Negarit - ነጋሪት

Negarit - ነጋሪት Negarit is a digital social media platform, providing news, information, insiders leaks and analysis for Ethiopian people.
(2)

Negarit is an independent and non partisan digital social media platform designed to inform, inspire and engage the people of Ethiopia. Reaching people through high-standard, high-quality and high impact multimedia content available in different formats such as youtube, facebook, twitter and other social media formats. Negarit recognizes and appreciates the efforts that citizens make each day in b

uilding a better Ethiopia for all people. Negarit strives to empower disadvantaged groups such as women, youth and people with disabilities etc. Working within collaboration of all people to enlighten, educate and strengthen citizens in order to expose corruption and to create unity between neighboring countries.

14 የሥራ አመራር አባላት ከሃላፊነታቸው ተሰናበቱየኢትዮጵያ ኮንስትራክሽን ሥራዎች ኮርፖሬሽን (ECWC) በውስጡ ያለውን "የአፈጻጸም፣ የተጠያቂነት እና የመልካም አስተዳደር ክፍተት" ለማረም ...
13/12/2025

14 የሥራ አመራር አባላት ከሃላፊነታቸው ተሰናበቱ

የኢትዮጵያ ኮንስትራክሽን ሥራዎች ኮርፖሬሽን (ECWC) በውስጡ ያለውን "የአፈጻጸም፣ የተጠያቂነት እና የመልካም አስተዳደር ክፍተት" ለማረም በሚል የወሰደውን እርምጃ ተከትሎ፤ 14 የሥራ አመራር አባላትን ከሃላፊነታቸው ማሰናበቱን አስታወቀ።

በቅርቡ የተሾሙት የኮርፖሬሽኑ ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ ሮቤል ፀጋዬ በታህሳስ 01 ቀን 2018 ዓ.ም ለሰራተኞች ባስተላለፉት የውስጥ ማስታወሻ እንዳመለከቱት፤ የኮርፖሬሽኑ የቦርድ አመራር ባደረገው ጥልቅ ግምገማ በተቋሙ ውስጥ ከፍተኛ የአፈጻጸም ክፍተቶች ተገኝተዋል።

በግምገማው የተለዩት ዋና ዋና ችግሮች የሚከተሉት ናቸው፦
• የፕሮጀክት አፈጻጸም በቋሚነት ከሚጠበቀው በታች መሆን፣
• የኮርፖሬሽኑን የፋይናንስ አቅም ያዳከሙ የስትራቴጂክ ውሳኔዎች መኖር፣
• ቁልፍ የአሰራር ስርዓቶች፣ የቁጥጥር እና የአስተዳደር ልምዶች እንደተፈለገው አለመስራት፣
• የተጠያቂነት እና የአመራር ቅንጅት ማነስ።

እነዚህን ችግሮች ተከትሎ የቦርድ አመራሩ የተቋሙን እና የሀገርን ጥቅም ለመጠበቅ ሲባል፤ ከላይ በተጠቀሰው ቀን ጀምሮ ተግባራዊ በሚሆን ውሳኔ የሚከተሉት 14 የስራ አመራር አባላት ከስራ እንዲሰናበቱ ወስኗል።

ከሃላፊነት የተነሱት አመራሮች ዝርዝር፡

1. አቶ አሰፋ ቀሴቶ
2. አቶ በምነት ጋሻው
3. ዶ/ር ቤዛዊት ግርማ
4. አቶ ኢሳያስ አንዳርጌ
5. አቶ ፍፁም ታምሩ
6. አቶ ሳሙኤል አማረ
7. አቶ ሸዋንግዛው ተስፋዬ
8. አቶ ሱራፌል አባይነህ
9. አቶ ታደለ ፉሌ
10. አቶ ዋቅጅራ ይልማ
11. አቶ ወገን ሰለሞን
12. አቶ ዮሃንስ አየለ
13. አቶ ዘሪሁን መኩሪያ
14. ወ/ሮ ዘይነባ ኡመር

ይህ እርምጃ የተወሰደው የአመራር ድክመቶችን ለማረም፣ ግልፅነትን ለማስፈን እና ኮርፖሬሽኑን ወደ ተሻለ የፕሮጀክት አፈጻጸም ለመመለስ እንደሆነ ዋና ስራ አስፈፃሚው አብራርተዋል።

በተጓደሉት ቦታዎች ላይ ጊዜያዊ አመራሮች እንደሚመደቡ የተገለጸ ሲሆን፤ ሁሉም ሰራተኞች ይህ የሽግግር ወቅት እስኪያልፍ ድረስ ሃላፊነታቸውን በዲሲፕሊን እንዲወጡ አቶ ሮቤል አሳስበዋል።

