Dawit Tefera ዳዊት ተፈራ

Dawit Tefera ዳዊት ተፈራ Welcome to my Page, voice of truth and fairness

Good Morning Kenya.
11/07/2025

Good Morning Kenya.

አንዳንድ ሰዎች ህዝቡን የሚረዱበት'ና የሚያዩበት መንገድ ይገርማል። ንቀታቸውም ከልክ ያልፋል ! የሆነ ሰው ስለጓደኛው ሞት ግድ ሳይሰጠው ፣ ስለፍትህ መዛባት ሳያስጨንቀው ከዝምታም ከተቃውሞም...
04/07/2025

አንዳንድ ሰዎች ህዝቡን የሚረዱበት'ና የሚያዩበት መንገድ ይገርማል። ንቀታቸውም ከልክ ያልፋል !

የሆነ ሰው ስለጓደኛው ሞት ግድ ሳይሰጠው ፣ ስለፍትህ መዛባት ሳያስጨንቀው ከዝምታም ከተቃውሞም ለማትረፍ'ና የራሱን ጥቅም ብቻ አስጠብቆ ለማለፍ ሲሞክር እንደነዚህ እከክ ሰዎች ሰዎች የሚቀፍ'ና ከሁለቱም ያጣ ይሆናል !

ቀነኔ አዱኛ እንደዛ በሚያሳዝን ሁኔታ በግፍ ስትሞት ፣ ለወራት ቤተሰቦቿ ድምፅ ሁኑን እያሉ በአደባባይ ሲለምኑ ፣ ህዝቡ ፍትህ እንድታገኝ በዛ ልክ ሲጮህ ፣ የፍትህ ስርዓቱ ላይ ጥያቄ ሲነሳ ፣ አንዱዓለም በዋስ እስኪለቀቅ ፣ ተለቆም የሃጫሉ አዋርድን እስኪሸለም ድረስ ዝምታን መርጠው ምንም እንዳልተፈጠረ በሶሻል ሚዲያ አካውንቶቻቸው የጭፈራና የፈንጠዝያ ቪዲዮ ብቻ ሲለቁ እንዳልነበሩ ፣ ገና ዛሬ በደል እንደደረሰባት የሰሙ ይመስል የህዝቡን ሚዛን አይተው የህፃን የተቃውሞ ቪዲዮ መልቀቅ ጀምረዋል !

አይደለም ለጓደኛ'ና አብረዋት ለበሉ ለዚች ምስን ሴት ለማያውቁት ሰውስ ፍትህ ለመጠየቅ የዚህን ያህል ይዘገያል ?

እንደ ጓደኛ እየደረሰባት ያለውን ግፍ ፣ ጉዳቷን ቀድመው ተረድተው በህይውት እንድትቆይ ባያግዟት እንዴት በሞቷ ላይ ትርፋቸውን እያሰቡ ይንቀሳቀሳሉ ?

ብቻ ከእነ እንደዚህ አይነት ሰዎች ይጠብቀን ማለት ነው እንጂ ምን ማለት የቻላል 😡😓🥵

አሳዛኝ ዜና😭ከ150 ሺ ብር በላይ ግምት ያላቸው የአንድ ግለሰብ ንብረት እና እንስሳት በመብረቅ አደጋ ጉዳት መድረሱ ተገለጸሰኔ 15/2017 ዓ.ም ከ150 ሺ ብር በላይ ግምት ያላቸው የአንድ...
24/06/2025

አሳዛኝ ዜና😭
ከ150 ሺ ብር በላይ ግምት ያላቸው የአንድ ግለሰብ ንብረት እና እንስሳት በመብረቅ አደጋ ጉዳት መድረሱ ተገለጸ

ሰኔ 15/2017 ዓ.ም ከ150 ሺ ብር በላይ ግምት ያላቸው የአንድ ግለሰብ ንብረት በመብረቅ አደጋ ጉዳት መድረሱ እና እንስሳቶችንም መግደሉን የኣሪ ማህበረሰብ ሬዲዮ ጣቢያ ሚዲያና ኮሚዩኒኬሽን ዘገባ ያመላክታል።

