Wollo Media Corporation - WMC

Wollo Media Corporation - WMC ፍቅር ፍቅር ሁሌም ፍቅር

 መስጅድን የግለሰብ ለማድረግ እየተከራከራ ያለው ፌኩ መንግስቱ ዘገየ ማንነት ሲጋለጥ‼️መንግስቱ ዘገየ ማለት በፌክ ማንነቱ ብዙዎችን የሸወደው በየመድረኩ ላይ እየወጣ ስለነ ሙሀመዶች ሲናገር ...
27/11/2025


መስጅድን የግለሰብ ለማድረግ እየተከራከራ ያለው ፌኩ መንግስቱ ዘገየ ማንነት ሲጋለጥ‼️

መንግስቱ ዘገየ ማለት በፌክ ማንነቱ ብዙዎችን የሸወደው በየመድረኩ ላይ እየወጣ ስለነ ሙሀመዶች ሲናገር የወሎየነት መንፈስ የያዘ የሚመስል የኦርቶ አማራ ፅንፈኛ እና የሙአ ተዋህዶ አቀንቃኝ ግለሰብ ነው።

ሰውየው ቀንበር ጠቦትና ወሎ ላይ ሁኖ ተቸግሮ ነውጅ በውስጡ የያዘውን መርዝ እና ድብቅ ማንነቱን መደበቅ አቅቶት ሳያስበው በቦሩ ሜዳው ጉዳይና በሰሞኑን ከተማችን ላይ በተከሰተው ክስተት ፈንቅሎት በመውጣት ራቁቱን የቀረበትና ሴራው የተጋለጠበት ፣ብዙዎች ፌክ ማንነቱን ያወቁበት ከስተት ነው የተፈጠረው።

አርቲፊሻሉ መንጌ አንድ የሚመፃደቅበት እና እኛ ደግሞ የምናውቀው ነገር አለ በድምፃችን ይሰማ የሙስሊሙ ትግል ማንም ደፍሮ ጠበቃ መቆም በማይችልበት እኔ በጀግንነት ቁሚያለሁ እያለ ጅብ ከማያውቁት ሀገር ሂዶ ከሌ አንጥፋልኝ አለ አይነት ተረቱን ሲተርትና ሲቀደድ ስናየው ስለሱ እኛ ሀፍረት ይሰማናል።

ፌኩ መንጌ በድምፃችን ይሰማ የሙስሊሙ ትግል ደሴ ከተማ ላይ ከደህንነቶችና ከነ ኮማንደር ደረጀ ጋር እነማን መታሰርና መገረፍ እንዳለባቸው ቢራውን እየከካ ሲያሴር ና ሲዶልት ያመሽና በቀን ደግሞ ጠበቃ ሁኖ ይቀርባል።

ይሄን ሴራውን ማንም ሰለማያውቅበት ደረቱን ነፋ አድርጎ በኩራትና በመኮፈስ ስሜት ማንም ደፍሮ ያልተጋፈጠውን እኔ እየተጋፈጥኩላችሁ ስለሆነ እከሌን አስፈተዋለሁ፣እከሌን እንዳይገረፍ አደርገዋለሁ ፣ ለነከሌ ደግሞ ጥብቅና እቆምላቸዋለሁ እያለ በርካታ ብሮችን እየተቀበለ ሰራሁላቸው አይነት ድራማውን ተውኖ ማታ ከአለቆቹ ጋር ቢራና ውስኪውን ሲራጭ ያመሽና ቀን የግል ቢዝነሱን ያጧጡፋል።

ፌኩ መንጌ ጊዜውንና ወቅቱን ተጠቅሞ ከሙስሊሙ ማህበረሰብ በጥብቅና ሰበብ በርካታ ብሮችን ተቀብሏል፣የግል ቢዝነሱን በደንብ ሰርቷል ሀብታምም አድርገንዋል።