የኢትዮጵያ ፌደራል ጠበቆች ማህበር  የስራ አስፈፃሚ ኮሚቴ እና የፕሬዚደንት ምርጫ ውጤት***************************ዛሬ በኤሊያና ሆቴል በተደረገው የስራ አስፈፃሚ ኮሚቴ እና የ...
13/12/2025

የኢትዮጵያ ፌደራል ጠበቆች ማህበር የስራ አስፈፃሚ ኮሚቴ እና የፕሬዚደንት ምርጫ ውጤት
***************************
ዛሬ በኤሊያና ሆቴል በተደረገው የስራ አስፈፃሚ ኮሚቴ እና የፕሬዚደንት ምርጫ ውጤት ታውቋል::

በዚህም ለስራ አስፈፃሚ ኮሚቴ

1. አቶ ዳዊት ኪዳኔ
2. አቶ ነብዩ ምክሩ
3. ወ/ሮ ጀሚላ ክብረት
4. ወ/ሮ ቤዛ ንጉሴ
5. አቶ ሰውበሰው አድማሱ
6. አቶ ቀለመወርቅ ሚደቅሳ
7. አቶ ሄኖክ ቻላ

ለፕሬዝዳንት እና ም/ፕሬዝዳንት

1. አቶ ተስፍዬ ደረሰ ፕሬዝዳንት
2. ወ/ሮ መሰረት አያሌው ም/ፕሬዝዳንት ሆነው ተመርጠዋል::

ድምፅ ቆጠራው በአሁኑ ወቅት ሙሉ በሙሉ ተጠናቋል:: የኢትዮጵያ ፌደራል ጠበቆች ማህበር ለአዳዲሶቹ ተመራጭ አመራሮች እንኳን ደስ አላችሁ መልካም የስራ ዘመን ይመኛል::

የኢትዮጵያ ፌደራል ጠበቆች ማህበር
ታህሳስ 04 ቀን 2018ዓ.ም
አዲስ አበባ፤

13/12/2025
"ጦርነትን ለማስወገድ እንሰራለን፣ ለሰላም ብለን የምንሸጠው ግዛት ግን የለም" _  ጀነራል ታደሰ ወረደየትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር ፕሬዝደንት ጀነራል ታደሰ ወረደ ይህን ያሉት 'የትግራይን ህ...
13/12/2025

"ጦርነትን ለማስወገድ እንሰራለን፣ ለሰላም ብለን የምንሸጠው ግዛት ግን የለም" _ ጀነራል ታደሰ ወረደ

የትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር ፕሬዝደንት ጀነራል ታደሰ ወረደ ይህን ያሉት 'የትግራይን ህልውና እና ደህንነት ለማረጋገጥ!' በሚል መሪ ሃሳብ ከታኅሣሥ 02/2018 ዓ.ም ጀምሮ ለሦስት ቀናት ሲካሄድ በቆየው የትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር የአመራር አቅጣጫዎች፣ እቅዶች እና አፈጻጸም ላይ ከክልል፣ ከዞንና ከወረዳ ከፍተኛ አመራሮች ጋር ባደረጉት ስብሰባ ላይ ነው።

ትግራይ በተለያዩ ዘርፎች እጅግ በጣም አስቸጋሪ እና ጫና የበዛበት ሁኔታ ውስጥ ትገኛለች ያሉት ፕሬዝደንት ታደሰ ወረደ፣ ያለን ምርጫ እነዚህን ተግዳሮቶች ተቋቁመን መውጣት ነው ብለዋል። በተለያዩ መንገዶች እገዳው እንዲጨምር እና እንዲወሳሰብ የሚያደርጉ ብዙ እንቅስቃሴዎች አሉ፤ በመሆኑም የአደጋው መጠን ከፍተኛ ነው ብለዋል።

ውስጣዊም ሆነ ውጫዊ አደጋ ከጊዜ ወደ ጊዜ እየጨመረ ይሄዳል፣ በመንግስታዊ አገልግሎት ላይ ያለው ጫና መጨመሩ፣ በፍትህ እና ዳኝነት ላይ ያለው ውስብስብ ችግር፣ ያለን ደካማ ኢኮኖሚ፣ ስርአታዊ የሚመስል የሙስና ችግር፣ ተጠናክሮ የሚቀጥለው እገዳ እና በውስጣችን ሆነው የሚሰሩ አካላት በመጨመራቸው የተጋላጭነታችን መጠን በእጥፍ እንዲጨምር አድርጎታል ሲሉ ጀነራል ታደሰ ወረደ ተናግረዋል።

