05/08/2026
“የሀገራችንን ኢኮኖሚ ሥሪት ምርታማና ተወዳዳሪ በማድረግ በተረጋጋ ማክሮ ኢኮኖሚ ዓውድ ፈጣን፣ መጠነ ሰፊ እና ተከታታይ ዕድገት ልናረጋገጥ ይገባል። ይህም መሆን ያለበት ከድህነት በፍጥነት መውጣት፣ በምግብ ራሳችንን መቻል እና ለወጣቶች አስተማማኝ የሥራ ዕድል መፍጠር የሚያስፈልግበት ወሳኝ ሀገራዊ ምዕራፍ ላይ ስለምንገኝ ነው። ከረጅም ጊዜ አኳያ ይኽንን ዓላማ ለማሳካት ሀገራችን በበቂ የቴከኖሎጂ ዐቅም ላይ የተመሠረት ዕውቀት መር ኢኮኖሚን የመገንባት ትልም ልትይዝ ይገባል። የዕውቀት መር ኢኮኖሚ ልማትን ለማምጣት በዘላቂነት በውጭ ሀገር ቁጠባ፣ ብድርና ርዳታ ላይ ያልተመረኮዘ፣ ራስ ገዝና ከራሱ እየተማረ፣ ራሱን እያረመ የሚያበቃ የኢኮኖሚ ሥርዓት መገንባት መሆን ይኖርበታል።”
ጠ/ሚር ዐቢይ አህመድ (መደመር - ገጽ 229)