AWLO MEDIA አውሎ ሚዲያ

AWLO MEDIA አውሎ ሚዲያ Awlo Media Center PLC. is a legally registered content producer organization in Ethiopia with an onli

Awlo Media Center PLC.is producing and presenting content on this YouTube, its website and other social media accounts (Facebook, twitter, Instagram, telegram and LinkedIn). It envisages to become the top quality content provider among the online platforms in Ethiopia. It practices professional journalism unlike other activism-based online media. It also aspires to take its best programs to TV & R

adio channels and own a magazine. Awlo's contents ranges from news and current affairs, serious national programs to entertainment. It maintains diversity of ideas, professional integrity and production quality.

ከአውሎ ሚዲያ የተሰጠ መግለጫየተከበራችሁ የአውሎ ሚዲያ ተከታታዮች:-  ድርጅታችን አውሎ ሚዲያ ሴንተር ባለፉት ሶስት አመታት  በበይነ መረብ የሚዲያ ዘርፍ ላይ  በመሰማራት  በርካታ የሚዲያ ...
28/10/2021

ከአውሎ ሚዲያ የተሰጠ መግለጫ

የተከበራችሁ የአውሎ ሚዲያ ተከታታዮች:- ድርጅታችን አውሎ ሚዲያ ሴንተር ባለፉት ሶስት አመታት በበይነ መረብ የሚዲያ ዘርፍ ላይ በመሰማራት በርካታ የሚዲያ ተግባራትን ሲያከናውን ቆይቷል፡፡ በተለይ ሀገራችን ኢትዮጵያ የገጠሟትን ውስብስብና ሁለንተናዊ ችግሮች ለመፍታት በሚደረገው ጥረት ውስጥ ገንቢ ሚና በመያዝ በተለይም የተራራቁ ፅንፍ ሃሳቦችን በማቀራረብና ብሎም እኩል ድምፅ በመስጠት በዘርፉ የሚፈጠሩ ወገንተኛነትና አግላይንት በመስበር በርካታ ስራዎችን ለአድማጭ ተመልካች ሲያደርስ ቆይቷል፡፡

ድርጅታችን እነዚህን ተግባራት ሲያከናውን ግልፅና ህጋዊ አሰራርን በመተግበር ነው፡፡ ለዚህም ግልፅ የሆነ የኤዲቶሪያል አሰራርን በመተግበር፤ ግልፅ የሆነ የፋይናስ አስራርን በመከትል ፤ ከመንግስት የንግድ ፈቃድ ፡የፕሮዳክሽን ፈቃድ እና የበይነ መረብ ፈቃድ በመውሰድ ነው፡፡

ድርጅታችን ከጊዜ ወደ ጊዜ የሚያቀርባቸውን ስራዎች ጥራትና ሙያዊ ደረጃ እያሻሻለ በሀገር ውስጥና በመላው ዓለም በርካታ ተመልካቾችን በማፍራት ተወዳጅነቱን ከፍ አድሮጎ ነበር፡፡ በተለይም የህዝቦችን አብሮ መኖር ፤እርቅና ስምምነትን ፤ ሰላማዊ ውይይትና ድርድርን ፤ የፍትህ መጓደልን ፤ የፖለቲካ ምህዳሩን በተመለከተ እንዲሁም ሃገራችን ብሄራዊ ጥቅምና እድገት የሚያስረዱ የሚተነትኑ ዝግጅቶቻችን የብዙዎችን ቀለብ የሳቡ ነበሩ፡፡

ነገር ግን ባለፈው ሰኔ 23/2013 ዓ.ም መንግስት የፌዴራል ፖሊሲን በመላክ በርካታ የድርጅቱን ንብረቶች ከመውሰዱም በላይ የስራ ቦታውን ሙሉ በሙሉ በማሸግ ፤ የድርጅቱን ሰራተኞች ኢ ፍትሃዊ በመሆነ መንገድ አፋር ክልል አዋሽ ሰባት የፈዴራል ፖሊስ ተቋም ውስጥ በማሰርና በማፈን ከፍተኛ ግፍ ፈፅሞባቸዋል፡፡

የሰብአዊ መብት ተቋማት ባደረጉት ጥረት ወደ ፍርድ ቤት ቀርበው ፍርድ ቤቱም እንዲለቀቁ በመወሰኑ ከበርካታ እንግልትና ስቃይ በኋላ ተለቀዋል፡፡ የፍትሕ ተቋማቱ የድርጅቱን ሰራተኞች እንዲለቀቁን ብሎም የድርጅቱም ሆነ የሰራተኞቹ የግል ንብረት እንዲመለስና ፖሊስ ያሸገው የድርጅቱ ቢሮ እንዲከፈት ቢወስኑም እስካሁን ድርስ ከፌዴራል ፖሊስ ይህ ነው የሚባል ህጋዊ መልስና ተግባር ሊገኝ አልቻለም፡፡