በተጨማሪም ጀነራል ታደሰ ወረደ እንዳሉት ደግሞ "ተቸገርኩ ብለህ ብትጮህ የሚሰማህ በሌለበት ዓለም አቀፍ ሁኔታ ውስጥ ነው ያለነው። ሀገራት የራሳቸውን ፍላጎት የሚያስቀድሙበት፣ ብትሞትም የሚሰማህ በሌለበት እና ለሰብአዊነት የሚሰጠው ትኩረት በቀነሰበት ዓለም አቀፍ ሁኔታ ውስጥ እንገኛለን" ብለዋል። ለዚህ መፍትሄውም በውስጣችን በምንፈጥረው አቅም ነው ሲሉ ፕሬዝደንት ታደሰ ገልጸዋል።

አደጋዎችን ተሸክሞ በማይቀጥልበት ሁኔታ ውስጥ ነው ያለነው፤ እነዚህንም መፍታት የምንችለው አንድ በመሆን፣ በመረጋጋት እንዲሁም በራሳችን አቅም ብቻ ነው ያሉት ጀነራል ታደሰ ወረደ፣ አንድ ከሆንን እና አቅም ከገነባን የመሰማት አቅማችንና የመደራደር አቅማችን ከፍ ያደርጋል ብለዋል።

በተጨማሪም ጀነራል ታደሰ ወረደ የበጋን መምጣት በመጠበቅ እና የመኸርን ምርት መጨመር በመምከር የሚለካ የኢኮኖሚ ጥንካሬ የለም ያሉ ሲሆን፣ ጠንካራ አቅም የሚኖረው ጠንካራ ኢኮኖሚ ሲገነባ እና በዝናብ ላይ ጥገኛ ያልሆነ ኢኮኖሚ ሲገነባ ነው ብለዋል።

ከጎረቤት ክልሎችና ከፌደራል መንግስት ጋር ያለውን ግንኙነት በአግባቡ እንሰራበታለን ያሉት ፕሬዝደንት ታደሰ፣ የሚኖረንና የምንፈጥረው ግንኙነት ግን በአቻ ለአቻ መርህ፣ በራስ መተሳሰርና መደጋገፍ ላይ የተመሰረተ መሆን አለበት ብለዋል።

በጊዜያዊ አስተዳደር ፕሬዝደንት ጀነራል ታደሰ የቀረበው የትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር የአመራር አቅጣጫዎች እና እቅዶች ሰነድ ላይ ውይይት ተደርጎበት ለተነሱ ጥያቄዎችና አስተያየቶች ምላሽ ከተሰጠ በኋላ ቀጣይ የአመራር አቅጣጫዎችና አፈጻጸማቸው ተብራርተው በሙሉ ድምፅ ጸድቆ ለሦስት ቀናት ሲካሄድ የቆየው መድረክ ዛሬ ታኅሣሥ 04/2018 ዓ.ም ተጠናቋል።

የፕሬዝደንቱ ጽሕፈት ቤት
ታኅሣሥ 04/2018 ዓ.ም

የአውሮፓ ህብረት "በኢትዮጵያና ኤርትራ መካከል የተፈጠረው ውጥረት አሳስቦኛል" አለ !የኢትዮጵያና የኤርትራ “ሉዓላዊነት፣ ነጻነትና የግዛት አንድነት እንዲከበር” ብሪታኒያና ቱርክን ጨምሮ አም...
13/12/2025

የአውሮፓ ህብረት "በኢትዮጵያና ኤርትራ መካከል የተፈጠረው ውጥረት አሳስቦኛል" አለ !

የኢትዮጵያና የኤርትራ “ሉዓላዊነት፣ ነጻነትና የግዛት አንድነት እንዲከበር” ብሪታኒያና ቱርክን ጨምሮ አምስት ሀገራት በጋራ ጥሪ አቀረቡ። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድና ፕሬዝደንት ኢሳያስ አፈወርቂ በሐምሌ 2010 በተፈራረሙት “የሰላም ሥምምነት መንፈስ ማንኛውም ውጥረት ወይም አለመግባባት በሰላምና በዲፕሎማሲያዊ መንገድ እንዲፈታ” ጠይቀዋል።

የካናዳ፣ ጃፓን፣ ኖርዌይ፣ ቱርክና ብሪታንያ መንግሥታት ጥሪውን ያቀረቡት የአልጀርስ ሥምምነት የተፈረመበትን 25ኛ ዓመት በማስመልከት ትላንት አርብ ባወጡት መግለጫ ነው።

ሀገራቱ በ1993 የቀድሞው ጠቅላይ ሚኒስትር መለስ ዜናዊና ፕሬዝደንት ኢሳያስ አፈወርቂ በአልጀርስ የተፈራረሙትን ሥምምነት፣ ሥምምነቱ የሚያራምዳቸውን መርሆዎችና በሥምምነቱ የተቋቋመው ኮሚሽን የወሰናቸውን ድንበሮች እንደሚደግፉ በጋራ መግለጫቸው ጠቁመዋል።

የአውሮፓ ኅብረት “የአልጀርስ ሥምምነትንና በድንበር ኮሚሽኑ የተወሰነውን” የኢትዮጵያና የኤርትራ ድንበር “ሙሉ በሙሉ” እንደሚደግፍ አስታውቋል።

