Amhara media commencation

Amhara media commencation እውነተኛ የህዝብ ድምፅ

01/05/2025

የሚኒስትሮች ምክር ቤት በተለያዩ ጉዳዮች ላይ ተወያይቶ ውሳኔ አሳለፈ

አዲስ አበባ፣ ሚያዝያ 23፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) የሚኒስትሮች ምክር ቤት በዛሬው ዕለት ባካሄደው 44ኛ መደበኛ ስብሰባ በተለያዩ ጉዳዮች ላይ ተወያይቶ ውሳኔ አሳልፏል።

ምክር ቤቱ ያሳለፋቸው ውሳኔዎች እንደሚከተለው ቀርቧል፡-

1. ምክር ቤቱ በቅድሚያ የተወያየው ከጣሊያን ሪፐብሊክ መንግሥት እና ከዓለም አቀፍ የልማት ማህበር ጋር በተፈረሙ ሁለት የፋይናንስ ድጋፍ ስምምነቶች ላይ ነው፡፡ ከጣሊያን ሪፐብሊክ መንግስት የተገኘው የ11,500,000 ዩሮ ለአካባቢያዊና አረንጓዴ ኢኮኖሚ ልማት የበጀት ድጋፍ ፕሮግራም ማስፈፀሚያ የሚውል ሲሆን የ16 ዓመት የችሮታ ጊዜን ጨምሮ በ30 ዓመት ተከፍሎ የሚጠናቀቅ ነው፡፡ ከዓለም አቀፍ የልማት ማህበር የተገኘው 38,100,000 ኤስ.ዲ.አር ለመማር ማስተማር ማጎልበቻ የትምህርት ዘርፍ ትራንስፎርሜሽን ፕሮግራም ማስፈፀሚያ የሚውል ሲሆን 0.75% የአገልግሎት ክፍያ የሚከፈልበት ሆኖ 6 ዓመት የችሮታ ጊዜን ጨምሮ በ38 ዓመት ተከፍሎ የሚጠናቀቅ ነው፡፡ ምክር ቤቱም ብድሮቹ ምንም አይነት ወለድ የማይታሰብባቸው እና ከአገራችን የብድር አስተዳደር ፖሊሲ ጋር የሚጣጣሙ መሆናቸውን በማረጋገጥ ረቂቅ አዋጆቹ ለህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት እንዲተላለፉ በሙሉ ድምጽ ወስኗል፡፡

2. በመቀጠል ምክር ቤቱ የተወያየው በአፍሪካ ፋይናንስ ኮርፖሬሽን መቋቋሚያ ስምምነት ማጽደቂያ ረቂቅ አዋጅ ላይ ነው፡፡ ኮርፖሬሽኑ ትኩረቱን በመሠረተ ልማት፣ በተፈጥሮ ሀብት እና በኢንዱስትሪ ዘርፍ ልማት ላይ በማድረግ ለግል አልሚዎችና ለመንግሥት አካላት የፋይናንስና የቴክኒክ ድጋፍ ለመስጠት የተቋቋመ ነው፡፡ ሀገራችን በአባልነት መቀላቀሏ ለግሉ ዘርፍ ተጨማሪ የፋይናንስ ሀብት በማቅረብና የግል ዘርፉን የማይተካ የኢኮኖሚ አንቀሳቃሽነት ሚና በማሳደግ ቀጣይነት ያለው የኢኮኖሚ ዕድገት ለማፋጠንና ድህነትን ለመቀነስ ጠቀሜታ ያለው በመሆኑ ምክር ቤቱ በቀረበው ረቂቅ አዋጅ ላይ ከተወያየ በኋላ ለህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት እንዲተላለፍ በሙሉ ድምጽ ወስኗል፡፡

