Addis-Finfine press

Addis-Finfine press It is the page on Ethiopia political, ecomonic and socail timely development

ይችን ሰውዬ በድራፍት ሆዷ እስክንጠለጠል ጋቷትና አስክረው እንደስልክ እንችጨት እቋሟት?የስራችውን ይስጣችሁ
23/08/2026

ይችን ሰውዬ በድራፍት ሆዷ እስክንጠለጠል ጋቷትና አስክረው እንደስልክ እንችጨት እቋሟት?
የስራችውን ይስጣችሁ

"ከተመካከርን፣ ከተነጋገርን፣ ከተደማመጥን ውጤት ላይ እንደምንደርስ አይተናል" - የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ዋና ኮሚሽነር መስፍን አርዓያ (ፕ/ር)
22/08/2026

"ከተመካከርን፣ ከተነጋገርን፣ ከተደማመጥን ውጤት ላይ እንደምንደርስ አይተናል" - የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ዋና ኮሚሽነር መስፍን አርዓያ (ፕ/ር)

የህዉሃት ድረሱልኝ ተማጽኖ ተቀባይነት አጥቷል የህዉሃት ቡድን የፌዴራል መንግስት እንዲሁም የአለምአቀፉ ማህበረሰብ አዉዳሚ ጦርነት ሳይፈነዳ ወደ ድርድር እንደሚመጣ ያደረጉትን ጥረት አልቀበልም...
22/08/2026

የህዉሃት ድረሱልኝ ተማጽኖ ተቀባይነት አጥቷል

የህዉሃት ቡድን የፌዴራል መንግስት እንዲሁም የአለምአቀፉ ማህበረሰብ አዉዳሚ ጦርነት ሳይፈነዳ ወደ ድርድር እንደሚመጣ ያደረጉትን ጥረት አልቀበልም በማለት ጦርነት መጀመሩ የሚታወቅ ነዉ፡፡
የጥቂት ግለሰቦችን ፋላጎቱን በሃይል ብቻ ለማስፈፀም የሚፍጨረጨረዉ ስብስቡ ዉጊያ ከፍቶ ሽንፈት ሲያስተናግድ የድረሱልኝ ልመና ላይ ተጠምዷል፡፡
በአሁኑ ሰዓት ትናንት ወደ ሰላም እና ድርድር እንዲመጣ ሲጎተጉተው የነበረውን የዓለማቀፍ ማህበረሰብ ፊት ነስቶ ካባረረ በኋላ እየተወሰደበት የሚገኘውን የድሮን ዕርምጃ እንዲያወግዝ እና እንዲያደራድር ድረስልኝ ብሎ ቢማጸነውም ጆሮ ዳባ ብሎታል፡፡
#የዲፕሎማሲ መንገድ ያዳከመዉ ህዉሃት የጀመረዉን ጦርነት ለመዉጣት ከፈለገ ለፌዴራል መንግስት እጅ መስጠት ብቻ እንደሆነ የአለምአቀፉ ማህበረሰብ አማራጭ መንገድ አመላክቷል፡፡

"ከተነጋገርን ችግሮቻችንን እንፈታለን። በመሣሪያ ምንጊዜም ያሸነፈ ኃይል የለም። ምንጊዜም ማሸነፍ የሚቻለው በጋራ ማሸነፍ ሲቻል ነው።"የሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ዋና ኮሚሽነር ፕሮፌሰር መስፍን...
22/08/2026

"ከተነጋገርን ችግሮቻችንን እንፈታለን። በመሣሪያ ምንጊዜም ያሸነፈ ኃይል የለም። ምንጊዜም ማሸነፍ የሚቻለው በጋራ ማሸነፍ ሲቻል ነው።"

የሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ዋና ኮሚሽነር ፕሮፌሰር መስፍን አርአያ

ተላላኪ ፅንፈኛ! #"ፅንፈኛ ሆድ እንጂ ህሊና የለውም የምንለው በምክንያት ነው" !በኢትዮጵያዊያን ባህልና እሴት ውስጥ ሀዘን የሁላችንም ወሰን የሌለው የጋራ ድልድይ ነው። ጠላት እንኳን ቢሆን...
22/08/2026

ተላላኪ ፅንፈኛ!

#"ፅንፈኛ ሆድ እንጂ ህሊና የለውም የምንለው በምክንያት ነው" !
በኢትዮጵያዊያን ባህልና እሴት ውስጥ ሀዘን የሁላችንም ወሰን የሌለው የጋራ ድልድይ ነው። ጠላት እንኳን ቢሆን በሀዘን ጊዜ መሳሪያውን አውርዶ ይደርሳል፤ የሰውን ህመም ያከብራል። ይህ የቆየ ጨዋነታችንና የህሊናችን ሚዛን ነበር።
ነገር ግን ዛሬ ላይ የፖለቲካ ትርፍና የላይክ/ቪው አባዜ ህሊናቸውን ያሳወራቸው እነ መሳይ መኮንን ያሉ ሀረመኔዎች እህታቸው በማረፏ ምክንያት የቤተሰብ ሀዘን ለመድረስ ወደ አሜሪካ ያቀኑትን ፕሮፌሰር መስፍን አርዓያን "ወደ አሜሪካ ኮበለሉ" በሚል የሀሰት ሰበር ዜና ሲያጧጡፉ ተስተውለዋል።
መላው የኢትዮጵያ ሕዝብ ማወቅ ያለበት እነዚህ ሰዎች
የሰዎችን እውነተኛ ሀዘንና ስቃይ ለርካሽ የፖለቲካ ንግድ እንዴት እንደሚያውሉና ምን ያህል የሞራል ዝቅጠት ውስጥ እንደገቡ ነው። ፅንፈኝነትና የትርክት ፖለቲካ የሰውን ልጅ አእምሮ ሲቆጣጠረው፣ እውነትን ከውሸት፡ ሰብአዊነትን ከጥል ማለያየት እንዳይችል በመሳይ መኮንን አይተናል።

