DAGU Television

DAGU Television #ሰምተዋል !?

ሠላሳ አምስት አባላት ያሉት የሰርከስ አርቲስቶች ቡድን በአምስት የአውሮፓ ሀገራት ትርኢቱን ሊያቀርብ ነው፡፡ …ሠላሳ አምስት አባላት ያሉትና ሙሉ ኢትዮጵያውያን ብቻ የሚሳተፉበት ከተለያዩ የሰ...
07/11/2024

ሠላሳ አምስት አባላት ያሉት የሰርከስ አርቲስቶች ቡድን በአምስት የአውሮፓ ሀገራት ትርኢቱን ሊያቀርብ ነው፡፡

ሠላሳ አምስት አባላት ያሉትና ሙሉ ኢትዮጵያውያን ብቻ የሚሳተፉበት ከተለያዩ የሰርከስ ማዕከላት አርቲስቶችን፣ የውዝዋዜ፣ ታዋቂ የሙዚቃ መሳሪያ ተጫዋቾችና ታዋቂ ድምጻውያንን ያካተተ ልዩ ቡድን በማዘጋጀት በፈረንሳይ ፓሪስ በሚገኝው በታዋቂው በሰርክ ፊኔክስ CIRK AFRIKA PAR LES ETOILES D’ETHIOPIE 2024/2025 (CIRK AFRIKA BY THE STARS OF ETHIOPIA) “ሰርክ አፍሪካ የኢትዮጵያ ኮኮቦች” በሚል ርእሰ ትርዒቱን ፖሪስ በፊኔክስ መድረክ፣ እንዲሁም በቤልጅዬም፣ በሞናኮ ሞንቴካርሎ፣ በስዊዘርላንና በአንዶራ የሀገራችን ኢትዮጵያን ባህል፣አለባበስ፣ ሙዚቃና ጭፈራ ያካተተ ሙሉ የሰርከስ ትርኢት የያዘ ቡድን ከህዳር 04 ቀን 2017ዓ/ም ጀምሮ ወደ ፈረንሳይ ሊጓዝ መሆኑን አፍሪካን ድሪም አርትስ እና አፍሪካን ድሪም ሰርከስ ዛሬ ጥቅምት 28 ቀን 2017ዓ/ም በቱሊፕ ኢን ኦሎምፒያ ሆቴል በሰጠው ጋዜጣዊ መግለጫ አስታውቋል፡፡

በጋዜጣዊ መግለጫው ላይ እንደተገለጸው፤ በሞደርን ሰርክስ የሚታወቀው ሰርክ ፊኔክስ መስራች Alain M. Pacherie ከዚህ ቀደመ CIRK AFRIKA 1፣2 ና 3 ከመላዉ ከአፍሪካ የተወጣጡ የሰርከስ፣ ሙዚቀኞችንና ዳንሰኞችን ከደቡብ አፈሪካና ከምእራብ አፍሪካ እንዲሁም ከኢትዮጵያ የሰርከስ አርቲስቶችን ይዞ ያቅርብ እንደነበረ ይታውሳል፡፡ ይህ የሰርክ ፊኔክስ ካምፓኒ በአገር ደረጃ የቻይና፣ የኩባ፣ ሞንጎልያ… ወዘተ ሙሉ ትርዒት ያቀርቡበት ሲሆን አሁን ደግሞ የሰርክ አፍሪካ አዲስ ሾው ከምድረ ቅደምት አገር ከኢትዮጵያ ብቻ ሙሉ አርቲስቶችን በመያዝ የማይረሳ ጉዞ ሊያደርግ እና አስደናቂ የባህል ውዝዋዜ፣አለባበስ፣ ዜማንና ሙዚቃ ለአውሮፓውያን ለማሳየትና ለማዝናናት በሰርክ ፊኔክስ CIRK AFRIKA PAR LES ETOILES D’ETHIOPIE 2024/2025 (CIRK AFRIKA BY THE STARS OF ETHIOPIA) “ሰርክ አፍሪካ የኢትዮጵያ ኮኮቦች” በልዩ የሰርከስ፣ የዳንስ እና የሙዚቃ ጥበብ ብዙ አስገራሚ ስራዎችን ይዞ በብሔር ብሔረሰብ አልባሳት በመዋብ በፓሪስ ውስጥ በልዩ የኪነጥበብ ከሰርከስ ትርኢት መሳጭ የቤተሰብ መዝናኛ ይዞ ፓሪስ በመጀመር በኋላ, ትርኢቱ በመላው ፈረንሳይ ለማሳየትና ከ Cirque Phénix ጋር በአውሮፓ ለመጓዝ ቅድመ ዝግጅቱን አጠናቋል ፡፡

