A D I S M E L K

A D I S M E L K መረጃና ዜና ከተለያዩ ቦታዎች ያገኘናቸውን
በሰፌዳችን አበጥረን ለናንተ እናቀርባለን

ሚጠጠቅመንን ብቻ እንውሰድ በማይጠቅመን ጊዜ አናጥፋ

ተማሪ ኻሊድ በሽር የ12ኛ ክፍል ማጠቃለያ ፈተና 591  ውጤት ማምጣቱ ተገለፀ።  የትምህርት ሚኒስቴር ብርሃኑ ነጋ በዛሬው እለት በሰጡት መግለጫ በዘንድሮ ዓመት የ12ኛ ክፍል ማጠናቀቂያ ፈተ...
14/09/2025

ተማሪ ኻሊድ በሽር የ12ኛ ክፍል ማጠቃለያ ፈተና 591 ውጤት ማምጣቱ ተገለፀ።

የትምህርት ሚኒስቴር ብርሃኑ ነጋ በዛሬው እለት በሰጡት መግለጫ በዘንድሮ ዓመት የ12ኛ ክፍል ማጠናቀቂያ ፈተና ከተፈተኑ 585 ሺህ 882 ተማሪዎች መካከል 8.4 በመቶ የሚሆኑ ተማሪዎች 50 በመቶ ውጤት ማምጣታቸው ገልፀዋል::

ከተፈጥሮ ሳይንስ ተፈታኞች 11.4 በመቶ አንዲሁም ከማኅበራዊ ሳይንስ ተፈታኞች 5.2 በመቶ ማምጣታቸውን ተናግረዋል፡፡

ከፍተኛ ውጤት ያስመዘገበው ተማሪ ካሊድ በሽር በተፈጥሮ ሳይንስ ትምህርት 591 በማምጣት ከፍተኛ ውጤት አንዳስመዘገበ ተገልፆል::

የ12ኛ ክፍል ማጠናቀቂያ ፈተና ካስፈተኑ ትምህርት ቤቶች መካከል 1 ሺህ 249 የሚሆኑት ትምህርት ቤቶች አንድም ተማሪ አለማሳለፋቸውን ተገለፀ።

በተጨማሪም 50 ትምህርት ቤቶች ሙሉ በሙሉ ተማሪዎቻቸውን ማሳለፋቸው ታውቆል።

መግለጫው… በ2017 ፈተና ከወሰዱ 585 ሺህ 882 ተማሪዎች መካከል  48ሺ ዘጠኝ መቶ ሀያ ዘጠኝ ተማሪዎች የዩኒቨርስቲ መግቢያ ነጥብ ማስመዝገባቸዉን መግለጫዉን እየሰጡ የሚገኙት የትምህርት...
14/09/2025

መግለጫው…

በ2017 ፈተና ከወሰዱ 585 ሺህ 882 ተማሪዎች መካከል 48ሺ ዘጠኝ መቶ ሀያ ዘጠኝ ተማሪዎች የዩኒቨርስቲ መግቢያ ነጥብ ማስመዝገባቸዉን መግለጫዉን እየሰጡ የሚገኙት የትምህርት ሚኒስትር ፕሮፌሰር ብርሀኑ ነጋ ተናግረዋል፡፡

ካለፈዉ አመት ጋር ሲነፃፀር 12ሺ በላይ ተማሪዎች በተጨማሪ ማሳለፍ ተችሏል ብለዋል፡፡

ፈተናው በሁሉም ክልሎችና ከተማ አስተዳደሮች በተቋቋሙ 216 የመፈተኛ ማዕከላት በበይነ መረብ በአራት ዙር እንዲሁም በወረቀት በሁለት ዙር መሰጠቱ የሚታወስ ነው።

ዶ/ር ፍፁም አሰፋ የብሔራዊ ባንክ ገዢ ሆነው ተሾሙ!ዶ/ር ፍፁም አሰፋ በመንግሥት በተለያዩ የስልጣን ዘርፍ ያገለገሉ ሲሆን የብሔራዊ ባንክ ገዢ ከመሆናቸው በፊት የፕላንና ልማት ኮሚሽን ሚኒስ...
12/09/2025

ዶ/ር ፍፁም አሰፋ የብሔራዊ ባንክ ገዢ ሆነው ተሾሙ!

