Inform Ethiopia

Inform Ethiopia Ethiopia Forever

ሁለት የኢትዮጵያ የተባበሩት መንግሥታት የሰላም አስከባሪዎች በደቡብ ሱዳን በደረሰባቸው የደፈጣ ጥቃት ተገደሉ በደቡብ ሱዳን ጆንግሌይ ግዛት ትናንት ሰኞ በደረሰ የደፈጣ ጥቃት፤ ሁለት የኢትዮጵ...
25/08/2026

ሁለት የኢትዮጵያ የተባበሩት መንግሥታት የሰላም አስከባሪዎች በደቡብ ሱዳን በደረሰባቸው የደፈጣ ጥቃት ተገደሉ

በደቡብ ሱዳን ጆንግሌይ ግዛት ትናንት ሰኞ በደረሰ የደፈጣ ጥቃት፤ ሁለት የኢትዮጵያ የሰላም አስከባሪዎች ሲገደሉ፣ ሌሎች ሰባት ሰዎች ደግሞ መቁሰላቸውን የተባበሩት መንግሥታት አስታወቀ። ይህም በተያዘው የአውሮፓውያኑ ዓመት በዓለም አቀፍ ደረጃ በሥራ ላይ እያሉ የተገደሉትን የሰላም አስከባሪዎች ቁጥር ወደ ዘጠኝ አድርሶታል።

ከተጎዱት መካከል ሦስቱ የተባበሩት መንግስታት የሰላም አስከባሪዎች፣ ሁለቱ የደቡብ ሱዳን ፖሊሶች እና ሁለቱ የሲቪል ሰራተኞች እንደሚገኙበት የድርጅቱ ዋና ጸኃፊ ቃል አቀባይ ስቴፋን ዱጃሪች በሰጡት መግለጫ ተናግረዋል።

ጥቃቱ ማንነታቸው ባልታወቀ ታጣቂዎች የተፈጸመ መሆኑን እና ፓትሮሉ ወይም የክትትል ቡድኑ ሆን ተብሎ የተላመደ ይመስላል ብለዋል።

“እነዚህ ድርጅቱ በአካባቢው ያለውን ዘላቂ የጸጥታ ችግር ለመፍታት ከሚያደርጋቸው መደበኛ የክትትል ሥራዎች አካል ናቸው” ብለዋል ቃልአቀባዩ።

የተባበሩት መንግስታት የሚመለከታቸው አካላት ጥፋተኞችን ለፍርድ ለማቅረብ አጣዳፊ እና አጠቃላይ ምርመራ እንዲያደርጉ መጠየቁን ዱጃሪች ገልጸዋል። አክለውም “በድርጅቱ የሰላም አስከባሪዎች ላይ የሚፈጸሙ ጥቃቶች በዓለም አቀፍ ሕግ መሠረት የጦር ወንጀል ሊሆኑ ይችላሉ” ሲሉ አጽንኦት መስጠታቸውን ሮይተርስ ዘግቧል።

ይህ የቅርብ ጊዜ ድርጊት “ከዚህ ዓመት ጥር 1 ጀምሮ በጥፋት ድርጊቶች የተገደሉትን የሰላም አስከባሪዎች ቁጥር ወደ ዘጠኝ ያደርሰዋል” ብለዋል።

በደቡብ ሱዳን በመንግስታቱ ድርጅት ሠራተኞች ላይ የሚፈጸሙ ጥቃቶች አልፎ አልፎ የሚከሰቱ ቢሆንም፣ ከዚህ በፊት ያልተከሰቱ አይደሉም፤ በተለይም የድርጅቱ ተንቀሳቃሽ ቡድኖች በማህበረሰቦች መካከል በሚደረጉ ግጭቶች፣ በታጠቁ ወጣቶች እንቅስቃሴ እና ከወታደራዊ ኃይሎች ጋር በሚደረጉ ግጭቶች በተጎዱ አካባቢዎች ይንቀሳቀሳሉ።

በሰኔ ወር የድርጅቱ የደኀንነት ምክር ቤት፣ እየጨመረ በመጣው የኃይል ድርጊት እና ዝቅተኛ የህግ ተጠያቂነት አፈጻጸም ምክንያት፣ በተመድ የሰላም አስከባሪዎች ላይ ለሚፈጸሙ ጥቃቶች ተጠያቂነትን ለማጠናከር የሚያስችል የውሳኔ ሃሳብ አጽድቆ ነበር።

