Wollo media house

Wollo media house Fast and accurate information

11/01/2023

በምእራብ የታሰረ የሩሲያ ዘይት በምትኩ ወደ እስያ ይሄዳል

ቻይና የአርክቲክ ደረጃዎችን ጨምሮ የሩስያ ድፍድፍ ዘይት ወደ ሀገር ውስጥ ያስገባችውን ደረጃ ከፍ አድርጋለች ሲል ብሉምበርግ ማክሰኞ ዘግቧል የዘይት ፍሰት መከታተያ መረጃን ከቮርቴክሳ እና ከፕለር በመጥቀስ።

የአውሮፓ ህብረት በሩሲያ የፔትሮሊየም ምርቶች ላይ እገዳው በሚተገበርበት በዚህ ወር እና በየካቲት ወር ማቅረቢያዎች ታቅደዋል ። አንዳንድ ነጋዴዎች እድገቱ የሩስያ አቅርቦቶችን በአለም አቀፍ ደረጃ መቀየርን እና ቻይና ከመካከለኛው ምስራቅ ዘይት መራቅን ያሳያል ብለው ያምናሉ.

ዓባይ ለኢትዮጵያ ብርሃን መስጠት ጀመረOn Feb 20, 2022  331አዲስ አበባ፣ የካቲት 13፣ 014 (ኤፍ ቢ ሲ) ዛሬ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ 375 ሜጋ ዋት የሚያመነጨውን የታላ...
20/02/2022

ዓባይ ለኢትዮጵያ ብርሃን መስጠት ጀመረ
On Feb 20, 2022 331
አዲስ አበባ፣ የካቲት 13፣ 014 (ኤፍ ቢ ሲ) ዛሬ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ 375 ሜጋ ዋት የሚያመነጨውን የታላቁ ህዳሴ የግድቡ የኤሌክትሪክ ኃይል የማመንጨት ሂደትን በይፋ አስጀምረዋል፡፡
የዓባይ ወንዝ በኢትዮጵያዊያን ዘንድ የስነ ቃልና ይትባሀሉ የቁጭት፣ የእንጉርጉሮና የወቀሳ ዜማ ሆኖ ኖሯል።
ዓባይ ማደሪያ ቢስነቱ በሊቃውንትና ጠቢባን አርዕስት ሆኖ ለዘመናት ተወቅሷል።
የዐባይ ውኃ መጠጥ ሆኖ እንዲጠጣ፣ መና ሆኖ እንዲጎረስ፣ ሲሳይ ሆኖ እንዲቆረስ የእልፍ ኢትዮጵያውያን ምኞት ነበር።
በትችትና ምኞት፣ በተስፋና ወቀሳ የተወገረው የዓባይ ወንዝ ግንድ ይዞ ዟሪነቱ ሊገታ፣ የልጅ ባዕዳነቱ ሊያከትም፣ ማደሪያ ቢስነቱ ሊቆም…የተወጠነው በታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ጥንስስ ነበር።
በወርሀ መጋቢት 24 ቀን 2003 ዓ.ም በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል፣ በጉባ ወረዳ የግንባታው የመሠረት ድንጋይ ተቀመጠ።
በህዝብ የድጋፍ ማዕበል ታጅቦ፣ በጠላት ዐይን ተገርምሞ፣ ዳፋና ተግዳሮቶችን ተሻግሮ ከ11 ዓመት በኋላ … የተስፋ ፍሬው ተቀመሰ።
የታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ሕዝባዊ ተሳትፎ አስተባባሪ ብሔራዊ ምክር ቤት ጽሕፈት ቤት መረጃ መሰረት የዋናው ግድብ ከፍታ 145 ሜትር ሲሆን÷ ርዝመቱ ደግሞ 1 ነጥብ 8 ኪሎ ሜትር ነው።
የዋናው ግድብ ውፍረት የግድቡ ግርጌ ላይ 130 ሜትር፤ የግድቡ ጫፍ ወይም የላይኛው ክፍል ደግሞ 11 ሜትር ነው።
1 ሺህ 680 ስኩዌር ኪሎ ሜትር የቦታ ስፋት ያለው ግድቡ 74 ቢሊየን ኪዩቢክ ሜትር የውሃ መጠን ይይዛል።
ከ375 እስከ 400 ሜጋ ዋት የሚያመየጩ 13 የኃይል ማመንጫ ዩኒቶች አሉት።
ኢትዮጵያ ከግድቡ አመንጭታ ፍጆታዋን ካሟላች በኋላ 2 ሺህ ሜጋዋት ገደማውን ለጎረቤት አገራት በመሸጥ በዓመት እስከ 580 ሚሊየን ዶላር ገቢ ማግኘት እንደምትችል ግምቶች ተቀምጠዋል።
ባለፉት ሁለት ዓመታት በነበረው ተከታታይ የክረምት ዝናብ የመጀመሪያና ሁለተኛው ዙር የግድቡ ውሃ ሙሌት ተከናውኗል።
ግድቡ ሲጠናቀቅ ውሃ የሚተኛበት መሬት 246 ኪሎ ሜትር ይረዝማል።
ዛሬ 375 ሜጋዋት የሚያመነጨው አንደኛው ዩኒት በይፋ ስራ ጀምሯል። ሁለተኛው ዩኒት ደግሞ በዝግጅት ላይ ይገኛል።
የግድቡ ግንባታ በአጠቃላይ ሲጠናቀቅም 6 ሺህ 450 ሜጋ ዋት የኤሌክትሪክ ኃይል ያመነጫል።
የታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ በአፍሪካ ውስጥ ትልቁ የኤክትሪክ ኃይል ማመንጫ ግድብ ይሆናል።
ኢትዮጵያን፦ እናልማ፣ እንገንባ፣ እንዘጋጅ
ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://m.facebook.com/109776264766956/

