Photo sisay guzay ፎቶ ሲሳይ ጉዛይ

Photo sisay guzay ፎቶ ሲሳይ ጉዛይ This page belongs to photographer Sisay Guzay who is well known by his funny, historical and and ent

ምርጥ ተዋናይት፦ ቃልኪዳን ጥበብ (ትዝታ)
16/11/2025

ምርጥ ተዋናይት፦ ቃልኪዳን ጥበብ (ትዝታ)

11ኛው የጉማ ሽልማት ስነስርዓት ዛሬ ምሽት ይካሄዳል ለዮናስ ብርሃነ መዋና  ለጉማ አዋርድ አዘጋጆች ያለኝን አድናቆት ለመግለፅ እወዳለሁ በነገሮች ሁሉ የተቃናላቸው ከዓመት ዓመት  የተሳካላቸ...
15/11/2025

11ኛው የጉማ ሽልማት ስነስርዓት ዛሬ ምሽት ይካሄዳል
ለዮናስ ብርሃነ መዋና ለጉማ አዋርድ አዘጋጆች ያለኝን አድናቆት ለመግለፅ እወዳለሁ በነገሮች ሁሉ የተቃናላቸው ከዓመት ዓመት የተሳካላቸው ይሁን

ከረጅም ቆይታ በኋላ በጉጉት ሲጠበቅ የነበረው ዳዊት መለሰ "ሚስጥር" በተሰኘው አዲስ አልበም ተለቀቀ ከኢትዮጵያ ተወዳጅ ድምፃዊያን መካከል አንዱ የሆነው ዳዊት መለሰ ከሁለት አስርትና ከዛ በ...
15/11/2025

ከረጅም ቆይታ በኋላ በጉጉት ሲጠበቅ የነበረው ዳዊት መለሰ "ሚስጥር" በተሰኘው አዲስ አልበም ተለቀቀ

ከኢትዮጵያ ተወዳጅ ድምፃዊያን መካከል አንዱ የሆነው ዳዊት መለሰ ከሁለት አስርትና ከዛ በላይ ዓመታት ካስቆጠረው የአልበም ስራ በኋላ "ሚስጥር" የተሰኘው አዲሱ አልበም ተመልሷል።

ህዳር 5 ቀን 2018 ዓ.ም ላይ የተለቀቀው ሚስጥር አልበም፣ 11 ሙዚቃዎችን በውስጡ ያካተተ ሲሆን የዳዊት መለሰ አምስተኛው አልበሙ ነው። በናፍቆትና ፈውስ ላይ የተመሰረተው ይህ አልበም ፍቅርን፣ መራራቅን፣ ትውስታን እና እንደገና ለመጀመር የሚያስፈልገውን ጥንካሬን ይገልጻል።

በሙዚቃ አሬንጅመንት አበጋዝ ክብረወርቅ፣ ሚካኤል ኃይሉ እና ቢኒያም ተሳትፈውበታል።

የአልበሙ ምርቃት ከረዥም ጊዜ የኢንዱስትሪ አጋሮች በመሆን በልዩ የኮክቴል ድግስ ትናንት ምሽት በሲግናቸር የተካሄደ ሲሆን ተጋባዥ እንግዶች በመጀመሪያ ከሚስጥር አልበም ውስጥ የተመረጡ ስራዎችን፣ በመቀጠልም ከሙዚቃው በስተጀርባ የነበረውን ሂደት ከዳዊትና የስራ አጋሮቹ ጋር በመሆን ታድመዋል።

ሙዚቃው በዳዊት መለሰ የዩቲዩብ ቻናል እና በዓለም አቀፍ የሙዚቃ ማሰራጪያ መተግበሪያዎች ላይ ተለቋል።

አባይ ሆምስ የዳውንታውን ፕሮጀክቱን በይፋ አስጀመረአባይ ሆምስ የዳውንታውን ፕሮጀክቱን በሜክሲኮ አፍሪካ ህብረት አካባቢ በዛሬው እለት በይፋ አስጀምሯልላለፉት ሁለት አስርት ዓመታት በርካታ ተ...
14/11/2025