ይህ የተከናወነው በሠራተኞቹ ላይ ከተፈጸሙ ተከታታይ አደጋዎች በኋላ ሲሆን፣ ከነዚህም መካከል በነሐሴ ወር መጀመሪያ ላይ፣ የእስራኤል እና የሂዝቦላህ አዲስ ግጭት ወቅት በሊባኖስ የድርጅቱ ጊዜያዊ ኃይል ውስጥ ያገለግሉ የነበሩ ሦስት የሰላም አስከባሪዎች መገደል ይገኝበታል።

የዓለም ጤና ድርጅት ዋና ዳይሬክተር ዶ/ር ቴዎድሮስ አድሃኖም የስራ ዘመናቸውን በ2027 እንደሚያጠናቅቁ አስታወቁየዓለም ጤና ድርጅት ዋና ዳይሬክተር ዶ/ር ቴዎድሮስ አድሃኖም በመጪው የፈረንጆ...
25/08/2026

የዓለም ጤና ድርጅት ዋና ዳይሬክተር ዶ/ር ቴዎድሮስ አድሃኖም የስራ ዘመናቸውን በ2027 እንደሚያጠናቅቁ አስታወቁ

የዓለም ጤና ድርጅት ዋና ዳይሬክተር ዶ/ር ቴዎድሮስ አድሃኖም በመጪው የፈረንጆቹ ነሐሴ 2027 የስራ ዘመናቸውን እንደሚያጠናቅቁ ይፋ አደረጉ።

ዋና ዳይሬክተሩ አፍሪካ የራሷን የጤና አጀንዳ በባለቤትነት መምራት እንዳለባትና የውጭ ጥገኝነትን በማስቀረት ራሷን መቻል እንደምትችል ተናግረዋል።

ዶ/ር ቴድሮስ በዛሬው ዕለት በአዲስ አበባ በተጀመረው የድርጅቱ ቀጣናዊ ኮሚቴ ስብሰባ ላይ በቪዲዮ ባደረጉት ንግግር እንደገለጹት ኃላፊነታቸውን ከማጠናቀቃቸው በፊት ይህ በዋና ዳይሬክተርነት የተገኙበት የመጨረሻው የቀጣናዊ ኮሚቴ ስብሰባ መሆኑን ገልጸዋል።

ከዘጠኝ ዓመታት በፊት በ2017 በዚምባብዌ ባደረጉት ንግግር አባል ሀገራት የየራሳቸውን የጤና አጀንዳ በመሪነት መያዝ አለባቸው ማለታቸውን ያስታወሱት ዶ/ር ቴድሮስ አሁን ላይ ይህ ሀሳብ አፍሪካ የራሷን ጤና በፋይናንስ የምትደግፍበት ፣ የምታስተዳድርበት እና የምታቀርብበት መሰረታዊ መርህ እየሆነ መምጣቱን ተናግረዋል።

አህጉሪቱ አሁን ላይ ወሳኝ በሆነ የለውጥ ምዕራፍ ላይ እንደምትገኝ የገለጹት ዶ/ር ቴድሮስ አፍሪካ ከምታገኘው የውጭ እርዳታ ይልቅ በገንዘብ ዝውውር እና በከፍተኛ የዕዳ ክፍያ ምክንያት የምታጣው ሀብት በእጅጉ እንደሚበልጥ ጠቁመዋል።

የጤና ታክሶችን በአግባቡ በመጠቀም አፍሪካ የህዝቧን ጤና በራሷ አቅም መደገፍ እንደምትችል ዶ/ር ቴድሮስ በንግግራቸው ገልጸዋል።

ዶ/ር ቴድሮስ ሁላችንም በጋራ የምንፈልጋትን ጤናማ ፣ ደህንነቷ የተጠበቀ እና ፍትሃዊ የሆነች አፍሪካ መገንባት አለብን ብለዋል።

በተጨማሪም አባል ሀገራት በመጪው ግንቦት በሚካሄደው የዓለም ጤና ጉባኤ ላይ የድርጅቱን ዘላቂ የፋይናንስ አቅም ለማሳደግ የሚደረገውን የመዋጮ ጭማሪ እንዲያጸድቁ ዶ/ር ቴድሮስ ጠይቀዋል።

