይ መሸጣቸው ተገልጾ በዚህም 10 ቢሊየን ብር ገቢ መገኘቱ የተነገረ ሲሆን የበዓል ቅናሹ በአሁኑ ወቅት በለገሃር፣ በተክለ ሀይማኖት፣ በ22 ማዞሪያ፣ በአትላስ ፣ በሲ ኤም ሲ እና በፈረስ ቤት እየገነባቸው ባሉት ዘመናዊ፣ ቅንጡ የመኖሪያና የንግድ አፓርትማ መንደሮች ላይ እንደሆነ ተነግሯል፡፡

በሚያምረው አዲስ በተሰራው አራት ኪሎ ፕላዛ ለአንባቢያን ለደራሲያን የሚመጥን ብራና መፅሐፍ መሸጫ ተከፍትዋል  ከዋካ ቡና ፉት እያሉ እያነበቡ  ስለሚያሳትሙት መፅሐፍ ከአቶ አማረ አበበ ጋር ...
24/12/2025

በሚያምረው አዲስ በተሰራው አራት ኪሎ ፕላዛ ለአንባቢያን ለደራሲያን የሚመጥን ብራና መፅሐፍ መሸጫ ተከፍትዋል ከዋካ ቡና ፉት እያሉ እያነበቡ ስለሚያሳትሙት መፅሐፍ ከአቶ አማረ አበበ ጋር እየተወያዮ ድንቅ ግዜ ያሳልፋሉ ብራና መፅሐፍ

Address

Addis Ababa

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Photo sisay guzay ፎቶ ሲሳይ ጉዛይ posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share