በ1993 በአልጀርስ እንዲሁም በ2010 በአስመራ በተፈረሙት ሥምምነቶች መሠረት ኢትዮጵያና ኤርትራ አንዳቸው የሌላቸውን “ሉዓላዊነት፣ ነጻነትና የግዛት አንድነት” እንዲያከብሩ የአውሮፓ ኅብረት ጥሪ አቅርቧል።

ሁለቱም ወገኖች “ማንኛውንም ውጥረት ወይም አለመግባባት በሰላማዊና በዲፕሎማሲያዊ መንገድ እንዲፈቱ” ጥሪ ያቀረበው የአውሮፓ ኅብረት፤ “ይህ ለቀጠናው መረጋጋት ቁልፍ” እንደሆነ አሳስቧል።

ሀገራቱ የአልጀርስ ሥምምነትን በማስታወስ ያወጧቸው መግለጫዎች በኢትዮጵያና በኤርትራ መካከል ያለው ውጥረት እንዳሳሰባቸው የሚጠቁሙ ናቸው።

Via DW

አሜሪካ በኢትዮጵያ ያለው ሁኔታ መሻሻሉን በመጥቀስ ለኢትዮጵያ ዜጎች ሰጥታ የነበረውን ጊዜያዊ ከለላ አነሳችየዩናይትድ ስቴትስ የሀገር ውስጥ ደህንነት ቢሮ የኢትዮጵያውያን ጊዜያዊ ከለላ አሰራር...
13/12/2025

አሜሪካ በኢትዮጵያ ያለው ሁኔታ መሻሻሉን በመጥቀስ ለኢትዮጵያ ዜጎች ሰጥታ የነበረውን ጊዜያዊ ከለላ አነሳች

የዩናይትድ ስቴትስ የሀገር ውስጥ ደህንነት ቢሮ የኢትዮጵያውያን ጊዜያዊ ከለላ አሰራር ማብቃቱን አስታውቋል።

ይህ ውሳኔ እ.ኤ.አ. በ2022 ከለላው ለመጀመሪያ ጊዜ ከተሰጠበት ጊዜ አንስቶ ህጋዊ የሆኑ ኢትዮጵያውያን በዩናይትድ ስቴትስ ውስጥ በሕጋዊ መንገድ እንዲኖሩና እንዲሠሩ ሲያስችላቸው የነበረውን ከለላ የሚያቋርጥ ነው ተብሏል።

የአሜሪካ የአገር ውስጥ ደህንነት ሚኒስትር ክርስቲ ኖኤም በዚህ ሳምንት በሰጡት መግለጫ ውሳኔው “የአገሪቱን ሁኔታ በጥንቃቄ ከመረመረ” በኋላ የተላለፈ መሆኑን ገልጸዋል።
አክለውም በኢትዮጵያ ውስጥ ያሉት ሁኔታዎች ጊዜያዊ ከለላ ሥር የመቆየት መብትን ለማራዘም የሚያስፈልገውን “የሕግ መስፈርት አያሟሉም” በማለት ደምድመዋል።

የዩናይትድ ስቴትስ የዜግነትና የስደተኞች አገልግሎት (USCIS) ቃል አቀባይ ጊዜያዊ ከለላ ሥር የመቆየት መብት የሚሰጠው ለተወሰነ ጊዜ ብቻ መሆኑን ጠቅሰው፣ ለዘለቄታው ለመኖር የሚያስችል መብት ማግኛ ፈቃድ እንዲሆን ፈጽሞ አልታሰበም ብለዋል። አክለውም፣ “በኢትዮጵያ ውስጥ ያሉት ሁኔታዎች ወደ ሀገራቸው ለሚመለሱ ኢትዮጵያውያን ደኅንነት አደጋ የሚያስከትሉ አይደሉም” ሲሉ ተናግረዋል።

Via Addis standard

"ሴትን ልጅ ከአባቷ በላይ ሊያፈቅራት የሚችል ወንድ ካሳየኸኝ መሬት ላይ የሚኖር አሳ አሳይሀለሁ" !..አሜሪካ ሀገር  ውስጥ ነው።.... አባት  የ4አመት ህፃን ልጁን ለማዝናናት ወደ ልጆች ...
13/12/2025

"ሴትን ልጅ ከአባቷ በላይ ሊያፈቅራት የሚችል ወንድ ካሳየኸኝ መሬት ላይ የሚኖር አሳ አሳይሀለሁ" !
..አሜሪካ ሀገር ውስጥ ነው።.... አባት የ4አመት ህፃን ልጁን ለማዝናናት ወደ ልጆች ጌም መጫወቻ መኪና እየነዳ እየወሰዳት እያለ በአንድ ሰካራም ሹፌር ከኋላ ከባድ ግ''ጭት ይደርስበታል...

