Ethiopian Independent

Ethiopian Independent "እንፈተናለን፤ መስዋዕትነት እንከፍላለን ነገር ግን ኢትዮጵያን እናፀናለን።

“የሀገራችንን ኢኮኖሚ ሥሪት ምርታማና ተወዳዳሪ በማድረግ በተረጋጋ ማክሮ ኢኮኖሚ ዓውድ ፈጣን፣ መጠነ ሰፊ እና ተከታታይ ዕድገት ልናረጋገጥ ይገባል። ይህም መሆን ያለበት ከድህነት በፍጥነት መ...
05/08/2026

“የሀገራችንን ኢኮኖሚ ሥሪት ምርታማና ተወዳዳሪ በማድረግ በተረጋጋ ማክሮ ኢኮኖሚ ዓውድ ፈጣን፣ መጠነ ሰፊ እና ተከታታይ ዕድገት ልናረጋገጥ ይገባል። ይህም መሆን ያለበት ከድህነት በፍጥነት መውጣት፣ በምግብ ራሳችንን መቻል እና ለወጣቶች አስተማማኝ የሥራ ዕድል መፍጠር የሚያስፈልግበት ወሳኝ ሀገራዊ ምዕራፍ ላይ ስለምንገኝ ነው። ከረጅም ጊዜ አኳያ ይኽንን ዓላማ ለማሳካት ሀገራችን በበቂ የቴከኖሎጂ ዐቅም ላይ የተመሠረት ዕውቀት መር ኢኮኖሚን የመገንባት ትልም ልትይዝ ይገባል። የዕውቀት መር ኢኮኖሚ ልማትን ለማምጣት በዘላቂነት በውጭ ሀገር ቁጠባ፣ ብድርና ርዳታ ላይ ያልተመረኮዘ፣ ራስ ገዝና ከራሱ እየተማረ፣ ራሱን እያረመ የሚያበቃ የኢኮኖሚ ሥርዓት መገንባት መሆን ይኖርበታል።”

ጠ/ሚር ዐቢይ አህመድ (መደመር - ገጽ 229)

በጠ/ሚ ዶ/ር ዐቢይ አሕመድ ሀሳብ አመንጪነት የተጀመረው ሀገራዊ ምክክር ኢትዮጵያ ለዘመናት ያስተናገደቻቸውን ፖለቲካዊ ማህበራዊና ታሪካዊ ስብራቶች በውይይትና በመግባባት ለመፍታት የተጀመረ ሀ...
05/08/2026

በጠ/ሚ ዶ/ር ዐቢይ አሕመድ ሀሳብ አመንጪነት የተጀመረው ሀገራዊ ምክክር ኢትዮጵያ ለዘመናት ያስተናገደቻቸውን ፖለቲካዊ ማህበራዊና ታሪካዊ ስብራቶች በውይይትና በመግባባት ለመፍታት የተጀመረ ሀገራዊ ጥረት ነው። ሀገራዊ ምክክር የተለያዩ ሀሳቦች አመለካከቶችና ተሞክሮዎች በነፃነት የሚቀርቡበት የጋራ መግባባት የሚፈጠርበትና ዘላቂ መፍትሄዎች የሚፈለጉበት የሰላም መድረክ ነው። ይህ ሂደት ያለፉ ቅሬታዎችንና አለመግባባቶችን በግጭት ሳይሆን በውይይት እንዲፈቱ የእርቅና የመተማመን መንፈስ እንዲጠናከርና በማህበረሰቡ ውስጥ የውይይት ባህል እንዲዳብር ትልቅ እድል ይፈጥራል።

ግብርና የኢትዮጵያ ኢኮኖሚ ዋና መሰረት ከሆኑ ዘርፎች አንዱ ነው።በልማት አርበኛው ጠ/ሚ ዶ/ር ዐቢይ አሕመድ የምትመራው ሀገራችን ኢትዮጵያ በጥቂት አመታት ውስጥ በስንዴ ምርት ያሳየችው አስደ...
05/08/2026

ግብርና የኢትዮጵያ ኢኮኖሚ ዋና መሰረት ከሆኑ ዘርፎች አንዱ ነው።በልማት አርበኛው ጠ/ሚ ዶ/ር ዐቢይ አሕመድ የምትመራው ሀገራችን ኢትዮጵያ በጥቂት አመታት ውስጥ በስንዴ ምርት ያሳየችው አስደማሚና አስደናቂ ለውጥ የሀገራችን የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ የገቢ አቅምን ለማሳደግና የግብርና ዘርፉን ወደ ተሻለ ደረጃ ለማሸጋገር ያለውን አቅም ከፍ አድርጓል።ይህ ዘርፍ ለሀገራችን አጠቃላይ ሀገራዊ ምርት ከፍተኛ አስተዋፅዖ ከማድረጉም በላይ ለውጭ ገበያ ከሚላኩ ምርቶች ውስጥ ከፍተኛውን ድርሻ የሚይዝ የኢኮኖሚ አምድ ነው።በተለይም በአሁኑ ጊዜ ግብርናችንን ከባህላዊ የአሰራር ልምዶች ወደ ዘመናዊ በቴክኖሎጂ የተደገፈና ምርታማነትን የሚያሳድግ የልማት ስርአት ለመሸጋገር ትልቅ ርምጃዎች ተወስደዋል።