26/01/2022

የአማራ ክልል የእስልምና ጉዳዮች ም/ቤት በክልሉ መስጂዶችና ምዕመኑ ላይ የሚደርሱ ትንኮሳዎችና ጥቃቶች ተባብሰዋል አለ!

የአማራ ክልል የእስልምና ከፍተኛ ጉዳዮች ምክር ቤት በክልሉ መስጂዶችና ምዕመኑ ላይ የሚደርሱ ትንኮሳዎችና ጥቃቶች ተባብሰዋል ሲል ባወጣው መግለጫ አመልክቷል፡፡

ምክር ቤቱ ባሰራጨው መግለጫ ባለፉት ሦስት ዓመታት በተለይ በደቡብ ጎንደር እና በምሥራቅ ጎጃም በተደራጀና በተቀነባበረ መንገድ በጠራራ ፀሐይ 7 መስጂዶችና በውስጡ የሚገኙ ቅዱስ ቁርኣን እና ሌሎች መጻሕፍት ‹‹በሃይማኖት ሽፋን እኩይ አላማቸውን ለማሳካት›› በሚንቀሳቀሱ ባላቸው አካላት መቃጠላቸውን አስታውሷል፡፡

ይህ ሁሉ ወንጀል በሕዝብ እና በአምልኮ ቦታዎች ላይ ሲፈጸም አንድም ወንጀለኛ ለሕግ ቀርቦ ውሳኔ እንዳልተሰጠው ያመለከተው ምክር ቤቱ፣ በዐል በመጣ ቁጥር የጎንደር ከተማን ጨምሮ በሌሎችም አካባቢዎች ስጋቱና ትንኮሳው መቀጠሉን ጠቁሟል፡፡

ምክር ቤቱ ለዚህ በማሳያነት ከቀናት በፊት በተከበረው የጥምቀት በዐል ወቅት ተፈጽመዋል ያላቸውን ‹‹ሕዝብን ለግጭት የሚዳርጉ›› እና ‹‹የቆሰለች›› ያላትን ኢትዮጵያን ሰላሟን የሚያናጋ ያላቸውን ተግባራት ዘርዝሯል፡፡

