Negarit - ነጋሪት

Negarit - ነጋሪት Negarit is a digital social media platform, providing news, information, insiders leaks and analysis for Ethiopian people.

Negarit is an independent and non partisan digital social media platform designed to inform, inspire and engage the people of Ethiopia. Reaching people through high-standard, high-quality and high impact multimedia content available in different formats such as youtube, facebook, twitter and other social media formats. Negarit recognizes and appreciates the efforts that citizens make each day in b

uilding a better Ethiopia for all people. Negarit strives to empower disadvantaged groups such as women, youth and people with disabilities etc. Working within collaboration of all people to enlighten, educate and strengthen citizens in order to expose corruption and to create unity between neighboring countries.

“በመንግስት ላይ ተገቢውን ጫና ለመፍጠር ለምናደርገው ትግል መራጩ ህዝብ ከጎናችን እንድትቆሙ” ሲል የተቃዋሚ ፖለቲካ ፓርቲዎች ኮክሰ ጠየቀየ ኢትዮጵያ ተቃዋሚ ፓርቲዎች ኮከስ፤ በአገራችን ያን...
28/07/2025

“በመንግስት ላይ ተገቢውን ጫና ለመፍጠር ለምናደርገው ትግል መራጩ ህዝብ ከጎናችን እንድትቆሙ” ሲል የተቃዋሚ ፖለቲካ ፓርቲዎች ኮክሰ ጠየቀ

የ ኢትዮጵያ ተቃዋሚ ፓርቲዎች ኮከስ፤ በአገራችን ያንዣበበው አደጋ ለመቀልበስ ዘላቂ ሠላም እንዲሰፍንና መጪው ምርጫ ነጻ፣ ዲሞክራሲያዊና ተዓማኒ ይሆን ዘንድ “በገዢው ፓርቲ/መንግስት/ ላይ ተገቢውን ጫና ለመፍጠር ለምናደርገው ትግል መራጩ ህዝብ የምናቀርበውን ጥሪ እንድትከታተሉና ከጎናችን እንድትቆሙ” ሲል ጠየቀ።

የኦሮሞ ፌዴራሊስት ኮንግረስ (አፌኮ)፣ የኦሮሞ ነፃነት ግንባር (ኦነግ) እና የኢትዮጵያ ህዝቦች አብዮታዊ ፓርቲን (ኢሕአፓ) ጨምሮ ስምንት ፓርቲዎችን ያካተተው ኮክሱ ዛሬ ባወጣው መግለጫ፤ "ጥያቄዎቻችን ከፖለቲካ ጥያቄ ባሻገር የአገር-አድን ፣የህዝብ መድህንነት አጀንዳ ናቸውና፤ የሲቪል ማኅበረሰብ አባላት በሁሉም መድረኮች፣ በሙሉ አቅማችው ከፓርቲዎቹ ጎን እንዲሰለፉ” በማለት ጥሪ አቅቧል።

ፓርቲዎቹ፤ ከመጪው ምርጫ በፊት የቦርዱ “ሀጋዊ የአሰራርና ተቋማዊ ችግር እስካልተፈታ ድረስ ለምርጫ መዘጋጀት የሚለው ሀሳብ ትርጉም አልባ ይሆናል” ሲሉ አስጠንቅቀዋል። በእነዚህ ሁኔታዎቸ “ነጻና ፍትሃዊ ምርጫ ሊኖር አይችልም” ያለው መግለጫው፤ “እውነተኛ ሪፎርም ከሌለ በኢትዮጵያ ተኣማኒ፣ አካታች፣ ነጻና ዲሞክራሲያዊ ምርጫ ሊኖር አይችልም” ብሏል።
(አስ)

የጣሊያን ተቃዋሚ ፓርቲዎች በአሜሪካ-አውሮፓ ህብረት የንግድ ስምምነት ላይ ሜሎኒን ወቀሱበዛሬው ዕለት ተቃዋሚ ፖለቲከኞች የአውሮፓ ህብረት ከአሜሪካ ጋር የተስማማው የንግድ ስምምነት፣ በአውሮፓ...
28/07/2025

