Leka Media

Leka  Media media News

08/04/2026
06/04/2026

ግራ የተጋቡ ጅላንፎዎች ዛሬም በኢንተርኔት ስብሰባ መንግስት እንጥላለን ብለው ህዝብን ለማደናገር ይሞክራሉ ነገር ግን ህዝቡ ቀድሞዋቸው እንድሄድ አልተረዱም

አንጋፋውን ክለብ ከውድቀት ስለታደጉልን ከተማ አስተዳደሩን እናመሰግናለን!!!የቅ/ጊዮርጊስ ክለብ በነበሩ ውስጣዊ ሁኔታዎች ችግር ውስጥ መሆኑን በሰሙ ጊዜ፤ ቢጂአይንና ሜድሮክን ስለጊዮርጊስ እ...
29/03/2026

አንጋፋውን ክለብ ከውድቀት ስለታደጉልን ከተማ አስተዳደሩን እናመሰግናለን!!!

የቅ/ጊዮርጊስ ክለብ በነበሩ ውስጣዊ ሁኔታዎች ችግር ውስጥ መሆኑን በሰሙ ጊዜ፤ ቢጂአይንና ሜድሮክን ስለጊዮርጊስ እንወያይ ብለው በጠረጴዛ ዙርያ ያወያዩ ክብርት ከንቲባ አመራሮቻቸው ናቸው። ከንቲባችን እና አስተዳደራቸው አንጋፉው የቅ/ጊዮርጊስ ክለብ እንዲህ ሳይቸገር ለበለጠ ጥንካሬ እና ስራ አስር ሚሊየን ብር ድጋፍ ማድረጋቸው የሚታወስ ነው፤ ቀጣይነት ያለው ድጋፍ ይልሃል ይኼው ነው። የቅ/ጊዮርጊስ ክለብ ለከተማችን ድምቀት መሆኑን በውል የተገነዘቡ ከንቲባችን እና አስተዳደራቸው ከደጋፊዎች ጋር ተደጋጋሚ ውይይት ሲያደርጉም ቆይተዋል።

ዛሬም ደማቁ የከተማችን ክለብ ቅ/ጊዮርጊስ ሲቸገር፥ ደጋፊ ሲፈልግ፣ “እኛ አለንለት” ለማለት ማንም አልጠራቸውም። ሚድሮክ “እምቢ” ብሎ እንደነበር መቼም መረጃው ደርሷችኋል? የሚድሮክንም እምቢታ በውይይት ፈትተው፣ ቢ. ጂ. አይንም አሳምነው የመልካም ሀሳቡ ተካፉይ፥ የሰናይ ተግባር ተጋሪ እንዲሆኑ ያደረጉት ከንቲባዋ ናቸው።

ከተማ አስተዳደሩና ክብርት ከንቲባችን ይሄን የከተማችን ድምቀት የሆነ ክለባችን ከመበተን ተርፎ አቅሙን እስኪያስተካክል፣ በአንድ እግሩ እንዲቆም ላደረጉት የላቀ ድጋፍ እናመሰግናለን። ይህ ክለብ የከተማችን ታሪክ መሆኑን ከማንም በላይ ተረድተው ክለቡ ከችግሩ እስኪወጣ ዛሬ በማቋቋም፣ ነገም ከጎናችሁ ነን በማለት የማይሻር ታሪክን በቅዱስ ጊዮርጊስ ክለብ ቤት ተፅፏል።

28/03/2026

የፋኖ አባት!
Abbaa Faannoo!

23/03/2026

#አቶ ይልቃል ጌትነት፣ ዛሬ የፋኖ ቃል አቀባይ ሆነው ትናንት በ Reoyt ሚዲያ ቀርቦ የተናገሩት ንግግር የፖለቲካ ድኩማን የመጨረሻ መሸሸጊያ የሆነውን "የዛቻ ፖለቲካ" ነው። "ወደ 4 ኪሎ እንዳንመጣ ህዝብም ጭምር እየከለከለን ስለሆነ እርምጃ እንወስዳለን" የሚለው ንግግራቸው፣ ግለሰቡ ለስልጣን ካላቸው ልክ የሌለው ጥማት ባሻገር ለህዝብ ያላቸውን ንቀት ቁልጭ አድርጎ የሚያሳይ ነው።