3. ሌላው ምክር ቤቱ ለአፍሪካ አህጉራዊ ነጻ ንግድ ቀጣና ስምምነት የዕቃዎች ቀረጥ ምጣኔ ቅነሳን ለማስፈፀም በቀረበ ረቂቅ ደንብ ላይ ተወያይቷል። ስምምነቱ በአባል ሀገራት መካከል ንግድ እንዲስፋፋ፣ የገበያ ትስስሩ እንዲጠናከር፣ የእሴት ሠንሰለቱ እንዲጎለብት እና የኢኮኖሚ ትራንስፎርሜሽን ማበረታታት የሚያስችል ነው፡፡ በአባል ሀገሮች መካከል የሚደረጉ ግብይቶች በታሪፍ ምክንያት ሳይደናቀፉ የእቃዎች ፍሰት የተሳለጠ እንዲሆን ከአባል አገራት በሚመጡ እቃዎች ላይ የጉምሩክ ታሪፍ ምጣኔ ለይቶ መወሰን አስፈላጊ መሆኑን በመወያዬት ምክር ቤቱ ደንቡ በፌዴራል ነጋሪት ጋዜጣ ታትሞ ከወጣበት ቀን ጀምሮ በአንድ ወር ጊዜ ውስጥ ተፈፃሚ እንዲሆን በሙሉ ድምጽ ወስኗል፡፡

4. ሌላው ምክር ቤቱ የተወያየው በትራንስፖርት እና ሎጂስቲክስ ሚኒስቴር ለሚሰጡ አገልግሎቶች እና በኢ.ፌዲ.ሪ የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች ባለሥልጣን ለሚሰጡ አገልግሎቶች የሚከፈሉ የአገልግሎት ክፍያዎችን ለመወሰን በቀረቡ ሁለት ረቂቅ ደንቦች ላይ ነው፡፡ ተቋማቱ አገልግሎት ለመስጠት የሚያወጡትን ወጪ በመሸፈን፣ ገቢያቸውን አሳድገው ጥራት ያለው አገልግሎት በመስጠት የተገልጋይ እርካታ ማሳደግ የሚያስችል የደንበኞችን አቅም ባገናዘበ መልኩ የአገልግሎት ክፍያ መወሰን አስፈላጊ ይሆናል፡፡ ምክር ቤቱም በረቂቅ ደንቦቹ ላይ በስፋት ከተወያየ በኋላ በነጋሪት ጋዜጣ ታትመው ከወጡበት ቀን ጀምሮ በስራ ላይ እንዲውሉ በሙሉ ድምጽ ወስኗል፡፡

5. የውጭ ዜጎች የማይንቀሳቀስ

19/07/2024
04/12/2023

ፋኖ ይለያል

14/06/2023

ኃይልን እወቅ!

በዚህች አለም ላይ 98%ከመቶ የሚሆኑት የሰው ልጆች የሚኖሩት የተሰጣቸው ኃይላቸውን ለመጠቀም መንገዱ ጠፍቱቸው ነው በእነዚህ በ2% በሚሆኑት ሰዎች ሥር ይኖሩታል። እግዚአብሐር ሰው ልጅን ስፍጥር ብዙ ስጦታዎች ሰጥቶሃልና ከእነዚህ ስጦታዎች አንዱና የተለየ ስጦታ አለ እሱም አዕምሮ ነው።

አዕምሮ እግዚአብሔር ከሰጠው ስጦታዎች ሁሉ ለሰው ልጅ የተለየ ነው ይህን ጥቅቶች ተረድቶ በአለም ቁንጮ ላይ ተቀምጠዋል አንዳንዶች ደግሞ በሕይወታቸው በማማረር አለም ውስጥ ያሳልፋሉ።ስለዚህ አሁን እኔ የሚልህ ወዳጄ ይህንን ስጦታ በአግባቡ ተጠቀም ያለፈው ትናንት ላይመለስ ነው የሄደው ነገ ደግሞ የማይታይ ምሥጢር ነው ዛሬ ደግሞ ለሕይወትህ የተሰጠች ውዱዋ ቀን ነች ስለዚህ የተሰጠችውን ቀን በአግባቢ በመጠቀም ስፖርት መሥራት ካለብህ ዛሬ በመሠራት ያሰብከው ቢዝነስ ካለህ አሁን ጀምረህ ማድርግ ስትችል መጽሐፍ ማንበብ ክለብህ አሁን ጀምር። እንደዛ ማድረግ በጀመረከው ሳዓት የአዕምሮን ኃይል መጠቀም ትጀምራለህ። ቁጭ ካልክ እንደ ብርት አዕምሮ ከመዛግ እንጂ ምንም አይነት ለውጥ አያመጣም።ዳይ ወደ ተግባር ወዳጄ።

መልካም ቀን ተመኘንላችሁ🙏

ሁሌም የእናንተው ምርጫ!