የጣሊያን ተቃዋሚ ፓርቲዎች በአሜሪካ-አውሮፓ ህብረት የንግድ ስምምነት ላይ ሜሎኒን ወቀሱ

በዛሬው ዕለት ተቃዋሚ ፖለቲከኞች የአውሮፓ ህብረት ከአሜሪካ ጋር የተስማማው የንግድ ስምምነት፣ በአውሮፓ ምርቶች ላይ የተጣለውን የ15% ታሪፍ ጨምሮ፣ በከፊል የጠቅላይ ሚኒስትር ጆርጂያ ሜሎኒ መንግስት የወሰደው አካሄድ ውድቀት ነው ሲሉ ተናግረዋል።

የመሀል-ግራኝ ዲሞክራቲክ ፓርቲ (ፒዲ) እንደገለጸው ሜሎኒ በአሜሪካ ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ እና በአውሮፓ መካከል ድልድይ የመሆን ሙከራዋ ከንቱ መሆኑን ያሳያል ብሏል።

የፒዲ ሴኔት አፈ-ቀላጤ ፍራንቼስኮ ቦቺያ “ትናንት በአውሮፓ ህብረት እና በአሜሪካ መካከል በታሪፍ ላይ የተፈረመው ስምምነት የአውሮፓ ለትራምፕ እጅ መስጠት ነው” ብለዋል።

“በአውሮፓ ምርቶች ላይ የ15% ታሪፍ በመጣሉ በመቶ ሺዎች የሚቆጠሩ ሰራተኞች ስራቸውን ሊያጡ ይችላሉ፣ እናም የእኛ የወጪ ንግድ አደጋ ላይ ነው።

750 ቢሊዮን ዶላር የአሜሪካ ጋዝ እንገዛለን፣ እናም 600 ቢሊዮን ዶላር በአሜሪካ ኢንቨስት ለማድረግ እንዲሁም የአሜሪካ የጦር መሳሪያዎችን ለመግዛት እንገደዳለን።

ይህ ስምምነት ‘ጥሩ’ ተብሎ ሊጠራ የሚችለው በጣሊያን ቀኝ እና በጆርጂያ ሜሎኒ ብቻ ነው።

ድልድዯ ሚሎኒ ስራቸወን አልተወጡም"በማለት ተችተዋል።

“ሜሎኒ በአውሮፓ እና በትራምፕ መካከል ያለው ስምምነት ዘላቂ እንደሆነ ታምናለች፣ ምንም እንኳን ዝርዝሩን እንደማታውቅ እና ኢንቨስትመንትና ጋዝ ግዥን በሚመለከት በሚነጋገሩበት ጊዜ ምን እንደሚነገር እንደማታውቅ በግልጽ ብትቀበልም” በማለት ።

“የት ነው የምትኖረው? ከ(የአውሮፓ ኮሚሽን ፕሬዝዳንት ኡርሱላ) ቮን ደር ሌየን ጋር የፈረመችውን ሌላ ሽንፈት ለመሸፈን በድጋሚ እየዋሸች ነው።

እናም እንደገና የጣሊያን ንግዶች እና የእኛ ‘በጣሊያን የተሰራ’ ብራንድ ዋጋ እየከፈሉ ነው።

የጦር መሳሪያዎች እና ትራምፕን ፍላጎት በመከተል የጣሊያንን ኢንዱስትሪ እንደ ታይታኒክ እያሰጠሙ ነው።

ይህ የአውሮፓ ኮሚሽን ጣሊያንን ወደ ታች እየወሰዳት ነው።” ሲሉም ተናግረዋል።
Ansa

በእስራኤል የሚገኙ ሁለት የሰብዓዊ መብት ተሟጋች ድርጅቶች "እስራኤል በጋዛ ላይ የዘር ማጥፋት ወንጀል እየፈጸመች ነው" አሉበእስራኤል የሚገኙ ሁለት አንጋፋ የሰብዓዊ መብት ተሟጋች ድርጅቶች ...
28/07/2025

በእስራኤል የሚገኙ ሁለት የሰብዓዊ መብት ተሟጋች ድርጅቶች "እስራኤል በጋዛ ላይ የዘር ማጥፋት ወንጀል እየፈጸመች ነው" አሉ

በእስራኤል የሚገኙ ሁለት አንጋፋ የሰብዓዊ መብት ተሟጋች ድርጅቶች የሆኑት በትሴለም (B’Tselem) እና 'ፒዚሽያንስ ፎር ሂውመን ራይትስ' እስራኤል በጋዛ በሚገኙ ፍልስጤማውያን ላይ "የዘር ማጥፋት ወንጀል እየፈፀመች ነው" ሲሉ አስታወቁ።