አባይ ሆምስ የዳውንታውን ፕሮጀክቱን በይፋ አስጀመረ

አባይ ሆምስ የዳውንታውን ፕሮጀክቱን በሜክሲኮ አፍሪካ ህብረት አካባቢ በዛሬው እለት በይፋ አስጀምሯል

ላለፉት ሁለት አስርት ዓመታት በርካታ ተሽከርካሪዎችን በመገጣጠም፣ በመጠገን፣ በማስመጣት እና በመሸጥ የሚታወቀው አባይ የቴክኒክ እና ንግድ አ.ማ. ላለፉት ሁለት ዓመታት አባይ ሆምስ በሚል የንግድ ስያሜ ወደ ሪል እስቴት ልማት በመግባት ሜክሲኮ ጠማማ ፎቅ ፊት ለፊት በሚገኘው ይዞታው ላይ 3B+G+30 የሆነ ግዙፍ እና በርካታ አገልግሎቶችን የያዘ ቅይጥ የንግድ እና የመኖሪያ ህንፃ ለመገንባት አስፈላጊውን ቅድመ ዝግጅት አጠናቆ ወደ ስራ መግባቱ ተገልጿል።

ይህ ፕሮጀክት 12,000 ካሬ ሜትር ይዞታ ውስጥ ያረፈ ጌትድ ኮምፓውንድ ሲሆን በውስጡም ምቹ እና በቂ የሆነ የመኪና ማቆሚያ ስፍራ፣ የኤሌክትሪክ መኪኖችን ቻርጅ ማድረጊያ፣ የከርሰ ምድር ውሃ፣ ለህጻናት እና አዋቂዎች የሚሆኑ 2 የዋና ገንዳዎች ፣ የጋራ መዝናኛ ስፍራን ፣ ለእያንዳንዱ ህንፃ 8 አሳንሰሮችን እንዲሁም ከ 12 ካሬ ጀምሮ ዘመናዊ የንግድ ሱቆችና ሌሎች በርካታ መገልገያዎችን በውስጡ ያካተተ ምቹ የንግድ ማእከል እና የመኖሪያ ስፍራ እንደሆነ ተነግሯል፡፡

የግንባታው ፕሮጀክት አጠቃላይ ተሰርቶ ሲያልቅ 576 አፓርትመንትና 700 የሚደርሱ የንግድ ሱቆችን የሚይዝ ሲሆን በአጠቃላይ 4.5 ቢሊየን ብር ወጪ ይፈጃል ተብሏል

በ3 አመት ተኩል ውስጥ ይጠናቀቃል ተብሎ የታሰበው ይህ ዳውን ታውን ፕሮጀክት በካሬ ከ81,000 ብር ጀምሮ የአፓርትመንት ቤቶችን በመሸጥ ላይ እንደሚገኝ ተነግሯል

150 የሚደርሱ ቋሚ ሰራተኞች ያሉት ሲሆን ይህ ዳውንትውን ፕሮጀክት ከ500 በላይ ለሆኑ ሰዎች የስራ እድል ይፈጥራል

በመግለጫው እንደተገለጸው በሪል እስቴት ዘርፉ ላይ የወጡ አዳዲስ የመንግስት ፖሊሲዎች በፕሮጀክቱ አጀማመር ላይ ትልቅ ተግዳሮት ፈጥረው እንደነበር ተገልጿል

አባይ ሆምስ የዛሬውን የማስጀመሪያ መርሀገብር ምክንያት በማድረግ ከዛሬ ጀምሮ እስከ እሁድ ህዳር 7 ድረስ በ5% ቅድመ ክፍያ ብቻ የቤት ሽያጭ ያካሄዳል ተብሏል

 #ምርቃት ከነገ ቅዳሜ እስከ ማከስኞ/20/18 በዘፐልስ ላውንጅ አይቀርም።አክበራችሁን ስለምትገኙ እናመሰግናለንAlemensh Kumsa  ነይ አድራሻ  ንገሪ
14/11/2025

#ምርቃት ከነገ ቅዳሜ እስከ ማከስኞ/20/18 በዘፐልስ ላውንጅ አይቀርም።አክበራችሁን ስለምትገኙ እናመሰግናለን
Alemensh Kumsa ነይ አድራሻ ንገሪ

በዳሞ መንግሥቱ የተጻፈ “ያልተሻገርነው ድልድይ” የተሰኘ ግሩም መጽሐፍ ለህትመት በቃ፡፡ደራሲው ከጥልቅ የህይወት ልምዱ በመነሳት ስለ ሀገራችን ኢኮኖሚያዊ እና ማህበራዊ ህይወት የሚመለከቱ ጉዳ...
13/11/2025