አውሎ ሚዲያ ያሉትን ሰራተኞች ህጋዊ ቅጥራቸውን በማስቀጠል እስከ ዛሬ ድረስ ከመንግስት ተቋማት መፍትሄ እየጠየቀ የቆየ ቢሆንም ሁሉም የመንግስት ተቋማት ማለትም የፌዴራል ፖሊስ ፤ የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙሃን ባለስልጣን እና የሚመለከታቸው ተቋማትና ሃላፊዎች እጅግ በሚያሳዝን ሁኔታ ይህ ነው የሚባል ህጋው መፍትሄም ሆነ እርምጃ ሊሰጡን አልቻሉም፡፡

ስለሆነም ድርጅቱ በመንግስት በተፈጠረ ችግር ምክንያት ሰራተኞችን ሙሉ በሙሉ አሰናበቷል ፡፡ የተከበራችሁ የድርጅታችን ሰራተኞች በነበሩን እጅግ ፈተና የበዛባቸው የስራ ጊዚያት ሙያችሁ የሚፈቅደውን መብትና ግዴታዎች በማክበር በታማኝነት ድርጂቱን በማገልገላችሁ ኩራት ሊሰማችሁ ይገባል፡፡

የተከበረውን የሚዲያ ዘርፍ ተጠቅማችሁ ለህዝብ ስትሉ ሃቅ በመስራታጭሁና እውነትን በመነፍነፍ ለተበደሉ ዜጎች ድምፅ በመሆናቸሁ በመንግስት ለፈጻመባችሁ በደል ድርጅቱ ከፈተኛ ሃዘን ተስምቶታል፡፡ ውድ ሰራተኞቻችን በተአማኒነት ሀገርና ወገን ለማግልግል የነበራችሁን ቁርጠኝነት እያደነቅን ለነበረን እጅግ ወርቃማ የስራ ጊዚያት ድርጅቱ እያመሰገነ በመንግስት በደረሰባችሁ በደልና ኢ ፍትሃዊ ተግባራት ሁሉ ፍትህ ባለመግኘቱና ወደ ምትወዱት ሙያና ተቋም ባለመመለሳችሁ እናዝናለን፡፡ በቀጣይም በርትታችሁ የምተሰሩበት ተቋምና ስራ እንዲገጥማችሁ እየተመኘን ለነበረን ጊዜ ሁሉ እናመሰግናለን፡፡

ክቡራንና ክቡራት የአውሎ ሚዲያ ተከታታዮችና ቤተሰቦች መንግስት ሆን ብሎና አስቦ ባደረሰብን ኢ ፍትሃዊ በደልና ከአቅም በላይ በሆነ ችግር ምክንያት ሙሉ በሙሉ ወደ ስራችን መመለስ ባለመቻላችን ይቅርታ እየጠየቅን ለነበረን አብሮት እጅግ እናመሰግናለን፡፡

አውሎ ሚዲያ ግልፅ በሆነ መንገድ በመንግስት በተፈፀመበት በደል ለመዝጋት በመገደዱ በትጋት መረጃ በማሰራጨት ሲያገለግሏችሁ የነበሩ ሰራተኞችን ከስራ ገበታቸው ማሰናበቱን እንድትረዱልን እናሳሳባለን፡፡

ድርጅታችን አውሎ ሚዲያ ሴንተር አሁንም ኢ ፍትሃዊ በሆነ መንገድ በመንግስት የተወሰዱብን በርካታ ንብረቶች እንዲመለሱልን ፤ የድርጀታችን ቢሮም እንዲከፈትልን እየጠየቅን ፤ መንግሰት የሚዲያ ምህዳሩን እጅግ ከሚያጠቡና ከሚያቀጨጩ ተግባራት በመቆጠብ በዘርፉ ያሳየውን መጠነኛ ነፃነት ከመጥፋት እንዲታደገው ጥሪ እናቀርባለን፡፡

አውሎ ሚዲያ
ጥቅምት 18/2014 ዓ.ም

ዶ/ር ዐብይ -ጦርነቱን ያቆምነው ተሸንፈን አይደለም  አቶ ጌታቸው ረዳ ወደ ኤርትራና አማራ እንዋጋለን አሉ  ወልቃይት ፣ ጠገዴ ጠለምትና ራያን አንሰጥም - የአማራ ብልፅግና
30/06/2021

ዶ/ር ዐብይ -ጦርነቱን ያቆምነው ተሸንፈን አይደለም
አቶ ጌታቸው ረዳ ወደ ኤርትራና አማራ እንዋጋለን አሉ
ወልቃይት ፣ ጠገዴ ጠለምትና ራያን አንሰጥም - የአማራ ብልፅግና