የሰብዓዊ መብት ተሟጋች ድርጅቶቹ ዛሬ ሐምሌ 21 ቀን 2017 ዓ.ም ባወጡት ሪፖርት እስራኤል ባለፉት ሁለት ዓመታት በተካሄደው ጦርነት መካከል በጋዛ የሚገኙ ንጹሃን ዜጎችን ፍልስጤማዊ በመሆናቸው ብቻ የጥቃት ኢላማ አድርጋቸዋለች ሲሉ ከሰዋል።

በዚህም በፍልስጤማውያን ላይ ከፍተኛ እና በአንዳንድ ሁኔታዎችም የማይጠገን ጉዳት ደርሷል ያሉት የመብት ተሟጋች ድርጅቶቹ፤ አያይዘውም የእስራኤል የምዕራባውያን አጋሮች ይህንን ድርጊት የማስቆም "ህጋዊና ሞራላዊ ግዴታ አለባቸው" ሲሉ ጥሪ አቅርበዋል።

ከተፈጸሙት ወንጀሎች መካከልም በአስር ሺዎች የሚቆጠሩ ሴቶች፣ ህፃናት እና አረጋውያን መገደላቸው፣ የግዳጅ መፈናቀልና የምግብ እጥረት፣ እንዲሁም የመኖሪያ ቤቶች እና የሲቪል መሠረተ ልማቶች መውደማቸው ፍልስጤማውያንን ከጤና አገልግሎት፣ ከትምህርት እና ከሌሎች መሰረታዊ መብቶች እንዲገፈፉ መንሰዔ መሆናቸው በሪፖርቱ ተመላክቷል።

የበትሴለም ዳይሬክተር የሆኑት ዩሊ ኖቫክ "እየተመለከትን ያለነው አንድን ቡድን ለማጥፋት ታስቦ በሰላማዊ ሰዎች ላይ የሚፈጸም ግልጽና ዓላማ ያለው ጥቃት ነው" ሲሉ ገልጸው፤ አፋጣኝ እርምጃ እንዲወሰድ ጥሪ አቅርበዋል።

ከተፈጸሙት ወንጀሎች መካከልም በአስር ሺዎች የሚቆጠሩ ሴቶች፣ ህፃናት እና አረጋውያን መገደላቸው፣ የግዳጅ መፈናቀልና የምግብ እጥረት፣ እንዲሁም የመኖሪያ ቤቶች እና የሲቪል መሠረተ ልማቶች መውደማቸው ፍልስጤማውያንን ከጤና አገልግሎት፣ ከትምህርት እና ከሌሎች መሰረታዊ መብቶች እንዲገፈፉ መንሰዔ መሆናቸው በሪፖርቱ ተመላክቷል።

የበትሴለም ዳይሬክተር የሆኑት ዩሊ ኖቫክ "እየተመለከትን ያለነው አንድን ቡድን ለማጥፋት ታስቦ በሰላማዊ ሰዎች ላይ የሚፈጸም ግልጽና ዓላማ ያለው ጥቃት ነው" ሲሉ ገልጸው፤ አፋጣኝ እርምጃ እንዲወሰድ ጥሪ አቅርበዋል።

አክለውም "የዘር ማጥፋት ሲካሄድ ምን መደረግ አለበት ብሎ እያንዳንዱ ሰው ራሱን መጠየቅ አለበት ብዬ አስባለሁ" ሲሉ ተናግረዋል።

ቀደም ሲል በርካታ ዓለም አቀፍ እና በፍልስጤም የሚንቀሳቀሱ ቡድኖች ጦርነቱን የዘር ማጥፋት ሲሉ የገለጹት ሲሆን ለአስርተ ዓመታት የመብት ጥሰቶችን ሲመዘግቡ ከቆዩት የሰብዓዊ መብት ድርጅቶች የወጣው ይህ ሪፖርት አስቸኳይ እርምጃ ለመውሰድ እና ጫና ለማሳደር አስተዋጽኦ እንደሚኖረው ዘ ጋርዲያንን ዋቢ አድርጎ የዘገበው አዲስ ስታንዳርድ ነው፡፡

በቅርቡ የሶማሌ ክልል ምክር ቤት ያፀደቀው መዋቅር አጎራባች በሆኑ የኦሮሚያ አካባቢዎች ተቋውሞ ማስነሳቱ ተነገረየክልሉ ምክር ቤት ባለፈው ሳምንት ባካሄደው መደበኛ ጉባኤ ውሳኔ ያስተላለፈባችው...
28/07/2025