የዋሁ ሙስሊም ማህበረሰብም የሰውየው ሴራና ተንኮል ስለማይገባው ፌኩን መንጌ ብቸኛው የሙስሊም ጠበቃ አድርጎ አናቱ ላይ ሰቀለው አሏህ ግን ማንነቱን ጠንቅቆ ስለሚያውቅ ራቁቱን አስቀርቶ እጃችን ላይ ጥሎ አጋለጠው ።

አሁን በቅርቡ ደግሞ ደሴ ከተማ መናፈሻ ክፍለ ከተማ ሙሀመድ ጌታ (ደሶ) መስጅድን የግለሰብ ነው ብሎ የደሴ ከተማ አስተዳደር እስልምና ጉዳይ ምክር ቤትን ጥብቅና ቁሞ እየተከራከረ ያለ ጉደኛ ፍጡር ነው።

ሙስሊም እወዳለሁ እያለ በፌክ ማንነቱ በየመድረኩ ሲጮህና በፌስቡክ ገፁ ሲለቀልቅ የሚውለው ፌኩ መንጌ በውስጡ ደብቆ የያዘውን መቆጣጠር አቅቶት የደሴ ከተማን ሙስሊም ማህበረሰብ ንቆ መስጅዱን ለግለሰብ አሳልፎ ለመስጠን እየተከራከረ ይገኛል።

ስለመንግስቱ ዘገየ ተንኮልና ሴራ ቀጣይ በሰፊው የምንመለስበት ቢሆንም ስለሰውየው ምንነት ብዙ ነገር እያወቅን ዝም ያልነው እሱን ላለማግነንና አጀንዳችንን እንዳንስት ብለን ነው።

ፌኩ መንጌ ግን ሳንጠራው አቤት ብሎ በቦሩ ሜዳው ጉዳያችን ላይ ዘሎ በመግባት አጀንዳ እንድናደርገው ፈልጎ ነበር እኛ አርቲፊሻል ማንነቱን ስለምናውቅ ንቀን ተውንውጅ

አሁን ደግሞ ደሴ አለማችም ስለተባለብቻ ሳንጠራው አቤት ሳንልከው ወደየት ብሎ ጥቅም ለሚያጋሩት ለነ እርገጤ ሞላ ጥብቅና ለመቆም ሲሞክር ስናየው አሳ ጎርጓሪ ዘንዶ ያወጣል ነውና በራሱ ጊዜ ራቁቱን ለመቅረት ብቅ ስላለ እናመሰግንሀለን ብለንዋል።
#ጠበቃመንግስቱዘገየ
©አርዱል ሀበሻ

መገን ደሴ:👉 ደሴ ተወልጄ ያደኩባት ሆና ከተማዋ የማትረሳኝ  ናት። ዛሬ ያለችበት ሁኔታ እጅግ ያሳዝናል። በቅርቡ ብዙ የኢትዩ ከተሞችን አይቻለሁ። እንደ ደሴ የተጣለ ወይም መሪዎቹ የማይወዱት...
27/11/2025

መገን ደሴ:👉 ደሴ ተወልጄ ያደኩባት ሆና ከተማዋ የማትረሳኝ ናት። ዛሬ ያለችበት ሁኔታ እጅግ ያሳዝናል። በቅርቡ ብዙ የኢትዩ ከተሞችን አይቻለሁ። እንደ ደሴ የተጣለ ወይም መሪዎቹ የማይወዱት አላየሁም። ችግሩ ደሴ አለማችም ስንል የኛ ገልቱዎች እስላም ስለሆናችሁ ጠልታችሁን ይላሉ። ባህርዳር ወይም ጎንደር ለምን አትለማም? ብንል ፋኖ ኮፍያውን አውልቆ "እግዜያብሄር ይስጣችሁ አማራ ማለት እንዲህ ለመብቱ የሚቆም ነው" እንደሚሉን አንጠራጠርም።