20/05/2023
ዛሬ፩ኛ ተወዳጇ ቅዳሜ ናት፪ኛ የታላቁ ሊቅ ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ መታሰቢያ ነው፫ኛ የቅድስት ክርስቶስ ሠምራ መታሰቢያ ነው፬ኛ የቅዱስ ሚካኤል ወርኃዊ በዓል ነው፭ኛ የአቡነ ተክለሃይማኖት መታ...
20/05/2023

ዛሬ
፩ኛ ተወዳጇ ቅዳሜ ናት
፪ኛ የታላቁ ሊቅ ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ መታሰቢያ ነው
፫ኛ የቅድስት ክርስቶስ ሠምራ መታሰቢያ ነው
፬ኛ የቅዱስ ሚካኤል ወርኃዊ በዓል ነው
፭ኛ የአቡነ ተክለሃይማኖት መታሰቢያ በዓል ነው

እንኳን አደረሳችሁ ክቡራን
በሁሉም የሚመሰገነው መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ሰላሙን፣ ፍቅሩን፣ ትሕትናውን፣ ደግነቱን ያድለን።

05/05/2023

የኢትዮጵያ ባህር ትራንስፖርት እና ሎጅስቲክስ/ኢባትሎ ሊገዛ ላቀደው ሁለት ግዙፍ መርከቦች የውጭ ምንዛሬ ፍቃድ ለማግኘት ለብሄራዊ ባንክ ለሁለተኛ ጊዜ የፕሮጀክት ማብራሪያ ሰነድ ማስገባቱን ይፋ አደረገ፡፡
ተቋሙ ላለፉት ከሁለት አመታት ቀደም ለሚል ጊዜ የጭነት አቅማቸው አሁን ካሉት መርከቦች ከፍ የሚሉ ሁለት ሁለገብ መርከቦችን ለመግዛት ሲንቀሳቀስ ቆይቶ ነበር፡፡
ፕሮጀክት ቀርጾ ሲንቀሳቀስ የቆየው ኢባትሎ የጥናት እና ዝግጅት ምእራፎችን አልፎ እና ጨረታ አውጥቶ ዚያንግዩ የተሰኘ የቻይና ድርጅት ለሁለቱ አልትራማክስ መርከቦች ግንባታ ስራ መምረጡንም አስታውቋል፡፡
በግዥ እቅዱ መሰረት የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ለመርከብ ግዥው 70 በመቶ ብድር እንዲያመቻች ከባንኩ ጋር ስምምነት የተደረሰ ሲሆን፤ ክፍያው ግን በውጭ ምንዛሬ እንደመሆኑ የሚያስፈልገውን የውጭ ምንዛሬ ለማግኘት ብሄራዊ ባንክን ማስፈቀድ አስፈልጎ ነበር፡፡
በዚህም መሰረት ኢባትሎ ቀደም ሲል ዝርዝር ሂደቱን የሚያስረዳ ሰነድ ለማእከላዊ ባንኩ አስገብቶ ነበር፡፡
በቅርቡም በድጋሜ በብሄራዊ ባንክ ማብራሪያ እንዳስገቡ የሎጅስቲክ ድርጅቱ ሃላፊዎች ለካፒታል ተናግረዋል፡፡
የመርከብ ግንባታው ሂደት ቢያንስ ሁለት አመት የሚፈጅ ሲሆን ክፍያውም በ5 ዙር የሚከናወን በመሆኑ ለውጭ ምንዛሬ አመዳደብ አመቺ እንደሚሆን የተቋሙ ሃላፊዎች አስረድተዋል፡፡
በመሆኑም ማእከላዊ ባንኩ ጥያቄውን እንደሚቀበል ነው ያላቸውን ተስፋ የገለጹት፡፡
በእቅዱ መሰረት የውጭ ምንዛሬ አመንጭው ተቋም 30 በመቶ የሚሆነውን የመርከብ ግንባታ ወጪ ሚሸፍን ሲሆን የቀረው ከኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የሚቀርብ ይሆናል፡፡
አዲስ የሚገዙት አልትራማክስ መርከቦች የመጫን አቅማቸው 63 ሺ ቶን እንደሚሆን የሚጠበቅ ሲሆን ይህን አይነት መርከብ ሚባትሎ አስከቅርብ ጊዜ ድረስ ኖሮት አያውቅም፡፡
ኢባትሎ በቅርቡ ከአስር አመት በላይ እድሜ ያስቆጠሩ ሁለት ነዳጅ ጫኝ መርከቦቹን ሰባት አመት እድሜ ባላት በአንድ አልትራማክስ መቀየሩ ይታወሳል፡፡
ቅያሬው ከመደረጉ በፊት የሚያስተዳድራቸው መርከቦች የመጫን አቅማቸው 28 ሺ ቶን ግድም ነበር በመሆኑም አዲስ የተቀላቀለችው መርከብ በመጫን አቅሟ ለኢባትሎ አድስ ምእራፍ የምትከፍት ናት፡፡

