07/03/2026
ከኪራይ በሚገኝ ገቢ ላይ ተፈጻሚ የሚሆኑ የግብር ምጣኔዎች ምን ይመስላሉ ?
የፌዴራል መንግሥት የገቢ ግብር አዋጅን ለማሻሻል ባወጣው አዋጅ ቁጥር 1395/2017 መሠረት፣ የግለሰቦች የኪራይ ገቢ ግብር ስሌት ላይ ማሻሻያ ማድረጉ ይታወቃል።
ይህ አዲስ ምጣኔ በተለይ ከመኖሪያ ቤትም ሆነ ከንግድ ቤቶች ኪራይ ገቢ የሚያገኙ ግለሰቦች የሚከፍሉትን የግብር መጠን በግልጽ የሚያስቀምጥ ነው።
ሚኔስቴር መስሪያ ቤቱ ከኪራይ የሚገኝ ገቢን በሚመለከት ይፋ ያደረገው የስሌት መረጃ ምን ይመስላል ?
በአዋጁ መሠረት በዓመት ውስጥ የሚገኝ የኪራይ ገቢ ግብር የሚሰላባቸው ደረጃዎች የሚከተሉት ናቸው ፡-
1. አንድ ግለሰብ በዓመት የሚያገኘው የኪራይ ገቢ እስከ 24,000 ብር ከሆነ፣ ምንም ዓይነት የገቢ ግብር (0%) እንዲከፍል አይገደድም።
2. ከ24,001 እስከ 48,000 ብር የገቢ ክልል ውስጥ የሚገኙ አከራዮች 15 በመቶ የግብር ምጣኔ የሚጣልባቸው ሲሆን፣ 3,600 ብር ተቀናሽ ይደረግላቸዋል።
3. ከ48,001 እስከ 84,000 ብር የገቢ ክልል ውስጥ የሚገኝ ገቢ 20 በመቶ ግብር የሚታሰብበት ሲሆን፣ ተቀናሽ መጠኑ ደግሞ 6,000 ብር ነው።
4. ከ84,001 እስከ 120,000 ብር የገቢ መጠን የግብር ምጣኔው 25 በመቶ ሲሆን፣ ተቀናሽ መጠኑ 10,200 ብር ሆኖ ተቀምጧል።
5. ከ120,001 እስከ 168,000 ብር በዚህ ደረጃ የግብር ምጣኔው ወደ 30 በመቶ ከፍ የሚል ሲሆን፣ የ16,200 ብር ተቀናሽ ተጠቃሚ ይሆናሉ።
6. ከ168,000 ብር በላይ ከፍተኛ የኪራይ ገቢ የሚያገኙ ግለሰቦች ከፍተኛውን የግብር ምጣኔ ማለትም 35% በመቶ ሚከፍሉ ሲሆን፣ ተቀናሽ መጠናቸው 24,600 ብር ነው።
AWDE NEWS
አዲስ አበባ
የካቲት 28 ቀን 2018 ዓ/ም
#ሰበርዜና #ዜና