ሀገራቱ ከዓለም አቀፍ የጤና መዋቅር ማሻሻያ ጋር በንቃት እንዲሳተፉ ፣ በዲሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ ለተከሰተው የኢቦላ ወረርሽኝ እየተደረገ ያለውን ምላሽ እንዲደግፉና ድርጅቱን ይበልጥ ቀልጣፋ ለማድረግ የሚሰራውን ስራ እንዲያግዙ አሳስበዋል።

በመጨረሻም "የእናንተ ዋና ዳይሬክተር ሆኜ ማገልገል በሕይወቴ ትልቁ ክብር ነው" ሲሉ የተናገሩት ዶ/ር ቴድሮስ ኃላፊነታቸውን እስከሚያስረክቡ ድረስ በቀሪው አንድ ዓመት ላስቀመጡት ራዕይ አባል ሀገራቱና የድርጅቱ ባልደረቦች ድጋፋቸውን እንዲቀጥሉ ጠይቀዋል።

@ፋሲል ሲሳይ

በኢትዮጵያ የ12ቱ ክልሎችና የዞኖች ስም ዝርዝር!1. ትግራይ ክልል — 6 ዞኖችምዕራባዊ ዞንሰሜን ምዕራባዊ ዞንማዕከላዊ ዞንምስራቃዊ ዞንደቡባዊ ዞንደቡብ ምስራቃዊ ዞን #መቀሌ ከተማ መስተዳድ...
25/08/2026

በኢትዮጵያ የ12ቱ ክልሎችና የዞኖች ስም ዝርዝር!

1. ትግራይ ክልል — 6 ዞኖች

ምዕራባዊ ዞን
ሰሜን ምዕራባዊ ዞን
ማዕከላዊ ዞን
ምስራቃዊ ዞን
ደቡባዊ ዞን
ደቡብ ምስራቃዊ ዞን

#መቀሌ ከተማ መስተዳድራዊ መዋቅር

2. አፋር ክልል — 6 ዞኖች

አውሲ ራሱ
ኪልበቲ ራሱ
ጋቢ ራሱ
ፋንቲ ራሱ
ሀሪ ራሱ
ማሂ ራሱ

3. አማራ ክልል — 14 ዞኖች

ሰሜን ጎንደር
ደቡብ ጎንደር
ምዕራብ ጎንደር
ማዕከላዊ ጎንደር
ምዕራብ ጎጃም
ምስራቅ ጎጃም
አዊ
ዋግ ህምራ
ሰሜን ወሎ
ደቡብ ወሎ
ሰሜን ሸዋ
አርጎባ
ኦሮሞ ብሔረሰብ ልዩ ዞን
ሰሜን ጎጃም

4. ኦሮሚያ ክልል — 22 ዞኖች

ምዕራብ ወለጋ
ምስራቅ ወለጋ
ሆሮ ጉድሩ ወለጋ
ቄለም ወለጋ
ኢሉባቦር
ቡኖ በደሌ
ጅማ
ምዕራብ ሸዋ
ደቡብ ምዕራብ ሸዋ
ሰሜን ሸዋ
ምስራቅ ሸዋ
አርሲ
ምዕራብ አርሲ
ባሌ
ምስራቅ ባሌ
ምስራቅ ሐረርጌ
ምዕራብ ሐረርጌ
ጉጂ
ምዕራብ ጉጂ
ቦረና
ምስራቅ ቦረና
ሰሜራ/ሸገር ከተማ