በዳሞ መንግሥቱ የተጻፈ
“ያልተሻገርነው ድልድይ” የተሰኘ
ግሩም መጽሐፍ ለህትመት በቃ፡፡

ደራሲው ከጥልቅ የህይወት ልምዱ በመነሳት ስለ ሀገራችን ኢኮኖሚያዊ እና ማህበራዊ ህይወት የሚመለከቱ ጉዳዮች ከአዝናኝ እና አስተማሪ ከሆኑ ዓለም አቀፍ ገጠመኞቹ ጋር በማዋሀድ ትዝብቱን እና ያልተሻገርናቸውን ድልድዮች ለመሻገር ምን ብናደርግ እንደሚሻል የግል ምልከታውን ከመፍትሔ ሃሳቦች ጋር ያጋራል ::

በእርግጠኝነት የምንነግሮ መፅሀፉን አንብበው ይወዱታል ኪስን በማይጎዳ ዋጋ አትርፋችሁ ትዝናኑበት ዘንድ እየጋበዘን መጽሀፉ :-

በጃፋር የመጽሐፍ መደብር፣
በሀሁ የመጽሐፍ መደብር እና በኤዞፕ የመጽሐፍ መደብር እንደሚገኝ ስንጠቁም በደስታ ነው፡፡

“ያልተሻገርነው ድልድይ”

13/11/2025

ዘ ፐልዝ ላውንጅ

ከ15  እስከ 20 ሚልየን  ብር  እንደ ፈጀ  የተነገረለት  ፐልዝ ላውንጅ የፊታችን ከህዳር 6 እስከ 9 በይፋ ይመረቃል ከተከፈተ 2 ወራትን ያስቆጠረው ዘ ፐልዝ ላውንጅ ከህዳር 6 እስከ 9...
13/11/2025

ከ15 እስከ 20 ሚልየን ብር እንደ ፈጀ የተነገረለት ፐልዝ ላውንጅ የፊታችን ከህዳር 6 እስከ 9 በይፋ ይመረቃል

ከተከፈተ 2 ወራትን ያስቆጠረው ዘ ፐልዝ ላውንጅ ከህዳር 6 እስከ 9 በይፋ እንደሚመረቅ ባለቤቶቹ በዛሬው እለት በሰጡት መግለጫ አስታውቀዋል

በመግለጫው እንደተገለጸው ዘ ፐልዝ ላውንጅን ለመክፈት ከ15 እስከ 20 ሚልየን ብር ብር ፈጅቷል ተብሏል።

በምረቃ ስነስርዓቱ ላይ ጥሪ የተደረገላቸው የተለያዩ እንግዶች የሚገኙ ሲሆን ሶስቱንም ቀን የተለያዩ የሙዚቃ ባንድ ባለሙያዎች ስራቸውን እንደሚያቀርቡ ተገልጿል።

ዘ ፐልዝ ላውንጅ ወደፊት ከቢዝነሱ ባለፈ የበጎ አድራጎት ስራ ላይ ለመሳተፍ ማሰቡም ተነግሯል

ከ 45 በላይ ሰራተኞች የስራ እድል እንደ ፈጠረ የተገለፀው ዘ ፐልዝ ላውንጅ የ24 ሰአት አገልግሎት ይሰጣል ተብሏል።
#ድሬቲዩብ

እናት ባንክ በኢትዮጵያ የመጀመሪያውን  የፆታ ቦንድ አስጀመረህዳር 4 2018  እናት ባንክ አ.ማ አካታችና ቀጣይነት ያለው የፋይናንስ ስርዓት በመዘርጋት ውስጥ ያለውን መሪነት የሚያጎላ ፈርቀ...
13/11/2025

እናት ባንክ በኢትዮጵያ የመጀመሪያውን የፆታ ቦንድ አስጀመረ
ህዳር 4 2018 እናት ባንክ አ.ማ አካታችና ቀጣይነት ያለው የፋይናንስ ስርዓት በመዘርጋት ውስጥ ያለውን መሪነት የሚያጎላ ፈርቀዳጅ ርምጃ በውሰድ የፆታ ቦንድ ሽያጭ መዋቅር መጀመሩን ይፋ አደረገ
በአፍሪካ በጥቂት ሃገራት ብቻ እየተተገበረ ያለው የጾታ ቦንድ ሽያጭ ኢትዮጵያም በእናት ባንክ በኩል ልትቀላቀል ነው