ከነዚህ መካከል የአማራ ክልል እስልምና ጉዳዮች ከፍተኛ ምክር ቤት የግንብ አጥር መፍረሱን፣ በተመሳሳይ ባህር ዳር ከተማ አባይ ማዶ የሚኖሩት ትልቅ የሙስሊም አባት መኖሪያ ቤት በድንጋይ መደብደቡን፣ በደሴ ከተማ የአረብ ገንዳ መስጅድ ሙስሊሞች በስግደት ላይ ባሉበት ወቅት መስጂዱ በጥይት መደብደቡን፣ በጎንደር የሚገኘው ነስረላህ የተሰኘ መስጅድ አጥር እና ጣሪያ በጥይት መመታቱን እንዲሁም በምዕራብ ጎጃም በሙስሊም መቃብር ላይ መስቀል የመትከል ድርጊት መታየቱንም ጠቅሷል፡፡

እነዚህን አና ሌሎችንም ድርጊቶች ያወገዘው የምክር ቤቱ ስራ አስፈጻሚ ፣ በተለይ በባህር ዳር የምክር ቤቱ አጥር ግንብ ሲፈርስ ስምሪት የተሰጣቸው የፖሊስ እና ሚሊሻ አባላት በዝምታ በመመልከታቸው እንዲጠየቁ ያለ ሲሆን፣ የክልሉ መንግስትና በየደረጃው ያለው አስተዳዳርም አደጋውን አርቆ በማሰብ ወንጀለኞች በሕግ አግባብ እንዲታረሙ እንዲያደርጉ አሳስቧል፡፡

ከዚሁ ጋር በተገናኘ የአማራ ክልል የእስልምና ከፍተኛ ምክር ቤት ይህ መግለጫ ሳይቆራረጥ እንዲተላለፍለት የተላከለት የአማራ ሚዲያ ኮርፖሬሽን መግለጫውን ለማሠራጨት ፍቃደኛ ሳይሆን መቅረቱ ተነግሯል፡፡ኮርፖሬሽኑ መግለጫውን ላለማስተላለፉ ያቀረበው ምክንያት ስለመኖሩ የተጠቀሰ ነገር የለም፡፡

20/01/2022

ጅብ ከሄደ በኋላ የውሻ መጮህ ምንም ውጤት አያመጣም፤ ትርፉ ድካም ነው፡፡ ውጤት የሚያመጣው ጅቡ ከመምጣቱ በፊት አስቀድሞ በማነፍነፍ ድምጽ ማሰማት ነው፡፡ ሁኔታዎችን፣ ሌሎች ሰዎችን፣ ዓለምን ወዘተ የሚወቅሱ ሰዎች በህይወታቸው የረባ ቁም ነገር አያከናውኑም፤ ሁልጊዜም ኃላፊነትን የሚያሸክሙት ከእነሱ ውጪ ላለ ሌላ አካል ነው፡፡ ኃላፊነትን መሸከም ስንችል ነው የህይወታችንን ጉዞ አቅጣጫ መወሰን የምንችለው፡፡ የተሸከርካሪውን መሪ ለሌላ አካል አሳልፈን ሰጥተን የምፈልገው ቦታ አይደለም የደረስኩት፤ በፈለኩት ፍጥነት አይደለም እየተጓዝኩ ያለሁት ወዘተ ልንል አንችልም፤ ብንልም ዋጋ የለውም፡፡ የጉዞውን አቅጣጫ፣ ፍጥነት እና አድራሻ የሚወስነው አሽከርካሪው ነው፡፡ ልምዳችን መውቀስ፣ ጣት መጠቆም፣ ራስን መከላከል ወዘተ ከሆነ እውነቱን ለመናገር የሚወቀስ ነገር ማግኘት አይከብድም፡፡ ዘወትር የእናቴ መቀነት አደናቅፎኝ ነው ማለት ህይወታችን ባለህበት እርገጥ እንዲሆን በር ወለል አድርጎ ይከፍታል፡፡ ስለዚህ ለውጥ ለማምጣት፣ የራሳችን ሰዎች ለመሆን፣ ውስጣችንን ድል ለማድረግ ወዘተ ሁልጊዜም ለገዛ ራሳችን ህይወት ሙሉ ኃላፊነት እንውሰድ፡፡ ቃላችንን የምናከብር፤ በአልንበት ቦታ የምንገኝ፤ በገዛ ራሳችን ጥረት የምንፈልገውን ማንኛውንም ዓይነት ነገር እጃችን ለማስገባት መጓዝ ያለብንን ያህል ርቀት መጓዝ የምንችል ሰዎች እንሁን፡፡ “ስራ እኮ ጠፋ! እኔ ምን ላድርግ?!” ከማለታችን በፊት ስራ ለማግኘት የምንችለውን ድንጋይ በሙሉ መፈንቀላችንን እርግጠኛ እንሁን፤ ቀጣሪዎች የሚፈልጉትን ዕውቀት እና ክህሎት ይዘን ለመገኘት ጥረት እናድርግ፤ የተለመደውንም ያልተለመደውንም አማራጭ እንፈትሽ፡፡ ሳይኮሎጂስቶች “Life is 10 % what happens to us and 90 % how we react to it” ይላሉ፡፡ የህይወታችንን አብዛኛውን (90 %) ክፍል በምንፈልገው መልኩ መስራት እንችላለን ማለት ነው፡፡ የምናጭደው የዘራነውን ነው፡፡