05/08/2026
"አንድን ጉዳይ ስናይ ታሪካችንን ባህላችንን ልማዳችንን እምነታችንን አብረን  ካላየናቸው በአንድ እጅ ማጨብጨብ ይሆናል።"ጠቅላዩ
05/08/2026

"አንድን ጉዳይ ስናይ ታሪካችንን ባህላችንን ልማዳችንን እምነታችንን አብረን ካላየናቸው በአንድ እጅ ማጨብጨብ ይሆናል።"

ጠቅላዩ

03/08/2026
 !         "የኢትዮጵያ ውበት እንጂ ተመልካች አጥቶ ገረጣ እንጂ አልሞተም፤አቧራ ተጭኖት ደበዘዘ ከነጭራሹ አልጠፋም፡፡ አላፈራም እንጂ ከነአካቴው አልረገፈም፡፡ኢትዮጵያ አሁንም ሊወጡ የ...
03/08/2026

!
"የኢትዮጵያ ውበት እንጂ ተመልካች አጥቶ ገረጣ እንጂ አልሞተም፤አቧራ ተጭኖት ደበዘዘ ከነጭራሹ አልጠፋም፡፡ አላፈራም እንጂ ከነአካቴው አልረገፈም፡፡ኢትዮጵያ አሁንም ሊወጡ የሚችለ ብዙ አስደማሚ የውበት ጸጋዎችን ታድላለች። ሀገራችን ጥበበኞች በአድናቆት የሰላ ብዕራቸዉን ቀለም የሚያንቆረቁሩባት፣ተዐምራትን መፍጠር የሚያስችል ዕምቅ ውበት ባለቤት ናት።"

 #ጠቅላዩ!         "የአረንጓዴ ዐሻራ ሥራችን የአንድ ሰሞን ዘመቻ አይደለም፤ የአጭር ጊዜ ግብን ታሳቢ ያደረገ ቁንጽል እርምጃ አይደለም። የትልቁ ዓላማችን አንድ ሰበዝ ነው።እንደ ሀገር...
03/08/2026

#ጠቅላዩ!
"የአረንጓዴ ዐሻራ ሥራችን የአንድ ሰሞን ዘመቻ አይደለም፤ የአጭር ጊዜ ግብን ታሳቢ ያደረገ ቁንጽል እርምጃ አይደለም። የትልቁ ዓላማችን አንድ ሰበዝ ነው።እንደ ሀገር የመበልጸግና የሁለንተናዊ ዕድገት ጉዟችን አካል ነው።"

 #ጠቅላዩ!      "ዘመናትን የሚሻገር ስልጣኔ በመሰረቱ ጥልቀት ይታወቃል። የዛሬ አረንጓዴ ዐሻራ ከብዙ የሥልጣኔ መሰረቶች አንዱ ነው።ልክ እንደ ኢነርጂ ልማት፣ የኢንደስትሪ ማስፋፋት፣ እን...
03/08/2026

#ጠቅላዩ!
"ዘመናትን የሚሻገር ስልጣኔ በመሰረቱ ጥልቀት ይታወቃል። የዛሬ አረንጓዴ ዐሻራ ከብዙ የሥልጣኔ መሰረቶች አንዱ ነው።ልክ እንደ ኢነርጂ ልማት፣ የኢንደስትሪ ማስፋፋት፣ እንደ ክህሎት ግንባታ ወዘተ የሚታይ ነው።"

 !      "የኢኮኖሚያችን መዋቅራዊ ሽግግር ለማምጣት ኢንዱስትሪና ዲጅታል ዘርፎች ላይ እንደምናተኩረው፤ የሁሉም ዐሻራ ያረፈባት ሀገርና ባለቤትነትን ለማጽናት አስተዳደራዊ ልህቀት ላይ እንደ...
03/08/2026

!
"የኢኮኖሚያችን መዋቅራዊ ሽግግር ለማምጣት ኢንዱስትሪና ዲጅታል ዘርፎች ላይ እንደምናተኩረው፤ የሁሉም ዐሻራ ያረፈባት ሀገርና ባለቤትነትን ለማጽናት አስተዳደራዊ ልህቀት ላይ እንደምንሰራው፤ስነ-ምኅዳራዊ ዘላቂነትን ለማምጣት አረንጓዴ ዐሻራ ላይ መስራት ይገባል።"

Address

Addis Ababa

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Ethiopian Independent posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Shortcuts

Share