አዘጋጆቹ ይህ ትርዒት በኢትዮጵያ የመጀመሪያ የሚሆን የሰርከስ፣ የዉዝዋዜና የሙዚቃ ባለሙያ የሚሳተፉበት ትልቅ ትርዒት መሆኑን በመግለጫው ተናግረዋል፡፡

አፍሪካን ድሪም አርትስ እና አፍሪካን ድሪም ሰርከስ በታዋቂው የሠርከስ አርቲስት፣ አሰልጣኝ፣ አርቲስቲክ ዳይሬክተርና ማናጅር የኔነህ ተስፋዬ የተቋቋመ ሲሆን ሃሳቡ “በቻይና ህቤይ ውቻው አክሮባቲክ አርት ት\ቤት በነበረበት ወቅት በአውሮፓያን ካላንደር በ2004 የተጠነሰሰው ህልም ሲሆን ወደ ሀገሩ ተመልሶ የአፍሪካ ድሪም ሰርከስን በ2010 ከስራ ባልደረባው ቢኒያም ነጋሽ ጋር መሰረተ። በአዲስ አበባ ውስጥ የሚገኙ የተለያዩ ሰርከሶች አዲስ አፍሪካ ሰርከስ ፣ ሸገር ሰርከስ ፣ ዊንጌት ሰርከስ፣ ቢጣ ብራዘር ሰርከስ ወዘተ እየተዘዋወረ ሙያዊ ድጋፍ በመስጠት አዳዲስ ስራዎችን በአገር ውስጥ በማስተዋወቅ በዳይሬክቲንግ ፣ በኬሮግራፊ ፣ ኮስቲዩም ዲዛይኒንግ ፣ ሙዚቃ ምርጫ እና ማኔጅ በማድረግ ለፕሮፌሽናል የሰርከስ አርቲስቶች የስራ እድል ፈጥሯል።

በተለያዩ አለም አቀፍ ፌስቲቫሎች ላይ አርቲስቶችን በማሳተፍ የወርቅ የብር የነሃስ እና ስፔሻል ፕራይዝ ተሸላሚዎች እንዲሆኑ እና የሀገርን ሰንደቅ አላማ ከፍ በማድረግ መልካም ገፅታዋን በመገንባት ሰርከስ የሃገር የባህል አምባሳደር እንዲሆን ከፍተኛ አስተዋፅዖ በማበርከት በተደጋጋሚ የወርልድ ጊኒየስ ሪከርድ በማስመዝገብ እና ለዓለም አቀፍ የሠርከስ ካምፓኒዎች በማቅረብ ለብዙ ኢትዮጵያዊያንና አፍሪካውያን የስራ እድል ማመቻቸት ችሏል፡፡ በተጨማሪም የተልያዩ ፕሮዳክሽን ሙሉ ሰራ በአሜሪካ፣ በአውስተራሊያ፣ በጃፓን፣ ቱርክና ቤላሩስ ወዘተ ማቅርብ ችሏል።

ጥቅምት 28 ቀን 2017ዓ/ም
አዲስ አበባ / ኢትዮጵያ

እናት ባንክ ለሶስቱ ህጻናቱ የገንዘብ ድጋፍ አበረከተ  | እናት ባንክ ለሕፃን ሶሊያና ፣ ለሕፃን ሄራን እና ለሕፃን አናኒያ የትምህርት ቤት ወጪ የሚሸፍን የሶስት መቶ ሺህ ብር የገንዘብ ድጋ...
24/09/2024