የጾታ ቦንድ ሽያች፣ የኢትዮጵያን የፋይናንስ ተደራሽነት የጾታ ከፍ+ትን ከ19 በመቶ ወደ 10 nama has th Oላማው ከሆነው Pltiራዊ የፋይናንስ ተደራሽነት ስልት - 1 12021-2025 AXA) ጋር A noሙA poሚስማማ : በተጨማሪም የዘላቂ ልማት ግቦችን (SDG 5: Pጸታ እኩልነት እና SDG 8: ከተስማሚ የNG ምኅዳር እና ኢኮኖሚያዊ እድገት) እንዲሁም ከአፍሪካ ኅብረት አጀንዳ 2063 ጋራ የተጣጣመ ነው።

ቦንዱ የኢትዮጵያ የካፒታል ገበያ ባለሥልጣን መመሪያዎች፣ የኢትዮጵያ የስነድ ሙዓለ ንዋዮች ገበያ የምዝገባ መስፈርቶች፣ የብሔራዊ ባንክ መመዘኛዎች፤ የዓለም ዐቀፉ የካፒታል ገበያ ማኅበር (ICMA) እና የማኅበራዊ ቦንድ መርሖዎችን (2025) መሠረት ባደረገ መልኩ የተዘጋጀ ሲሆን፣ ደምብ እና ግዴታዎች በሙሉ የተከበሩበት ሂደትን ያለፈ ነው።

ይህ ጅማሮ በብሔራዊ ባንክ ዕውቅና ላይ የተመሠረተ ሲሆን፣ ባንኩ እንደ አውሮፖውያን አቈጣጠር በ2025 በተካሄደው የመጀመሪያው የጾታ ፋይናንስ ተደራሽነት መረጃ ጠቋሚ ላይ "ለውጥ አምጪ" ደረጃ ያገኘ ብቸኛው የንግድ ተቋም ሆኖ ተመዝግቧል። ይህ ዕውቅና ለጾታ ተደራሽነት ምላሽ ሰጪ አመራር፣ በአዳዲስ እገልግሎቶች እና በብሔራዊ ባንክ ሁሉን ዐቀፍ ፋይናንስ እና የጾታ እኩልነት አጀንዳ የእናት ባንክን ቀዳሚነት የሚያጎላ ሆኖ ቀርቧል።

ይሀ ስልታዊ ትስስር እያደገ የመጣውን የኢትዮጵያ የካፒታል ገበያ እና የፋይናንስ ተቆጣጣሪ መሠረተ ልማ7 በመጠቀም፣ ለጾታ እኩልነትና ሁሉን ዐቀፍ እድገት፣ የግል ኢንቨስትመንትን በማሰባሰብ ረገድ እናት ባንክን ቀዳሚ ተዋናይ አድርጎ ያስቀምጠዋል።

ለቀጣይነት ላለው ተጽዕኖ የሚደረግ አጋርነት

አይ ካፒታል ኢንስቲትዩት ንላፊነቱ የተወሰነ የግል ማኅበር፣ እንደ ግብይት አማካሪነቱ የጾታ ቦንድ ሽያጭ መዋቅርበመዘርጋት እና ማዕቀፍ በማዘጋጀት ያማክራል። ይህንም የሚያደርገው በኢትዮጵያ ካፒታል ገበያ ባለሥልጣን (ECMA)፣ በብሔራዊ ባንክ እና በኢትዮጵያ የሰነድ ሙዓለ ንዋዮች ገበያ (ESX) አግባብነት ያላቸው መመሪያዎችን መሠረት በማድረግ ነው። አማካሪው ተቋም፣ የቦንድ ሽያጩ በዓለም ዐቀፍ ደረጃ ተቀባይነት ካለው አሠራር ጋራ የተስማማ እና የተመረጡ ልምዶችን ከግምት የከተተ መሆኑን የማረጋገጥ ኀላፊነት አለበት።

በተጨማሪም፣ ይሀን ታላቅ የቦንድ ሽያጭ ገበያ ክፍት በማድረግ ከባለድርሻ አካላት ጋር ያለውን ተሳትፎ

ይህ ትብብር፣ የኢትዮጵያን የመጀመሪያውን የጾታ ቦንድ ማዕቀፍ በማዘጋጀት ከተቆጣጣሪዎች፣ ከባለሀብቶች እና ከልማት አጋሮች ጋር በመተባበር በመሥራት፣ለወደፊቱ በዚሁ ሞዴል ልዩ ትኩረት በሚፈልጉ እና እንደ ማኅበራዊ ጕዳዮች፣ አረንጓዴ እና ዘላቂነት ባላቸው ሌሎች ተመሳሳይ የቦንድ ፋይናንስ አቅርቦቶች ላይይሰማራል።

በ   Taye (ፋቡላ) የተዘጋጀው "መልቲ" አዲስ ኮሜዲ ቴአትር እሁድ በ11:30 በአዶት ሲኒማ ይመረቃል እንዳያመልጣችሁ!
13/11/2025

በ Taye (ፋቡላ) የተዘጋጀው "መልቲ" አዲስ ኮሜዲ ቴአትር እሁድ በ11:30 በአዶት ሲኒማ ይመረቃል እንዳያመልጣችሁ!