#አውሎማለዳ #ሰኔ23 #2013ዓም

አቤቱታዎቻው ታይቶ ተቀባይነት ካላቸው ድጋሚ ምርጫ ለማድረግ፤ ተቀባይነት ከሌለው ደግሞ ውጤት የሚገለጽ መሆኑንም ገልጸዋል።አውሎ ሚድያ ሰኔ 23/ 2013 ዓ.ም  ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መ...
30/06/2021

አቤቱታዎቻው ታይቶ ተቀባይነት ካላቸው ድጋሚ ምርጫ ለማድረግ፤ ተቀባይነት ከሌለው ደግሞ ውጤት የሚገለጽ መሆኑንም ገልጸዋል።

አውሎ ሚድያ ሰኔ 23/ 2013 ዓ.ም
ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት
ቴሌግራም፦ https://t.me/awlomedia
ትዊተር፦ https://twitter.com/AwloMedia
ዩትዩብ፦https://www.youtube.com/channel/UCFRuICCV8fHJGa3AbcA3zOA
ድረ ገጽ፦ https://awlomediatv.com
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/awlomedia

ዜና ፓርቲዎች በ160 የምርጫ ክልሎች ላይ ቅሬታ አቅርበዋል- ምርጫ ቦርድ June 30, 2021 0 3 ያጋሩ Facebook Twitter Google+ Pinterest WhatsApp ፓርቲዎች በ160 የምርጫ ክልሎች ላይ ቅሬታ መቅረቡን የኢትዮጵያ ብሄራዊ ....

29/06/2021

#አውሎዜና #ሰኔ22 #2013ዓም

የዩኒሴፍ ዋነኛ አላማ በትግራይ የሚገኙ ጠኔ የተጋረጠባቸዉ ከ140 ሺህ በላይ ህጻናትን ማገዝ ነዉ፡፡ በየትኛዉም መስፈርት ድርጅታችን የጥቃት ኢላማ መሆን አልነበረበትም ሲሉ ዋና ዳይሬክተሩ ገ...
29/06/2021

የዩኒሴፍ ዋነኛ አላማ በትግራይ የሚገኙ ጠኔ የተጋረጠባቸዉ ከ140 ሺህ በላይ ህጻናትን ማገዝ ነዉ፡፡ በየትኛዉም መስፈርት ድርጅታችን የጥቃት ኢላማ መሆን አልነበረበትም ሲሉ ዋና ዳይሬክተሩ ገልጸዋል፡፡

አውሎ ሚድያ ሰኔ 22/ 2013 ዓ.ም
ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ቴሌግራም፦ https://t.me/awlomedia
ትዊተር፦ https://twitter.com/AwloMedia
ዩትዩብ፦https://www.youtube.com/channel/UCFRuICCV8fHJGa3AbcA3zOA
ድረ ገጽ፦ https://awlomediatv.com
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/awlomedia

የተባበሩት መንግሥታት የህፃናት መርጃ ድርጅት (ዩኒሴፍ) በትግራይ ክልል ዋና ከተማ የሆነችው በመቐ

ዙማ በዚህ የኮሚሽኑ ፍርድ ቤት ለመቅረብ ፍቃደኛነት ባለመሆናቸው ባለፈ ፈርድ ቤቱ ገለልተኛ አይደለም በማለታቸው ፍርድ ቤት ተዳፍረዋል የሚል ክስ ቀርቦባቸዋል።አውሎ ሚድያ ሰኔ 22/ 2013 ...
29/06/2021

ዙማ በዚህ የኮሚሽኑ ፍርድ ቤት ለመቅረብ ፍቃደኛነት ባለመሆናቸው ባለፈ ፈርድ ቤቱ ገለልተኛ አይደለም በማለታቸው ፍርድ ቤት ተዳፍረዋል የሚል ክስ ቀርቦባቸዋል።

አውሎ ሚድያ ሰኔ 22/ 2013 ዓ.ም
ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ቴሌግራም፦ https://t.me/awlomedia
ትዊተር፦ https://twitter.com/AwloMedia
ዩትዩብ፦https://www.youtube.com/channel/UCFRuICCV8fHJGa3AbcA3zOA
ድረ ገጽ፦ https://awlomediatv.com
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/awlomedia

ይህ እውነትን አፈላላጊ ኮሚሽን አቋቁሞ የዙማን ጉዳይ እየተመለከተ የነበረ ሲሆን ጃኮብ ዙማ ግን በ

የተባበሩት አረብ ኢምሬትስ በትግራይ ክልል የተኩስ አቁም መታወጁ በደስታ ተቀብላ በሀገሪቱ የተፈጠረውን ግጭት ለማስቆም የፖለቲካ መፍትሄ ብቸኛው አማራጭ መሆኑን አሳስባለች፡፡አውሎ ሚድያ ሰኔ ...
29/06/2021