5. ሶማሌ ክልል — 11 ዞኖች

አፍዴር
ዳዋ
ዶሎ
ፋፋን
ጃራር
ኮራሄ
ሊበን
ኖጎብ
ሸበሌ
ሲቲ
ኤረር

6. ቤኒሻንጉል–ጉሙዝ ክልል — 3 ዞኖች

አሶሳ
መተከል
ካማሺ

#ሁለት ልዩ ወረዳዎች ማኦኮሞና ፓዌ ልዩ ወረዳ

7. ማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል — 7 ዞኖች

ጉራጌ
ምስራቅ ጉራጌ
ሀዲያ
ሀላባ
ስልጤ
ከምባታ
የም

#ሶስት ልዩ ወረዳዎች: ጠምባሮ፣ ማረቆና ቀቤና

8. ደቡብ ኢትዮጵያ ክልል — 12 ዞኖች

ወላይታ
ጋሞ
ጎፋ
ጌዴኦ
ደቡብ ኦሞ
አሪ
ኮንሶ
ጋርዱላ
ቡርጂ
አማሮ ኮሬ
ባስኬቶ
አሌ

9. ደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ክልል — 6 ዞኖች

ከፋ
ሸካ
ቤንች ሸኮ
ኮንታ
ዳውሮ
ምዕራብ ኦሞ

10. ጋምቤላ ክልል — 3 የአስተዳደር ክፍሎች

አኝዋክ
ኑዌር
ማጃንግ

#ኢታንግ ልዩ ወረዳ

11. ሲዳማ ክልል — 5 ዞኖች

ሰሜን ሲዳማ
ማዕከላዊ ሲዳማ
ምስራቅ ሲዳማ
ደቡብ ሲዳማ
ምዕራብ ሲዳማ/አዲስ የተደራጀ ክፍል

12. ሀረሪ ክልል —

24/08/2026
ሱዳን ከኢትዮጵያ ተነሳ ያለችውን ድሮን መትቼ ጣልኩ አለችየሱዳን መከላከያ ሚኒስቴር ከኢትዮጵያ ድንበር አጠገብ ባለው ቦታ ላይ የ"ጠላት" ነው ያለውን አንድ ድሮን መትቶ መጣሉን  አስታወቀ።እ...
24/08/2026

ሱዳን ከኢትዮጵያ ተነሳ ያለችውን
ድሮን መትቼ ጣልኩ አለች

የሱዳን መከላከያ ሚኒስቴር ከኢትዮጵያ ድንበር አጠገብ ባለው ቦታ ላይ የ"ጠላት" ነው ያለውን አንድ ድሮን መትቶ መጣሉን አስታወቀ።

እንደ ሚኒስቴሩ መግለጫ፣ ድሮኑ የተመታው በሱዳን ደቡብ ምስራቅ ክፍል በኩል ባለው የኩርሙክ አካባቢ አየር ላይ እየበረረ ሳለ ነው። ሱዳን ድሮኑ የተነሳው ከኢትዮጵያ መሬት ነው ብላለች፤ ነገር ግን ስለ ድሮኑ ዝርዝር መረጃም ሆነ ማን እንደላከው አላስታወቀችም።

በኢትዮጵያ በኩል በዚህ ጉዳይ ላይ እስካሁን የተሰጠ ምላሽ ወይም ማስተባበያ የለም።

የቴሌግራም ቻናልችንን በመቀላቀል የአዲስ አድማስን መረጃ ይከታተሉ…
https://t.me/AdissAdmas

የትምህርት ሚኒስትር ብርሃኑ ነጋ (ፕ/ር) ምን አሉ ?(የ2018 ዓ/ም የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ውጤት መግለጫ)- የዘንድሮው ውጤት ከአምናው በጥሩ ደረጃ ተሻሽሏል። - ተማሪዎችን ወደ ዩኒ...
24/08/2026

የትምህርት ሚኒስትር ብርሃኑ ነጋ (ፕ/ር) ምን አሉ ?

(የ2018 ዓ/ም የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ውጤት መግለጫ)

- የዘንድሮው ውጤት ከአምናው በጥሩ ደረጃ ተሻሽሏል።

- ተማሪዎችን ወደ ዩኒቨርስቲ አስገብቶ ማስፈተን በተጀመረበት የመጀመሪያ አመት ያለፉ 3.2% ፣ በሁለተኛው 2.9% ፣ በሶስተኛው 5.2% ፣ በአምናው አራተኛው ዓመት 8.9% ደረሰ አሁን በአምስተኛው ዓመት 12.8% ነው ያለፉት።

- ዘንድሮ በ2018 ብሔራዊ ፈተና የተመዘገበው ተማሪ ቁጥር 563,960 ሲሆን 550,210 ተማሪ ነው የተፈተነው።

- ፈተናውን ያለፈው ተማሪ ብዛት 70,544 ነው።

- ከተፈጥሮ ሳይንስ 16.6% አልፈዋል። ከማህበራዊ ሳንይስ 8.3% አልፈዋል።

#በፐርሰንት - ክልሎች ካስፈተኗቸው ተማሪዎች ምን ያህል ተማሪ አሳለፉ ? (ያሰፈተኗቸው ተማሪዎች ቁጥር ይለያያል)