የደሴ ባለሀብት ከንቲባውን ጋር ቀርቦ ሲሰራ አይተን ነበር። ሆኖም በአብዛሀኛው አባላት መነሳሳታቸው ሰጥቶ በመቀበል ሚና ሆኖ ቀጣይ አልሆነም። የሆነ ግንብ ቀለም ተቀብቶ ውስጡ ታደሰ። ከንቲባው ከቢሮ ሲወጡ ኮረኮንች እንዳያስቸግራቸው መንገዱ ተጠገነ እናም መብራት ተደረገላቸው። ታሪኩ አለቀ።

እና ደሴ ላይ ያሉ የብልጽግና ቡድንተኛ ሰዎች መነሳት ያለባቸው ናቸው። ችግሩ ብልጽግና በ ፌስቡክ ተመርተን ሰው ካነሳን ሁሌ እንረበሻለን ብሎ ስለሚያስብ አስቸጋሪ ነው።

ለክልሉ የምመክረው እስከዚያ ድረስ መፍትሄ የሚሆነው ጠንካራ የሆኑ የግልጋሎት ሊቅ ሰዎችን (technocrats) ወደ ከተማዋ ማምጣት ነው።

መርሳት የሌለብን እስላም ክርስቲያኑ ሳሙኤል "ያማልዳል" ያላለ አልነበረም። ብዙዎች ምክትሉ አሳስቶት አበላሸው ቢሉም አልስማም። ሁለቱም የገዱ ምልምል አፍቃሪ ፋኖ እንደሆኑ ሁሉም ያውቃል። ያው ባህርዳርም ያለው የገዱ ሀይል ጠንካራ ስለሆነ ብልጽግና ምንም ማድረግ የሚችል አይመስለኝም።

ግጥም እወዳለሁና
**************
አይጠየፍ ሆኖ ይታያል ከሚሴ
ፍቅር ያልገባው ሰው ምን ያደርጋል ደሴ
**************************
እባክህ ጌታየ አድርገኝ እንደ ደሴ
አንደዜ ሳዱላ አንደዜ ፈሰሴ
*******************
©KHA Abate

26/11/2025

ምን አይነት አውሬነት ነው?

ተይዘው የመጡት ስልኮች ብዙ ነገር እየነገሩን ነው። ጃውሳዎች ከማን ጋር እንደሚገናኙ፣ ማን ገንዘብ እንደሚልክላቸው፣ እነማንን እንደ ደፈሩ፣ እነማንን እንደ ገደሉ፣ እነ ማንን እንዳገቱ፣ ብዙ...
25/11/2025

ተይዘው የመጡት ስልኮች ብዙ ነገር እየነገሩን ነው።

ጃውሳዎች ከማን ጋር እንደሚገናኙ፣ ማን ገንዘብ እንደሚልክላቸው፣ እነማንን እንደ ደፈሩ፣ እነማንን እንደ ገደሉ፣ እነ ማንን እንዳገቱ፣ ብዙ ብዙ ነገር እየነገሩን ነው። ሰዎቹ በግፍ ስለሚዝናኑ ነውሩን ሁሉ ቀድተው ያስቀምጣሉ።
ከተያዙት መረጃዎች መካከል አንዳንዶቹ ይለቀቃሉ። አንዳንዶቹ ግን ለሕዝብ እና ለሞራል ሲባል ይቀመጣሉ።

ይህ የግፍ ቪዲዮ በመለቀቁ ዛሬ ከሚንጨረጨሩት ብዙዎቹ እነዚህ ስልኮች ውስጥ አሉ።
©Daniel Kibret

እይውላችሁ ድርጊቱ የተፈፀመው ከቀናት በፊት ነው።እነርሱ ይሄንን የብልፅግና ደጋፊ ያሉትን እጁን ከቆረጡና በርካታ ግፎችን በወረኢሉ ህዝብ ላይ ከፈፀሙ በሗላ መከላከያ ሰራዊት ከህዝብ በቀረበው...
25/11/2025