እናት ባንክ ለሶስቱ ህጻናቱ የገንዘብ ድጋፍ አበረከተ

| እናት ባንክ ለሕፃን ሶሊያና ፣ ለሕፃን ሄራን እና ለሕፃን አናኒያ የትምህርት ቤት ወጪ የሚሸፍን የሶስት መቶ ሺህ ብር የገንዘብ ድጋፍ በዛሬው እለት አበርክቷል።

በርካታ ማህበራዊ ኃላፊነቱን በመወጣት ላይ የሚገኘው እናት ባንክ አዲሱን አመትና በቀጣይ የሚከበረውን የመስቀል በዓልን ምክንያት በማድረግ የእናት ባንክ ማርኬቲንግ ዳይሬክተር እና ሰራተኞች በሕጻናቶቹ ቤት በመገኘት ስጦታውን ያበረከቱ ሲሆን የሕጻናቱ እናት ወይዘሮ ትግስት ካሳ እና ሕጻናቶቹ እናት ባንክ ላደረገላቸው የገንዘብ ድጋፍ ምስጋናቸውን አቅርበዋል።

ሕፃን ሶሊያና ፣ ሕፃን ሄራን እና ሕፃን አናኒያ በቅርቡ ከባንኮክ መመለሳቸው የሚታወስ ነው።

እናት ባንክ ከተመሠረተበትና እየተገበረ ካለው የተሟላ የባንክ አገልግሎት አቅርቦት በተጓዳኝም ከሌሎች ተቋማት ጋር በትብብር በመሥራት ማኅበረሰብን የመጥቀም አካሔድ ወደፊትም ዘርፈ ብዙና ለተለያዩ የማኅበረሰብ ክፍሎች የሚጠቅሙና ችግር ፈቺ በሚሆኑ ሥራዎች ላይ በስፋት አጠናክሮ በመስራት ላይ ይገኛል።

14/09/2024

አርቲስት ንዋይ ደበበ ከደረሰብህ መሪር ሀዘን እግዚአብሔር ያፅናናህ ፣ የልጅህን ነፍስ ይማር !

ከአሜሪካን ሃገር የመጣው የበጎ ፈቃደኛ  ሐኪሞች ቡድን ነጻ የልብ ሕክምና አገልግሎት እየሰጠ ነው፡፡  …በአሜሪካን ሃገር በሚኖሩት ዶ/ር ተስፋዬ ተሊላ እና ዶ/ር ኦብሲኔት መርዕድ የተመሰረተ...
26/08/2024

ከአሜሪካን ሃገር የመጣው የበጎ ፈቃደኛ ሐኪሞች ቡድን ነጻ የልብ ሕክምና አገልግሎት እየሰጠ ነው፡፡

በአሜሪካን ሃገር በሚኖሩት ዶ/ር ተስፋዬ ተሊላ እና ዶ/ር ኦብሲኔት መርዕድ የተመሰረተው ሃርት አታክ ኢትዮጵያ የግብረ ሰናይ ድርጅት በኢትዮጵያ የልብ ሕሙማን ሕጻናት መርጃ የልብ ማዕከል ከነሐሴ 13 ቀን 2016ዓ/ም ጀምሮ ለሁለት ሳምንታት የሚቆይ የነጻ የልብ ሕክምና አገልግሎት በመስጠት ላይ ነው።

ለሁለተኛ ጊዜ በተዘጋጀው በዚህ ነጻ የሕክምና አገልግሎት መርሐግብር ከማዕከሉ በተጨማሪ በቅዱስ ጳውሎስ ሆስፒታል ህክምና የሚሰጥ ሲሆን በሁለት ሳምንት ጊዜ ውስጥ ከ100 በላይ በልብ ሕመም የሚሰቃዩ ታካሚዎች ተጠቃሚ እንደሚሆኑና የሕክምና አገልግሎቱን ለመስጠት ከ17 በላይ የልብ ሕክምና ዘርፍ ላይ የተሰማሩ የጤና ባለሞያዎች እንደሚሳተፉ ማዕከሉ አስታውቋል፡፡

