Amhara Today አማራ ዛሬ

Amhara Today አማራ ዛሬ ሰለዐማራ ሁሉናዊ ጉዳዮች ታሪክ ግዛት ስነልቦና ባህልና ማንነ

እስራኤል ከአልቡርሃን ጋር ግንኙነት እንዳታደርግ አሜሪካ አሳሳበችየአሜሪካ ስቴት ዲፓርትመንት እስራኤል ሲቪል መንግስት ገልብጦ በወታደሮች የሚመራ መንግስት ከመሠረተው አካል ጋር ዲፕሎማሲያዊ ...
30/05/2022

እስራኤል ከአልቡርሃን ጋር ግንኙነት እንዳታደርግ አሜሪካ አሳሳበች
የአሜሪካ ስቴት ዲፓርትመንት እስራኤል ሲቪል መንግስት ገልብጦ በወታደሮች የሚመራ መንግስት ከመሠረተው አካል ጋር ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነቷን ከማደስ እንድትቆጠብ አሳሳበ፡፡
“እስራኤል ዓለም አቀፍ ማህበረሰቡን በመቀላቀል በይፋ ወታደራዊው አመራሮች ላይ ጫና እንድትፈጥር እንዲሁም ተዓማኒነት ላለው የሲቪሊያን መንግስት ሥልጣኑን እንዲያስርከብ እየተደረጉ ያሉ ርብርቦችን እንድትደግፍ እናበረታታለን” ብሏል መግለጫው፡፡
እንደ አሜሪካ መግለጫ በአልቡርሃን የሚመራው ወታደራዊው ክንፍ በሲቪል መንግስት ላይ ያደረገው መፈንቅለ-መንግስት አሁን ላይ ከአገሪቱ ጋር ግንኙነት ማድረግን አስተማማኝ እንዳይሆን አድርጎታል፡፡ በመሆኑም ሱዳን ለጊዜው ወዳጅነቷን ለማሻሻል ከምታደርገው ጥረት ይልቅ ሱዳን ወደ ሰላም እንድትመለስ የሚደረገውን እንቅስቃሴ እንድትቀላቀል ግብዣ አድርጓል፡፡
በፕሬዝዳንት ትራምፕ አግባቢነት በአረብ አገራትና በእስራኤል አገራት መካከል የተደረሰው “የአብርሃም ስምምነት” በዩ.ኤ.ኢ፣ ባህሬይን፣ ሞሮኮ እና ሱዳን ከእስራኤል ጋር ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት እንዲሚሰረቱ ያደረገ ሲሆን ከሱዳን በስተቀር የሌሎቹ ግንኙነት በመልካም ሁኔታ ላይ ይገኛል፡፡
እስራኤል ከሱዳን ጋር ያላትን ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት በፍጥነት እንዲከናወን ፍላጎቱ የነበራት ቢሆንም የሱዳን የውስጥ አለመረጋጋት፣ መፈንቅለ መንግስት እና ወታደራዊ አመራሮቹ በዓለም አቀፍ ማህበረሰቡ እያስተናገዱ ያሉት ተቃውሞ ግንኙነቱን ውስብስብ አድርጎታል፡፡ አልቡርሃን ልዑካኖቹን ወደ እስራኤል በተደጋጋሚ በመላክ ጉዳዩ በቶሎ እንዲያልቅ በዛውም ተቃዋሚ ሰልፈኞችን መበተን የሚያስችል ድጋፍ ከእስራኤል እንዲሰጠው ሲጠይቅ ነበር፡፡
አልቡርሃን “ከእስራኤል ጋር የሚኖረውን ፖለቲካዊ ግንኙነቱን የሚመረጠው የሲቪል መንግስት የሚያከናውነው በመሆኑ እኛ የጸጥታ ትብብር ብቻ ነው ያደረግነው” ማለቱ ተቃዋሚዎችን በብልሃት ለማስወገድ ከእስራኤል የስለላ እና የቁሳቁስ ድጋፍ ለማግኘት ነው ሲሉ ለውጥ ፈላጊዎች ድምጻቸውን እያሰሙ ነው፡፡
አልቡርሃን በግብጽ አማላጅነት የእስራኤልንና የአሜሪካን ልብ ለማግኘት ተደጋጋሚ ሙከራዎችን ቢያደርግም ከአሜሪካ ድጋፍ ውጭ እስራኤል ከሱዳን ጋር ግንኙነት መመስረት የማትችል በመሆኑ ለጊዜው የአልቡርሃን ህልም መጨናገፉ አይቀሬ ይመስላል፡፡
ተሰሚነት ያላቸው የሱዳን ተቃዋሚዎች እስራኤል ከአሁኑ ወታደራዊውን መንግስት በመቃወም አቋሟን ግልጽ ካላደረገች ወደ ፊት ከሚኖረው የሲቪል መንግስት ጋር የሚኖራት ግንኙነት ጥያቄ ውስጥ ይገባል እያሉ ነው፡፡
እስራኤል በይፋ ወታደራዊውን መንግስት መቃወም ባትፈልግ እንኳን ቀስ ቀስ እያለች ማፍግፈጓ አይቀሬ በመሆኑ አልቡርሃን ከአስራኤል የፈረጠመ ወታደራዊ ቴክኖሎጂ ተቋድሼ ተቃዋሚዎቼን አጠፋለሁ የሚለው ምኞቱ መና ይሆናል የሚል እምነት በሱዳን ልሂቃን በስፋት የታመነበት ጉዳይ ነው፡፡
Abay Tube
የዩቲዩብ ቻናል
•YouTube: - https://www.youtube.com/channel/UCvOuOX2nVqsK_gX-J0fcvsw
•Facebook: - https://www.facebook.com/AbayOnYoutube/
•Instagram: - https://www.instagram.com/abayentertainment
•Telegram: - https://t.me/AbayonYouTube
ስብስክራይብ ማድረጉዏን እንዳይረሱ ስለጉበኙን እናመሰግናለን።