በወላይታ ሶዶ በደረሰ የትራፊክ አደጋ የ3 ሰዎች ሕይወት አለፈ*******************በወላይታ ሶዶ ከተማ በደረሰው የትራፊክ አደጋ እስካሁን የ3 ሰዎች ሕይወት አልፏል።በከተማው ዛሬ ከ...
24/06/2025

በወላይታ ሶዶ በደረሰ የትራፊክ አደጋ የ3 ሰዎች ሕይወት አለፈ
*******************

በወላይታ ሶዶ ከተማ በደረሰው የትራፊክ አደጋ እስካሁን የ3 ሰዎች ሕይወት አልፏል።

በከተማው ዛሬ ከሰዓት ማሪያም ቤተክርስቲያን ፊት ለፊት 21 ማዞሪያ ተብሎ በሚጠራ አካባቢ በተከሰተው አደጋ ነው የሰዎች ሕይወት ያለፈው።

የወላይታ ሶዶ ከተማ ፖሊስ አዛዥ ኮማንደር ሀብታሙ አሰፋ ለኢቢሲ እንደተናገሩት በአደጋው እስካሁን የ3 ሰው ሕይወት ያለፈ ሲሆን፤ በ3 ሰዎች ላይ ከፍተኛ የአካል ጉዳት ደርሷል።

እንዲሁም በስድስት ተሽከርካሪዎች ላይ ጉዳት የደረሰ ሰሆን አደጋው የተከሰተው በተሽከርካሪ የቴክኒክ ችግር መሆኑን ኮማንደር ሀብታሙ ተናግረዋል።

በአደጋው የተጎዱ ሰዎች በአቅራቢያ ወደሚገኙ የህክምና ማዕከል እየተወሰዱ እንደሚገኝም ኮማንደር ሀብታሙ ጠቅሰዋል፡፡

በትዕግስቱ ቡቼ

'ጣናነሽ 2' ጀልባን ከቤትዋ ለማድረስ ዕድል በማግኘታችን ደስተኞች ነን -አሽከርካሪዎች*************************ከጂቡቲ ዶላሬ ወደብ ተነስታ ወደ ኢትዮጵያ ጉዞ ላይ የምትገኘው ...
15/06/2025

'ጣናነሽ 2' ጀልባን ከቤትዋ ለማድረስ ዕድል በማግኘታችን ደስተኞች ነን -አሽከርካሪዎች
*************************

ከጂቡቲ ዶላሬ ወደብ ተነስታ ወደ ኢትዮጵያ ጉዞ ላይ የምትገኘው 'ጣናነሽ 2' ጀልባን፤ ወደ መዳረሻዋ የመውሰድ ዕድል በማግኘታችን እጅግ ደስተኞች ነን ሲሉ አሽከርካሪዎች ገለፁ።

ለኢትዮጵያ ከጀልባነት በላይ ብዙ ተምሳሌታዊ ትርጉም ያላትን ጀልባ በማጓጓዝ የታሪኩ አካል በመሆናቸው የተሰማቸውን ደስታም ገልፀዋል፡፡

አሽከርካሪዎቹ ባለፉት ወራት በከባድ እና አስቸጋሪ መልከዓ ምድር ላይ ያደረግነው ጉዞ፤ ጥምረት የተሞላው በመሆኑ የከፋ ችግር አላጋጠመንም ሲሉም ነው በተለይ ለኢቢሲ ዶትስትሪም የተናገሩት።

በየከተማው ስንደርስ በአመራሮች እና በከተማው ነዋሪዎች የሚደረግልን አቀባበል እጅግ ከጠበቅነው በላይ ከመሆኑ ባሻገር ወደ ፊት ለሚጠብቀን ጉዞ እንድንበረታ አድርጎናልም ነው ያሉት።

ጣናነሽ 2 ጀልባ እያደረገችው ባለው ጉዞ አራት ተሸከርካሪዎች አጅበው የሚጓዙ ሲሆን እንደየመልከዓ ምድሩ አቀማመጥ በመጎተት፣ በመደገፍ እና የመለዋወጫ እቃ በመጫን በጉዞ ላይ የሚሳተፉም ናቸው።