05/05/2023

በትረማርያም አበባው:
+_ኤጲስ ቆጶሳት__+
#፩ኛ ክብራቸው
ኤጲስ ቆጶሳት የእግዚአብሔር ደጋግ ሹማምንት ናቸው (ፍት. ነገ. ፭)። (ድስቅ ፱፣፯) ከእግዚአብሔር በታች አባት ለሆነህ ለኤጲስ ቆጶሱ እጅ ንሣ እንዲል ኤጲስ ቆጶሳት ከእግዚአብሔር በታች የሃይማኖት አባቶቻችን ስለሆኑ ክቡራን ናቸው። ምእመናን አባግዕ ከተባሉ ዘንድ ኤጲስ ቆጶሳት ደግሞ ምእመናንን የሚጠብቁ ጠባቂዎች ናቸው (ድስቅ. ፩፣፬)። ቤተክርስቲያን በምድርም በሰማይም በሁሉ ያለች የእግዚአብሔር መንግሥት ናት። ትምህርቷን የሚያስተምሩ፣ ሥርዓቷን የሚፈጽሙ ሹማምንትን ደግሞ እግዚአብሔር ከዐፃዌ ኆኅት እስከ ፓትርያርክ ይሾሞላታል። ኤጲስ ቆጶስ የምእመናን አባት እንደመሆኑ ይራራላቸው። (ድስቅ ፮፣፲፭) ኤጲስ ቆጶስ ስለ ሕዝቡ ኃጢአት ያዝን ዘንድ ይገባል እንዲል። (ድስቅ ፮:፴፩) ኤጲስ ቆጶሱ ሕዝቡን እንደልጆቹ ሊወዳቸው ይገባል። ዲድስቅልያ ፬፣፳፮ ኤጲስቆጶሳት ሆይ ሕዝቦችን አስተምራችሁ ከስሕተት ታድኗቸው ዘንድ ለእናንተ ይገባል።