የ4አመት ልጁ ከኋላ ስለነበረች በግጭቱ ተጎድታ ጭንቅላቷ አካባቢ ደ''ም ይፈሳታል...አባቷም በሁኔታው በመደናገጥ አምፑላንስ ይጠራና በአፋጣኝ ወደ ሆስፒታል ይወስዳታል።

ሆስፒታል ሲደርስ ዶክተሮቹ የተተ''ረተረውን የጭንቅላቷን ክፍል መስ''ፋት እንዳለባቸው ነግረውት በ1ሰአት ውስጥ ሰፍ''ተዋት ይጨርሱና ወደ ቤት ይሸኝዋቸዋል።

ቤታቸው ከገቡ በኋላ የ4አመት ልጁን እንቅልፏን ከአስተኛት በኋላ አባትየው የጭንቅላቷን ስፌት አይታ አይምሮዋ እንዳይረበሽ እና ሞራሏ እንዳይጎዳ ብሎ እሱም ጭንቅላቱን በተሰበረ በመስታወት ይቆርጥና ሆስፒታል ሄዶ ከታች ፎቶው ላይ በምታዩት በተመሳሳይ ሁኔታ ተሰፍቶ ይመጣል።

ይህም ተግባሩ የአለም ሚዲያዎች እንዳለ በአንድ ድምፅ ተስማምተው የአለማችን ምርጥ አባት የምል ስያሜን ሰጥተውታል።

የሴት ልጅ የመጀመሪያ እውነተኛ ፍቅረ''ኛዋ አባቷ ነው የሚባለውም ለዚህ ነው።

የአባት ትልቁ ድክመቱ መውደዱን በቃላት አለመግለፁ ሲሆን ጠንካራ ጎኑ ግን መውደዱን ፍቅሩን በድርጊት ማሳየቱ ነው።

ፈጣሪ ለሁሉም አባቶች ረጅም እደሜ ከጤና ጋር ይስጣቸው🙏❤️🙏

ከዚሁ መንደር የተገኘ

የእምዬን ለአበየ ማለት ይሄ ነው!ጋዜጠኛ ኤልያስ መሰረት ከ ኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር የ 500 ሚሊዮን የኦዲት ግኝት ተገኘ ብሎ አነጋጋሪ የተባለለትን ዜና ዘግቦ ነበር እውነታው ሲገለጥ ...
13/12/2025

የእምዬን ለአበየ ማለት ይሄ ነው!

ጋዜጠኛ ኤልያስ መሰረት ከ ኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር የ 500 ሚሊዮን የኦዲት ግኝት ተገኘ ብሎ አነጋጋሪ የተባለለትን ዜና ዘግቦ ነበር እውነታው ሲገለጥ ግን የኦዲት ግኝቱ ከኪሱ መገኘቱ ነው።

ቀደም ሲል በህወሃት ሊቀመንበር በሚመራው ተቋም የተገኘን የኦዲት ግኝት ኤልያስ መሰረት በዶ/ር በለጠ በሚያመራው ተቋም የተገኘ አስመስሎ ዘግቦ ጥሩ ተከታይ ዘንቦለታል ።ለጊዜውም ቢሆን ``መዘገብ እንደ ኤልያስ ነውጂ``ተብሎለታል።

ኤልያስ ጉዳዩን ከድርጅት ባለፈም ግለሰባዊ ማጥቂያ መሳሪያ አድርጎትም ነበር።የአሁኑን የሚኒስቴር ተቋም የሚመራው ሚኒሰትር ከመምጣቱ ከአመታት በፊት የነበረን የኦዲት ግኝት በአሁኑ የሚኒስቴር ተቋም የተፈፀመ አስመስሎ ያስጮኸበት መንገድ አስገራሚ ነበር።

በርግጥ ኤልያስ ጉዳዩን ከፍየሏ በላይ ያስጮኸው ``ሳልቀደም ልቅደም`` ብሎ ነው።ኤልያስ መሰረት ከዚህ ከ500ሚሊዮን ብር ምን ያክሉ ደርሶት እንደሆነ የሚያውቀው እሱና ሰጭው ነው።ኤልያስ የ ደብረጽዮንን የሙስና ተግባር ለመደበቅ ያን ያህል ርቀት የሄደው እሱም የጉዳዩ ተጋሪ ስለሆነ ነው።

በሚኒስትሩ ስለጉዳዩ በ NBC Ethiopia በዝርዝር ተብራርቷል። የሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ የኮሚኒኬሽን ክፍል በሰዓቱ እንዲህና መሰል አደናጋሪ መረጃዎችን ማጥራት ይችል ነበር።የሆነው ሆኖ ለሁሉም ጊዜ አለውና ዛሬ በዝርዝር ተገልጿል።