1. አዲስ አበባ 32.3%
2. ሀረሪ 22.67%
3. አፋር 15.6%
4. አማራ 15.56%
5. ድሬዳዋ 11.29%
6. ትግራይ 11.2%
7. ኦሮሚያ 10.53%
8. ማዕከላዊ ኢትዮጵያ 9.23%
9. ሶማሌ 9.2%
10. ሲዳማ 6.95%
11. ቤኒሻንጉል ጉሙዝ 6.12%
12. ደቡብ ኢትዮጵያ 5.82%
13. ደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ 4.92%
14. ጋምቤላ 3.74%

በቁጥር ምን ያህል ተማሪ ከየክልሉ አለፉ ? (ያስፈተኑት ቁጥር ይለያያል)

1. ኦሮሚያ ➡ 20,807 ተማሪዎች
2. አዲስ አበባ ➡ 18,646 ተማሪዎች
3. አማራ ➡ 15,225 ተማሪዎች
4. ትግራይ ➡ 3,146 ተማሪዎች
5. ደቡብ ኢትዮጵያ ➡ 3,011 ተማሪዎች
6. ማዕከላዊ ኢትዮጵያ ➡ 2,800 ተማሪዎች
7. ሲዳማ ➡ 1,827 ተማሪዎች
8. ሶማሌ ➡ 1,616 ተማሪዎች
9. ደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ➡ 835 ተማሪዎች
10. አፋር ➡ 705 ተማሪዎች
11. ሀረሪ ➡ 599 ተማሪዎች
12. ቤኒሻንጉል ጉሙዝ ➡ 457 ተማሪዎች
13. ድሬዳዋ ➡ 410 ተማሪዎች
14. ጋምቤላ ➡ 280 ተማሪዎች

- ባለፈው ዓመት ምንም ተማሪ ያላሳለፉ ትምህርት ቤቶች 1,232 ነበሩ ዘንድሮ ምንም ተማሪ ያላሳለፉ 565 ናቸው።

- ከዚህ ቀደም ምንም ተማሪ ካላሳለፉ ትምህርት ቤቶች ውስጥ በኮፒዩተር ፈተና ወደ 4,500 ተማሪዎች አልፈዋል።

ምንም ተማሪ ያላሳለፉ ትምህርት ቤቶች በክልል ምን ያህል ናቸው ?

• ኦሮሚያ 156
• አማራ 98
• ደቡብ ኢትዮጵያ 86
• ደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ 69
• ትግራይ 48
• ቤኒሻንጉል ጉሙዝ 29
• ማዕከላዊ ኢትዮጵያ 22
• አፋር 21
• ሲዳማ 16
• ሶማሌ 9
• ድሬዳዋ 5
• ሀረሪ 3
• ጋምቤላ 2
• አዲስ አበባ 1

- ሁሉንም ያስፈተኑትን ተማሪዎች ያሳለፉ 100% ያሳለፉ ትምህርት ቤቶች ባለፈው አመት 62 ነበሩ ዘንድሮ 88 ሆነዋል።

በክልሎች ምንም ያህል ትምህርት ቤቶች 100% አሳለፉ ?

• ኦሮሚያ 37
• አዲስ አበባ 24
• አማራ 8
• ደቡብ ኢትዮጵያ 4
• ትግራይ 4
• ማዕከላዊ ኢትዮጵያ 3
• ሲዳማ 2
• አፋር 1
• ድሬዳዋ 1
• ሀረሪ 1
• ሶማሌ 1
• ደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ 1

- በኮምፕዩተር እና በወረቀት በተፈተኑ ተማሪዎች መካከል ያለው የማለፍ ምጣኔ ትልቅ ልዩነት አለው። ኦንላይ የተፈተኑ 18.3% አልፈዋል። በወረቀት የወሰዱ 4.2% ናቸው ያለፉት። አንዱ ቶሎ በወረቀት ከመፈተን መውጥቶ ኦላይን ለመስጠት እቅድ አለው 60% ነው ዘንድሮ ቀጣይ አመት 100% ኦንላይን ሁሉንም።

- የዘንድሮው ከፍተኛ ውጤት ስንት ነው ?