በቅርቡ የሶማሌ ክልል ምክር ቤት ያፀደቀው መዋቅር አጎራባች በሆኑ የኦሮሚያ አካባቢዎች ተቋውሞ ማስነሳቱ ተነገረ

የክልሉ ምክር ቤት ባለፈው ሳምንት ባካሄደው መደበኛ ጉባኤ ውሳኔ ያስተላለፈባችው ጉዳዩች መካከል አድስ የዞን፣ የወረዳ እና ከተማ አስተዳደደር መዋቅር አንዱ ሲሆን ይሄንን ውሳኔ የተቃወሙ የህብረተሰብ ክፍሎች አደባባይ ወጥተዋል።

የሶማሌ ክልል በተለይም በአዲሱ አወቃቀር
የሞያሌ ከተማ (“የሶማሌ ክልል አካል የተባለውን”) ወደ ምክር ቤት መስተዳደር ደረጃ ለማሳደግ መወሰኑ የተቃወሞ አንደኛው ነጥብ እንደሆነ ተነግሯል።

የአካባቢው ምንጮች እንዳስታወቁት ለተቃውሞ የወጡ የህብረተሰብ ክፍሎች ትላንት የጀመሩት ተቃውሞ ዛሬም ቀጥሎ እስከ ቦረና ደርሷል።

የOMN ምንጮቹ እንዳስታወቁት በያቤሎ የተጀመረው ተቃውሞ እንደ ነጌሌ፣ ዱቡልቅ እና ሜጋ ባሉ ከተሞች መስፋፋቱን አሳውቀዋል።

በሌሎች የኦሮሚያ አካባቢዎች ህዝቡ ለተቃውሞ በዝግጅት ላይ መሆኑም ተጠቅሷል።

የራሺያ የህዝብ ብዛት በከፍተኛ ሁኔታ እየቀነሰ መሆኑን ተከትሎ ብዙ ለወለዱ ቤተሰቦች የገንዘብና የታክስ እፎይታ ድጋፍ ይደረጋል ተባለ ጉዳዩ ‹‹ብሄራዊ ህልውና›› በመሆኑ ሴቶች እስከ ስምንት...
28/07/2025

የራሺያ የህዝብ ብዛት በከፍተኛ ሁኔታ እየቀነሰ መሆኑን ተከትሎ ብዙ ለወለዱ ቤተሰቦች የገንዘብና የታክስ እፎይታ ድጋፍ ይደረጋል ተባለ

ጉዳዩ ‹‹ብሄራዊ ህልውና›› በመሆኑ ሴቶች እስከ ስምንት ልጆች እንዲወልዱ ይበረታታሉም ተብሏል ።

ራሺያ ከዩኩሬን ጋር እያደረገችው ባለው ጦርነት ሳቢያ የህዝብ ብዛቷ በከፍተኛ ሁኔታ ወደ ታች እያሽቆለቆለ መሆኑ ተገልጿል።

ይህ የተባለው በሀገሪቱ የስነ ህዝብ ብዛት አወቃቀር እና ጤና ላይ ያተኮረ ስብሰባ የሰራተኛ ሚኒስትሩ አንቶን ኮትያኮቭ ከፕሬዝዳንት ቭላድሚር ፑቲን ጋር ባደረጉበት ወቅት ነዉ፡፡

በውይይቱ ሚኒስትሩ በ2030 ራሺያ 11 ሚሊዮን አዲስ የስራ ሃይል ያስፈልጋታል ሲሉ አፅንኦት ሰጥተው ለፑቲን ተናግረዋል።

ኮትያኮቭ ይህ ቁጥር ያስፈለገው በተለያዩ ዘርፍ ላይ ያሉትን 10.1 ሚሊየን ለጡረታ የደረሱትን ለመተካት እና 8መቶ ሺህ የሚጠጉትን ደግሞ እንደ አዲስ ወደ ኢኮኖሚው ለማስገባት ነው ብለዋል።

እስከሚቀጥሉት አምስት ዓመታት የውልደት መጠን ማሳደግ ካልተቻለ ሀገሪቱ ለከፍተኛ የሰራተኛ ሃይል ችግር ትጋለጣለች ሲሉ አስጠንቅቀዋል።

ሆኖም የወሊድ መጠንን ለመጨመር በሚደረገው ጥረት ዙሪያ የፑቲን የካቢኔ አባላት ትላልቅ ቤተሰቦች ላላቸው እንደ ገንዘብ እና የግብር እፎይታ ያሉ ማበረታቻዎችን ለመስጠት ተወያይተዋል።

