Ethio Education News/ኢትዮ ትምህርት

Ethio Education News/ኢትዮ ትምህርት Educational information at all levels

በቀጣይ አመት ማስተማር የማይችሉ ት/ቤቶች በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የትምህርትና ስልጠና ጥራት ቁጥጥር ባለስልጣን በ2018 የትምህርት ዘመን ማስተማር የማይችሉና እውቅናቸው የተሰረዘ ት...
26/06/2025

በቀጣይ አመት ማስተማር የማይችሉ ት/ቤቶች

በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የትምህርትና ስልጠና ጥራት ቁጥጥር ባለስልጣን በ2018 የትምህርት ዘመን ማስተማር የማይችሉና እውቅናቸው የተሰረዘ ትምህርት ቤቶችን አሳውቋል።

በ2016 ዓ.ም ማጠቃለያ ላይ በተደረገው የእድሳት ፍቃድ ምዘና ለ2017 የትምህርት ዘመን ካሳዩት ዝቅተኛ ውጤት መሻሻል እንዲያሳዩ እስከ 2017 ዓ.ም ታህሳስ ድረስ ዝግጅት እንዲያደርጉ ፤ በ2017 የትምህርት ዘመን ላይ በማስጠንቀቂያ እንዲያስተምሩ ጊዜ ቢሰጣቸውም በታህሳስ 2017 በተደረገ የእድሳት ፍቃድ ምዘና ውጤታቸው መሻሻል ባለማሳየቱና ዝቅተኛና ከደረጃ በታች በመሆኑ ምክንያት በ2018 የት/ት ዘመን ማስተማር የማይችሉ መሆኑን የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የትምህርትና ስልጠና ጥራት ቁጥጥር ባለስልጣን አሳውቋል።

በመሆኑም የትምህርት ማህበረሰቡ እና ወላጆች ይህን በማወቅ የቅድመ ዝግጅት ተግባራት እንድታከናውኑ ሲል አሳውቋል።

21/12/2024
ትምህርት ሚኒስቴር የሪሚዲያል ፕሮግራም ተቋርጧል በሚል ሐሰተኛ መረጃ እየተሰራጨ መሆኑን አስገነዘበየተማሪዎች አቅም ማሻሻያ (ሪሚዲያል) ፕሮግራም ተቋርጧል በሚል በማህበራዊ ሚዲያ ሐሰተኛ መረ...
01/11/2024

ትምህርት ሚኒስቴር የሪሚዲያል ፕሮግራም ተቋርጧል በሚል ሐሰተኛ መረጃ እየተሰራጨ መሆኑን አስገነዘበ

የተማሪዎች አቅም ማሻሻያ (ሪሚዲያል) ፕሮግራም ተቋርጧል በሚል በማህበራዊ ሚዲያ ሐሰተኛ መረጃ እየተሰራጨ መሆኑን ትምርት ሚኒስቴር አስታወቀ፡፡

የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ተፈትነው የማለፊያ ነጥብ ያላመጡ ተማሪዎች አቅማቸውን በማሻሻል ወደ ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት እንዲገቡና ትምህርታቸውን እንዲከታተሉ እየተደረገ እንደሚገኝም አስታውሷል።

ይሁንና ሰሞኑን በተለያዩ የማህበራዊ ሚዲያዎች ትምህርት ሚኒስቴር የሪሚዲያል ፕሮግራም በበጀት ዕጥረት መቋረጡን ትምህርት ሚኒስቴር አስታውቋል በሚል እየተሰራጨ ያለው መረጃ መሰረተ ቢስ መሆኑን የሚኒስቴሩ መረጃ ገልጿል።

ጥብቅ ማስታወቂያ ለ12ኛ ክፍል ተፈታኞች በሙሉትምህርት ሚኒስቴር የ2016 ዓ.ም የ 12ተኛ ክፍል ማጠናቀቂያ ብሔራዊ ፈተና በበይነ መረብና በወረቀት እንደሚሰጥ መግለጹ ይታወቃል። ሆኖም በተለ...
07/07/2024

ጥብቅ ማስታወቂያ ለ12ኛ ክፍል ተፈታኞች በሙሉ

ትምህርት ሚኒስቴር የ2016 ዓ.ም የ 12ተኛ ክፍል ማጠናቀቂያ ብሔራዊ ፈተና በበይነ መረብና በወረቀት እንደሚሰጥ መግለጹ ይታወቃል።

ሆኖም በተለያዩ ማህበራዊ ሚዲያ ገጾች የበይነ መረብ ፈተናው እንደቀረ ተደርጎ እየቀረበ ያለው መረጃ በፍጹም ከእውነት የራቀ ሃሰተኛ መሆኑን እየገለጽን ፈተናው በሁለቱም በወረቀት እና በኦንላይን እንደሚሰጥ በድጋሜ እንገልጻለን።