ሙሉ መረጃውን NBCEthiopia የዩቲዩብ ቻናል ላይ በመሄድ ማድመጥ ትችላላችሁ።ሌሎች በክፍል ሁለት የተዳሰሱ መረጃዎችንም ታገኛላችሁ።
📌 ዩቱዩብ፦ https://youtube.com/

ኪም ጆንግ ዑን ከሩሲያ የውጊያ ስምሪትየተመለሱ የኮሪያ  ወታደሮችን አወደሱ !የሰሜን ኮሪያው መሪ፣ በሩሲያ የኩርስክ ክልል ለ120 ቀናት የባሕር ማዶ ስምሪቱን አጠናቅቆ ለተመለሰው የጦር ምህ...
13/12/2025

ኪም ጆንግ ዑን ከሩሲያ የውጊያ ስምሪት
የተመለሱ የኮሪያ ወታደሮችን አወደሱ !

የሰሜን ኮሪያው መሪ፣ በሩሲያ የኩርስክ ክልል ለ120 ቀናት የባሕር ማዶ ስምሪቱን አጠናቅቆ ለተመለሰው የጦር ምህንድስና ክፍል በተዘጋጀ የአቀባበል ሥነ–ስርዓት ላይ ተገኝተዋል።

ወታደሮቹ በሩሲያ "የውጊያና የምህንድስና ተልዕኮዎችን" ሲያካሂዱ "ጀብዱ" በማሳየታቸውና ከገዥው ፓርቲ የተሰጣቸውን ትዕዛዝ በመፈጸማቸው ተወድሰዋል ተብሏል፡፡

ቻይና ክብረ–ወሰን የሰበረውን ግዙፉን ጂዩቲያን ሰው አልባ አውሮፕላን ይፋ አደረገች !ፕሮጀክቱን የሚመራው የቻይና አቪዬሽን ኢንዱስትሪ ኮርፖሬሽን እንዳስታወቀው፣ የድሮኑ የሲቪል ተግባራት የሚ...
13/12/2025

ቻይና ክብረ–ወሰን የሰበረውን ግዙፉን ጂዩቲያን ሰው አልባ አውሮፕላን ይፋ አደረገች !

ፕሮጀክቱን የሚመራው የቻይና አቪዬሽን ኢንዱስትሪ ኮርፖሬሽን እንዳስታወቀው፣ የድሮኑ የሲቪል ተግባራት የሚከተሉትን ያካትታሉ፡-

🔹ለአደጋ ጊዜ ምላሽ መስጠት
🔹መልክዓ ምድራዊ ቅኝት ማካሄድ
🔹የደን ቃጠሎን መከታተል

(ስፑትኒክ)

የአለማችን ሀብታም ደራሲያን እና ሀብታሙ አለባቸውአሜሪካዊው የልብወለድ ደራሲ ስቲቭን ኪንግ ፡  በሚሰራበት ልብስ ማጠቢያ ድርጅት ፡  ከፋብሪካ ፡ ከሆስፒታሎችና ከተለያዩ ቦታዎች ተሰብስበው ...
13/12/2025

የአለማችን ሀብታም ደራሲያን እና ሀብታሙ አለባቸው

አሜሪካዊው የልብወለድ ደራሲ ስቲቭን ኪንግ ፡ በሚሰራበት ልብስ ማጠቢያ ድርጅት ፡ ከፋብሪካ ፡ ከሆስፒታሎችና ከተለያዩ ቦታዎች ተሰብስበው የሚመጡለትን ልብሶች ቀኑን ሙሉ ሲያጥብ ፡ ሲያጣጥፍ ፡ ሲተኩስ ይውልና ፡ ማታ ቤት ሲገባ የተገኘውን ቀማምሶ ፡ ከማርጀቱ የተነሳ መዛግ በጀመረው ታይፕራይተር ሲፅፍ ያመሻል ።

ኪንግ በዚህ መልኩ ልብስ እያጠበ በከባድ ስራ ውስጥ ቢያሳልፍም ፡ በሚያገኘው ደሞዝ ለቤተሰቡ የሚያስፈልገውን መሠረታዊ ነገር እንኳን ማሟላት ባለመቻሉ ፡ በትርፍ ጊዜው በትምህርት ቤቶች ስነ ፅሁፍ ያስተምር ነበር ።...

እንደዛም ሆኖ ግን የሚገኘው ገንዘብ ከምግብ ተርፎ አደለም ለሌላ ለዳይፐር እንኳን ሊበቃ አይችልም ፡ ስለዚህ የስቲቭን ኪንግ ባለቤት ታቢታ ፡ ለልጆቿ ዳይፐር የምታደርገው ቤት ውስጥ በምታዘጋጀው ጨርቅ ነበር ።

እና በዚህ መልኩ ያዘጋጀችው ዳይፐር አንድ ጊዜ ተጠቅሞ የሚጣል ሳይሆን ፡ መልሳ እያጠበች ትጠቀምበት ነበር ።.....