በውይይቱ ወቅት የራሺያው ፕሬዚዳንት ቭላድሚር ፑቲን ፤የህዝብ ቁጥርን መጨመር ሀገራዊ ቀዳሚ ጉዳይ መሆኑን ገልፀው፣ ጉዳዩ ‹‹ብሄራዊ ህልውና›› በመሆኑ ሴቶች እስከ ሰምንት ልጆች እንዲወልዱ ይበረታታሉ ብለዋል።

እንደ ፈረንጆቹ አቆጣጠር በ2024 በሩሲያ ውስጥ ከ1999 ወዲህ የውልደት መጠን ወደ 1.22 ሚሊየን ዝቅ ብሏል የተባለ ሲሆን ፤ ሞት ደግሞ በ 3.3 በመቶ ጨምሮ ወደ 1.82 ሚሊዮን ማደጉን የባለስልጣኑ መረጃ ያሳያል።

የሩሲያ ህዝብ ባለፈው አመት 146 ሚሊዮን ገደማ ነበር ሲል የዘገበው ቢዝነስ ኢንሳይደር ነው።

የትግራይ ክልል አመራሮችና ፓለቲከኞች አሁንም በፍፁም ትዕግስትና ቻይነት የተጀመረውን ሰላም እንዲያፀኑና ከዳር እንዲያደርሱ ተማፅኖ ቀረበ።ተማፅኖ ያቀረቡት ከ12 ክልሎችና የከተማ አስተዳደሮች...
28/07/2025

የትግራይ ክልል አመራሮችና ፓለቲከኞች አሁንም በፍፁም ትዕግስትና ቻይነት የተጀመረውን ሰላም እንዲያፀኑና ከዳር እንዲያደርሱ ተማፅኖ ቀረበ።

ተማፅኖ ያቀረቡት ከ12 ክልሎችና የከተማ አስተዳደሮች የተውጣጡ የሃይማኖት አባቶችና የአገር ሽማግሌዎች ናቸው።

ቁጥራቸው 50 የሆኑት መላ የኢትዮጵያ ክልሎችና የከተማ አስተዳደሮች የወከሉ የሰላም ልኡካን ዛሬ ሀምሌ 21/2017 ዓ.ም ጠዋት መቐለ አሉላ አባነጋ አውሮፕላን ማረፍያ ሲደርሱ የጊዚያዊ አስተዳደሩ ከፍተኛ አመራሮች ፣ የሃይማኖት አባቶች ፣ የአገር ሽማግሌዎች ፣ ባለሃብቶችና ታዋቂ ሰዎች አቀባበል አድርገውላቸዋል።

ከአውሮፕላን ማረፍያ ውይይቱ ወደ ሚካሄድበት ቦታ ያቀኑት የሰላም ልኡካኑ ፕሬዜዳንት ሌ/ጄነራል ታደሰ ወረደና እና ካቢኔያቸው በተገኙበት በየእምነታቸው ፀሎት አድርሰዋል።

የክልሉ አመራሮችና ፓለቲከኞችም ለተሻለ ሰላምና አገራዊ መረጋጋት አሁንም በፍፁም ትዕግስትና ቻይነት ተጨማሪ ግጭት እንዲያስቀሩ አባታዊና ሃይማኖታዊ ምክርና ተማፅኖ ቀርበውላቸዋል።

የሰላም ልኡካኑ ከጦርነቱ በፊት ወደ ትግራይ ተመላልሰው ያደረጉት ጥረት ግጭቱ ማስቀረት ባለመቻሉ በቁጭት አስታውሰው ከፕሪቶሪያ የሰላም ስምምነት በኃላ ለሦሥተኛ ጊዜ መምጣታቸውና የሰላም ጥረታቸው ሳይታክቱ እንደሚቀጥሉ አረጋግጠዋል።

" የጀመረው ሰላም እንዲፀና ፤ ዳግም ጦርነት እንዳይቀሰቀስ ከመስራትና ከመጣር የበለጠ ሃይማኖታዊና አባታዊ ተልእኮ የለንም ለዚህም የሚከፈለውን ሁሉም ዓይነት መስዋእትነት እንከፍላለን " ብለዋል።