 የባሕርዳር ከተማ አስተዳደር በማህበር ለተደራጁ የመኖሪያ ቤት ህብረት ሥራ ማህበራት ቦታ ማስረከብ ጀመረየባሕርዳር ከተማ አስተዳደር በማኅበር ለተደራጁ የመኖሪያ ቤት ኅብረት ሥራ ማኅበራት ቦ...
27/05/2022


የባሕርዳር ከተማ አስተዳደር በማህበር ለተደራጁ የመኖሪያ ቤት ህብረት ሥራ ማህበራት ቦታ ማስረከብ ጀመረ
የባሕርዳር ከተማ አስተዳደር በማኅበር ለተደራጁ የመኖሪያ ቤት ኅብረት ሥራ ማኅበራት ቦታ ማስረከብ መጀመሩን አስታወቀ።
የባሕር ዳር ከተማ አስተዳደር የመንግሥት ኮሙኒኬሽን መምሪያ ኃላፊ አቶ በትግሉ ተስፋሁን በዚህ ዓመት በሁለት ዙር በማኅበር ለተደራጁ ማኅበራት ቦታ ለማስረከብ እየተሠራ መሆኑን ገልጸዋል።
አሁኑ ሰዓትም በመጀመሪያው ዙር ለ196 ማኅበራት በመሸንቲ ሳይት ቦታ ርክክብ ተደርጓል ብለዋል፡፡
እስከ ግንቦት መጨረሻም ለተጨማሪ 469 የመኖሪያ ቤት ኅብረት ሥራ ማኅበራት በዘንዘልማ ሳይት ቦታ ለመስጠት ከሶስተኛ ወገን መሬት ነጻ መደረጉን ገልጸዋል፡፡
በሁለተኛ ዙርም ከተማ አስተዳደሩ ሁሉንም የተደራጁ ማኅበራት ቦታ ለማስረከብ የቅድመ ዝግጅት ሥራዎች ማጠናቀቁን ገልጸዋል።
ዝቅተኛ ገቢ ያላቸው የህብረተሠብ ክፍሎችም መጠለያ ያገኙ ዘንድ ከባለሀብቶችና ከተለያዩ አካላት ጋር ሥራዎች እየተሠሩ መሆኑንም ነው የተናገሩት፡፡
የእርሻ መሬታቸውን ለማኅበራቱ የሚለቁ አርሶአደሮችም ካሳ መከፈሉንና የመኖሪያ ቤት መስሪያ ቦታ መሠጠቱን ጠቅሰው፥ ለአቅመ አዳም የደረሱ የአርሶ አደር ልጆችም በ11ማኅበራት በማደራጀት የመኖሪያ ቤት መስሪያ ቦታ መሰጠቱን አስረድተዋል፡፡
ከተማው ካለው ውስን የመሬት ሀብት አኳያ ከዚህ በኋላ ሌሎች ማኅበራትን ለማስተናገድ አስቸጋሪ መሆኑን ያነሱት ኃላፊው÷ የጋራ የመኖሪያ ቤት አፓርትመንት በመገንባት ነዋሪዎችን የመኖሪያ ቤት ባለቤት ለማድረግ ከክልሉ መንግስት አቅጣጫ እየጠበቁ መሆናቸውንም ገልጸዋል።
Abay Tube
የዩቲዩብ ቻናል
•YouTube: - https://www.youtube.com/channel/UCvOuOX2nVqsK_gX-J0fcvsw
•Facebook: - https://www.facebook.com/AbayOnYoutube/
•Instagram: - https://www.instagram.com/abayentertainment
•Telegram: - https://t.me/AbayonYouTube
ስብስክራይብ ማድረጉዏን እንዳይረሱ ስለጉበኙን እናመሰግናለን።

አልሸባብ በአዲስ አበባ ሊፈጽም የነበረው የሽብር ተግባር መክሸፉን ፖሊስ አስታወቀአዲስ አበባ፣ ግንቦት 18፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) አልሸባብ በኢትዮጵያ በተለይም በአዲስ አበባ ሊፈጽም የነበረ...
26/05/2022

አልሸባብ በአዲስ አበባ ሊፈጽም የነበረው የሽብር ተግባር መክሸፉን ፖሊስ አስታወቀ
አዲስ አበባ፣ ግንቦት 18፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) አልሸባብ በኢትዮጵያ በተለይም በአዲስ አበባ ሊፈጽም የነበረው የሽብር ተግባር መክሸፉን ፖሊስ አስታወቀ፡፡
የፌደራል ፖሊስ እና የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን በጋራ ባካሄዱት ዘመቻ ነው የሽብር ቡድኑን ተግባር ማክሸፍ የተቻለው።
ጉዳዩን አስመልክቶ በጋራ በሰጡት መግለጫም ሸኔን ጨምሮ የህወሓት ተላላኪዎች በመዲናዋ የሽብር ተግባር ለመፈጸም ሲንቀሳቀሱ የነበሩ እና በሙስና እና በሕገ ወጥ ተግባራት ላይ የተሰማሩ ከ340 በላይ ተጠርጣሪዎች በቁጥጥር ስር ውለው ምርመራ እየተደረገባቸው መሆኑን የፌዴራል እና የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን የወንጀል ምርመራ የሥራ ኃላፊዎች አብራርተዋል።