እንደ ሃርት አታክ ኢትዮጵያ ዋና ሥራ አስፈጻሚ ዶ/ር ኦብሲኔት ገለጻ በዚህ ዙር ደረት ሳይከፈት ከሚሰሩ ሕክምናዎች በተጨማሪ የልብ ቀዶ ሕክምና እና የልብ ምት ችግር ላለባቸው ሕሙማን የሚሰጡ ሕክምናዎች መኖራቸውን ጠቅሰዋል። በዚህ የሕክምና ተልዕኮ ከ1.4 ሚ ዶላር በላይ ዋጋ ያላቸውን ለሕክምና አስፈላጊ የሆኑ ግብዓቶችን አሰባስበው መምጣታቸውን ተናግረዋል። ድርጅቱም በዚህ ብቻ ሳይወሰን ተጨማሪ ተልዕኮዎችን ወደፊት እንደሚያካሂድ ተናግረዋል።

የልብ ማዕከል ኢትዮጵያ ሜዲካል ዳይሬክተር ዶ/ር ሚክሎል መንግስቱ በበኩላቸው በዚህ የሕክምና ተልዕኮ በርካታ ወረፋ በመጠበቅ ላይ የሚገኙ ሕሙማን ተጠቃሚ እንደሚሆኑ ጠቅሰው የሕክምና ተልዕኮው ስኬታማ እንዲሆን ማዕከሉ ከዝግጅት ጊዜ ጀምሮ አስፈላጊ ሥራዎችን ሲሰራ መቆየቱን ተናግረዋል።

የሃርት አታክ ኢትዮጵያ በዶ/ር ተስፋዬ ተሊላ እና በዶ/ር ኦብሲኔት መርዕድ በተሰኙ በሁለት ትውልደ ኢትዮጵያውያን አሜርካውያን የሕክምና ባለሞያዎች የተመሰረት ሲሆን ባለፉት 14 ወራት ሁለት የልብ ሕክምና ተልዕኮዎችን በልብ ማዕከል ኢትዮጵያ አድርጓል። ድርጅቱ ከ2 ሚ ዶላር በላይ ዋጋ ያላቸው ሕክምናዎችን በነጻ ለልብ ሕሙማን ሰጥቷል።
HelloEthiopia On FM Addis 97.1
The Children's Heart Fund of Ethiopia - በኢትዮጵያ የልብ ሕሙማን ሕፃናት መርጃdren

ኢትዮጵያዊ ስራ ፈጣሪ ፤ የኩሪፍቱ ሪዞርትና ስፓ መስራችና ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ ታዲዮስ ጌታቸው ስራ ላይ ናቸው ። Kuriftu Resort & Spa
08/04/2022

ኢትዮጵያዊ ስራ ፈጣሪ ፤ የኩሪፍቱ ሪዞርትና ስፓ መስራችና ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ ታዲዮስ ጌታቸው ስራ ላይ ናቸው ።
Kuriftu Resort & Spa

ሱፐርስፖርት ዲኤስቲቪ የስፖርት ይዘቶችን ለኢትዮጵያውያን በአማርኛ የሚያቀርብ "ሱፐርስፖርት ልዩ" የተሰኘ ቻነልን በይፋ ስራ አስጀመረ.የኢትዮጵያውያንን ስፖርት አፍቃሪያን ተደራሽ የሚያደርጉ ...
26/03/2022

ሱፐርስፖርት ዲኤስቲቪ የስፖርት ይዘቶችን ለኢትዮጵያውያን በአማርኛ የሚያቀርብ "ሱፐርስፖርት ልዩ" የተሰኘ ቻነልን በይፋ ስራ አስጀመረ.
የኢትዮጵያውያንን ስፖርት አፍቃሪያን ተደራሽ የሚያደርጉ ዓለም አቀፍና ሀገር አቀፍ የስፖርት ይዘቶች በሱፐርስፖርት/ዲኤስቲቪ የሚያቀርብ “ሱፐርስፖርት ልዩ” ቻነል 240 ትናንት በይፋ የስፖርት፣ ባህል፣ ሚዲያና ኪነጥበብ የመንግስት ኃላፊዎችና ታላላቅ ሰዎች በተገኙበት በሀያት ሪጄንሲ ሆቴል ተመርቋል፡፡ በዕለቱ የዲኤስቲቪ አቦል ቴሌቪዥን አንደኛ ዓመት ክብረ በዓልም ተከብሯል፡፡