በመሆኑም ተማሪዎች ይህንኑ ተገንዝባችሁ ዝግጅታችሁን እንድትቀጥሉና ትምህርት ሚኒስቴር ፈተናውን የተሳካ ለማድረግ እንደተለመደው ከሚመለከታቸው ባለድርሻ አካላት ጋር በጥምረት እየሰራ መሆኑንና ለዚህም ከፍተኛ ዝግጅት ማድረጉን አስታውቋል።

37A+ ውጤት ያመጣችው ቀለሜዋ ምሩቅ ሠብለወንጌል መንግስቱ ትባላላች። ከኮተቤ የትምህርት ዩኒቨርሲቲ በማኔጀመንት የተወረቀች ሲሆን ከወሰደቻቸው  ኮርሶች መካከል 37ቱን "A+" (እጅግ በጣም...
07/07/2024

37A+ ውጤት ያመጣችው ቀለሜዋ ምሩቅ

ሠብለወንጌል መንግስቱ ትባላላች። ከኮተቤ የትምህርት ዩኒቨርሲቲ በማኔጀመንት የተወረቀች ሲሆን ከወሰደቻቸው ኮርሶች መካከል 37ቱን "A+" (እጅግ በጣም ከፍተኛ) ውጤት በመደርደር ልዩ የማዕረግ ተመራቂ ሆናለች።

ሠብለወንጌል በሶስት ኮርሶች ብቻ "A-" ውጤት ስለነበራት 'ሙሉ አራት ነጥብ'(4:00) ማምጣት ባትችልም" አጠቃላይ አማካይ ውጤቷ(CGPA) 3 ነጥብ 99 በማስመዝገብ የዩኒቨርሲቲው የዋንጫ ተሸላሚ ናት።

አዲስ አበባ ተወልዳ ያደገችው የሠብለወንጌል ቀለሜነት ከቅድመ መደበኛ(ኬጂ) ትምህርት ቤት የጀመረ ሲሆን ከአንደኛ እስከ አስራ ሁለተኛ ክፍል የተማሪነት ዘመኗ በደረጃ ተማሪነት ቀጥላለች።

በ8ኛ ክፍል ከተማ አቀፍ ፈተና 99 በመቶ ፐርሰንታይል፣ በ10 ክፍል ሀገር አቀፍ መልቀቂያ ፈተና (ማትሪክ) ሁሉንም ትምህርቶች 'ኤ' (Straight-A) ውጤት በመያዝም ወደ ቀጣዩ ክፍል ተዛውራለች።

እንደሁም በ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ብሔራዊ ፈተና ከ700 አጠቃላይ ድምር 545 ውጤት በማስመዝገብ ኮተቤ የትምህርት ዩኒቨርሲቲን ተቀላቅላ ለዛሬው ስኬት በቅታለች።

በመዲናዋ የሚገኙ የ12ተኛ ክፍል የኦንላይን ተፈታኞች ከዛሬ ጀምሮ የተግባር ልምምድ ማድረግ ይጀምራሉበኦንላይን ፈተና የሚወስዱ የ12ኛ ክፍል ተማሪዎች የተግባር ልምምድ የሚያደርጉበት የመለማመ...
29/06/2024

በመዲናዋ የሚገኙ የ12ተኛ ክፍል የኦንላይን ተፈታኞች ከዛሬ ጀምሮ የተግባር ልምምድ ማድረግ ይጀምራሉ

በኦንላይን ፈተና የሚወስዱ የ12ኛ ክፍል ተማሪዎች የተግባር ልምምድ የሚያደርጉበት የመለማመጃ ፈተና ከሰኔ 22 ጀምሮ እንደሚሰጥ የአዲስ አበባ ትምህርት ቢሮ አስታወቀ።

የሚደረገው ልምምድ የመፈተኛ ጣቢያዎች የኦንላይን ፈተናውን ለመስጠት ያላቸውን አቅም ለማረጋገጥ የሚረዳ መሆኑም ተገልጿል።

የአዲስ አበባ ትምህርት ቢሮ ኃላፊ ዘላለም ሙላቱ እንዳሉት በከተማ አስተዳደሩ የ2016 ዓም የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና በኦንላይንና በወረቀት ለመስጠት የቅድመ ዝግጅት ስራ እየተጠናቀቀ ይገኛል።

የኦንላይን ፈተናው በአይነቱ አዲስ በመሆኑ ተማሪዎች እንዲረዱት እንዲሁም የመፈተኛ ጣቢያዎች የማስፈፀም አቅምና ምቹና ሳቢ መሆናቸውን የማረጋገጥ ስራ እስከፈተናው መዳረሻ ድረስ ይሰራል ብለዋል።