በዚህ ሁኔታ ውስጥ እያሉ ፡ አንድ ቀን ይህች ሚስቱ ታቢታ ፡ በቆሻሻ መጣያቸው ውስጥ ብዙ ገጾች ያሉት ጥራዝ ትመለከታለች ።
ታቢታ ይህን በታይፕ የተጻፈ ጥራዝ እንዳየች ወደ ቤት ይዛው ገብታ አነበበችው ።.......
ባለቤቷ ስቲቭን ከስራ እንደመጣም ከቆሻሻ መጣያ ውስጥ ያገኘችውን ፅሁፍ እያሳየችው ፡ ይህኮ የሚገርም መፅሀፍ ነው ፡ ለምን እንደጣልከው አልገባኝም ፡ አለችው ።.....
ኪንግ አይረባም ፡ አይሆንም ብሎ ቆሻሻ መጣያ ውስጥ የወረወረውን መፅሀፍ በሚስቱ ታቢታ ግፊት ለመጨረስ ይፅፍ ጀመር ።
.....
ከጥቂት ጊዜያት በኋላም ይህንን መፅሀፍ ጨርሶ ለአሳታሚዎች አሳያቸው ።
ካሪ የሚል ርእስ የሰጣት ይህች ስራው መፅሃፍ ተፅፎ ገንዘብ ማግኘት እንደሚቻል ለሱ ያረጋገጠችለት መፅሀፍ ሆነች ። ስቲቭን ኪንግ ከቆሻሻ ውስጥ ተገኝቶ በታተመው መፅሀፉ ባገኘው ገንዘብ ብዙም ባይሆን ከባሰ ድህነት አውጥቶ ለመጀመሪያ ጊዜ የተሻለ መኪና፣ የተሻለ ቤት እና ከሁሉም በላይ የመጻፍ ነፃነት አገኘ።.....

በካሪ መፅሀፍ ባገኘው ተቀባይነት የመጻፍ ሞራሉ የተነቃቃው ስቲቭን ኪንግ በየጊዜው ማሳተም ጀመረ ።
......
ብዙም ሳይቆይ ድህነትን ረሳው ፡ እሱና ቤተሰቡ የቅንጦት ህይወትን መኖር ጀመሩ ።
ዘመናዊ ቪላ ፡ አዳዲስ መኪኖች ፡ ምርጥ የሚባል ህይወት ጋር ተላምደው ህይወትን እንደ አዲስ ማጣጣም ለመዱ ።.....
የስቲቭን ኪንግ መፅሃፎች ወደ ፊልም እየተቀየሩ የአመት ገቢው በሚሊዮኖች የሚቆጠር መሆን ጀመረ ።

በዛች መፅሀፍ የተነሳሳው ኪንግ ከዛን ጊዜ ጀምሮ እስካሁን ከስልሳ በላይ የልብወለድ መፅሀፍትና 2 መቶ አጫጭር ታሪኮችን ለህትመት ያበቃ ሲሆን ፡ እነዚህ ስራዎቹም በ40 የተለያዩ ቋንቋዎች ተተርጉመው ከ350 ሚሊየን ኮፒ በላይ ተሽጦለታል ።

ባለቤቱ ታቢታ በአንድ ወቅት ለልጆቿ የዳይፐር መግዣ አጥታ ጨርቅ አጥባ እንዳልተጠቀመች ፡ አሁን ላይ መኪና ቀያይራ የምትነዳ የፈለገችውን ልብስ ፡ ያማራትን ጌጥ መግዛት የምትችል ሴት ሆነች ።....
በአንድ ወቅት ፡ የሆስፒታል አንሶላ ፡ የፋብሪካ ቱታ ሲያጥብ የነበረው ስቲቭን ኪንግ ህይወት ማለት ለካ እንደዚህ ነው እስኪል ድረስ ላይፍን ማጣጣም ጀመረ ።.....

ስቲቭንና ቤተሰቡ ከዛን ጊዜ በኋላ አደለም መልሶ ከድህነት ጋር ሊገናኙ ፡ ጭራሽ የሀብቱ መጠን ዝም ብሎ እየጨመረ ፡ አሁን ላይ ከአምስት መቶ ሚሊየን ዶላር በላይ ሀብት ያለው ሰው ሆኗል ።.........

ኪንግ ፡ በአለም ዙሪያ ከሚወደዱ ምርጥ ፊልሞች መካከል አንዱ የሆነው The Shawshank Redemption የተባለውን ፊልም ጨምሮ ከ 50 በላይ ፊልሞችን ፅፏል ። ....
በሰለጠኑት ሀገራት ፡ የሰው ንባብ ልማድ ከፍተኛ በመሆኑ ፡ ደራሲያን በአንድ ወቅት በአስከፊ ድህነት ውስጥ ቢያልፉ እንኳን ፡ በርትተው ከጻፉና አንድ ጊዜ የህትመት ገበያውን ከተቀላቀሉ ፡ ዳግም አይቸገሩም ። ............