የሰላም ልኡካኑ ከትግራይ ጊዚያዊ አስተዳደርና ካቢኔያቸው ፣ የፐብሊክ ዲፕሎማሲ አባላት፣ የተፎካካሪ የፓለቲካ ፓርቲ አመራሮችና ስቪክ ማህበራት እንደሚወያዩ ከወጣው መርሀ ግብር ሐመረዳት ተችሏል።

ያልመከነ ተተኳሽ ፈንድቶ የሦሥት ህፃናት ህይወት ተቀጨሦሥቱ ወንድሟሟች የአንድ አባትና እናት ልጆች ናቸው።አደጋው ሀሞሌ 18/2017 ዓ.ም በትግራይ ሰሜናዊ ምዕራብ ዞን ታሕታይ ቆራሮ ወረዳ ...
28/07/2025

ያልመከነ ተተኳሽ ፈንድቶ የሦሥት ህፃናት ህይወት ተቀጨ

ሦሥቱ ወንድሟሟች የአንድ አባትና እናት ልጆች ናቸው።

አደጋው ሀሞሌ 18/2017 ዓ.ም በትግራይ ሰሜናዊ ምዕራብ ዞን ታሕታይ ቆራሮ ወረዳ ልዩ ስሙ ዓዲ መናብር ነው ያጋጠመው።

ህፃናቱ ለጨዋታ በተንቀሳቀሱበት መንደራቸው አጠገብ የሚገኘው ጫካ ውስጥ የወደቀ ሹል ድምቡልቡል ብረት ያገኛሉ።

የልጅ ነገር ሆኖባቸው ብረቱ በደንጋይ እየቀጠቀጡ ሳጫወቱ ፈንድቶባቸው ወድያውኑ ህይወታቸው አልፈዋል።

በትግራዩ ጦርነት ምክንያት በየቦታው ያሉ ያልመከኑ ተተኳሾት በሰውና እንስሳት ከፍተኛ ጉዳት በማድረስ ላይ መሆናቸው በተደጋጋሚ መረጃ ማካፈላችን ይታወሳል።

ዓለም አቀፍ የቀይ መስቀል ኮሚቴና የኢትዮጵያ ቀይ መስቀል ማህበር በትግራይ የተለያዪ ወረዳዎች የሚገኙ ያልመከኑ ተተኳሾች በማስወገድ ሰብአዊ ኃላፊነታቸው በመወጣት ላይ ቢገኙም ጦርነቱ ከተካሄደበት የቦታ የቆዳ ስፋት አንፃር በቂ እንዳልሆነ ይገለፃል።

ኢትዮጵያ በምግብ ራሷን ለመቻል የሰራችው ስራ የሚደነቅ ነው - አንቶኒዮ ጉቴሬዝየተባበሩት መንግስታት ዋና ጸሐፊ አንቶኒዮ ጉተሬዝ ኢትዮጵያ በምግብ ራሷን ለመቻል የሰራችው ስራ የሚደነቅ ነው ...
28/07/2025

ኢትዮጵያ በምግብ ራሷን ለመቻል የሰራችው ስራ የሚደነቅ ነው - አንቶኒዮ ጉቴሬዝ

የተባበሩት መንግስታት ዋና ጸሐፊ አንቶኒዮ ጉተሬዝ ኢትዮጵያ በምግብ ራሷን ለመቻል የሰራችው ስራ የሚደነቅ ነው አሉ።

ዋና ጸሐፊው በኢትዮጵያ አስተናጋጅነት በአዲስ አበባ እየተካሄደ በሚገኘው የተባበሩት መንግሥታት የምግብ ሥርዓት ጉባኤ ላይ የቪዲዮ መልዕክት አስተላልፈዋል።

በመልዕክታቸውም እንዳሉት፤ ኢትዮጵያ በምግብ ራሷን ለመቻል ሰፊ ስራ ሰርታለች።

በተለይም በስንዴ ልማት እና ለአየር ንብረት የማይበገር የግብርና ልማት ላይ ያስመዘገበችው ስኬት የምግብ ሉአላዊነትን ለማረጋገጥ ለተቀረው ዓለም እንደምሳሌ የሚወሰድ ስለመሆኑ ገልጸዋል።