ዶ/ር ፍፁም አሰፋ በመንግሥት በተለያዩ የስልጣን ዘርፍ ያገለገሉ ሲሆን የብሔራዊ ባንክ ገዢ ከመሆናቸው በፊት የፕላንና ልማት ኮሚሽን ሚኒስተር እንደነበሩ ይታወቃል! የቀድሞ የብሔራዊ ባንክ ገዢ የነበሩ አቶ ማሞ ምህረቱ በገዛ ፍቃዳቸው ከስልጣን መልቀቃቸው እና የአፍሪካ ልማት ባንክ ምክትል ፕሬዚዳንት ሆነው መሾማቸው የሚታወስ ነው!

ለ ዶ/ር ፍፁም አሰፋ መልካም የስራ ዘመን እንዲሆን እንመኛለን።

አይ ዱንያ 😢😢በምስሉ ላይ የምትመለከቱት    (ሳታም አል-ፋይሃ )ይባላል በሀይል ከተማ ሳውዲ አረቢያ ነዋሪ ነው በ መልካም ስነ ምግባሩ እና በኢማኑ የታወቀ ሰው ነበር።ትላንት ይህ ሰው  ከ...
10/09/2025

አይ ዱንያ 😢😢
በምስሉ ላይ የምትመለከቱት (ሳታም አል-ፋይሃ )ይባላል በሀይል ከተማ ሳውዲ አረቢያ ነዋሪ ነው
በ መልካም ስነ ምግባሩ እና በኢማኑ የታወቀ ሰው ነበር።

ትላንት ይህ ሰው ከሚስቱና ከሰባት ወንዶችና ሴቶች ልጆቹ ጋር ሁሌ እንደሚኖረው ኖርማል ሒወት እየኖረ ነበር።

በመጨረሻ ሰአቶቹ ሁለት ነገሮች ነበረ ያደረገው ልጆቹን ሰላት ከመድረሱ በፊት በመናፈሻ ቦታ ተሰብስበው ሲጫወቱ የሚያሳይ ቪዲዮ ፓስት አርጓል፣ ከዛም በሚገርም ሁኔታ መሞቱ የታወቀው ይመስል በትዊተር ገፁ ላይ “ ” የሚል ፁሁፍ ለጠፈ ።

ከጥቂት ሰአታት በሗላ ከባድ የመኪና አደጋ አጋጥሟቸው እሱና ሰባቱ ወንድና ሴት ልጆቹ ህይወታቸው አልፏል። ሁሉም ሞቱ😢
አላህ ይዘንላቸው🤲

ዱንያ እንዲ ናት አለን ስንል ድንገት እልም የምንልባት ጠፊ አለም 🥹

ድንገት ለሚጠናቀቅ ህይወት ለአኼራችን ሚጠቅመንን እንስራ ዛሬን ለማደራችን ምንም ዋስትና የለንም እያንዳንዱን ጊዜ ለሞት ዝግጁ እንሁን ‼

اعْلَمُوا أَنَّمَا الْحَيَاةُ الدُّنْيَا لَعِبٌ وَلَهْوٌ وَزِينَةٌ وَتَفَاخُرٌ بَيْنَكُمْ وَتَكَاثُرٌ فِي الْأَمْوَالِ وَالْأَوْلَادِ ۖ كَمَثَلِ غَيْثٍ أَعْجَبَ الْكُفَّارَ نَبَاتُهُ ثُمَّ يَهِيجُ فَتَرَاهُ مُصْفَرًّا ثُمَّ يَكُونُ حُطَامًا ۖ وَفِي الْآخِرَةِ عَذَابٌ شَدِيدٌ وَمَغْفِرَةٌ مِّنَ اللَّهِ وَرِضْوَانٌ ۚ وَمَا الْحَيَاةُ الدُّنْيَا إِلَّا مَتَاعُ الْغُرُورِ

