
26/06/2025
በቀጣይ አመት ማስተማር የማይችሉ ት/ቤቶች
በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የትምህርትና ስልጠና ጥራት ቁጥጥር ባለስልጣን በ2018 የትምህርት ዘመን ማስተማር የማይችሉና እውቅናቸው የተሰረዘ ትምህርት ቤቶችን አሳውቋል።
በ2016 ዓ.ም ማጠቃለያ ላይ በተደረገው የእድሳት ፍቃድ ምዘና ለ2017 የትምህርት ዘመን ካሳዩት ዝቅተኛ ውጤት መሻሻል እንዲያሳዩ እስከ 2017 ዓ.ም ታህሳስ ድረስ ዝግጅት እንዲያደርጉ ፤ በ2017 የትምህርት ዘመን ላይ በማስጠንቀቂያ እንዲያስተምሩ ጊዜ ቢሰጣቸውም በታህሳስ 2017 በተደረገ የእድሳት ፍቃድ ምዘና ውጤታቸው መሻሻል ባለማሳየቱና ዝቅተኛና ከደረጃ በታች በመሆኑ ምክንያት በ2018 የት/ት ዘመን ማስተማር የማይችሉ መሆኑን የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የትምህርትና ስልጠና ጥራት ቁጥጥር ባለስልጣን አሳውቋል።
በመሆኑም የትምህርት ማህበረሰቡ እና ወላጆች ይህን በማወቅ የቅድመ ዝግጅት ተግባራት እንድታከናውኑ ሲል አሳውቋል።