የሚደረገው የሙከራ ፈተና አሰጣጥ ሂደት የኢንተርኔት ፍጥነትና አቅም፣ የኤሌክትሪክ ኃይል አገልግሎት ዘላቂና አስተማማኝነት ለማረጋገጥ የሚረዳ መሆኑንም ጠቁመዋል።

ተማሪዎች ከቴክኖሎጂው ጋር የማላመድ ሂደት ለመመልከትና በፈተና ጣቢያዎች የሚኖሩ ችግሮችን በመለየት ለመፍታት የሚያስችል መሆኑንም ተናግረዋል።

በአብርሆት ቤተመፃህፍት ከ3ሺህ በላይ ታብሌቶች የመሰረተልማት ዝርጋታ ስራ በማከናወን መዘጋጀታቸውንም ተናግረዋል።

በአዲስ አበባ ደረጃ ያሉ 163 መፈተኛ ጣቢያዎች የአቅም በመፈተሽ እስከፈተናው ሳምንት ድረስ የጣቢያዎችን አቅም የማጠናከርና የሚታዩ ጉድለቶችን የማስተካከል ስራ ይሰራል ነው ያሉት።

በፈተና ወቅት አስተማማኝ የኤሌክትሪክ ኃይል አቅርቦት እንዲኖር ከሚመለከተው ተቋም ጋር በቅንጅት ከመስራት በተጨማሪ በሁሉም መፈተኛ ጣቢያዎች የጄኔሬተር አቅርቦት እንዲኖር ተሰርቷል ብለዋል።

የኦንላይን ፈተና ሂደቱ አስተማማኝ እንዲሆን ለማድረግ በመፈተኛ ጣቢያዎች የተደረገው ቅድመዝግጅት ተማሪዎችም የሚኖርባቸውን ስጋት በማስወገድ ፈተናውን በተመቸ አግባብ እንዲወስዱ የሚያስችል መሆኑን ጠቁመዋል።

የፈተና ሂደቱ ውጤታማ እንዲሆን ባለድርሻ አካላት ሚናቸውን እንዲወጡም ጠይቀዋል።

በዘንድሮ አመት በአዲስ አበባ ደረጃ የ12ኛ ክፍል ፈተና ከሚወስዱ 50ሺህ በላይ ተማሪዎች መካከል 28ሺህ ያህሉ በኦንላይን ፈተና እንደሚወስዱም ተናግረዋል።

የፋርማሲ የመውጫ ፈተና ላይ የቴክኒክ ችግር በማጋጠሙ በድጋሚ እንደሚሰጥ ትምህርት ሚኒስቴር አስታወቀከሰኔ 14 እስከ 19/2016 ድረስ ሲሰጥ ከቆየው የፋርማሲ የመውጫ ፈተና ውስጥ የመጨረሻው...
27/06/2024

የፋርማሲ የመውጫ ፈተና ላይ የቴክኒክ ችግር በማጋጠሙ በድጋሚ እንደሚሰጥ ትምህርት ሚኒስቴር አስታወቀ

ከሰኔ 14 እስከ 19/2016 ድረስ ሲሰጥ ከቆየው የፋርማሲ የመውጫ ፈተና ውስጥ የመጨረሻው ቀን ፈተና የቴክኒክ ችግር በማጋጠሙ በድጋሚ እንደሚሰጥ አስታወቀ።

ሚኒስቴሩ ዛሬ ባወጣው ማስታወቂያ እንዳመላከተው በ 244 ፕሮግራሞች በ57 የመንግስትና በ124 የግል ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ትምህርታቸውን ሲከታተሉ ለነበሩ ተማሪዎች የመውጫ ፈተና ሲሰጥ ቆይቷል።

ለስድስት ቀናት የተሰጠው ፈተናም ያለምንም እንከን የተጠናቀቀ ሲሆን በመጨረሻው ቀን የተሰጠው የፋርማሲ ፈተና ብቻ የቴክኒክ ችግር እንዳጋጠመው ገልጿል።

በመሆኑም ቅዳሜ ሰኔ 22 ቀን 2016 ዓ.ም ጠዋት ከ 3:00 ሰአት ጀምሮ እና ከሰአት ከ 8:00 ሰአት ጀምሮ ለፈተናው ተቀምጠው የነበሩ የፋርማሲ ተማሪዎች በተፈተኑበት የፈተና ጣቢያ በሰዓቱ በመገኘት በድጋሚ የሚሰጠውን ፈተና እንዲወስዱ ሚኒስቴሩ አሳስቧል።

የከፍተኛ ትምህርት ተማሪዎች የዩኒቨርስቲ መውጫ ፈተና ተጠናቀቀበ244 የቅድመ ምረቃ መርሐ ግብሮች ከሰኔ 14 እስከ 19 ቀን 2016 ዓ.ም ሲሰጥ የቆየው  የ2016 ዓ.ም የከፍተኛ ትምህርት ...
26/06/2024