እይውላችሁ ድርጊቱ የተፈፀመው ከቀናት በፊት ነው።
እነርሱ ይሄንን የብልፅግና ደጋፊ ያሉትን እጁን ከቆረጡና በርካታ ግፎችን በወረኢሉ ህዝብ ላይ ከፈፀሙ በሗላ መከላከያ ሰራዊት ከህዝብ በቀረበው ጥሪ ኦፕሬሽን ያደርጋል ።
በዚህ ጊዜ እርሱና የሚመራው ጦር ወደ ቆላ ይሸሻል። መከላከያም ተከታትሎ የገደለውን ገድሎ እነዚህን ይማርካቸዋል።
እናም መከላከያ ከተቆጣጠራቸው በሗላ ስልክ ሲፈትሽ ነው ይህ ሁሉ ጉድ የተገኘው።
ስልካቸው ሲፈትሽ በውስጡ እጅ መቁረጥና መግደል ብቻ ሳይሆን ለብዙ ሆነው የደፈሯቸውንና ሲደፍሯቸው የቀረጿቸውም ሁሉ ተገኝቷል። ከእነዚህ ውስጥ አንዷን የወረኢሉ ልጅ ለ 5 ሆነው ሲደፍሯት የሚያሳየው ቪዲዮን መከላከያ ይዟል።
በጣም ለመገር የሚከብዱ ሰቅጣጭ ወንጀሎችን እየፈፀሙ እየተቀራረፁ ያስቀምጣሉ።

እናም የሞአ ተዋህዶ አቀንቃኞች ልጁና ጦሩ በመከላከያ ስለተማረከ ውሸት ነው ለማለት ሊያስተባብሉ እየሞከሩ ነው። ግና እንደዚያ አይደለም።
በመከላከያ ተማርኳል ወይ? አዎ ተማርኳል። ከተማረከ በሗላ ነው እነዚህ ቪዲዮዎች የተገኙት።

እንግድህ ህዝባችን ላይ ያልተነገረ እንጅ ያልተፈፀመ ግፍ የለም። ተመልከቱ ባይማረክ አሁን ይሄኛው ግፍ ሳይታይ ይቀራል ማለት ነው።
ቢታዩ በቁጣ ህዝብን የሚንጡ በርካታ ግፎች በዚህ የሽብር ቡድን እየተፈፀሙ ነው።

በቆላማው አካባቢ ወላጆች ልጃገረድ ልጆቻቼውን እንዲያስረክቡ እየተገደዱ እየተደፈሩነው። ለአማራ እጮሀለሁ የሚለው የፖለቲካ ጥቅመኛ ይህ የህዝብ ለቅሶ አይታየውም።

የእያንዳንዱ ፋኖ ስልክ ቢፈተሽ ጨርሶ እንደዚሆ ነው።
አስገድዶ ሲደፍሩ ያልቀረፀ ፋኖ እምብዛም ነው። እንዳለ መድፈር ፤ በሬና ላም ማረድ በግ ፍየል ማረድ ፤ እገታና ገንዘብ መሰብሰብ ብቻ ሆኗል ስራቸው!

ቴሌግራም
via 👉 t.me/Seidsocial

ምን አይነት አረመኔነት ነው?
25/11/2025

ምን አይነት አረመኔነት ነው?

ሰበር መረጃየሰሜን ወሎ ፋኖ መሪ ምሬ ወዳጆ በሰላም ወደ ቤታችን እንድንገባ ይፍቀድልን ሲል ጠየቀበአማራ ክልል የተከሰተውን ቀውስ በግንባር ቀደምትነት የቀሰቀሰው ምሬ ወዳጆ የባለወልድ አባቶች...
11/04/2023