"መልቲ" የተሰኘ አዲስ ትያትር ለዕይታ ሊበቃ ነው።የኮሜዲ ዘውግ ያለው "መልቲ" ትያትር በመልቲ የትያትር ቡድን ተደርሶ በስንታየሁ ታዬ (ፋቡላ) የተዘጋጀ ነው።የትያትር ወዳጆችን እርካታ ለመ...
12/11/2025

"መልቲ" የተሰኘ አዲስ ትያትር ለዕይታ ሊበቃ ነው።

የኮሜዲ ዘውግ ያለው "መልቲ" ትያትር በመልቲ የትያትር ቡድን ተደርሶ በስንታየሁ ታዬ (ፋቡላ) የተዘጋጀ ነው።

የትያትር ወዳጆችን እርካታ ለመሙላት በማሰብ ከፍ ባለ ሙያዊ ጥንቃቄ ለአንድ አመት ያህል በተዋንያን መረጣ፣ አልባሳትና መሰል ሙያዊ ዝግጅቶች ላይ ቆይቷል።

የታሪክ ማጠንጠኛውን በዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች ላይ ያደረገው ትያትሩ ከአመታት በፊት በአዲስ አበባ ቴአርትና ባህል አዳራሽ-ማዘጋጃ ቤት ለዕይታ በቅቶ በተመልካቾች ዘንድ ከፍ ያለ አድናቆትና ተወዳጅነትን ማግኘት ችሎም ነበር።

ዘመኑን በሚመጥንና በአዳዲስ ሀሳቦች ዳግም የተዘጋጀው ትያትሩ ምትኩ በቀለ፣ ኤልሻዳይ ከበደ፣ ሱራፌል ብስራት፣ ቴዎድሮስ ሸዋንግዛው፣ አቤል ሰለሞን እና ሰላማዊት ካሳዬ ይተውኑበታል።

የትያትሩ አዘጋጆች በሰጡት መግለጫ ህዳር 7 ቀን 2018 ዓ.ም ጥሪ የተደረገላቸው ታላላቅ የኪነ ጥበብ ባለሙያዎች፣ የትያትርና ፊልም መምህራን ብሎም የተመረጡ እንግዶች በተገኙበት በቀይ ምንጣፍ ስነ ስርዓት ይመረቃል።

ከምርቃቱ በኋላም ዘወትር አርብ በ12:00 ሰዓት ብስራተ ገብርኤል በሚገኘው አዶት ሲኒማ መታየት ይጀምራል።

በዕለቱም አንጋፋ የኪነ ጥበብ ባለሙያዎች እና ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች በተገኙበት የትያትሩ ምርቃት ይከናወናል፤ ትያትር ወዳጆች እንዲገኙም ተጋብዘዋል።

በሌላ በኩል
የትያትር ተመልካቾች የቴአትር ቤት መግቢያ ትኬታቸውን በእናት ባንክ የዲጂታል ባንኪንግ ሲስተም መቁረጥ የሚያስችላቸውን አሰራር በዕለቱ ይፋ ሆኗል።

በዚህ አሰራር መሰረት ትያትር ተመልካቾች የመግቢያ ትኬታቸውን በእናት ባንክ ዲጂታል ባንኪንግ አማካኝነት በቀላሉ መቁረጥ የሚችሉ ይሆናል።

ይህንን አሰራር ለመጀመሪያ ጊዜ አዶት ሲኒማ ከእናት ባንክ እና ከመልቲ የትያትር ቡድን ጋር የመግባቢያ ስምምነት ፊርማ በመፈራረም ያስጀመሩ ሲሆን በቀጣይ በሌሎች ትያትር እና ሲኒማ ቤቶች አሰራሩ ተግባራዊ መሆን ይጀምራል።

አትሌት መሰረት ደፋር የአእምሮ አድገት ዉስንነት ያለባቸዉን ህፃናትን ጎበኘች! ራዕይ የህፃናት መርጃ ድርጅት እ.ኤ.አ 2016 ዓ.ም  በዶክተር ፅጌ  ጥበቡ አማካኝነት በኢትዮጵያ የተቋቋመ መ...
11/11/2025

አትሌት መሰረት ደፋር የአእምሮ አድገት ዉስንነት ያለባቸዉን ህፃናትን ጎበኘች!