Abay Tube
የዩቲዩብ ቻናል
•YouTube: - https://www.youtube.com/channel/UCvOuOX2nVqsK_gX-J0fcvsw
•Facebook: - https://www.facebook.com/AbayOnYoutube/
•Instagram: - https://www.instagram.com/abayentertainment
•Telegram: - https://t.me/AbayonYouTube
ስብስክራይብ ማድረጉዏን እንዳይረሱ ስለጉበኙን እናመሰግናለን።

21/03/2022

ʺውበቷን ማሳየት ጀመረች፣ የደበቀችውን ገለጠች"

የወተት ማለቢያ ግሬራው፣ የነጭ ጤፍ ማስቀመጫ ጎተራው፣ የሽንበራ ጎታው፣ የእንቦሶች መፈንጫ ሜዳው ውል ይላል፡፡ ግሬራውና ካቦው ክረምት ከበጋ ወተት አይታጣበትም፣ የሽንበራው ጎታ፣ የጤፉ ጎተራ አይጎድልም፣ ነጭና ሰርገኛ፣ ቀይና ሙሬ ጤፍ የሚታፈስበት፣ ማርና ወተት የማይታጣበት፣ ጮማ የሚቆረጥበት፣ ጠጅና ጠላ የሚወርድበት ያ ምድር ትዝ ይላል፡፡

ክረምት ከበጋ አረንጓዴ ካባ የሚለብሰው፣ ምድሩ እንደ መዳፍ የሚለሰልሰው፣ ንቦች የሚወዱት፣ ሳያቋርጡ ማር የሚሰጡበት፣ እንቦሶች የሚሮጡበት፣ እረኞች በደስታ የሚቦርቁበት ያ ሥፍራ ውል ይላል፡፡ ጀግኖች ይፈጠሩበታል፣ ጀግንነትም ይሰሩበታል፣ በጀግና ሕዝብና በመልካም ቦታ ጀግና ይዳብርበታል፣ ጥጃ ያድግበታልና፣ ወይፈን በሬ ይሆንበታል፣ በሬው ይዳብርበታል፡፡

በጥበብ የተሸበበው፣ በጥበብ የቆመው፣ ጥበባትን ያቀፈው፣ የገዳማትና የአድባራት መገኛ፣ የመነኮሳትና መነኮሳይት መማጸኛ ታላቁ ጣና በማዕበል እየተወዛዋዘ ለዚያ ምድር ግርማ ሰጥቶታል፡፡ በሚታዩትና በማይታዩት፣ በሚደረስባቸውና በማይደረስባቸው ገዳማት ውስጥ ያሉት መነኮሳት ሳያቋርጡ ለምድር ይጸልያሉ፡፡ ምድር መከራው እንዳይበዛባት፣ ደስታና ሰላም እንዲበዛላት፣ ክፉ ነገር ሁሉ እንዳይቀርባት፣ ሳቅ እንጂ እንባ እንዳይበዛባት ሳያቋርጡ በጸሎት ይጣደፋሉ፡፡ ለምድርም በረከት ያሰጣሉ፡፡

በበረከት ከተመላው፣ እልፍ አዕላፍ ምስጢራትን ከታቀፈው ጣና አጠገብ ያለው ሜዳማው ምድርም በዚያ በረከት የሚኖር ይመስላል፡፡ መልካም ነገር አይታጠበትምና፡፡ ላሞች ወተት ይሰጣሉ፣ ንቦች ማር ይሠራሉ፡፡ የሀገሬው ሰው ከላሙ ወተት ከበሬው እሸት አያጣም፡፡ መሶቡ ሰፊ ነው፣ ጎተራው ሙሉ ነው፡፡

ʺነጭ ጤፍ እንጀራ ማር ቅቤው ወተት፣
ሀገራችን ጎንደር ደንቢያና ሰቀልት " የተባለለት መልካሙ የደንቢያ ምድር ታይቶ አይጠገብም፣ እኒያ የደንቢያ ጀግኖች ከላሞቻቸው ወተት፣ ከበሬዎቻቸው እሸት እንደማያጡት ሁሉ በወገባቸው ዝናር ሙሉ ጥይት አይለቁም፡፡ ምንሽር፣ ጓንዴና አብራረው፣ በልጅግና ክላሽ ይዘው ሀገር ስትጠራ፣ ክፉ ቀን ሲመጣ አልመው ይተኩሳሉ፣ መሽገው ጠላት ይደመስሳሉ፣ በደምና በአጥንት ሀገር ያጸናሉ፡፡

እኒያ የጎንደር ነገሥታት በማለዳ ከቤተ መንግሥታቸው ሰገነት ላይ ተቀምጠው መልካሙን የደንቢያን ምድር በአሻገር እየተመለከቱ መንፈሳቸውን የሚያድሱ፣ በአዲስ ቀን ለአዲስ ሥራ የሚነሱ ይመስላል፡፡ ቤተ መንግሥታቸው መልካሙን ምድር በአሻገር ለማየት የተመቸ ነው፡፡ ያ የጀግኖች ሀገር ለነብስም ለስጋም የሚሆን አያሌ ነገር ታቅፏል፡፡ ለሥጋ ማርና ወተቱ፣ ጮማና እሸቱ፣ ለነብስ ገዳምና አድባራቱ የተመቸ ነው፡፡ በዚያ ምድር ከደረሱ በኋላ እየመረጡ የሚበጀውን ማድረግ ነው፡፡ ነብሱን የፈለገ ወደ ገዳማቱ፣ ስጋውን ያስቀደመም ወደ ማርና ወተቱ ይጠጋል፡፡ ሁሉም ሙሉ ነውና፡፡