የተባበሩት አረብ ኢምሬትስ በትግራይ ክልል የተኩስ አቁም መታወጁ በደስታ ተቀብላ በሀገሪቱ የተፈጠረውን ግጭት ለማስቆም የፖለቲካ መፍትሄ ብቸኛው አማራጭ መሆኑን አሳስባለች፡፡

አውሎ ሚድያ ሰኔ 22/ 2013 ዓ.ም
ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ቴሌግራም፦ https://t.me/awlomedia
ትዊተር፦ https://twitter.com/AwloMedia
ዩትዩብ፦https://www.youtube.com/channel/UCFRuICCV8fHJGa3AbcA3zOA
ድረ ገጽ፦ https://awlomediatv.com
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/awlomedia

ዜና መንግስት በትግራይ ክልል የተኩስ አቁም ማወጁ እደግፋለሁ – የተባበሩት አረብ ኢምሬት June 29, 2021 0 1 ያጋሩ Facebook Twitter Google+ Pinterest WhatsApp በፌደራል መንግስትና በህዝባዊ ወያነ ሓርነት ትግ....

የፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ዐቃቤ ህግ በእነ እስክንድር ነጋ ላይ የቆጠራቸው 16 ምስክሮች በክፍት ችሎት እንዲሰሙ ወሰነ።አውሎ ሚድያ ሰኔ 22/ 2013 ዓ.ም  ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መ...
29/06/2021

የፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ዐቃቤ ህግ በእነ እስክንድር ነጋ ላይ የቆጠራቸው 16 ምስክሮች በክፍት ችሎት እንዲሰሙ ወሰነ።

አውሎ ሚድያ ሰኔ 22/ 2013 ዓ.ም
ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ቴሌግራም፦ https://t.me/awlomedia
ትዊተር፦ https://twitter.com/AwloMedia
ዩትዩብ፦https://www.youtube.com/channel/UCFRuICCV8fHJGa3AbcA3zOA
ድረ ገጽ፦ https://awlomediatv.com
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/awlomedia

የፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ዐቃቤ ህግ በእነ እስክንድር ነጋ ላይ የቆጠራቸው 16 ምስክሮች በክፍት ች

የመከላከያ ሚኒስቴር የ33ኛ ዙር ምልምል ወታደሮችን በአሁኑ ሰዓት በማስመረቅ ላይ ይገኛል።በብርሸለቆ መሠረታዊ ውትድርና ማሠልጠኛ ት/ቤት ሲሰለጥኑ የነበሩ ወታደሮች የተሰጣቸውን ስልጠና አጠና...
29/06/2021

የመከላከያ ሚኒስቴር የ33ኛ ዙር ምልምል ወታደሮችን በአሁኑ ሰዓት በማስመረቅ ላይ ይገኛል።

በብርሸለቆ መሠረታዊ ውትድርና ማሠልጠኛ ት/ቤት ሲሰለጥኑ የነበሩ ወታደሮች የተሰጣቸውን ስልጠና አጠናቀዋል።

ተመራቂዎቹ ከመደበኛው ሠራዊቱ ጋር በመቀላቀልከ ውስጥ እና ከውጭ የሚቃጣን ወረራ በመመከት እንዲሁም የኢትዮጵያን አንድነት አጠናክው ያስቀጥላሉ ተብሎ ይጠበቃል ሳ የሀገር መከላከያ ሰራዊት አሳውቋል።

አውሎ ሚድያ ሰኔ 22/ 2013 ዓ.ም
ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ቴሌግራም፦ https://t.me/awlomedia
ትዊተር፦ https://twitter.com/AwloMedia
ዩትዩብ፦https://www.youtube.com/channel/UCFRuICCV8fHJGa3AbcA3zOA
ድረ ገጽ፦ https://awlomediatv.com
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/awlomedia

 #አውሎማለዳ  #ሰኔ22  #2013ዓምተኩስ አቁም ወይስ መሸነፋ ? ጌታቸው ረዳ - ወደ ቦታችን ተመልሰናል ኢሳያስ አፈወርቂ ምን አሉ ?
29/06/2021

#አውሎማለዳ #ሰኔ22 #2013ዓም
ተኩስ አቁም ወይስ መሸነፋ ?
ጌታቸው ረዳ - ወደ ቦታችን ተመልሰናል
ኢሳያስ አፈወርቂ ምን አሉ ?