የምግብ ስርዓትን ሚዛናዊነት ማመጣጠን እንደሚገባ ገልጸው፤ ሁሉም ባለድርሻዎች በትኩረት ሊይዙት እንደሚገባ አስገንዝበዋል።

በአየር ንብረት ላይ ተገቢውን ስራ መስራትና በዓለም ላይ ሰላምን ማረጋገጥ የምግብ ሉአላዊነትን ለማረጋገጥ ወሳኝ ነው ብለዋል።

ኢትዮጵያ ሁለተኛውን የተባበሩት መንግስታት የምግብ ስርዓት ጉባኤን ለማስተናገድ ላሳየችው ቁርጠኝነትም ምስጋና አቅርበዋል።

FBC

ታይላንድ እና ካምቦዲያ በአራት ቀናት ውጊያ በኋላ ለድርድር በማሌዥያ ለመገናኘት ተስማሙየታይላንድ እና ካምቦዲያ መሪዎች ለአራት ቀናት ሲካሄድ የቆየውን ድንበር ተሻጋሪ ውጊያ ለማስቆም በማሌዥ...
27/07/2025

ታይላንድ እና ካምቦዲያ በአራት ቀናት ውጊያ በኋላ ለድርድር በማሌዥያ ለመገናኘት ተስማሙ

የታይላንድ እና ካምቦዲያ መሪዎች ለአራት ቀናት ሲካሄድ የቆየውን ድንበር ተሻጋሪ ውጊያ ለማስቆም በማሌዥያ ለመገናኘት መስማማታቸው ተሰማ።

የሁለቱ ሀገራት መሪዎች ነገ ሰኞ በማሌዥያ ሊያደርጉት ባቀዱት ውይይት፣ በድንበር አካባቢ ለቀናት ሲካሄድ በቆየው ግጭት ምክንያት የተፈጠረውን ቀውስ በመፍታት ላይ እንደሚነጋገሩ ይጠበቃል።

ግጭቱ በሁለቱም ወገኖች በኩል የበርካታ ሰዎችን ህይወት ቀጥፎ ከ150,000 በላይ የሚሆኑ ሰዎችን ከመኖሪያ ቀያቸው አፈናቅሏል ተብሏል።

ይህ ስምምነት የተደረሰው የአሜሪካው ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ በሁለቱ ሀገራት መሪዎች መካከል ሽምግልና ካደረጉ በኋላ ነው። ሁለቱም ወገኖች ለግጭቱ መባባስ እርስ በእርስ ተወነጃጅለዋል።

 : የህወሀት ጦር ወደ ህዝብ መተኮስ ጀመረ‼️የዋጅራት 20ዓዲ ህዝብ የተቋውሞ ሰልፍ በማድረግ ላይ እያለ ፥ የደብረፅዮን እና ሞንጀሪኖ ተላላኪ ጦር ወደ ሰልፈኞች በመተኮስ ጉዳት አድርሷል። ...
27/07/2025

: የህወሀት ጦር ወደ ህዝብ መተኮስ ጀመረ‼️

የዋጅራት 20ዓዲ ህዝብ የተቋውሞ ሰልፍ በማድረግ ላይ እያለ ፥ የደብረፅዮን እና ሞንጀሪኖ ተላላኪ ጦር ወደ ሰልፈኞች በመተኮስ ጉዳት አድርሷል።

እስካሁን ከአከባቢው በደረሰን መረጃ መሰረት፥ የዋጅራት 20ዓዲ ምከትል አፈጉባኤ አቶ ደስታ ገብረዝጊ በደብረፅዮን እና ሞንጀሪኖ ተላላኪ ጦር መገደላቸውን ለማወቅ ተችሏል።

የቀድሞ ህወሓት በትግራይ ህዝብ ዘንድ እጅግ ተጠልቷል‼️

ግዕዝ ሚዲያ

ደቡብ አፍሪካ ከምዕራባውያን ተፅዕኖ ተላቀቀች !በBRICS ቡድን መስራቾች ብራዚል፣ ሩሲያ፣ ህንድ፣ ቻይና እና ደቡብ አፍሪካ የተመሰረተው NDB በአለም አቀፍ የገንዘብ ተቋም ደቡብ አፍሪካ ላ...
27/07/2025

ደቡብ አፍሪካ ከምዕራባውያን ተፅዕኖ ተላቀቀች !