18/01/2022

በአፋር እና በትግራይ ክልሎች አዋሳኝ በምትገኘው የአብአላ ከተማ እና በዙሪያዋ በሚደረገው ውጊያ 40 ሺሕ ገደማ ነዋሪዎች መፈናቀላቸውን የአፋር ክልል የአደጋ ሥጋት ሥራ አመራር ቢሮ ኃላፊ ተናገሩ። የቢሮው ኃላፊ አቶ መሐመድ ሑሴን ለዶይቼ ቬለ እንደተናገሩት ተፈናቃዮቹ በክልሉ አምስት ጣቢያዎች ይገኛሉ።
F759B726_2.mp3
ከትግራይ ክልል ጋር ሰፊ የአስተዳደር ወሰን ያለው የአፋር ክልል በሰሜን ኢትዮጵያው ጦርነት ከተጠቁና ከፍተኛ ሰብዓዊ ቀውስ ከተከሰተባቸው ነው፡፡ በሰሜን የአገሪቱ ክፍል የኢትዮጵያ መንግስትን የሚዋጋው ህወሓት በአፋር በርካታ ስፍራዎችን ከተቆጣጠረበት ከወጣም በኋላ ከሳምንታት በፊት እንዳድስ የማያቋርጥ የከባድ መሳሪያ ተኩስ ከፍቶበታል በተባለው የአፋር ክልል ዞን ሁለት ዋና ከተማ አብዓላ ከፍተኛ የሰብዓዊ ቀውስ መከሰቱ ነው የሚነገረው፡፡ ከትግራይ ክልል ዋና ከተማ መቀሌ 40 ኪ.ሜ. ገደማ ቅርበት ላይ እንደምትገኝ በሚነገረው አብዓላ በዚሁ የቅርብ ጊዜ ግጭት ብቻ ከ40 ሺህ በላይ የከተማዋ ነዋሪዎች ተፈናቅለው አብዛኞቹ አሁን ላይ በመጠለያ ካምፕ ውስጥ እንደሚገኙ ነው የክልሉ አደጋ ስጋት ስራ አመራር ቢሮ ኃላፊ አቶ መሃመድ ሁሴን ለዶይቸ ቬለ የተናገሩት፡፡
በሰመራ-አብዓላ-መቀሌ ኮሪደር ወደ ትግራይ ክልል ሰብዓዊ ድጋፎችን ለማድረስ ብቸኛው መንገድ እንደሆነ የሚነገረው በዚህ የአፋር ዞን 2 አብዓላ ከተማ ላይ ቅጭት የተቀሰቀሰው የፌዴራሉ መንግስት ወታደራዊ ሰራዊቱ ወደ ትግራይ ክልል እንዳይገባ ትዕዛዝ ባስተላለፈበት ማግስት መሆኑን ነው ኃላፊው ሚጠቁሙት፡፡

Address

Bole
Addis Ababa

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Wollo media house posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to Wollo media house:

Share