ሰበር መረጃ

የሰሜን ወሎ ፋኖ መሪ ምሬ ወዳጆ በሰላም ወደ ቤታችን እንድንገባ ይፍቀድልን ሲል ጠየቀ

በአማራ ክልል የተከሰተውን ቀውስ በግንባር ቀደምትነት የቀሰቀሰው ምሬ ወዳጆ የባለወልድ አባቶችን ሽምግልና ልኳል። ምሬ ወዳጆ ከልዩ ኃይሉ እና ከህዝቡ ድጋፍ አገኛለው በሚል ወደ ግጭት ቢገባም ባሰበው ልክ ድጋፍ ማግኘት ባለመቻሉ ለመከላከያ ሰራዊት ሽምግልና ልኳል። በዚህ ሽምግልና የተሳትፉ የባለወልድ አባቶችም "ጦርነት በቃን፣ ከዚህ በላይ ጦርነት ውስጥ መቆየት አንፈልግም" ብለው ምሬን የገሰፁ መሆኑን እና መከላከያ ሰራዊትም ኢመደበኛ አደረጄጀቱ ትጥቁን ለመከላከያ ሰራዊት በማስረክብ በሰላም ወደየ ቤቱ እንዲገባ ያስቀመጠውን ቅድመ ሁኔታ ኢመደበኛ አደረጃጀቱ ተቀብሎታል። በዚህ መሰረት መከላከያ ሰራዊት ያስቀመጠው ቅድመ ሁኔታዎች፤

1. ከዚህ በኋላ ምንም አይነት መንገድ እንዳይዘጋ፣
2. ምንም አይነት የታጠቀ አካል ከተማ ውስጥ እንዳናገኝ እርቅም ይሁን ግጭት ከከተማ ውጭ ጫካ ላይ ይሁን፣

3. አፈሙዝ ወደ መከላከያ ሰራዊት እንዳያዞሩ ሠራዊቱ የሚላቸውን ትዕዛዝ አክብረው ይቀመጡ፣

4. የመከላከያን ጥቁር ክላሽ ሰብስበው ያስረክቡን በሚል ቅድመ ሁኔታ ካስቀመጠ በኋላ የሽምግልና ሂደቱን እንዲያስቀጥሉ ተስማምተው ከሽማግሌዎቹ ጋር ተለያይተዋል። ተለያይተዋል። ።

ይህን ተከትሎ ምሬ ወዳጆ በሰጠው ምላሽ "ግጭቱ ሲፈጠር እኔ ምንም አላውቅም እንደ ቡድንም አልተወያየንበትም አልወሰንም ሁሉም የሆነው በዳንኤል አለሙ ትዕዛዝና ፍላጎት ነው ብሏል። በተጨማሪም "ጫካ የገባነው ራሳችንን ለማዳንና መከላከያ እንደሚመታን ስናውቅ ነው የምንተኩሰው ጥይትም ሰው ላይ እንዲያርፍ አይደለም ለመከላከል ያክል ነው" ብሏል።

በመሆኑም የነ ምሬ ወዳጆ ቡድን በዛሬው እለት መግለጫ ሰጥቶ በሰላም እንደሚገባ ታውቋል።
Via natinael

ልዩ ኃይሉን እንደገና …ምክረ ሃሳብ!★★★//♦//★★★አንድ ሀገር፣ አንድ መንግስት፣ አንድ የሀገር መከላከያ እንዲኖር ለዘመናት ተመኝተናል።የክልል ልዩ ኃይሎች፣ ኢ—መደበኛ አደረጃጀቶች የየክ...
10/04/2023

ልዩ ኃይሉን እንደገና …ምክረ ሃሳብ!