#አውሎማለዳ #ሰኔ22 #2013ዓም

“በትግራይ ክልል ውስጥ ውጤታማ የሆነ የተክሱ ማቆም ይጀመራል የሚል እምነት አለኝ” ብለዋል ጉቴሬዝ በመልእክታቸው፡፡አውሎ ሚድያ ሰኔ 22/ 2013 ዓ.ም  ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎች...
29/06/2021

“በትግራይ ክልል ውስጥ ውጤታማ የሆነ የተክሱ ማቆም ይጀመራል የሚል እምነት አለኝ” ብለዋል ጉቴሬዝ በመልእክታቸው፡፡

አውሎ ሚድያ ሰኔ 22/ 2013 ዓ.ም
ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ቴሌግራም፦ https://t.me/awlomedia
ትዊተር፦ https://twitter.com/AwloMedia
ዩትዩብ፦https://www.youtube.com/channel/UCFRuICCV8fHJGa3AbcA3zOA
ድረ ገጽ፦ https://awlomediatv.com
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/awlomedia

ዜና በትግራይ ውጤታማ የተኩስ አቁም እንደሚተገበር እምነት አለኝ- አንቶኒዮ ጉቴሬዝ June 29, 2021 0 1 ያጋሩ Facebook Twitter Google+ Pinterest WhatsApp የተመድ ዋና ጸሃፊ አንቶኒዮ ጉቴሬዝ በትላንትናው ዕለት ...

ሰበር ዜናመንግስት የትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር ላቀረበው የተኩስ አቁም ስምምነት ይደረግ ጥያቄ ውሳኔ አሳለፈሙሉ መረጃ እነሆ!መንግስት የትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር ላቀረበው የተኩስ አቁም ስም...
28/06/2021

ሰበር ዜና

መንግስት የትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር ላቀረበው የተኩስ አቁም ስምምነት ይደረግ ጥያቄ ውሳኔ አሳለፈ

ሙሉ መረጃ እነሆ!

መንግስት የትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር ላቀረበው የተኩስ አቁም ስምምነት ይደረግ ጥያቄ ውሳኔውን ገልጿል።

የጠቅላይ ሚኒስትር ጽህፈት ቤት ለትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር ውሳኔውን በደብዳቤ አስታውቋል።

የደብዳቤው ሙሉ ቃል እንነደሚከተለው ቀርቧል፡-

ለትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር
መቐለ

ጉዳዩ፥ የትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር ክልሉ ያጋጠመውን ችግር ለመፍታት ያቀረበውን የመፍትሔ ሐሳብ በተመለከተ የኢፌዲሪ መንግሥት ውሳኔ

አሸባሪው የሕወሐት ቡድን ባለፉት ሰላሳ ዓመታት በሀገሪቱ ላይ ትውልድ ገዳይ መከራ ማስከተሉ ይታወቃል፡፡ ኢትዮጵያውያን ከዳር እስከዳር ባደረጉት መራራ ትግል ይህ መከራ ተወግዷል፡፡ ያለፉ በደሎችን በይቅርታ ለመሻገር የለውጡ ኃይል አድርጎት የነበረውን ተደጋጋሚ ጥረት ማንም የሚያስታውሰው ነው፡፡ በፍቅር እንደመር፣ በይቅርታ እንሻገር በሚለው መርሐችን መሠረት፣ ሁልጊዜ እያፈረስን ከምንገነባ፣ያለፈውን በይቅርታ፣የሚመጣውን በካሣ ለማለፍ ጥረት አድርገን ነበር፡፡ የኢትዮጵያ ሕዝብም ለሁላችንም የመታረሚያ ዕድል ሰጥቶን ነበር፡፡

ይሁን እንጂ የሕወሐት ቡድን ኢትዮጵያን አፈራርሼ ፍርስራሹን እየሸጥኩ ካልተጓዝኩ በሚል የሕዝቡን ይቅርታ ከቁብ አልቆጠረውም፡፡ ራሱንም ከለውጥ ሂደቱ ከማውጣት አልፎ ለውጡን ለማደናቀፍ መሰናከል ማብዛት ጀመረ፡፡ በዚህ አቋሙም ተደጋጋሚ የሆኑ የመታረሚያ ዕድሎችን አበላሸ፡፡ ይባስ ብሎ ግጭቶችን እየጠነሰሰ፣ እልቂት እየደገሠ ሀገር ለማፍረስ መሥራት ቀጠለ፡፡ በኢሕአዴግ እና በመንግሥት መድረኮች ችግሩን በውይይት ለመፍታት የነበረውን ዕድል አጨናገፈው፡፡ በሀገር ሽማግሌዎች፣ በሃይማኖት አባቶች እና ሕወሐትን ከፌዴራል መንግሥት ጋር ሊያቀራርቡ ይችላሉ በተባሉ አካላት በኩል የተሞከሩ የሽምግልና ሙከራዎች ሁሉ በሕወሐት አልጠግብ ባይነት ከሸፉ፡፡