በዚያ ምድር ከጣና ጋር የተወዳጀች፣ ቀደም ብላ የተመሰረተች ከተማ ትገኛለች፡፡ ይህች ከተማ እንደ እድሜዋ ሳትሰፋ፣ እንደ መረሳቷ ደግሞ ሳትጠፋ ዘመናትን አሳልፋለች፡፡ ይህች የቀደመ የእሳር ልብሷን ከማታወልቀው፣ የማይመስላትን ከማታጠልቀው፣ በታሪክ ከፍ ብላ ከምትታወቀው ደብረ ሲና ማርያም ጋር የጠበቀ ቁርኝት እንዳላት የሚነገርላት ከተማ በጣና ሐይቅ እየታጀበች፣ በአእዋፋት ዝማሬ እየተመሰጠች፣ በሊቃውንት ዜማ ጭንቁን እየረሳች፣ መልካሙን እያሰበች፣ በደስታ እየተዋጠች ዘመናትን ተሻግራለች፡፡ ጎርጎራ ድንቋ ሥፍራ፡፡

የኢጣሊያ ወራሪ ሠራዊት በኢትዮጵያ በቆየበት በዚያ ዘመን ጎርጎራን ይወዳት ነበር ይባላል፡፡ ከኢት

ወልቃይት በአማራ ክልል ስር በብልፅግና ማዕከላዊ ኮሚቴ ተወከለችብልፅግና ፓርቲ ባደረገው ጉባኤ ወልቃይት ጠገዴ ሰቲት ሁመራ ዞን አስተዳዳሪ በአማራ ክልል ስር የማዕከላዊ ኮሚቴ አባል ሆነው ተ...
14/03/2022

ወልቃይት በአማራ ክልል ስር በብልፅግና ማዕከላዊ ኮሚቴ ተወከለች

ብልፅግና ፓርቲ ባደረገው ጉባኤ ወልቃይት ጠገዴ ሰቲት ሁመራ ዞን አስተዳዳሪ በአማራ ክልል ስር የማዕከላዊ ኮሚቴ አባል ሆነው ተመርጠዋል። የትግራይ ብልፅግና በእነ ዶ/ር አብርሃም በላይ ጨምሮ የማዕከላዊ ኮሚቴ አባል ያስመረጠ ሲሆን ወልቃይት ጠገዴ ሰቲት ሁመራ የተወከለው በአማራ ብልፅግና ስር ነው። የወልቃይት ጠገዴ ሰቲት ሁመራ አስተዳዳሪ አቶ አሸተ ደምለው የአማራ ብልፅግና አባል ሲሆኑ ትናንት በተደረገው የብልፅግና ጉባኤ ወልቃይት ጠገዴ ሰቲት ሁመራ ዞንን ወክለው የብልፅግና የማዕከላዊ ኮሚቴ አባል ሆነዋል።

የየክልሎቹ ዞን አመራሮች የብልፅግና ማዕከላዊ ኮሚቴ አባል ሆነው የተመረጡ ሲሆን ለአብነት ያህልም የምዕራብ ጎጃም ዞን አስተዳዳሪ አቶ መልካሙ ተሾመ፣ የምዕራብ ጎንደር ዞን አስተዳደር አቶ ደሳለኝ ጣሰው፣ የደቡብ ወሎ ዞን አስተዳደሪ ዶ/ር አብዱ ሁሴንና ሌሎች የዞን አስተዳዳሪዎች የብልፅግና ማዕከላዊ ኮሚቴ አባል እንደሆኑት አቶ አሸተ ደምለው የአማራ ክልል አንድ ዞን የሆነው ወልቃይት ጠገዴ ሰቲት ሁመራን ወክለው በአማራ ክልል ኮታ የብልፅግና ማዕከላዊ ኮሚቴ ሆነው ተመርጠዋል።

12/03/2022

ብልጽግና ፓርቲ አቶ አደም ፋራህ እና አቶ ደመቀ መኮንን ምክትል ፕሬዚዳንቶች አድርጎ መረጠ
ብልጽግና ፓርቲ እያካሄደ ባለው አንደኛ ጉባኤ የፓርቲውን ምክትል ፕሬዚዳንቶች መርጧል።

በዚህ መሰረት አቶ አደም ፋራህን እና አቶ ደመቀ መኮንን ምክትል ፕሬዚዳንት አድርጎ መርጧል።
ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡

ፌስቡክ፡-https://www.facebook.com/AbayOnYoutube/
ዩትዩብ፦https://www.youtube.com/channel/UCvOuOX2nVqsK_gX-J0fcvsw
ቴሌግራም፦ https://t.me/AbayonYouTube/UCvOuOX2nVqsK_gX-J0fcvsw
ቴሌግራም፦ https://t.me/AbayonYouTube

ABAY Tube is a fully integrated audio, video and art. We also put on concerts around the world and mange talented artists who share passion for music and art.

የዜጎችን ሰላምና ደህንነት ለማስጠበቅ ከምንም ጊዜ በላይ አበክሮ እንደሚሰራ የብልጽግና ፓርቲ አስታወቀአዲስ አበባ፣ መጋቢት 3፣ 2014 (ኤፍ ቢሲ) የዜጎችን ሰላም እና ደህንነት ለማስጠበቅ ...
12/03/2022

የዜጎችን ሰላምና ደህንነት ለማስጠበቅ ከምንም ጊዜ በላይ አበክሮ እንደሚሰራ የብልጽግና ፓርቲ አስታወቀ

አዲስ አበባ፣ መጋቢት 3፣ 2014 (ኤፍ ቢሲ) የዜጎችን ሰላም እና ደህንነት ለማስጠበቅ ከምንም ጊዜ በላይ አበክሮ እንደሚሰራ የብልጽግና ፓርቲ አስታወቀ።