22/08/2026
"ዕዙ ከሕዝብና ከመንግሥት የሚሰጠውን ማንኛውንም ግዳጅ ከትናንት በላቀ ደረጃ ለመወጣት ዝግጁ ነው" - ሌተናል ጄኔራል ሹማ አብደታየልዩ ዘመቻዎች ዕዝ ዋና አዛዥ ሌተናል ጄኔራል ሹማ አብደታ ...
22/08/2026

"ዕዙ ከሕዝብና ከመንግሥት የሚሰጠውን ማንኛውንም ግዳጅ ከትናንት በላቀ ደረጃ ለመወጣት ዝግጁ ነው" - ሌተናል ጄኔራል ሹማ አብደታ

የልዩ ዘመቻዎች ዕዝ ዋና አዛዥ ሌተናል ጄኔራል ሹማ አብደታ ይህንን የገለጹት፤ ዕዙ በብላቴ ማሰልጠኛ ማዕከል ልዩ ሥልጠናቸውን ሲከታተሉ የቆዩ የ45ኛ ዙር 'ጽናት' ኮርስ ኮማንዶ ሠልጣኞችን ባስመረቀበት ወቅት ነው።

በምረቃ መርሐ-ግብሩ ላይ ዋና አዛዡ እንደተናገሩት፤ የልዩ ዘመቻዎች ዕዝ ወታደራዊ ዝግጁነቱንና የማስፈጸም አቅሙን ወደ ላቀ ደረጃ እያሸጋገረ ይገኛል። ዕዙ “በየትኛውም ቦታና ጊዜ ከመንግሥት፣ ከሕዝባችንና ከተቋማችን የሚሰጠንን ማንኛውንም ግዳጅ ከትናንት በላቀ ደረጃ ለመወጣት ጠላቶች ከሚገምቱት በላይ ዝግጁ ነን” ብለዋል።

የልዩ ዘመቻዎች ዕዝ ከተመሠረተበት ጊዜ አንስቶ የተሰጡትን ታላላቅ ሀገራዊ ግዳጆች ሁሉ በላቀ ድል እየፈጸመ የመጣ ጠንካራ ኃይል መሆኑን ያነሱት ሌተናል ጄኔራል ሹማ አብደታ፤ ዕዙ በአስቸጋሪ ወቅትና ሁኔታዎች ከፊት በመሰለፍ እናት ሀገሩንና ሕዝቡን ከተጋረጠበት አደጋ መታደጉንም አስታውሰዋል።

ዛሬ ላይ ዕዙ ታሪኩን ጠብቆ ለመጓዝና ራሱን ለበለጠ ሀገራዊ ግዳጅ ለማዘጋጀት፤ ዘመኑን በዋጀ መንገድ ለኢትዮጵያ የሚመጥኑ ልዩ ኃይሎችን በላቀ ደረጃ እያበቃ እና አቅሙን እያጠናከረ እንደሚገኝም አብራርተዋል።

በወንድወሰን አፈወርቅ

Ethiopian Broadcasting Corporation #መከላከያ #ኢትዮጵያ

የፀረ ሰው ልጆች ጥምረት የሆነው ጽምዶ በይፋ እየተበታተነ ነው !!በግብጽ የገንዘብ ድጋፍ፣ በሻዕቢያ ማኒፌስቶ ቀራጭነት እና በህወሓት የቅርብ አስተባባሪነት የተመሰረተው የፀረ ሰላሞችና የፀረ...
22/08/2026

የፀረ ሰው ልጆች ጥምረት የሆነው ጽምዶ በይፋ እየተበታተነ ነው !!

በግብጽ የገንዘብ ድጋፍ፣ በሻዕቢያ ማኒፌስቶ ቀራጭነት እና በህወሓት የቅርብ አስተባባሪነት የተመሰረተው የፀረ ሰላሞችና የፀረ ልማቶች ስብስብ የሆነው ጽምዶ በይፋ እየተፈረካከሰ ይገኛል። በተለይም በዚህ የጸረ ሰው ልጆች ጥምረት የጉልበት ድጋፍ የሚሰጡት የአማራ እና የኦሮሞ ጽንፈኛ ሃይሎች ጥምረቱ እነሱ ጋር በፈለጉት እና በታሰበለት መንገድ እየሄደ በመሆኑ እርስ በራሳቸው ግጭት ውስጥ ገብተዋል።

በዚህ የጽንፈኞች ጥምረት ላይ ቀድሞ ተሳፍሮ የነበረው የኦሮሞ ጽንፈኞችን የሚወክለው ጃዋር መሃመድ ከጽምዶ ቡድን በቀዳሚነት የተባረረ ሰው መሆን ችሏል። በመሆኑም ሻዕቢያ እና ህወሓት የነኩት ነገር በሙሉ ስደት፣ ሞት ፣ ርሃብ እና ግጭት ነውና እነዚህ ጽንፈኛ ሃይሎች የዚህ ጽምዶ አባልነታቸውን በመተው የጽምዶን መክሰም በይፋ በአፋቸው እየተናገሩ፣ በድርጊታቸውም እያሳዩን ይገኛሉ።

Address

African Union
Addis Ababa

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Addis-Finfine press posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to Addis-Finfine press:

Shortcuts

Share