ቅርቢቱ ሕይወት ጨዋታና ዛዛታ፣ ማጌጫም፣ በመካከላችሁም መፎካከሪያ፣ በገንዘቦችና በልጆችም ብዛት መበላለጫ ብቻ መኾንዋን ዕወቁ፡፡ (እርሷ) በቃዩ ገበሬዎችን እንደሚያስደስት ዝናም፣ ከዚያም በቃዩ እንደሚደርቅና ገርጥቶ እንደምታየው፣ ከዚያም የተሰባበረ እንደሚኾን ብጤ ናት፣ በመጨረሻይቱም ዓለም ብርቱ ቅጣት ከአላህም ምሕረትና ውዴታ አልለ፡፡ የቅርቢቱም ሕይወት የመታለያ ጥቅም እንጅ ሌላ አይደለችም፡፡(ቁ57:20)
Hijra Tube ኢስላማዊ ድህረ ገፅ

10/09/2025

ግብፅ ህልውናዋን ለማስጠበቅ ሁሉንም አይነት እርምጃዎችን የመውሰድ መብቷ የተጠበቀ ነው" ለፀጥታው ምክር ቤት የፃፈችው ደብዳቤ፡፡ የህዳሴው ግድብ ዛሬ መመረቁን በተመለከተ የግብፅ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ለተመድ የፀጥታው ምክር ቤት በፃፉት ደብዳቤ ‹‹ኢትዮጵያ ግድቡን በማስመረቋ አለም አቀፍ ህግን ጥሳለች›› በማለት ገልፀው ግብፅ ለግድቡ እውቅና እንደማትሰጠው አስረድተዋል፡፡

እሷ እውቅና ባለመስጠቷም የተናጠል እርምጃ ተደርጎ እንደሚቆጠር ገልፀው ግድቡ ኢትዮጵያ በምስራቃዊ ጥቁር አባይ ወንዝ ላይ የማስተዳደር መብት እንደሚሰጣት አስታውቀዋል፡፡ ደብዳቤያቸው ሲቀጥልም ‹‹የአባይ ወንዝ የጋራ ንብረት ተደርጎ የሚቆጠር ነው›› ያለ ሲሆን ኢትዮጵያ ግድቡን የሰራችው ለልማት ሳይሆን ለፖለቲካዊ አጀንዳ እንደሆነም ጠቅሷል፡፡

ጨምሮም ‹‹ግብፅ በአባይ ውሀ ላይ የህልውና ስጋት ሲገጥማት አይኗን ጨፍና አትመለከትም፡፡ ኢትዮጵያም የአባይ ውሀ ሀብትን በበላይነት ለማስተዳደር እንድትችል አትፈቅድም፡፡ ስለዚህም ግብፅ በአለም አቀፍ ህግ መሰረት ህልውናዋን ለማስጠበቅ ሁሉንም አይነት እርምጃዎችን የመውሰድ መብቷ የተጠበቀ ነው›› በማለት ለፀጥታው ምክር ቤት ዛሬ የላከውን ደብዳቤ አጠቃሏል፡፡

የቀድሞ የኦሮሚያ ብ/ክ/መ ፕረዝደንትና የአገር መከላከያ ሚኒስትር አቶ ለማ መገርሳ መልዕክት====ቀን፡ ጳጉሜ 4, 2017በመላው የኢትዮጵያውያን ተሳትፎና ጥረት የተገነባው ታላቁ የህዳሴ ግድ...
09/09/2025