ይህ ሁሉ ቢሆንም እንኳን የከፋ ሀገራዊ ቀውስ እስካልተፈጠረ ድረስ ችግሩን በሆደ ሰፊነት ማየት ይገባል የሚል አቋም መንግሥት ነበረው፡፡ የሕወሐት ቡድን ለክልሉ የተላከውን በጀት ለጦርነት ድግስና ለጥፋት እያዋለው መሆኑ እየታወቀ ህዝቡ እንዳይጎዳ ሲባል የክልሉ በጀት ሳይቋረጥ እንዲያውም ተጨማሪ በጀት ተሰጥቶታል፤ ክልሉ በፌዴራል መንግሥት የነበረው ውክልና ሳይነካ በሰላም ለመቀጠል ተሞክሯል፡፡ በሀገሪቱ ውስጥ በተለያዩ ቦታዎች ግጭትና መፈናቀል እያስከተለ እንኳን የትግራይን ክልል ከማስተዳደር ያገደው አልነበረም፡፡

ይሄንን ሁሉ የመንግሥት ትእግሥት እንደ ፍርሃት የቆጠረው የሕወሐት ቡድን በጥቅምት ወር በሰሜን ዕዝ ላይ ሀገር ሊያፈርስ የሚችል ጥቃት ፈጸመ፡፡ ከሃያ ዓመታት በላይ ድንበር ሲጠብቅና የትግራይን ሕዝብ ሲረዳ በኖረው የሰሜን ዕዝ ላይ አሰቃቂ ግፍ ሠራ፡፡ አንዳንዶችን ገደለ፤ አንዳንዶችን አረደ፤ በአንዳንዶች ላይ ኢሰብአዊ ተግባር ፈጸመ፤ ሴት ወታደሮችን አዋረደ፡፡ የሰሜን ዕዝን መሣሪያ ወስዶ በኢትዮጵያ ላይ ግልጽና ቅርብ አደጋ ደቀነ፡፡

የመከላከያ ሠራዊታችን በሕገ መንግሥቱ በተጣለበት የሀገርን ሉዓላዊነትና ህልውና የመጠበቅ ኃላፊነት መሠረት፣ በወሰደው ሕግ የማስከበር ርምጃ የሕወሐት ቡድን ከጥቅም ውጭ ሆነ፡፡ መዋቅሩ ፈረሰ፤ ወታደራዊ አቅሙ ተደመሰሰ፤ አመራሩ ምርኮኛ ሙትና ቁስለኛ ሆነ፤ የቀረውም ተበተነ፡፡

የኢትዮጵያ መንግሥት ሕግ የማስከበር ዘመቻ ሲከፍት ዓላማው የሕወሐትን ቡድን ከጥቅም ውጭ ማድረግና ኢትዮጵያን መታደግ ነበር፡፡ በዚህ ዓላማም ቡድኑ ከዚህ በኋላ ሀገራዊ አደጋ ከማይደቅንበት ደረጃ ወርዶ፣ የተረፈው ኃይል የተበተነ ርዝራዥ ሆኗል፡፡ አደጋ ሊያደርስበበት የነበረውን የጦር መሣሪያም ተነጥቋል፡፡ የኢኮኖሚና የፖለቲካ ዐቅሙም ኢምንት ሆኗል፡፡ በአጎራባች አገሮችና ክልሎች የነበረው የጥፋት ሃይሉ ማምለጫ መንገድ በመከላከያ ሃይል ስለተዘጋ ወንጀለኞች ያሚያመልጡበት እድል ተመናምኗል። በዚህም የተነሣ ፈፋ ለፈፋ እንደ እየዘለለ የሚኖር ሽፍታ ሆኗል፡፡

የኢትዮጵያ መንግሥት ሕግ የማስከበር ዘመቻውን በዋናነት ካጠናቀቀ በኋላ ፊቱን ወደ መልሶ ግንባታ በማዞር የሕወሐት ቡድን ባደረሰው ጥፋት የወደሙትን መሠረተ ልማቶች ለመገንባት የህይወት መስዋእትነት ጭምር ተከፍሎ ሰፊ ርብርብ አድርጓል ። በግጭቱ የተጎዱ ወገኖችን ለመርዳትና አገልግሎቶች እንዲጀመሩ ለማድረግም ሰፊ ሥራ ሠርቷል፡፡ ይሄንን የርዳታና የመልሶ ግንባታ ሥራ ለማገዝ የፌዴራል መንግሥቱና የክልል መንግሥታት ከመቶ ቢልዮን ብር በላይ ወጭ አውጥተዋል፡፡ ከሰላሳ በላይ የእርዳታ ድርጅቶችና አራት መቶ የሚጠጉ ሰራተኞቻቸው ክልሉን ገብተው እንዲረዱ አድርጓል፡፡ ሌላው ቀርቶ የመገናኛ ችግር እንኳን እንዳይፈጠር በተለየ መልኩ ለዓለም አቀፍ ድርጅቶች የራሳቸው የመገናኛ መሣሪያዎችን ለመጠቀም የሚያስችል ዕድል ተፈጥሯል፡፡ ሀገር አቀፍና ዓለም አቀፍ የሚዲያ ተቋማት ሂደቱን እንዲዘግቡ ተፈቅዷል፡፡ የቪዛና የጉዞ ፈተናዎች እንዳይኖሩ ሁኔታዎች ሁሉ ተመቻችተዋል፡፡