የመልቲቾይስ ኢትዮጵያ የሬጉላቶሪና ኮርፖሬት ጉዳዮች ኃላፊ አቶ መታሰቢያ በላይነህ ባደረጉት የመክፈቻ ንግግር ለአቦል ቤተሰቦችና የፊልም ኢንዱስትሪው ባለድርሻ አካላት ለአቦል አንደኛ ዓመት እንኳን አደረሳችሁ ያሉ ሲሆን ለስፖርቱ ባለድርሻዎችም አዲሱ የሱፐርስፖርት ልዩ ቻናል240 ስራ በመጀመሩ እንኳን ደስ አላችሁ ብለዋል።

አቶ መታሰቢያ የአፍሪካ ግዙፉ ስፖርትና መዝናኛ ይዘቶች አቅራቢው መልቲቾይስ አፍሪካ በሚሰራባቸው አገራት የህዝብና የሀገር ገፅታ ፣ ባህልና ታሪክ ለዓለም እንዲደርሱ እየሰራ ነው ያሉ ሲሆን በኢትዮጵያ ይህንኑ የሚያንፀባርቁ "አቦልና ሱፐርስፖርት ልዩ" የተሰኙ ቻነሎች ተከፍተዋል ብለዋል። ከአማርኛ በተጨማሪም ኦሮምኛን ጨምሮ ሌሎች የኢትዮጵያ ቋንቋዎችን በስርጭት ጊዜ የመጠቀም ዕቅድ አለ ያሉ ሲሆን ከፍተኛ ኢንቨስትመንት በመመደብ ከአፍሪካ ሀገራት በላቀ መልኩ በኢትዮጵያ ለመስራት መልቲቾይስ እየተንቀሳቀሰ ነው ብለዋል።

በዕለቱ የተገኙት የክብር እንግዳው የኢትዮጵያ ባህልና ስፖርት ሚኒስቴር የስፖርት ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ አምባሳደር መስፍን ቸርነት እንደተናገሩት “ ስፖርት መዝናኛ ብቻ አይደለም፡፡ ይልቁንም የልማት አንዱ ምሶሶ ነው፡፡ ኢትዮጵያ እንደ መንግስት የያዘችው ስትራቴጂ ስፖርት ለልማት የሚል ነው፡፡ በዚህ አግባብ ከመልቲቾይስ ጋር በትብብር እንሰራለን፡፡ በጀመርነው ልማትና አገራዊ የገፅታ ግንባታ ትክክለኛ ሚዲያ እንደሆነ እናምናለን፡፡ በመሆኑም የድርሻችንን የምናግዝ ይሆናል፡፡ መልቲቾይስም ስፖርቱንና ባህሉን አስተሳስሮ የገፅታ ግንባታና የሰው ኃይል አቅም ግንባታ ላይ በትኩረት እንዲሰራ አደራ እንላለን፡፡” ብለዋል፡፡

የኢትዮጵያ የመገናኛ ብዙኃን ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር መሀመድ ኢድሪስ በበኩላቸው “ዲኤስቲቪ ትናንት በአቦል የጀመረውን ዛሬ ደግሞ በሱፐርስፖርት ልዩ መምጣቱ አስዳሳች ነው፡፡ ዲኤስቲቪ ዓለምን ወደኛ እኛን ደግሞ ዓለም የወሰደ ነው፡፡ ኢትዮጵያን ለአፍሪካና ለዓለም ፤ ዓለምንና አፍሪካን ደግሞ ለእኛ በማስተዋወቅና በማስተሳሰር ትልቅ የገፅታ ግንባታ ስራ እየሰራ ይገኛል፡፡ ዲኤስቲቪ በዚህ ረገድ አይቻልም የተባለውን ችሎ ያሳየ ነው፡፡ በቀጣይ በሌሎች ተጨማሪ ቻናሎችና ቋንቋዎች እንደምናገኘው ተስፋ እናደርጋለን፡፡ ” ሲሉ ተናግረዋል፡፡