ፓርቲው አንደኛውን ድርጅቲዊ ጉባኤው እያካሄደ ይገኛል።

የጉባኤውን ሁለተኛ ቀን ውሎ አስመልክቶ የብልጽግና ፓርቲ የህዝብ እና ዓለም አቀፍ ግንኙነት ዘርፍ ሀላፊ ዶክተር ቢቂላ ሁሪሳ መግለጫ ሰጥተዋል።

የብልጽግና ፓርቲ አመራሮች፣ አባላት እና ደጋፊዎች የዜጎችን ሰላም እና ደህንነት ማስጠበቅ ቅድሚያ የሚሰጡት ስራ እንደሆነ በጉባኤው ከስምምነት መደረሱን አስታውቀዋል።

ፓርቲው ከሰላም የሚያስቀድመው ነገር አለመኖሩን ነው የተመለከተው።

የፓርቲውን አደረጃጀት፣ አመራር እና አባላት አስተሳሰብ በሚገባ በመግራት ሰላምን ማስጠበቅ የብልጽግና ፓርቲ ትልቁ ፕሮጀክት ነውም ብለዋል።

አሁን የሚፈጠረው የብልጽግና አመራር የሀገሪቱን የፖለቲካ፣ የኢኮኖሚ ፣ የደህንነት እና ማህበራዊ ችግሮች መፍታት 24 ሰዓት የሚሠራው ስራ እንደሆነም በጉባኤው ከስምምነት ተደርሷል ብለዋል ።

የትግራይ ህዝብን በተመለከተም ጉባኤው የመከረ ሲሆን፥ በአሸባሪው ህወሓት ድርጊት ሳቢያ ህዝቡ ለችግር መዳረጉን አንስቷል ።

ብልጽግና ፓርቲ በትግራይ ህዝብ ላይ የሚደርሰውን ሰቆቃ ለማስቀረትና እፎይ ብሎ እንዲኖር ለማስቻል አሉ የተባሉ የሰላም አማራጮችን በሙሉ እንደሚጠቀም አስታውቀዋል።

ጉባኤው ድርቅ በተደጋጋሚ በሚከሰትባቸው ቆላማ የሀገሪቱ አካባቢዎች የዜጎችን ችግር በዘላቂነት የሚፈታ ስራ መሰራት እንደሚገባም ተመልክቷል።

የፓርቲው ጉባኤ አምስት አጀንዳዎች እንዳሉትም ዶክተር ቢቂላ ገልጸዋል።

እስካሁንም ከአጀንዳዎቹ መካከል የፓርቲውን ማዕከላዊ ኮሚቴ ሪፖርት እና የፓርቲውን የኢንስፔክሽን ዕና ስነ ምግባር ሪፖርት አድምጦ አጽድቋል ።

👇👇👇👇
https://www.youtube.com/channel/UCvOuOX2nVqsK_gX-J0fcvsw

Abay Tube is a fully integrated audio, video and art. We also put on concerts around the world and mange talented artists who share passion for music and ar...

10/03/2022

ብልጽግና ፓርቲ ነገ በሚጀምረው ጉባኤው የኢትዮጵያውያንን ሁለንተናዊ ብልጽግና የሚያረጋግጡ ውሳኔዎች እንደሚተላለፉ አስታወቀ

አዲስ አበባ፣መጋቢት 1፣2014 (ኤፍ ቢ ሲ) ብልጽግና ፓርቲ ነገ በሚጀምረው ጉባኤ የኢትዮጵያውያንን ሁለንተናዊ ብልጽግና የሚያረጋግጡ ውሳኔዎች ይተላለፍበታል አለ።

ጉባኤውን አስመልክቶ የፓርቲው የህዝብና ዓለም አቀፍ ግኑኝነት ዘርፍ ሀላፊ ዶክተር ቢቂላ ሁሪሳ መግለጫ ሰጥተዋል።

ዶክተር ቢቂላ የብልጽግና አንደኛ ጉባኤ ባለፉት ሶስት አመታት ፓርቲው በሁሉም መስክ የተጎናጸፋቸውን ድሎች ይገመግማል ብለዋል።

የገጠሙትን ችግሮች እና ተግዳሮቶች በጥልቀት ገምግሞ ለማረም ታሪካዊ ውሳኔ ያሳልፋልም ብለዋል ።

ጉባኤው በጸጥታ ሁኔታ፣ በኢኮኖሚ እንዲሁም በሀገረ መንግስት ግንባታ ላይ ሰፊ ትኩረት ሰጥቶ እንደሚመክርም ገልጸዋል ።

በዚህም ለዜጎች ሁለንተናዊ ብልጽግና የሚያመጡ ውሳኔዎች ይተላለፋሉ ነው ያሉት።

የብልጽግና ፓርቲ አንደኛ ጉባኤ ነገ ከቀኑ ስምንት ሰዓት ይጀምራል ።

በጉባኤው 1 ሺህ 600 የፓርቲው አባላት በድምፅ የሚሳተፉ ሲሆን፥ 400 ከተለያየ የህብረተሰብ ክፍሎች እና ከውጭ ሀገራት የተጋበዙ እንግዶች ያለ ድምፅ ይሳተፋሉ ።

ጉባኤው የፓርቲው አመራሮች፣ አባላት እና ደጋፊዎች የአስተሳሰብ እና የተግባር አንድነት የሚጎናጸፉበት፣ ፓርቲው በአደረጃጀት እና አሰራር ራሱን የሚያጠናክርበት እንዲሁም ፓርቲውን ሊያሻግሩ እና የኢትዮጵያን ሁለንተናዊ ብልጽግና ሊያረጋግጡ የሚችሉ ጠንካራ የፓርቲ አመራሮች የሚመረጡበትም ይሆናል ብለዋል.

ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ፌስቡክ፡-https://www.facebook.com/AbayOnYoutube/
ዩትዩብ፦https://www.youtube.com/channel/UCvOuOX2nVqsK_gX-J0fcvsw
ቴሌግራም፦ https://t.me/AbayonYouTube

ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!

ABAY Tube is a fully integrated audio, video and art. We also put on concerts around the world and mange talented artists who share passion for music and art.

ከፍተኛ ገንዘብ የዘረፉ አማራ ብልፅግና ከፍተኛ አመራሮች ስም ዝርዝርና የገንዘብ መጠን ይፋ ሆነ የአማራ ብልፅግና ከፍተኛ አመራሮች በርካታ ሚሊዮን ብሮችን ለግላቸው ጥቅም ለማዋል ዘርፈዋል። ...
04/03/2022

ከፍተኛ ገንዘብ የዘረፉ አማራ ብልፅግና ከፍተኛ አመራሮች ስም ዝርዝርና የገንዘብ መጠን ይፋ ሆነ የአማራ ብልፅግና ከፍተኛ አመራሮች በርካታ ሚሊዮን ብሮችን ለግላቸው ጥቅም ለማዋል ዘርፈዋል። ፓርቲው ዛሬ ዘረፋውን የፈፀሙ ሰዎች ከእነ ወለዱ እንዲመለሱ ከመወሰኑም በላይ በርካቶቹ ከስራቸውና ከሀላፊነታቸው እንዲታገዱ ወስኗል።

የክልሉ ፕሬዚዳንት የነበሩት አቶ አገኘሁ ተሻገርን ጨምሮ ከፍተኛ ገንዘብ ዘርፈዋህ ተብሎ ሲወራ የነበረ ቢሆንም አቶ አገኘሁ ተሻገርና የክልሉ የብልፅግና ፓርቲ ሀላፊ የነበሩት አቶ አብርሃም አለኸኝ ከዘራፊዎቹ ውጭ ናቸው ተብሏል።

ዘራፊዎቹ የፓርቲው የተለያዩ የስራ ዘርፍ ሀላፊዎች ሲሆኑ የወርደ መወዛቸው ከ5,000 እስከ 16,9988 ብር ነው ተብሏል።

1. ባህሩ ፈጠነ 8.9 ሚሊዮን የፋይናስ ሀላፊ

2. ጌትነት አይቸው 8.4 ሚሊዮን የፋይናንስና የሰው ሀይል ሀላፊ

3. ጉሹ እንዳለማው 5 ሚሊዮን የፖለቲካ ዘርፍ ሀለፊ

4. ጥላሁን ወርቅነህ 3.9 ሚሊዮን ም/ፖለቲካ ዘርፍ

5. ፍሰሀ ደሳለኝ 3.8 የአደረጃጀት ሀላፊ

6. ደሳለኝ በለይ 3 ሚሊዮን አደረጃጀት ሀላፊ የነበረ

7. አማኑኤል ፈቀደ 3.6 ሚሊዮን የአደረጃጀት ምክትል

8.አቶ ጋሸ ሻው ተቀባ 1.8 ሚሊዮን ወጣት ሊግ ሀላፊ

9. በላቸው ብርሀኑ 1.8 ሚሊዮን

10. ፍቃዱ ዳምጤ 1.5 ሚሊዮን ኦዲት ሀላፊ

11. አዲሴ በጋለ 1.2 ሚሊዮን የሰው ሀይል ሀላፊ

12. እየሩስ አበበ 1.1 ሚሊዮን ንብረት ክፍል

13. መሠረት መለሰ 370 ሺህ ተላላኪ

14. ዘነቡ ጋንፈር 550 ሺህ ገንዘብ ያዥ

15 ስራነሽ ዩኋንስ 500 ሽህ ገንዘብ ያዥ
https://www.facebook.com/109915567592273/posts/439527991297694/?app=fbl

የአማራ ብልፅግና ፓርቲ በብድር ስም የወጣው የፓርቲው ገንዘብ ያለምንም ቅድመ ሁኔታ ከነ ወለዱ ታስቦ ተመላሽ እንዲደረግ ወሰነ

የአማራ ብልፅግና ፓርቲ በብድር ስም የወጣው የፓርቲው ገንዘብ ያለምንም ቅድመ ሁኔታ ከነ ወለዱ ታስቦ ተመላሽ እንዲደረግና ዝርዝር ሁኔታው ተጣርቶ የመጨረሻ ውሳኔ እስከሚሰጥ ድረስ በብድር ስም ገንዘብ የወሰዱ አመራርና ሰራተኞችም ከያዙት የመንግስትና የፓርቲ ኃላፊነት ከየካቲት 25/2014 ዓ.ም ጀምሮ እንዲነሱ መወሰኑን አስታወቀ።

ከጉዳዩ ጋር በተያያዘ ፓርቲው መግለጫ አውጥቷል።

ሙሉ መግለጫው እንደሚከተለው ቀርቧል፡-

ከአማራ ብልጽግና ፓርቲ ጽ/ቤት ለአመራርና ሰራተኞች ሲሰጥ የነበረን የገንዘብ ብድር በተመለከተ የተሰጠ መግለጫ፤

የአማራ ብልጽግና ፓርቲ ጽ/ቤት ወቅታዊ ሁኔታውን ከግምት ውስጥ ባስገባ መልኩ በየደረጃው ያለው አመራር የአስተሳሰብና የተግባር አንድነት በመፍጠር ለዋናው ዓላማችን ስኬት ማለትም ለክልላችንና በአጠቃለይም ለሀገራችን ብልጽግና ተግቶ እየሰራ ይገኛል፡፡