• በተፈጥሮ ሳይንስ •
🥇 ከወንድ 👉 591/600 ኦዳ ስፔሻል ቦርንዲግ ትምህርት ቤት አዳማ
🥇 ከሴት 👉 583/600 ከአገው ምድር ትምህርት ቤት እንጅባራ

• በማህበራዊ ሳንይንስ •
🥇 ከወንድ 👉 576/600 ዶዶላ ኢፋ ቦሩ ትምህርት ቤት
🥇 ከሴት 👉 569/600 አዲስ አበባ ቦሌ ሱፐርሆሊሴቪየር ትምህርት ቤት

- ስልክ ይዘው የገቡ 265 ተማሪዎች ከፈተናው ተሰርዘዋል።

- ኮምፒዩተር ላይ ባለ " ኢሬጉላተሪ " ተብለው ጉዳያቸው እየተጣራ ያለ አለ።

- ከዚህ በፊት ከነበረው መሻሻል እየታየ ስለሆነ በጣም ደስተኞች ነን።

- ዘንድሮም ወደ ሬሜዲያል የሚገቡ ተማሪዎች ይኖራሉ።

- ሬሜዲያል ሁሌ የሚኖር አይደለም። በሚያልፈው ተማሪ ብዛት ነው የሚወሰነው። ዘንድሮ 70 ሺህ ተማሪ ስላለፈ ዘንድሮ ሬሜዲያል የሚገባው ይቀንሳል።

📌 ተማሪዎች ውጤታቸውን ከነገ ሰኞ ወይም ከነገ ወዲያ ማክሰኞ ጀምሮ ውጤታቸው ማየት ይችላሉ። ቲክቫህ ኢትዮጵያ ተማሪዎች ውጤት የሚመለከቱባቸውን አማራጮች ተከታትሎ ያቀርባል።

በኦሮሚያ ክልል የደገም ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ በታጣቂዎች ተገደሉበኦሮሚያ ክልል ሰሜን ሸዋ ዞን ደገም ወረዳ ትናንት ነሐሴ 17 ቀን 2018 ዓ.ም. በደረሰ የጥቃት አደጋ የወረዳው ዋና አስተዳ...
24/08/2026

በኦሮሚያ ክልል የደገም ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ በታጣቂዎች ተገደሉ

በኦሮሚያ ክልል ሰሜን ሸዋ ዞን ደገም ወረዳ ትናንት ነሐሴ 17 ቀን 2018 ዓ.ም. በደረሰ የጥቃት አደጋ የወረዳው ዋና አስተዳዳሪ አቶ ተፈራ ደሴ መገደላቸው ተገለጸ።

ጥቃቱ የተፈጸመው በወረዳው አኖ ቀሬ ቀበሌ ውስጥ ሲሆን፣ በተመሳሳይ አጋጣሚ የቀበሌው ሊቀ መንበር አቶ አስፋወሰን ኃይሌን ጨምሮ ሌሎች ሰዎችም አካላዊ ጉዳት ደርሶባቸው በሰላሌ ዩኒቨርሲቲ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል ሕክምና በመከታተል ላይ ይገኛሉ።

በዕለቱ በመንግሥት የጸጥታ ኃይሎች እና በታጣቂዎች መካከል የተኩስ ልውውጥ ሲደረግ እንደነበር የጠቀሱት የዞኑ የጸጥታ መዋቅር ምንጮች፣ ለጥቃቱ በክልሉ የሚንቀሳቀሰውን የኦሮሞ ነጻነት ሠራዊት (ኦነሠ) ተጠያቂ አድርገዋል።

ታጣቂ ቡድኑም ሆነ የዞኑ እና የክልሉ አስተዳደር አካላት ስለሁኔታው እስካሁን የሰጡት ይፋዊ መግለጫ የለም።

በሰሜን ሸዋ ዞን በመንግሥት ባለሥልጣናት ላይ ጥቃት ሲፈጸም የመጀመሪያው አለመሆኑ የሚታወስ ሲሆን፣ ቀደም ሲልም የሱሉልታ እና የወጫሌ ወረዳ አስተዳዳሪዎችን ጨምሮ በርካታ የዞን ኃላፊዎች ተመሳሳይ ግድያ ተፈጽሞባቸዋል።

ምንጭ፦ ቢቢሲ አፋን ኦሮሞ (BBC Afaan Oromoo)

 #ከ18 ዓመታት የስቃይ ጥላ ወደ ደስታና ተስፋ||በየካቲት 12 ሆስፒታል ሜዲካል ኮሌጅ በተሳካ የፕላስቲክና ሪኮንስትራክቲቭ ሰርጀሪ የ18 ዓመቷን ትዕግስት አበበን ህይወት ወደ አዲስ ምዕራፍ...
23/08/2026