ከመልቲቾይስ ጋር በትብብር ስምምነት የኢትዮጵያን ፕሪሚየር ሊግ በሱፐርስፐርት/ዲኤስቲቪ አማካኝነት አህጉራዊ ስርጭት መሰጠቱ ያስገኘውን ጠቀሜታ በተመለከተ ንግግር ያደረጉት የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ አ/ማ ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ ክፍሌ ሰይፈ “ ዲኤስቲቪ ፕሪሚየር ሊጋችንን በፋይናንስ ከመደገፍ ባለፈ በአቅም ግንባታ ረገድ ከፍተኛ እገዛ እያደረገልን ነው፡፡ በአሁኑ ጊዜ የፕሪሚየር ሊጉ አሸናፊዎች ሽልማት በመጠንና በዓይነት ከፍተኛ ዕድገት አሳይቷል፡፡ ዲኤስቲቪ የሊጋችንን የመታየት ዕድል በመፍጠሩ የነበረብንን ክፈተት እንድናውቅ ብቻም ሳይሆን ክፈተታችንን ለመሙላት ተግተን እንድንሰራ መነሳሳት ፈጥሮልናል፡፡” ብለዋል፡፡

የዓለም የምንጊዜም ምርጡ አትሌት ሻለቃ ኃይሌ ገብረስላሴም ሱፐርስፖርት ለስፖርቱ ያደረገውን ከፍተኛ አስተዋጽኦ በመድረኩ ራሱን እንደምሳሌ በመጥቀስ መስክሯል፡፡ ኃይሌ “ እኔን ያደመቀኝ ሱፐርስፖርት ነው፡፡ በተከታታይ ሶስት ዓመታት ማለት በ1995፣ 1996 እና 1997 እኤአ የሱፐርስፖርት ኮከብ ተሸላሚ አትሌት ነበርኩ፡፡ እኔን በዓለም ላይ እንዳደመቃችሁኝ ሁሉ የአሁኑን የአትሌቲክስ ትውልድ ለዓለም እንድታስተዋውቁ አደራ እላለሁ” ብሏል፡፡

ሰርቢያ ቤልግሬድ የ2022 የዓለም የቤት ውስጥ አትሌቲክስ ሻምፒዮና የኢትዮጵያ አትሌቶችን ከዓለም በአንደኝነት ማሸነፍ በአዲሱ ሱፐርስፖርት ልዩ በቀጥታ በአማርኛ መሰራጨቱን በተመለከተ በመድረኩ የተጠየቁት የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ቡድን ዋና አሰልጣኝ ኮማንደር ሁሴን ሸቦ “ ዲኤስቲቪ ዓይናፋርነታችንን የሚገፍ በዓለም መድረክ ላይ አትሌቶቻችን ራሳቸውን የሚገልፁበት፣ ስለሀገራቸውና ስለአትሌክሱ የሚናገሩበት የሚዲያ አማራጭ በመሆኑ ደስ ይለኛል፡፡ ከዚህ ቀደም ዲኤስቲቪ በኢትዮጵያ ለእግር ኳሱ የነበረውን ትኩረት በአትሌቲክሱ በመድገም የቤልግሬድ የቤት ውስጥ የዓለም አትሌቲክስ ሻምፒዮናን የቀጥታ ዘገባ በማስተላለፉ የሚያስመሰግን ስራ ሰርቷል፡፡ እኛም በጣም ደስተኞች ነን፡፡ በተጨማሪም ለሌሎች ስፖርቶችም የመታያ ሜዳ ይሆናል ብዬ አምናለሁ” ብለዋል፡፡