★★★//♦//★★★

አንድ ሀገር፣ አንድ መንግስት፣ አንድ የሀገር መከላከያ እንዲኖር ለዘመናት ተመኝተናል።

የክልል ልዩ ኃይሎች፣ ኢ—መደበኛ አደረጃጀቶች የየክልሉ የናፖሊዮን ውሾች ሆነው ክልሎች በውስጦቻቸው ያሉ ማይኖሪቲዎችን የሚጨፈጭፉበት፣ የሚያፈናቅሉበት፣ የሚያሳድዱበት፣ ተገዳዳሪ እና አዋሳኝ ክልሎችን የሚያስፈራሩባቸው፣ የሌሎች ክልል ተወላጆችን የሚያንገላቱባቸው ሆነው በርካታ ግፍ ተፈፅሟል።

ለአንድ ወሎየ የነዚህ ከሀገር መከላከያ ውጭ ያሉ አደረጃጀቶች መታረም እጅግ ታሪካዊ ስኬት ነው። እናም በመርህ ደረጃ ታሪካዊ ድል ሊባል የሚችል ነው።

ይሁን እንጅ መንግሥት የልዩ ኃይል አደረጃጀቶችንም ሆነ ሌሎች ኢ—መደበኛ ኃይሎች እንደገና በማደራጀት አንድ ሀገራዊ የሆነ የሁሉም፣ ከሁሉም፣ በሁሉም የሆነ የጋራ የአገር መከላከያ ኃይልን ማጠናከር እቅዱን ለማከናወን ሲነሳ የሚከተሉት ክፍተቶች አሉበት ብየ አምናለሁ:—

አንደኛ የቅድመ መረጃ አሰጣጥ፣ የኢንዶክትሪኔሽን ስራና ግልፀኝነት ጉድለት።ይህም የመንግስት እቅድ በተዛባ ሁናቴ ለህዝቡ እንዲደርስ እድሉን ፈጥሯል።

ሁለተኛ አማራ ክልል በብሶት እና ስጋት ላይ ያለ ክልል ነው። በዋናነትም የሚለተሉት መሰረታዊ ስጋቶች አሉት። እነዚህም:—

1⃣ አማራ ክልል ከትግራይ ጋር ያለው የድንበር ነባር ጭቅጭቅ
2⃣ የልዩ ኃይል መልሶ የመከለስና የማደራጀት እንቅስቃሴው በተጓዳኝ በሁሉም ክልል በአንድ ጊዜ ከመጀመር ይልቅ አማራ ክልል ላይ ብቻ የተጀመረ የሚያስመስሉ ሁነቶች መፈጠሩ
3⃣ አማራ ክልል አሁን ባለው የመከላከያ ኃይል ስብጥርና ተክለ ቁመና ላይ እርግጠኛ አለመሆኑ
4⃣የ አማራ ክልል ህዝብ ለባለፉት አምስት አመታት ካሳለፈው ምስቅልቅል ሁኔታ በፌደራል መንግስቱ ላይ አመኔታ ማጣት
5⃣ በፌደራል መንግስቱ አንዳንድ ባለስልጣኖች የተለቀቀው መረጃ የተዛባ መሆኑ

ተጨባጩ ይህ ከሆነ መንግሥት የተለየ ዓላማ ከሌለው ጉዳዩን በሠላምና ሁሉንም አሳማኝ በሆነ መልኩ ማከናወን የሚችልበት እድል እንዳለው ይሰማኛል።

ምክረ ሃሳብ‼
_______

የሁሉንም ክልል ልዩ ኃይሎችና ኢ—መደበኛ ታጣቂ ኃይሎች በተመሳሳይ ሰአት በፌዝ መልሶ ማደራጀት። ለምሳሌ

በመጀመሪያ ዙር— ሁሉም ክልሎች በተመሳሳይ ወቅት 25% ያክል ልዩ ኃይሎቻቸውን መልሰው እንዲያደራጁ

በሁለተኛ ዙር— ሁሉም ክልሎች በተመሳሳይ ወቅት 25% ያክል ልዩ ኃይሎቻቸውን መልሰው እንዲያደራጁ

በሶስተኛ ዙር— ሁሉም ክልሎች በተመሳሳይ ወቅት 50% ያክል ልዩ ኃይሎቻቸውን መልሰው እንዲያደራጁ
©Abdujelil

Address

Addis Ababa

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Wollo Media Corporation - WMC posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share