#ከ18 ዓመታት የስቃይ ጥላ ወደ ደስታና ተስፋ||

በየካቲት 12 ሆስፒታል ሜዲካል ኮሌጅ በተሳካ የፕላስቲክና ሪኮንስትራክቲቭ ሰርጀሪ የ18 ዓመቷን ትዕግስት አበበን ህይወት ወደ አዲስ ምዕራፍ ቀይሯል።

የካቲት 12 ሆስፒታል ሜዲካል ኮሌጅ አዲስ አበባ ነሃሴ 16/2018 ዓ.ም

አንዳንድ የህይወት አጋጣሚዎች ሰውን ለጥቂት ጊዜ ብቻ አይፈትኑም የሚቆዩት ለዓመታት ነው አንድ የልጅነት አደጋ የ18 ዓመቷን ትዕግስት አበበን ለዚህ ዓመታት የሚዘልቅ ፈተና ዳርጓት ነበር። ዛሬ ግን ያ ረጅም የስቃይ ጉዞ በተስፋ፣ በደስታና በአዲስ የህይወት እድል መቀየር ጀምሯል።

ትዕግስት በአማራ ክልል ደቡብ ወሎ አካባቢ ከ18 ዓመታት በፊት ተወለደች ገና የስድስት ወር ህፃን ሳለች የልጅነት ህይወቷን በአንድ አሳዛኝ አጋጣሚ ተለወጠ ከፍራሽ ላይ ተንከባላ በእሳት ላይ ወደቀች።

የቃጠሎው አደጋ በእጇ ላይ ከባድ ጠባሳና መጨማደድ አስከትሎ የእጅዋን እንቅስቃሴ ሙሉ በሙሉ ገደበ በወቅቱ ወደ ህክምና ተቋም ብትወሰድም የተሟላ የህክምና እና የሪኮንስትራክቲቭ ሰርጀሪ እድል ሳታገኝ ቀረች።

ከዚያ በኋላ ዓመታት አለፉ። ትዕግስትም ከልጅነቷ ጀምሮ የእጇን እንቅስቃሴ በመገደብ እና በዕለት ተዕለት ኑሮዋ ላይ ተጽዕኖ በማሳደር የቆየውን የቃጠሎ መጨማደድ ይዛ አደገች። እጇን ሙሉ በሙሉ መዘርጋትና መታጠፍ፣ የፈለገችውን ነገር በነፃነት መያዝ እና እንደሌሎች ሰዎች በእጇ ተጠቅማ የዕለት ተዕለት ተግባሯን ማከናወን ለእሷ በፍፁም አይታሰብም።

18 ዓመታት ከህፃንነት እስከ ወጣትነት እነዚህ ዓመታት ትዕግስት እጇን ብቻ ሳይሆን በልቧም የተሸከመችው የትዕግስት ጉዞ ነበሩ። በስሟ ያለውን “ትዕግስት” በእውነት እንድትኖረው ያደረገ ጉዞ።

ከዚያ ግን አንድ ቀን ተስፋ መጣ ለ18 ዓመታት የቆየውን ችግር በመቀየር ትዕግስት ወደ የየካቲት 12 ሆስፒታል ሜዲካል ኮሌጅ ለህክምና እንድትመጣ የሚያደርግ አጋጣሚ አገኘች።

በተቋሙ የፕላስቲክና ሪኮንስትራክቲቭ ሰርጀሪ ባለሙያዎች ትዕግስትን በጥንቃቄ መርምረው፣ የቃጠሎው መጨማደድ እጅግ ከፍተኛ ደረጃ በመሆኑ በእጇ ላይ ያስከተለውን ጉዳት በመገምገም ተስማሚ የህክምና እቅድ አዘጋጁ።

በዶ/ር ዳግማዊ ገረመዉ የፕላስቲክና ሪኮንስትራክቲቭ ሰርጀሪ ሀኪምና ረዳት ፕሮፌሰር የተመራው የህክምና ቡድን የላቀ እና የተሳካ የፕላስቲክና ሪኮንስትራክቲቭ ሰርጀሪ አከናወነላት።