በዚህ ጉዞ ውስጥ ግን አንዳንድ ዓለም አቀፍ አጋሮቻችን ችግሩን ለመገንዘብ ፍላጎት አላሳዩም፡፡ ለርዳታ የከፈትንላቸውን መሥመርም ላልተገባ ተግባር ሲጠቀሙበት ታይተዋል፡፡ አንዳንድ ሚዲያዎችም ከእውነት በተቃራኒ መቆምን መርጠዋል፡፡ ከሚደርሱት ርዳታዎች ከሰባ በመቶ በላይ የሚሸፍነው የኢትዮጵያ መንግሥት መሆኑ እየታወቀ ለመንግሥት ተግባር ዕውቅና ነፍገዋል፡፡

የኢትዮጵያ መንግሥት የትግራይ ሕዝብ ከሚጎዳ ጫናውን ተሸክሞ ማለፍ ይሻላል በሚል መርሕ ይሄን ሁሉ ጫና ተቋቁሞ አልፏል፡፡ የትግራይን ሕዝብ ችግር የመፍታት ቀዳሚውና ዋናው ኃላፊነት የኢትዮጵያ መንግሥት እንጂ ርዳታ ሳይሰጡ ስለ ርዳታ የሚያወሩ አካላት እንዳይደለ በማመን የተቻለውን ሁሉ አድርጓል፡፡
ከሕግ ማስከበር ዘመቻው በኋላ የነበረው ጊዜ ርዳታ ለማድረስ፣ መንግሥታዊ አገልግሎቶችን ለማስጀመር፤ የጸጥታና የፍትሕ አካላትን ለማሠልጠንና ለማሠማራት፣ መሠረተ ልማቶችን መልሶ ለመገንባት፣ ለመንግሥት ሠራተኞች ደመዝ ለመክፈል፣ ሕዝቡን አስቀድሞ ሕወሐት ካቆራረጠው ወገኑ ጋር ለማገናኘት ውሏል፡፡ ከዚሁ ጎን ለጎን የተበተነውን ሽፍታ አመራር ለመያዝ ባደረግነው ዘመቻ ዋና ዋናዎቹ አንድም ተደምስሰዋል፤ ወይም ተይዘዋል፡፡ የቀሩትም በሃገር ላይ አደጋ ከማድረስ አንፃር ትርጉም የሌላቸው ሆነዋል፡፡

ከላይ የተገለፀው ሁኔታ እንዳለ ሆኖ ህግ ማስከበር ሁኔታ ጎን ለጎን የክልሉን ችግር በዘላቂነት ለመፍታት በኢትዮጵያውያንና በኢትዮጵያ ወዳጆች ሲቀርቡ የነበሩ የመፍትሔ ሃሳቦችን የፌደራል መንግስት ስያጤናቸው ቆይቷል። ይህ በእንዲህ እንዳለ የትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር በተካታታይ ያቀረበውን ጥያቄ መንግሥት ከተለያየ አቅጣጫ ተመልክቶታል፡፡ በአንድ በኩል አካባቢው ከሚመራ አካል የቀረበ በመሆኑ፤ በሌላ በኩል ጥያቄው ከመቅረቡ በፊት በተለያየ ጊዜ ከክልሉ ተወላጆች፣ ከሀገር ሽማግሌዎችና ከሃይማኖት አባቶች ጋር ውይይት የተደረገበት መሆኑን ከግምት ውስጥ አስገብተናል፡፡ በስድስተኛው ሃገራዊ ምርጫ የኢትዮጵያ ህዝብና ተፎካካሪ ፓርቲዎች ከመቸውም በላይ ለሃገራችን ሰላም የሰጡት ልዩ ትኩረት ከግምት ውስጥ ገብቷል፡፡ ይህንንም ሰላም የኢትዮጵያ አንዱ አካል የሆነውን የትግራይ ህዝብ ተቓዳሽ ሊሆን ይገባል ተብሎ ስለሚታመን። የትግራይም ህዝብ ሰላምና ለውጥ ፈላጊ መሆኑ በተለያዩ መንገዶች ሲገልፅ የቆየ መሆኑን ስለሚታወቅ። የሀገሪቱን ሉዓላዊነት ከውጭ ኃይሎች ከተሰነዘሩ ትንኮሳዎች ለመከላከልና ሁለተኛውን ዙር የሕዳሴ ግድብ ለመሙላት ትኩረት መስጠት የወቅቱ አንገብጋቢ ጥያቄ በመሆኑ።

የትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር እንደገለጠው፣ መላው ሕዝብም እንደሚረዳው፣ የተበተነው የሕወሐት የጥፋት ኃይል በሚሽሎከሎኩባቸው አካባቢዎች ገበሬው ተረጋግቶ ወደ እርሻ ሥራ መግባት አልቻለም፡፡ ባለፈው አመት የአምበጣ መንጋ በስፋት ያጠቃው ክልል በመሆኑ የግብርና ሰብል ምርት በበቂ ሁኔታ አላገኝም፤ ከአንበጣ የተረፈውን መሰብሰብ እንዳይችል በመሰብሰብያ ግዜው በህዝብ ስም የሚነግደው ሕወሐት አከባቢውን የግጭት ቀጣና አደረገው። በዚህ ሁኔታ ይሄንን ክረምት ያለ እርሻ ሥራ የሚያሳልፍ ከሆነ፣ ለገበሬው በዕንቅርት ላይ ጆሮ ደግፍ ይሆንበታል፡፡ የሕወሐት የጥፋት ኃይል በሚነዛው ሽብር የተነሣ ሕዝቡ የጦርነት ጋሻ ሆኖ እየተማገደ ይገኛል፡፡ ሲዋጋ ሚሊሻ ሲጠቃ ሲቪል የሚሆን ኃይል እየተፈጠረ ነው፡፡ በዚህ የተነሣ ሕወሐት በፈጠረው ቀውስ ቤታቸው የፈረሰባቸው፣ እርሻቸው የተስተጓጎለባቸው፣ አካባቢያቸውን ለቅቀው የተፈናቀሉ ሁሉ የተረጋጋ ኑሮ ለመኖር አልቻሉም፡፡

በአንድ በኩል እነዚህን ነገሮች ከግምት ውስጥ በማስገባት፤ በሌላ በኩል ደግሞ በረሐ ከተበተነው ኃይል ውስጥ ሁኔታዎች ቢመቻቹለት ወደ ሰላም ሊመጣ የሚችል ኃይል ይኖራል ተብሎ ስለታመነ፣ የጊዜያዊ አስተዳደሩን ጥያቄ መንግሥት በአዎንታዊነት ተቀብሎታል፡፡
ይህ እንደተጠበቀ ሆኖ ዋነኞቹን የጥፋት መሪዎች ለህግ የማቅረብ ስራ እና፡የተጀመረው የምርመራ ተግባር ተጠናክሮ የሚቀጥል ይሆናል።
በዚህም መሠረት ገበሬው ተረጋግቶ የእርሻ ሥራውን እንዲከውን፣ የርዳታ ሥራው ከወታደራዊ እንቅቃሴ ነጻ ሆኖ እንዲሠራጭ፣ ሰላምን የሚመርጡ የሕወሐት ርዝራዥ አካላት ወደ ሰላም መንገድ እንዲመጡ፤ ሳያውቁ ርዝራዡን የጥፋት ኃይል የተከተሉ እንደገና ለማሰብና ወደ ሰላማዊ መንገድ ለመምጣት ዕድል እንዲያገኙ ለማስቻል፣ ይህ የእርሻ ወቅት እስኪጠናቀቅ ድረስ የሚቆይ ያለቅድመ ሁኔታ በሰብአዊነት ላይ የተመሠረተ በተናጠል የተኩስ አቁም ከዛሬ ከሰኔ 21 ቀን 2013 ጀምሮ መንግሥት አውጀዋል፡፡

ሁሉም የፌዴራልና የክልል ሲቪልና ወታደራዊ ተቋማት፣ ከመንግሥት በሚሰጣቸው ዝርዝር አፈጻጸም መሠረት ይሄን የተኩስ አቁም እንዲያከብሩና እንዲያስከብሩ ታዝዘዋል፡፡ ይሄን መልካም ዕድል ለክፉ የሚጠቀሙ ወገኖች ካጋጠሙ ግን አስፈላጊው ሕግን የማስከበር ተግባር እንደ አግባቡ የሚከናወን ይሆናል፡፡

የኢትዮጵያ ፌደራላዊ ዲሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ መንግሥት

Address

Bole Medhanialem, Awlo Business Center 1st Floor
Addis Ababa

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when AWLO MEDIA አውሎ ሚዲያ posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to AWLO MEDIA አውሎ ሚዲያ:

Share