አንድ የፖለቲካ ድርጅት ወይም ታጣቂ ቡድን "ለህዝብ ቆሜያለሁ" የሚል ከሆነ፣ የትግሉ ማጠንጠኛ የህዝብ ሰላም እና ነጻነት ሊሆን ይገባ ነበር። ይሁን እንጂ የይልቃል ጌትነት ንግግር የሚያረጋግጠው ትግላቸው ለህዝብ ሳይሆን ለቤተ-መንግስት ወንበር መሆኑን ነው። "ህዝብ እንቅፋት ሆነብን" ብሎ እርምጃ ለመውሰድ መዛተን የመሰለ የፖለቲካ እብሪት የለም።

ገና ስልጣን ሳይያዝ በአሜርካ ጥላ ስር ሆኖ ህዝብን የሚያስፈራራ ኃይል፣ ነገ ስልጣን ላይ ቢወጣ ምን ሊያደርግ እንደሚችል መገመት አያዳግትም። "የትኛውንም እርምጃ እንወስዳለን" የሚለው ፉከራ የጨለማ እና የጥፋት አዋጅ ነው።

ይልቃል ጌትነት ህዝብን በማሸበር ስልጣን ለመያዝ ማለም የጥንታዊ አምባገነኖች መንገድ እንጂ የሰለጠነ ፖለቲካ ውጤት አይደለም። 4 ኪሎን እንደ ግል ርስት፣ ህዝብን ደግሞ እንደ መወጣጫ በመቁጠር የሚደረግ ጉዞ መጨረሻው ውድቀት ብቻ ነው።

15/03/2026

"ማን ያርዳ የቀበረ" እንደሚባለው ከኔ የተሻለ የአዲስ አበባን መንገድ ሚያውቅ ያለ አይመስለኝም በጣም ነው የተለውጠችው :: አሁን አዲስ አበባ ላይ በመንገዱ ምክኛት አደጋ ደረሰብኝ የሚል ሰው ያለ አይመስልእኝም ::

ኢኒስፔክተር አሰፋ መዝገቡ!

የአዲስ አበባ ሁለንተናዊ ለውጥ በሁሉም መስክ እውቅና ማግኘቱን ቀጥሏል!ከዚህ ቀደም በአውሮፓ እና በአሜሪካ ከተሞች ላይ ብቻ ይዘወተር የነበረው የከተማ ውስጥ የብስክሌት ውድድር ለመጀመሪያ ጊ...
13/03/2026

የአዲስ አበባ ሁለንተናዊ ለውጥ በሁሉም መስክ እውቅና ማግኘቱን ቀጥሏል!

ከዚህ ቀደም በአውሮፓ እና በአሜሪካ ከተሞች ላይ ብቻ ይዘወተር የነበረው የከተማ ውስጥ የብስክሌት ውድድር ለመጀመሪያ ጊዜ በአፍሪካዊቷ ከተማ አዲስ አበባ ሊካሄድ ነው። ይህ በአዲስ አበባ ከተማ እ.አ.አ. መጋቢት 29, 2026 (ከሁለት ሳምንታት በኋላ) የሚከናወነው የ MTB Eliminator Pro League ውድድር በዓለም አቀፍ ደረጃ የዓመቱ የመክፈቻ ውድድር ጭምር ነው።

በኢትዮጵያ በተለይ በአዲስ አበባ እየተከናወነ ያለው የከተማ ትራንስፎርሜሽን አዲስ አበባን በውድድሩ አዘጋጆች ተመራጭ አድርጓታል።

በመሆኑም በአፍሪካ ደረጃ በአዲስ አበባ ለመጀመሪያ ጊዜ የሚካሄደው ውድድር የከተማዋን ለውጥ ተከትሎ የመጣና ከተማዋን የበለጠ የሚያስተዋውቅ ዓለም አቀፍ ኩነት ነው።

አዘጋጁ City Mountainbike የውድድሩን በአዲስ አበባ መዘጋጀት "ልዩ ክስተት" እና "በአፍሪካ የማውንቴንባይክ ውድድር አዲስ ምዕራፍ" በማለት ገልጾታል።

እንኳን ደስ አለን!!

Address

Piyassa
Addis Ababa
1000

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Leka Media posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share