የቀዶ ህክምናው ዓላማ የእጇን ገደብ ማስወገድና የእጅዋን እንቅስቃሴ በተቻለ መጠን ማሻሻል ነበር ለትዕግስት ግን ይህ ከቀዶ ህክምና በላይ ነበር፤ ለ18 ዓመታት የተዘጋችበትን የነፃነት በር እንደገና የከፈተ እድል ነበር።

የህክምናው ውጤት ከተስፋ በላይ የሆነ ደስታን ይዞ መጣ ትዕግስት እጇን ከቀድሞው በተሻለ ሁኔታ መዘርጋትና መታጠፍ ጀመረች የፈለገችውን ነገር ጨብጣ መያዝ ቻለች ሰውን በእጅ መጨበጥ ቻለች ከሁሉም በላይ ግን በእጇ ላይ የነበረው ገደብ በህይወቷ ላይ ያሳደረው የመተማመን ማነስ በአዲስ ተስፋ መተካት ጀመረ።

ከዚህ በፊት ለእሷ ቀላል ያልነበሩ ነገሮች አሁን በተሻለ ሁኔታ ይቻላሉ እጇን በነፃነት ማንቀሳቀስ ብቻ ሳይሆን የወደፊት ህይወቷንም በተስፋ ማየት ጀምራለች።

ከህመም ወደ ደስታ ከገደብ ወደ ነፃነት ከተስፋ መቁረጥ ወደ ተስፋ ከ18 ዓመታት የቃጠሎ መጨማደድ ወደ አዲስ የህይወት ምዕራፍ።

ህክምናውን ያከናወኑት ዶ/ር ዳግማዊ ገረመዉ እንደሚገልፁት የፕላስቲክና ሪኮንስትራክቲቭ ሰርጀሪ የአካል ገጽታን ለማስተካከል ብቻ የሚደረግ ህክምና አይደለም በተለይም እንደ ትዕግስት ያሉ ታካሚዎች ለዓመታት የተሸከሙትን የአካል ገደብ በማሻሻል ወደ የተሻለ የኑሮ ጥራት እንዲመለሱ የሚያስችል የህይወት ለውጥ ነው ያሉት።

የትዕግስት ጉዳይም ይህንኑ ያሳያል ለ18 ዓመታት ከእሷ ጋር የኖረው የቃጠሎ ጠባሳ ዛሬ የህይወቷ መጨረሻ ሳይሆን አዲስ ምዕራፍ መጀመሪያ ሆኗል።

በየካቲት 12 ሆስፒታል ሜዲካል ኮሌጅ የፕላስቲክና ሪኮንስትራክቲቭ ሰርጀሪ ቡድን የተሰራው ስራም አንድ ህክምና ተሳክቷል ከሚል በላይ የሚገልጽ ነው አንዲት ወጣት እንደገና በራሷ እንድትተማመን፣ እጇን በነፃነት እንድትጠቀም እና የወደፊት ህይወቷን በተስፋ እንድትመለከት እድል ሰጥቷል።

የትዕግስት ታሪክ በአንድ ቃል ሲጠቃለል “ተስፋ እስካለ ድረስ ለውጥ ይቻላል” የሚል ትልቅ መልዕክት ነው።

ዛሬ የ18 ዓመቷ ትዕግስት የትናንቱን ህመም ትታ የነገውን ህይወት በተስፋ ለመገንባት በአዲስ መንፈስ ወደፊት ትመለከታለች።

ይህ ተአምር ብቻ አይደለም የህክምና እውቀት የሙያ ትጋት የታካሚ ትዕግስት እና ተስፋ ተደምረው የፈጠሩት የህይወት ለውጥ ነው።

#ማስታወሻ: የፎቶ እና ሕክምና ታሪክ ፈቃድ ከታካሚ ተወስዷል::

የየካቲት 12 ሆስፒታል ሜዲካል ኮሌጅ — ህይወትን በህክምና መለወጥ።

"አንድ ቤት ውስጥ አይጥ ገባ ብለን ቤቱን አናቃጥልም!" - ሌተናል ጄኔራል ይልማ መርዳሳ
23/08/2026

"አንድ ቤት ውስጥ አይጥ ገባ ብለን ቤቱን አናቃጥልም!" - ሌተናል ጄኔራል ይልማ መርዳሳ

Address

Churchil
Addis Ababa

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Inform Ethiopia posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to Inform Ethiopia:

Shortcuts

Share

Category