#፪ኛ የሹመት መስፈርታቸው
ኤጲስቆጶስነትን የሚሾም ሰው ነውር ነቀፋ የሌለበት ይሁን (ፍት. ነገ. ፭)። ሕዝቡ (ምእመናን) እና ጳጳሳቱ ካልፈቀዱለት ማንም ቢሆን ኤጲስ ቆጶስነት አይሾምም። ቤተክርስቲያን የምእመናንም የካህናትም የጳጳሳትም ስለሆነች ምእመናንም ካህናትም ያልፈለጉትን እንዳይሾም ማድረግ ይችላሉ። የፈለጉትን እንዲሾምም ማድረግ ይችላሉ። የሚከተሉት የቀኖና መጻሕፍት ምእመናን ያልፈቀዱለት ኤጲስ ቆጶስ መሆን እንደማይችል ይናገራሉ። ሁሉንም አስተውሏቸው። ፍት. ነገ.፭፣ ፴፮ "ኤጲስ ቆጶስ በሚሾምባቸው ሕዝብ ፈቃድና በሊቀ ጳጳሱ ፈቃድ ይሾም" ስለሚል ሕዝቡ ያልፈቀደለት ሰው ጵጵስና መሾም አይችልም። ስለዚህ በጳጳሳት ሹመት ሕዝቡም ድርሻ ስላለው ድርሻውን ሊወጣ ይገባል። እንዲሁም ሐዋርያት በአብጥሊሳቸው አብጥሊስ ፪:- ኤጲስ ቆጶስ ሆኖ ሊሾም የቀረበ ሰው ካለ ይህ በሀገረ ስብከቱ ባሉ ሰዎች ሁሉ ስምምነት ይሁን ብለዋል። በተጨማሪም ቀሌምንጦስ ቀኖና ፪:- ኤጲስ ቆጶስ ሆኖ እንዲሾም ያመጡት (የመረጡት) ሰው ሹመቱ የሚሰጠው በሀገሩ ሰዎች ስምምነት ይሁን ይላል። ቀኖና ዘኒቅያ ቁጥር ፬:- ኤጲስ ቆጶሳትና ሕዝቡ ሁሉ የወደዱት ኤጲስ ቆጶስ ይሾም። ቀኖና ዘኒቅያ ቁጥር ፮:- ኤጲስ ቆጶስ ያለ ጳጳሱና ያለሕዝቡ ፈቃድ አይሾም። ሲኖዶስ ዘአንጾኪያ ትእዛዝ ፲፱:- ኤጲስ ቆጶስ በሀገሩ ሰዎችና በኤጲስ ቆጶሳት ሥምረት ይሾም። በትእዛዝ ሲኖዶስ ፶፩ እንደተገለጸውም መስማት የተሳነውና ዓይነ ሥውር ኤጲስ ቆጶስነት አይሾምም። ኤጲስ ቆጶስ ሊቃውንትን የሚወድ መሆን እንዳለበትም አብጥሊስ ፴፫:- ኤጲስ ቆጶስ የሊቃውንትን ክብር የሚያውቅ ይሁን ተብሎ ተገልጿል። እድሜን በተመለከተ ደግሞ ዲድስቅልያ ፬፣፩-፬ "ኤጲስ ቆጶስ የሚሾም ሰው 50 ዓመት የሞላው ይሁን። ሀገሪቱ ትንሽ ብትሆን እና 50 ዓመት የሞላው ባይገኝ ሌላውን መሥፈርት ካሟላ ከ50 ዓመት በታችም ይሾም ተብሏል። ኤጲስ ቆጶስነት የሚሾም ሰው ሃይማኖት ከምግባር አስተባብሮ የያዘ መሆን ይገባዋል። ዲድስቅልያ ፬፣፲-፲፩ ኤጲስ ቆጶስ የሚሾም ሰው ቂም ክፋትና ዐመፅ የሌለበት ልበ ንጹሕ ይሁን። የማይቆጣ፣ የማይሰክር፣ የማይበቀል፣ ጸብና ክርክር የሌለው፣ የማይሳደብ ይሁን እንዲል። ፍትሐ ነገሥት አንቀጽ ፭ ኤጲስ ቆጶስነት የሚሾመው ድንግልና ከምንኩስና ያለው ነው። ይህ ሥርዓት ከሠለስቱ ምእት ወዲህ የሆነ ነው። ከዚያ በፊት አንድ ያገባ ኤጲስ ቆጶስ ይሆን ነበርና።

"50,000 ጠያቂ በአንድ ጀንበር" ! የታሪክ ሰሪ ልጆች ብቻ አይደለንም፤ታሪክ ሰሪዎችም እንጅ።ጀግኖች አባቶቻችን ጠላትን አሸንፈው ታሪክ በሰሩበት ዕለት እኛም ጀግናችን ለመጠየቅ 50,000...
02/03/2023

"50,000 ጠያቂ በአንድ ጀንበር" !