ይህንን ስንፅፍ ፡ ሰሞኑን በፌስቡክ ያየነው የደራሲ ሀብታሙ አለባቸው ነገር ትዝ እያለን ነው ።
ይህ ታላቅ ደራሲ ፡ የሱፍ አበባ ፣አውሮራ ፣ የቄሳር እንባ፣ ታላቁ ተቃርኖ ፣ አንፋሮ፣ ሕንፍሽፍሽ ፣ አስኳላ እና ጉልጥምት የሚል ርእስ ያላቸውን ታዋቂ የሆኑ መፅሀፍትን ለአንባቢያን ያቀረበ ሰው ነው ።

እርግጥ ነው የእኛና የሌሎች ሀገራት የንባብ ባህልና የመፅሀፍ ሽያጭ ሊነጻጸር ባይችልም ፡ አሁን ባለው በሀገራችን ሁኔታ እንኳን ሀብታሙ አለባቸው ካበረከታቸው ስራዎች አንጻር ፡ ጥሩ ህይወት ሊኖር የሚገባው ሰው ነበር ።

ሆኖም ነገሩ ከዛ በተቃራኒ ሆኖ ስምንት መፅሀፍትን የሰጠን ይህ ታላቅ ደራሲ እጅ እንዳጠረው መስማት የሚያሳዝን ነገር ነው ።

ይህ ነገር ከተሰማ በኋላ በቅርብ ወዳጆቹ አስተባባሪነት እርሱን ለመርዳት የገቢ ማሰባሰብ ዘመቻ እንደተጀመረ ሰምተናል ። እናም ቢያድለን ፡ የንባብ ባህላችን የዳበረ ቢሆን ፡ እንዲሁም በአሳታሚ ድርጅቶች በኩል ያለው አወዛጋቢና ፡ ተገቢ ያልሆነ የተጠቃሚነት ጉዳይ ቢስተካከል ኖሮ ሀብታሙን የመሰለ ሰው .... አደለም ለራሱ ለሰው መትረፍ ይችል ነበር ። ....
ስነ ፅሁፍ የአእምሮ ስራ እንደመሆኑ ይህ ሰው የተሻለ ህይወት ቢኖረው ብዙ እና አስገራሚ ስራዎችም ሊሰጠን ይችል ነበር ። ሆኖም አሁን ባለበት ሁኔታ ጥያቄው የመጻፍ መቻል ሳይሆን ፡ ከችግር መውጣት መቻል ሆኗል ። ይህ ሰው ሊታገዝ ይገባል ፡ አጋዦቹም ልንሆን የሚገባን እኛው ነን ፡ የቻልን ፡ የፈቀድን ሁሉ በምንችለው አቅም አለውህ እንበለው ፡

በ ዋሲሁን ተስፋየ

ጥያቄ፦ ስመጥር አትሌት ነህ። ገንዘብም አለህ። በውጭ ሀገር እንደምናውቀውም አትሌቶች ቅንጡ መኪኖችን ያሽከረክራሉ። አንተስ ውድ መኪና ለምንድነው የማትነዳው?ቀነኒሳ በቀለ፦ እውነት ለመናገር ...
13/12/2025

ጥያቄ፦ ስመጥር አትሌት ነህ። ገንዘብም አለህ። በውጭ ሀገር እንደምናውቀውም አትሌቶች ቅንጡ መኪኖችን ያሽከረክራሉ። አንተስ ውድ መኪና ለምንድነው የማትነዳው?

ቀነኒሳ በቀለ፦ እውነት ለመናገር በኛ ሀገር ''አለኝ...'' ብለህ ቅንጡ መኪና ይዘህ ለመውጣት ኅሊናህ አይፈቅድልህም። ምክንያቱም ከቤት ወጣ ብለህ እስከምትመለስ ምግብና ማደሪያ አጥቶ የሚለምንህ ብዙ ነው። በዚህ ሁኔታ አንተ ''አለኝ...'' ብለህ በዚህ ሕዝብ ላይ ''ልታይ... ልታይ'' ማለት ምን ያደርጋል?

አንድ አበባል አለ። ደሃ በበዛባት ሀገር ሀብታምም ደሃ ነው!

ታላቁ አትሌት ቀነኒሳ በቀለ በአንድ ወቅት በሚዲያ ካደረገው ንግግሩ የተቀነጨበ።

Address

Addis Ababa
00000

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Negarit - ነጋሪት posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to Negarit - ነጋሪት:

Share

Category