በአፎሚያ ክበበው

14/06/2025
Gech & our presidentTigray Communication Affairs BureauTigray EthiopiaTirhas Gebrekidan
14/06/2025

Gech & our president

Tigray Communication Affairs Bureau
Tigray Ethiopia
Tirhas Gebrekidan

ሶስቱ ቱለማዎች (sadeen ilmaan Tuulamaa) የስርዓተ ገዳ ጉዞ/godaansa ላይ ናቸው።  በዝህም1. ዳጭ- ከሀዋስ እስከ ጩቃላ፣ ከሰላሌ እስከ ቦሰት፣ ከአደአ እስከ ሰደን ሶዶ ...
14/06/2025

ሶስቱ ቱለማዎች (sadeen ilmaan Tuulamaa) የስርዓተ ገዳ ጉዞ/godaansa ላይ ናቸው። በዝህም

1. ዳጭ- ከሀዋስ እስከ ጩቃላ፣ ከሰላሌ እስከ ቦሰት፣ ከአደአ እስከ ሰደን ሶዶ ባሉት መልካዎች እና ጨፌዎች ተወጣጥቶ ጉዞ ወደ ኦዳ ነቤ ጀምረዋል

2- በቾ- ከሀዋስ፣ ሜታ እና ከሌሎች ቦታዎች ተሰብስቦ ጉዞውን ወደ ኦዳ ነቤ እያደረገ ነው

3.ጅሌ - ከገፈርሳ ኮርማ፣ ኦዳ ቱታ እና ከጨፌ ደምበል፣ ከጨፌ ወንጂ… ተጠራርቶ ወደ ኦዳ ነቤ እየሄደ ነው

ጉዞ ከተጀመረ ዛሬ አረተኛ ቀኑ ነው። ነገ ሁሉም በቦታው ODAA NABEE ይደርሳሉ።

የዝህ ስርዓት ዋናው ባለቤት በሙደና (ሚቺሌ) ምድብ ውስጥ ያሉ ቱለማዎች ናቸው።

በዝሁም የቱለማ የበኩር ልጅ ጅዳዎች ከወረ ጃርሶ እና ሰደን ሶዶ ጋር በመሆን ኦዳ ሀምዴ ካደሩ በኋላ ወደ ቅልጡ ገቺ በመሄድ መልካ ሰደቃ አድሮ ኦዳ ነቤን ይደርሳሉ።

ኦቦ እና ገላን ፎቃ ሉሜን በማደር ኦዳ ነቤ ይደርሳሉ። ጂሌዎች ደግሞ ገፈርሳ ኮርማ ካደሩ በኋላ ወደ ኦዳ ነቤ ይጓዛሉ።

ሁሉም ሶስቱ የቱለማ ልጆች ነገ ሀሙስ ኦዳ ነቤን ይደርሳሉ። ከዛም ይመራረቃሉ። የገዳ ስርዓት በሚያዘው መልኩ ስራዎችን ይጀምራሉ። አዳድስ ህጎች፣ የሚሻሻሉ ስርዓቶች፣ ደንቦችን ካሉ ያረቃሉ። ብዙ ስርዓቶችም በኦዳ ነቤ ይፈፀማል።

በመሆኑ ውድ የቱለማ ኦሮሞ ወንድሞች መጫ፣ ሲኮ-መንዶ፣ ኢቱ ሁምበና፣ እና ራያ አዜቦ፣ እንድሁም ቦረና፣ ጉጂዎች በዝህ ስርዓት ላይ እንድትገኙ ወንድማዊ ጥሪ ተደርጓል።

ገዳ የስኬት፣ የደስታ እና የጥጋብ ነው።
ፈጣሪ ያሳካልን!

ኦዳ ነቤ፣ ኦሮሚያ

Shaggar City Communication Office
Oromia Prosperity Party / OPP /
Addis Standard
Gedeo Cultural Landscape World Heritage Site

Address

Addis Ababa

Telephone

+251988117876

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Dawit Tefera ዳዊት ተፈራ posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to Dawit Tefera ዳዊት ተፈራ:

Share