የታሪክ ሰሪ ልጆች ብቻ አይደለንም፤ታሪክ ሰሪዎችም እንጅ።ጀግኖች አባቶቻችን ጠላትን አሸንፈው ታሪክ በሰሩበት ዕለት እኛም ጀግናችን ለመጠየቅ 50,000 ሁነን ሰባታሚት ማረሚያ ቤት ተገናኝተን ታሪክ እንሰራለን።ባህርዳር፣ጎንደር ፣ደብረማርቆስ፣ደብረታቦር፣ፍኖተሰላም ፣ደባርቅ፣ደብረብርሃን ደሴ፣ ወልዲያ፣ወረታ ፣አዲስ ዘመን፣አዴት ፣መራዊ፣ዱርቤቴ፣ሊበን፣ሞጣ፣ደጀን፣ቢቸና ደብረወርቅ እና ሌሎችም ስማቸውን ያልጠቀስናቸው ከተሞች ወደ አርበኛ ዘመነ ካሴ በነገው ዕለት ያመራሉ። በተለይም ባህርዳር ከተማ ከ30,000 በላይ ጠያቂ ወደ ሰባታሚት እስር ቤት እንደሚተም ይጠበቃል። የባህርዳር ጠያቂዎች እስከ ጠዋቱ 2:00 ሰአት ፓፒረስ አደባባይ ይደረሳሉ። 3:00 ሰባታሚት ማረሚያ ቤት ከሌሎች ጠያቂዎች ጋር ይገናኛሉ። ለዚህ ዘመቻ መሰካት አስፈላጊ የሆኑ የትራንስፖርት የሚዲያ አካላት አስፈላጊውን ትብብር እንድታደርጉ ጥሪ እናቀርባለን።

-ቀጣዩ የትግል ምዕራፍ ነገ ከሰዓት በኋላ ይፋ ይደረጋል::

አስተባባሪ ኮሚቴው

09/02/2023

መንግስት ከአጉል እልከኝነቱ ወጥቶ ከሕገ ወጦቹ ግለሰቦች ጋር በመተባበር በአደባባይ እየፈጸመ ያለውን የሕግ ጥሰት ዛሬን ጨምሮ በቀጣዮቹ ፪/ሁለት/ ቀናት ውስጥ እንዲያቆም እና ሕግ እና ሥርዓትን እንዲያስከብር፣ በኃይል የወረራቸውን መንበረ ጵጵስና እና አጥቢያ አብያተ ክርስቲያናት ለቆ ለቤተክርስቲያኒቱ ሕጋዊ መዋቅር እንዲያስረክብ፣ ያለአግባብ ያሠራቸውን ካህናት እና ምእመናን ያለምንም ቅድመ ሁኔታ እንዲለቅ፣ ቤተ ክርስቲያኒቱ ላይ ለፈፀመው በደል በአደባባይ ይቅርታ እንዲጠይቅ፤ በካህናት እና ምእመናን ላይ ለደረሰው ሞት እና የአካል ጉዳት ተገቢውን ካሳ እንዲክስ እና የወደሙ ንብረቶቿን እንዲጠግን በጥብቅ እንጠይቃለን ፡፡

