
28/07/2025
“በመንግስት ላይ ተገቢውን ጫና ለመፍጠር ለምናደርገው ትግል መራጩ ህዝብ ከጎናችን እንድትቆሙ” ሲል የተቃዋሚ ፖለቲካ ፓርቲዎች ኮክሰ ጠየቀ
የ ኢትዮጵያ ተቃዋሚ ፓርቲዎች ኮከስ፤ በአገራችን ያንዣበበው አደጋ ለመቀልበስ ዘላቂ ሠላም እንዲሰፍንና መጪው ምርጫ ነጻ፣ ዲሞክራሲያዊና ተዓማኒ ይሆን ዘንድ “በገዢው ፓርቲ/መንግስት/ ላይ ተገቢውን ጫና ለመፍጠር ለምናደርገው ትግል መራጩ ህዝብ የምናቀርበውን ጥሪ እንድትከታተሉና ከጎናችን እንድትቆሙ” ሲል ጠየቀ።
የኦሮሞ ፌዴራሊስት ኮንግረስ (አፌኮ)፣ የኦሮሞ ነፃነት ግንባር (ኦነግ) እና የኢትዮጵያ ህዝቦች አብዮታዊ ፓርቲን (ኢሕአፓ) ጨምሮ ስምንት ፓርቲዎችን ያካተተው ኮክሱ ዛሬ ባወጣው መግለጫ፤ "ጥያቄዎቻችን ከፖለቲካ ጥያቄ ባሻገር የአገር-አድን ፣የህዝብ መድህንነት አጀንዳ ናቸውና፤ የሲቪል ማኅበረሰብ አባላት በሁሉም መድረኮች፣ በሙሉ አቅማችው ከፓርቲዎቹ ጎን እንዲሰለፉ” በማለት ጥሪ አቅቧል።
ፓርቲዎቹ፤ ከመጪው ምርጫ በፊት የቦርዱ “ሀጋዊ የአሰራርና ተቋማዊ ችግር እስካልተፈታ ድረስ ለምርጫ መዘጋጀት የሚለው ሀሳብ ትርጉም አልባ ይሆናል” ሲሉ አስጠንቅቀዋል። በእነዚህ ሁኔታዎቸ “ነጻና ፍትሃዊ ምርጫ ሊኖር አይችልም” ያለው መግለጫው፤ “እውነተኛ ሪፎርም ከሌለ በኢትዮጵያ ተኣማኒ፣ አካታች፣ ነጻና ዲሞክራሲያዊ ምርጫ ሊኖር አይችልም” ብሏል።
(አስ)