የከፍተኛ ትምህርት ተማሪዎች የዩኒቨርስቲ መውጫ ፈተና ተጠናቀቀ

በ244 የቅድመ ምረቃ መርሐ ግብሮች ከሰኔ 14 እስከ 19 ቀን 2016 ዓ.ም ሲሰጥ የቆየው የ2016 ዓ.ም የከፍተኛ ትምህርት ተማሪዎች የመውጫ ፈተና መጠናቀቁ ተገልጿል።

57 የመንግስትና 124 የግል ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት ተማሪዎቻቸውን ያስፈተኑ ሲሆን ፈተናውም በ51 የፈተና ማዕከላት ተሰጥቷል።

ለፈተናው ከተመዘገቡት 169ሺህ 790 ተማሪዎች መካከል ለመጀመሪያ ጊዜ 117ሺህ 192 ተማሪዎች የመውጫ ፈተናውን መውሰዳቸው ተጠቅሷል፡፡

እንዲሁም 52ሺህ 598 ተማሪዎች ደግሞ ፈተናውን በድጋሚ ለመውሰድ የተመዘገቡ መሆናቸውን ከትምህርት ሚኒስቴር ያገኘነው መረጃ ያመለክታል።

ለትምህርት ማስረጃ ማረጋገጫና አቻ ግመታ አገልግሎት ፈላጊዎችየትምህርት ማስረጃ ማረጋገጫ እና አቻ ግመታ አገልግሎት ፈላጊዎች የሚከተሉትን መስፈርቶች በማሟላት ባላችሁበት ሆናችሁ ከዚህ በታች ...
13/03/2024

ለትምህርት ማስረጃ ማረጋገጫና አቻ ግመታ አገልግሎት ፈላጊዎች

የትምህርት ማስረጃ ማረጋገጫ እና አቻ ግመታ አገልግሎት ፈላጊዎች የሚከተሉትን መስፈርቶች በማሟላት ባላችሁበት ሆናችሁ ከዚህ በታች በተቀመጠው ማስፈንጠሪያ https://neta.gov.et ካመለከታችሁ በኋላ፡-
1. መስፈርቱን የምታሟሉ፡-
1.1. በSMS መልእክት የምትመጡበት ቀነ ቀጠሮ ይደርሳችኋል ነገር ግን ከቀነ ቀጠሮው በፊት ወደ ባለሥልጣን መ/ቤቱ ብትመጡ አገልግሎት መስጠት የማንችል በመሆኑ እንዳትጉላሉ እናሳስባለን፤
1.2. ቀነ ቀጠሮ መቀየር ቢያስፈልጋችሁ በSMS/በኢ-ሚይል/በስ.ቁ(+251) 0111 26 14 52 /(+251)0111 26 16 23 በመደወል አዲስ ቀነ ቀጠሮ ማግኘት የምትችሉ መሆኑን እንገልጻለን፡፡
2. መስፈርቱን ለማታሟሉ፡-
2.1 . ያላሟላችሁት ማስረጃ ወይም ምክንያት በSMS መልእክት የሚደርሳችሁ በመሆኑ ሳታሟሉ መምጣት የለባችሁም፤
2.2 . ያላሟላችሁት ማስረጃ ካላችሁ በድጋሚ እንድታሟሉ እና ማሟላታችሁ ተረጋግጦ በSMS መልእክት ሲደርሳችሁ ብቻ እንድትመጡና እንዳትጉላሉ እናሳስባለን፡፡
3. በሀገር ውስጥ ተምራችሁ የትምህርት ማስረጃችሁን ለማረጋገጥም ሆነ በውጭ ሀገር ተምራችሁ የአቻ ግመታ ለማሰራት በኦንላይን ሳታመለክቱ በአካል ብትመጡ የማናስተናግድ መሆኑን እንገልጻለን፡፡

የ32ኛው አገር አቀፍ የትምህርት ጉባኤ ተጠናቀቀ።ትምህርት ሚኒስቴር በሶማሌ ክልል ጅግጅጋ ከተማ ሲያካሂድ የነበረው የ32ኛው አገር አቀፍ  የትምህርት ጉባኤ በተለያዩ ጉዳዮች ከመከረ በኋላ ባ...
29/11/2023

የ32ኛው አገር አቀፍ የትምህርት ጉባኤ ተጠናቀቀ።
ትምህርት ሚኒስቴር በሶማሌ ክልል ጅግጅጋ ከተማ ሲያካሂድ የነበረው የ32ኛው አገር አቀፍ የትምህርት ጉባኤ በተለያዩ ጉዳዮች ከመከረ በኋላ ባለ 11 ነጥብ የአቋም መግለጫ በማውጣት ተጠናቋል።

Address

Addis Ababa

Telephone

+251945355440

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Ethio Education News/ኢትዮ ትምህርት posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share

Category