መንግሥት በዚሁ አካሄድ ሕግ እየጣሰ እና የቤተ ክርስቲያኒቱን ክብር እና ልእልና እያዋረደ የሚቀጥል ከሆነ ቤተ ክርስቲያን መንግሥት የጣሰውን ሕግ መሠረት በማድረግ መብቷን ለማስከበር እስከአሁን ድረስ ፍጹም ሰላማዊ የሆነውን እንቅስቃሴዋን አድማሱን በማስፋት በየካቲት ፭ ቀን ፳፻፲፭ ዓ.ም ለማድረግ ያቀደችውንና ያሳወቀችውን ሀገር አቀፍ እና ዓለም አቀፍ ሰላማዊ ሰልፍ ያለማንም ከልካይነት በራሷ አደባባይ የምታከናውን መሆኑን እያሳወቅን መንግሥትም ድርሻው ሰልፉ ሰላማዊ ሆኖ እንዲጠናቀቅ መንግሥታዊ ኃላፊነቱን በአግባቡ መወጣት ብቻ መሆኑን እያሳሰብን ዛሬም ቢሆን መንግሥት ቆም ብሎ በማሰብ ከእኛ ከአባቶች ጋር ሃይማኖታዊ፣ ቀኖናዊና መንፈሳዊ የአስተዳደር ሥርዓታችንን ባልጣሰ መልኩ ለመነጋገር እና ችግሩን በዘላቂነት ለመፍታት ጥረት ካደረገ በውይይት ለመፍታት መንፈሳዊ በራችን ክፍት መሆኑንም እናሳውቃለን፡፡

ከዚህ ውጭ ግን በሁለቱ አባቶች መካከል የተፈጠረ ችግር እየተባለ የሚነገረው ፖለቲካዊ ጨዋታ የመንግሥት እንጂ በሀገሪቱ ሕጋዊ ሰውነት የሌላቸውና ከቤተ ክርስቲያን የተለዩ ግለሰቦች ጋር ማነጻጸር ሕገ መንግሥታዊም ሆነ ሞራላዊ የሕግ መሠረት የለውም፡፡

ስለዚህ ቤተ ክርስቲያናችን የጠራችውን ሰላማዊ እና ሕጋዊ የሆነ የመብት ጥያቄ የማፈን ሂደትን በጥብቅ እንቃወማለን፡፡

የተወደዳችሁ የመንፈስ ቅዱስ ልጆቻችን እስከአሁን ባደረጋችሁት ጽናትና ተጋድሎ ሃይማኖታችሁንና ቅድስት ቤተ ክርስቲያንችሁን እንዳላሳፈራችሁ ሁሉ አሁንም ከስሜታዊነት በወጣ ሁኔታ በከፍተኛ ጽናት እና ጥንካሬ የአባቶቻችሁን ድምጽ ብቻ እንድትሰሙ፣ ቤተ ክርስቲያንን በየአጥቢያችሁ ተደራጅታችሁ እንድትጠብቁ፤ ለአባቶቻችሁ መንፈሳዊ ጥሪ ፈጣን ምላሽ እንድትሰጡ፣ እየመጣው ላለ መከራና ስደት ለመንፈሳዊ ተጋድሎ እንድትዘጋጁና በፍፁም መንፈሳዊ ጨዋነት በአንድነት የመጣብንን ፈተና እንድትወጡ አደራ እያልን አባታዊ መልእክታችንን እያስተላለፍን ሰላማዊ ሰልፉን በተመለከተም በአጭር ጊዜ ውስጥ ዝርዝር መግለጫ የምንሰጥ መሆኑን እያሳውቅን በዚህ ጥቃት መስዋእትነት የከፈሉ እና ያረፉ ልጆቻችንን ነፍሳቸውን በአጸደ ገነት በክብር ያሳርፍልን እያልን ጸሎተ ፍትሐትም በየደረጃው የሚከናወን መሆኑን እያሳወቅን በተለያዬ ጊዜ ዛሬን ጨምሮ በወለቴ እና በሰበታ ከተሞች የደረሰውን የአካል ጉዳት እና ሞት እግዚአብሔር ምህረት እና መጽናናቱን ያድልልን፡፡ እግዚአብሔርም ገድላችሁን፣ ጽናታችሁንና ጸሎታችሁን ይቀበል፤ የቅዱሳን አምላክ ከሁላችን ጋር ይሁን፡፡

ወስብሐት ለእግዚአብሔር

“እግዚአብሔር ሀገራችንን ይባርክ”
የካቲት ፪ ቀን ፳፻፲፭ ዓ.ም.
አዲስ አበባ ኢትዮጵያ

Address

Bihardar
Addis Ababa
COMMUNICATION

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Amhara media commencation posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to Amhara media commencation:

Share