ራዕይ የህፃናት መርጃ ድርጅት እ.ኤ.አ 2016 ዓ.ም በዶክተር ፅጌ ጥበቡ አማካኝነት በኢትዮጵያ የተቋቋመ መንግስታዊ ያልሆነ ለትርፍ ያልተቋቋመ አለም አቀፍ ድርጅት ሲሆን የአእምሮ እድገት ውስንነትና ሌሎች የአካል ጉዳት ያለባቸውን ህፃናትና ወጣቶች በመንፈሳዊ ስሜታዊ ትምህርታዊና ሙያዊ ፕሮግራሞች በመደገፍ በክብርና በነፃነት እንዲማሩ እንዲሰሩና እንዲኖሩ የሚያስችል ከባቢን ለመፍጠር እየሰራ የሚገኝ በጎ አድራጎት ድርጅት ነዉ።

ራዕይ የህፃናት መርጃ ከ2014 ዓ.ም ጀምሮ የአእምሮ እድገት ውስንነት ያለባቸውን ወጣቶች በሸማ ሙያ፣ በኮምፒውተር (ኮዲንግ) በሙዚቃ, በሥነ ሥዕል በስፖርት እና በሌሎችም ዘርፎች 1300 በላይ ተጠቃሚዎችን በማሰልጠን እንዲሁም የሕክምናና ሌሎች አስፈላጊ ድጋፎችን እየሠደረገ ይገኛል።

ለትምህርት ከፍተኛ ትኩረት በመስጠት ራዕይ የህፃናት መርጃ በአዲስ አበባ ኢትዮጵያ ውስጥ በመንግስት ትምህርት ቤቶች ለተመዘገቡ ህጻናት የትምህርት ቁሳቁሶችን ያቀርባል። እስካሁን 126 ተማሪዎችን ደግፏል።

ራዕይ የህፃናት መርጃ ዓላማው ልጆችን በትምህርት ቤት ለመወጣት ጠንካራ ሙያዎችን ለማዳበር እና የማህበረሰባቸው ንቁ አባላት እንዲሆኑ የሚያስፈልጋቸውን ችሎታዎች ለማጉላት እንዲያግዝ አትሌት መሰረት ደፋርን ብራንድ አንባሳደር አድርጎ ሾሟል።

በህብረተሰባችን ውስጥ ችላ ከተባሉ ልጆች ጋር በመስራት ራዕይ የህፃናት መርጃ የወደፊት ህይወታቸውን ከፍ ለማድረግ እና ለህይወታቸው አዎንታዊ እይታን ለመስጠት ብዙ ስራዎችን እንደምትሰራም አትሌት መሰረት ደፋር ገልፃለች።

ራዕይ የህፃናት መርጃ ዓላማው ልጆች በትምህርት ቤት ስኬታማ እንዲሆኑ የሚያስፈልጋቸውን ችሎታዎች ለማስታጠቅ ጠንካራ ሙያዎችን ለማዳበር እና የማኅበረሰባቸው-ግንኙነታቸው ንቁ አባላት እንዲሆኑ ማድረግ እንደሆነ እና በዚህ በጎ አድራጎት ስራ ላይ እነዚህን ህፃናት በመደገፍ እና ህይወታቸዉ ላይ ለዉጥ ለማምጣት ህብረተሰቡ እንዲቀላቀል የድርጅቱ መስራች ዶ/ር ፅጌ ጥበቡ ጥሪ አቅርበዋል።

ራዕይ የህፃናት መርጃ ድርጅት በበዛሬው ዕለትም ድጋፍ ከሚያደርግባቸው ት/ት ቤቶች ውስጥ በትንቢተ ኤርሚያስና በስብስቴ ነጋሲ ት/ቤቶች የሚማሩ የአእምሮ እድገት ውስንነት ያለባቸው ልጆች የሚሰሯቸውን የሙያ ስራዎች እንዲሁም ህፃናቱን ያሉበትን ሁኔታ በአካል በመገኘት ጉብኝት አካሂዷል።

Address

Addis Ababa

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Photo sisay guzay ፎቶ ሲሳይ ጉዛይ posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share