ባለፉት ሦስት ዓመታት ከፍተኛ ትኩረት ሰጥተን ከሰራንባቸውና ጉልህ ስኬት ካስመዘገብንባቸው ጉዳዮች አንዱ ብቁ አመራርና የፓርቲ መዋቅር ለመገንባት የሰራነው ተግባር ነው፡፡

የአማራ ብልጽግና ፓርቲ ጽ/ቤት በቀጣይነትም የውስጠ ድርጅት ዴሞክራሲውን በማጠናከር የፓርቲያችን አስተሳሰብ፣ አደረጃጃቱንና በአጠቃላይም አባላቱን ለማብቃት እየሰራ ይገኛል፡፡

በተጨማሪም ፓርቲያችን የአመራሩንና የአባላቱን ዕውቀት፣ ክህሎት፣ ጥበብና አቅም በተከታታይነት ለማብቃት ጥረት ከማድረጉም በላይ መታረም የሚገባቸውን የተቋም፣ የአመራርና የአባላት ጉድለቶች ጊዜ ሳይሰጣቸው እንዲታረሙ የማድረግ ስራ እየሰራ ይገኛል፡፡

ይህን የውስጠ ድርጅት ዴሞክራሲ የማጠናከር ስራ የምንሰራው ፓርቲያችን የተፈጠረው ሁሉን አቀፍ ሀገራዊ ብልጽግናን እውን ለማድረግ በመሆኑና የትኛውም ዓይነት መታረም ያለበት ተግባር በወቅቱ ካልታረመ የብልጽግና ጉዟችንን ያደናቅፋል የሚል ዕምነት ስላለን ነው፡፡

ከውስጠ ድርጅት ዴሞክራሲ ማጠናከር ስራችን አንዱ የፓርቲውን አሰራርና መመሪያ ማጠናከርና ሳይሸራረፍ ተፈፃሚ ማድረግ ነው፡፡

በመሆኑም በአማራ ብልጽግና ፓርቲ ጽ/ቤት የፓርቲው ሃብት የሆነ ተቀማጭ ገንዘብ ለአመራሮችና ሰራተኞች የረጅም ጊዜ ብድር አሰራር ስርዓት በመዘርጋት ከፋይናንስ ተቋማት ጋር በመዋዋል ሲከናወን መቆየቱ ይታወቃል፡፡ ሆኖም ይኸው አሰራር ከፓርቲ የገንዘብና ሃብት አስተዳደር ስርዓት አኳያ ህገ ደንቡን የሚጣረስ ሆኖ ተገኝቷል፡፡

የውሳኔ አሰጣጥና የስራው አፈፃፀም ከፓርቲው ህገ ደንብና አሰራር ጋር የሚቃረን መሆኑም ተረጋግጧል፡፡

በመሆኑም በብድር ስም የወጣው የፓርቲው ገንዘብ ያለምንም ቅድመ ሁኔታ ከነ ወለዱ ታስቦ ተመላሽ እንዲደረግና ዝርዝር ሁኔታው ተጣርቶ የመጨረሻ ውሳኔ እስከሚሰጥ ድረስ በብድር ስም ገንዘብ የወሰዱ አመራርና ሰራተኞችም ከያዙት የመንግስትና የፓርቲ ኃላፊነት ከየካቲት 25/2014 ዓ.ም ጀምሮ እንዲነሱ ተደርጓል፡፡

ሆኖም ለአሰራሩ ተገዥ በመሆን ተፈፃሚ የማያደርጉ ግለሰቦች ካጋጠሙ በህጉ መሰረት ተጠያቂነታቸው የሚከናወን ይሆናል፡፡

ይህ የማጣራትና የውሳኔ አሰጣጥ ሂደት በፓርቲው ህገ ደንብና አሰራር መሰረት በኦዲት ቁጥጥርና ኢንስፔክሽን ኮሚሽን መርማሪነት የውሳኔ ሃሳብ አቅራቢነት ተመስርቶ የክልሉ አስተባባሪ ኮሚቴ መርምሮ ውሳኔ የሰጠበት ሲሆን ዝርዝር ሁኔታው በፓርቲው የውስጥ አሰራር መሰረት ለመላ የፓርቲው አባላትና አመራሮች በተዋረድ በግልጽ ይፋ የሚደረግ ይሆናል፡፡

የአማራ ብልጽግና ፓርቲ ጽ/ቤት
የካቲት 25/2014

https://t.me/Amharatoday2
04/03/2022

https://t.me/Amharatoday2

ሰለዐማራ ሁሉናዊ ጉዳዮች ታሪክ ግዛት ስነልቦና ባህልና ማንነት እንዲሁም ማህበራዊ ኢኮኖሚያዊ ፖለቲካዊና ወቅታዊ ጉዳዮችም ይዳሰሱበታል።

የአማራ ብልፅግና ፓርቲ  በብድር ስም የወጣው የፓርቲው ገንዘብ ያለምንም ቅድመ ሁኔታ ከነ ወለዱ ታስቦ ተመላሽ እንዲደረግ ወሰነየአማራ ብልፅግና ፓርቲ  በብድር ስም የወጣው የፓርቲው ገንዘብ ...
04/03/2022

የአማራ ብልፅግና ፓርቲ በብድር ስም የወጣው የፓርቲው ገንዘብ ያለምንም ቅድመ ሁኔታ ከነ ወለዱ ታስቦ ተመላሽ እንዲደረግ ወሰነ

የአማራ ብልፅግና ፓርቲ በብድር ስም የወጣው የፓርቲው ገንዘብ ያለምንም ቅድመ ሁኔታ ከነ ወለዱ ታስቦ ተመላሽ እንዲደረግና ዝርዝር ሁኔታው ተጣርቶ የመጨረሻ ውሳኔ እስከሚሰጥ ድረስ በብድር ስም ገንዘብ የወሰዱ አመራርና ሰራተኞችም ከያዙት የመንግስትና የፓርቲ ኃላፊነት ከየካቲት 25/2014 ዓ.ም ጀምሮ እንዲነሱ መወሰኑን አስታወቀ።