በBRICS ቡድን መስራቾች ብራዚል፣ ሩሲያ፣ ህንድ፣ ቻይና እና ደቡብ አፍሪካ የተመሰረተው NDB በአለም አቀፍ የገንዘብ ተቋም ደቡብ አፍሪካ ላሉት ዋና ዋና የመሠረተ ልማት ፕሮጀክቶች የገንዘብ ምንጭ በፍጥነት የሚያገኙበት አማራጭ ይዞ ብቅ ማለቱ ተሰማ።

በምዕራባውያን ኃያላን ሀገራት ከመጠን በላይ የሆነ የበላይነት ለመታገል እ.ኤ.አ. በ2009 የተቋቋመውና
እንደ የዓለም ባንክ፣ የሰባት ሃያላን ቡድን ሀገራት (G7) እና የተባበሩት መንግስታት የፀጥታው ምክር ቤት ባሉ ዋና ዋና የባለብዙ ወገን ተቋማት ሀገራት የምዕራቡ ዓለም ጥገኛ እንዲሆኑ አድርጓል ሲል የሚደመጠው BRICS ደቡብ አፍሪካ ለመገንባት ላሰበቻቸዉ የትራንስፖርት አገልግሎቶች ብድር መፍቀዱን ቢዝነስ ኢንሳይደር አፍሪካ ዘግቧል ።

በደቡብ አፍሪካ ብሔራዊ መንገዶች ኤጀንሲ (SANRAL) በጆሃንስበርግ የብድር ስምምነቱ ሲፈረም እንደገለፀው ከሆነ ብድሩ ወሳኝ የትራንስፖርት መስመሮችን ለማሻሻል፣ ግንኙነትን ለማሻሻል፣ መጨናነቅን በመቀነስ እና በወሳኝ የኢኮኖሚ ኮሪደሮች ላይ ደህንነትን ወደ ማሳደግ እንደሚዉል ገልጿል ።

የSANRAL ዋና ሥራ አስፈፃሚ ሬጂናልድ ዴማና እንደተናገሩት ብድሩ በደቡብ አፍሪካ የግንባታ እና የትራንስፖርት ዘርፎች በጣም አስፈላጊ የሆነውን ካፒታል ያስገባል ። እንዲሁም የተቀላጠፈ የሸቀጦች እና የሰዎች ዝውውርን በማስቻል የስራ እድል ፈጠራን የሚደግፍ እና የሀገር ውስጥ ኢኮኖሚን ለማነቃቃት ያስችላል ብለዋል።

ኤጀንሲው በበኩለ ይህ ብድር በደቡብ አፍሪካ ከታየዉ ካለዉ የዓመታት ዝቅተኛ የኢንቨስትመንት ፍላጎት በኋላ እየጨመረ የመጣውን የትራንስፖርት ፍላጎት ለማሟላት ከሚደረገው ጥረት አንዱ አካል መሆኑን ጠቁሟል።

እንደሚታወቀው በባለብዙ ወገን ተቋማት ውስጥ በማደግ ላይ ያሉ የኢኮኖሚ አመለካከቶችን አንድ ግንባር ለመፍጠር ሙከራዎች እያደረገ የሚገኘውና 40% በላይ የአለም ኢኮኖሚ እና ከአለም ህዝብ ግማሽ ያህሉን ያቀፉ ሀገራችን በዉስጡ የያዘዉ BRICS እ.ኤ.አ. በ 2023 BRICS የመሪዎች ስብሰባ ላይ ግብፅና ኢትዮጵያን ጨምሮ ሌሎች ሀገራትን ወደ ቡድኑ የቀላቀለ ሲሆን በ2024 ባደረገው የመሪዎች ጉባኤ ላይም ቤላሩስ፣ ቦሊቪያ፣ ኩባ፣ ካዛኪስታን፣ ማሌዥያ፣ ናይጄሪያ፣ ታይላንድ፣ ኡጋንዳ እና ኡዝቤኪስታን “የአጋር አገሮች” ምደባ በመቀላቀል ተደራሽኘቱን እያሰፋ ይገኛል ።
ህብረቱ የአባላቱን ኢኮኖሚያዊ እና ዲፕሎማሲያዊ ፖሊሲዎች ለማስተባበር ፣ አዳዲስ የፋይናንስ ተቋማትን ለማግኘት እና በአሜሪካ ዶላር ላይ ጥገኝነትን ለመቀነስ እየሞከረ እንደሚገኝ በህብረቱ ድህረገጽ ያገኘነው መረጃ ያሳያል ።

በታዴ የማመይ ልጅ

27/07/2025

የአርሰናል አካዳሚ ሄልኢንድ Max Dowman የሚባል እጅግ አደገኛ የአጥቂ አማካይ አፍርቷል። ተመልከቱት

Address

Addis Ababa

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Negarit - ነጋሪት posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to Negarit - ነጋሪት:

Share

Category