በሌላ መልኩ የዲኤስቲቪ አቦል ቴሌቪዥንን አንደኛ ዓመት ክብረ በዓል ምክንያት በማድረግ ልምዳቸውን ያካፈሉት አርቲስቶች አቦል ቴሌቪዥን ለኢትዮጵያ ፊልም ባለሙያዎች በፋይናንስና በተደራሽነት ከፍተኛ ሚና እየተጫወተ ነው ብለዋል፡፡

በሳምንት ለተከታታይ አምስት ቀናት የሚተላለፈውን “አደይ” የተባለውን የመጀመሪያውን ቴሌኖቬላ ፕሮዲዩስ እያደረገ የሚገኘው አርቲስቲት ሰውመሆን ይስማው “አቦል ለፊልም ባለሙያዎች ዕድልም አቅምም ነው፡፡ ለምሳሌ በእኔ የረጅም ጊዜ የቀረፃ ልምድ ትልቁ በቀን የምንሰራው ስምንት ሲን ነበር። በኬንያ የሚገኝ ኩባንያ በቀን 35 ትዕይንቶችን መሥራቱን ስንሰማ ተገረምን በዚህም ቁጭት አድሮብን ተነሳን። በዚህ ቁጭታችን በቀን 36 ትዕይንቶች ሌት ተቀን ብለን በጥራት መስራት ችለናል። ይሄ አቦል ውጤት ነው። ዛሬ ላይ ልባችንን ሞልተን የምንናገረው ቢኖር በፕሮዳክሽን ጊዜ አጠቃቀም በጥራትና በጊዜ ለስርጭት በማስረከብ ውጤታማ እንድንሆን አስተምሮናል።" ብሏል።

ጥላ የተሰኘ አዲስ የቴሌቪዥን ድራማ ይዞ በአቦል ብቅ ያለው አርቲስት ሚካኤል ሚሊዮን በበኩሉ " የዓለም የፊልም እይታ አማራጭ መስኮት እያደገ መጥቷል። የቴሌቪዥን ቻነሎች ለፊልም ኢንዱስትሪው ትልቅ አቅም ሆነዋል። እኛም በተበጣጠሰ መንገድ የምንሰራውን ስራ የተቀናጀ ሆኖ እንዲወጣ ዲኤስቲቪ አስተምኖናል። ተጨማሪ ዕድልም ሰጥቶናል። በማሳያነት በአሁኑ ሰዓት የአቦልን መምጣት ተከትሎ ብዙ የፕሮዳክሽን ኩባንያዎችና ወጣት የፊልም ሰሪዎች እየተፈጠሩ ነው። ፕሮዲዩስ የሚደረጉ የድራማ ፅሁፎችን ተደራጅተው የሚሰሩ ወጣቶች ተገኝተዋል። ይህንን ያደረገው ዲኤስቲቪ ነው።"

ወጣቷ የፊልም ፕሮዲዩሰርና ዳይሬክተር ኤደን ጌታቸው በቅርቡ በአቦል ቴሌቪዥን ለስርጭት ስለሚበቃው የባስሊቆስ እምባ እንደናገረችው " አቦል ለእንደኔ ዓይነቱ አዲስ የፊልም ኢንዱስትሪ ዳይሬክተር እምነትን በማሳደር አዲስ ሰው እና አዲስ ፊት ለፊልም ኢንዱስትሪው አሻራ እንዲያስቀምጥ የፕሮዳሽን ስራዎች የፋይናንስ አቅምና የማሰራጫ ዕድል መፍጠር መቻሉ ትልቅ አስተዋፅኦ ነው።"

በዕለቱ በርካታ የኪነ ጥበብ፣ ስፖርትና የሚዲያ ባለሙያዎች የታደሙ ሲሆን በአቦል የሚቀርቡ የአማርኛ ይዘቶች ከሚቀጥለው ዓመት ጀምሮ የግርጌ የትርጉም ጹሑፍ (Subtitles) ታክሎባቸው ለዕይታ ይበቃሉ ተብሏል።

Address

Bole Friendship Business Center 7th Floor
Addis Ababa

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when DAGU Television posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to DAGU Television:

Share