ከጉዳዩ ጋር በተያያዘ ፓርቲው መግለጫ አውጥቷል።

ሙሉ መግለጫው እንደሚከተለው ቀርቧል፡-

ከአማራ ብልጽግና ፓርቲ ጽ/ቤት ለአመራርና ሰራተኞች ሲሰጥ የነበረን የገንዘብ ብድር በተመለከተ የተሰጠ መግለጫ፤

የአማራ ብልጽግና ፓርቲ ጽ/ቤት ወቅታዊ ሁኔታውን ከግምት ውስጥ ባስገባ መልኩ በየደረጃው ያለው አመራር የአስተሳሰብና የተግባር አንድነት በመፍጠር ለዋናው ዓላማችን ስኬት ማለትም ለክልላችንና በአጠቃለይም ለሀገራችን ብልጽግና ተግቶ እየሰራ ይገኛል፡፡

ባለፉት ሦስት ዓመታት ከፍተኛ ትኩረት ሰጥተን ከሰራንባቸውና ጉልህ ስኬት ካስመዘገብንባቸው ጉዳዮች አንዱ ብቁ አመራርና የፓርቲ መዋቅር ለመገንባት የሰራነው ተግባር ነው፡፡

የአማራ ብልጽግና ፓርቲ ጽ/ቤት በቀጣይነትም የውስጠ ድርጅት ዴሞክራሲውን በማጠናከር የፓርቲያችን አስተሳሰብ፣ አደረጃጃቱንና በአጠቃላይም አባላቱን ለማብቃት እየሰራ ይገኛል፡፡

በተጨማሪም ፓርቲያችን የአመራሩንና የአባላቱን ዕውቀት፣ ክህሎት፣ ጥበብና አቅም በተከታታይነት ለማብቃት ጥረት ከማድረጉም በላይ መታረም የሚገባቸውን የተቋም፣ የአመራርና የአባላት ጉድለቶች ጊዜ ሳይሰጣቸው እንዲታረሙ የማድረግ ስራ እየሰራ ይገኛል፡፡

ይህን የውስጠ ድርጅት ዴሞክራሲ የማጠናከር ስራ የምንሰራው ፓርቲያችን የተፈጠረው ሁሉን አቀፍ ሀገራዊ ብልጽግናን እውን ለማድረግ በመሆኑና የትኛውም ዓይነት መታረም ያለበት ተግባር በወቅቱ ካልታረመ የብልጽግና ጉዟችንን ያደናቅፋል የሚል ዕምነት ስላለን ነው፡፡

ከውስጠ ድርጅት ዴሞክራሲ ማጠናከር ስራችን አንዱ የፓርቲውን አሰራርና መመሪያ ማጠናከርና ሳይሸራረፍ ተፈፃሚ ማድረግ ነው፡፡

በመሆኑም በአማራ ብልጽግና ፓርቲ ጽ/ቤት የፓርቲው ሃብት የሆነ ተቀማጭ ገንዘብ ለአመራሮችና ሰራተኞች የረጅም ጊዜ ብድር አሰራር ስርዓት በመዘርጋት ከፋይናንስ ተቋማት ጋር በመዋዋል ሲከናወን መቆየቱ ይታወቃል፡፡ ሆኖም ይኸው አሰራር ከፓርቲ የገንዘብና ሃብት አስተዳደር ስርዓት አኳያ ህገ ደንቡን የሚጣረስ ሆኖ ተገኝቷል፡፡

የውሳኔ አሰጣጥና የስራው አፈፃፀም ከፓርቲው ህገ ደንብና አሰራር ጋር የሚቃረን መሆኑም ተረጋግጧል፡፡

በመሆኑም በብድር ስም የወጣው የፓርቲው ገንዘብ ያለምንም ቅድመ ሁኔታ ከነ ወለዱ ታስቦ ተመላሽ እንዲደረግና ዝርዝር ሁኔታው ተጣርቶ የመጨረሻ ውሳኔ እስከሚሰጥ ድረስ በብድር ስም ገንዘብ የወሰዱ አመራርና ሰራተኞችም ከያዙት የመንግስትና የፓርቲ ኃላፊነት ከየካቲት 25/2014 ዓ.ም ጀምሮ እንዲነሱ ተደርጓል፡፡

ሆኖም ለአሰራሩ ተገዥ በመሆን ተፈፃሚ የማያደርጉ ግለሰቦች ካጋጠሙ በህጉ መሰረት ተጠያቂነታቸው የሚከናወን ይሆናል፡፡

ይህ የማጣራትና የውሳኔ አሰጣጥ ሂደት በፓርቲው ህገ ደንብና አሰራር መሰረት በኦዲት ቁጥጥርና ኢንስፔክሽን ኮሚሽን መርማሪነት የውሳኔ ሃሳብ አቅራቢነት ተመስርቶ የክልሉ አስተባባሪ ኮሚቴ መርምሮ ውሳኔ የሰጠበት ሲሆን ዝርዝር ሁኔታው በፓርቲው የውስጥ አሰራር መሰረት ለመላ የፓርቲው አባላትና አመራሮች በተዋረድ በግልጽ ይፋ የሚደረግ ይሆናል፡፡

የአማራ ብልጽግና ፓርቲ ጽ/ቤት
የካቲት 25/2014

Address

Joseph Tito
Addis Ababa
1983

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Amhara Today አማራ ዛሬ posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to Amhara Today አማራ ዛሬ:

Share