የቀድሞ የኦሮሚያ ብ/ክ/መ ፕረዝደንትና የአገር መከላከያ ሚኒስትር አቶ ለማ መገርሳ መልዕክት
====

ቀን፡ ጳጉሜ 4, 2017

በመላው የኢትዮጵያውያን ተሳትፎና ጥረት የተገነባው ታላቁ የህዳሴ ግድብ በመጠናቀቁ እንኳን ደስ አላችሁ: እንኳን ደስ አለን።
እያንዳንዱ ኢትዮጵያዊ ከትንሽ እስከ ትልቅ:ከደሃ እሰከ ሀብታም ይህንን ግድብ ለመገንባት የአቅሙን ያህል ሀብት በማዋጣት አሻራውን ያሳረፈበት ታሪካዊ ግድብ ነው። የአንድነታችን ተምሳሌት ነው። ከዚህ ግድብ በቀጥታ ከምናገኘው ጥቅም በላይ ታሪካዊ የምያሰኘው: መላው ኢትዮጵያዊ ሁሉ አንድ የሆነበትና በአንድነት በጋራ የማይደፈረውን ደፍሮ መስራቱ ነው። ይህም የሚያሳየው ስንከፋፈል ሳይሆን ስንተባበርና አንድ ስንሆን አትዮጵያውን የማንሠራው ድንቅና ደማቅ ታሪክ እንደሌለ ይህ የህዳሴ ግድብ የክፍለ ዘመኑ ህያው ምስክር ነው። ስለሆነም መላው ኢትዮጵያውያን ምንግዜም አንድነታችን የድላችን መሠረት መሆኑን በመገንዘብ ለነገይቱ የተሻለች ኢትዮጵያ: አንድነታችንን መጠበቅና ማጠናከር የግድ ይለናል።
ይህንን ታሪካዊ የህዳሴ ግድብ አስጀምረው በማጠናቀቅ ሂደት ውስጥ አስተዋጽኦ የነበራቸው የአገራችን መሪዎችና ባለሙያዎች ሁሉ እንደየድርሻቸውና አስተዋጽኦአቸው መጠን ምስጋና ይገባቸዋል። ከዚሁ ህዳሴ ግድብ ምርቃት ጎን ለጎን በየቀኑ ስለሚጠፋው የዜጎቻችን ህይወት:ስለሚፈሰው ደምና ስለምታነባው ኢትዮጵያዊ እናት: በጥቅሉ ስለአገራችን ሠላምና ደህንነት ቆም ብለን ልናስብበትና በጋራ መቋጫ ልናበጅለት ግድ ይለናል።

ለማ መገርሣ ዋቆ

ሳሊኒ ስለ ሕዳሴ ግድቡ ምን አሉ?“ኢትዮጵያ  ይህን ግድብ እንድትገነባ ማንም አልፈለገምከ15 ዓመታት በኋላ ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ እውን ሆነ ያሉት የጣሊያኑ ሳሊኒ (ዊ ቢውልድ) ኩባን...
09/09/2025

ሳሊኒ ስለ ሕዳሴ ግድቡ ምን አሉ?

“ኢትዮጵያ ይህን ግድብ እንድትገነባ ማንም አልፈለገም

ከ15 ዓመታት በኋላ ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ እውን ሆነ ያሉት የጣሊያኑ ሳሊኒ (ዊ ቢውልድ) ኩባንያ ስራ አስኪያጅ ፔትሮ ሳሊኒ፤ ግድቡን ለመገንባት የነበረውን ውጣ ውረድ እና የተከፈለውን ዋጋ ገልፀዋል።

“ለእኔና ለአገሪቱ ሕልማችን እውን ሆነ። ዛሬ ከዚህ በላይ እንዴት መኩራት ይቻላል?” ያሉት ሳሊኒ፤ ይህን ስኬት እውን ላደረጉ የግንባታውን ሠራተኞች ምስጋና አቅርበዋል።

የህዳሴግድብ ፕሮጀክትን “በዓለም በጣም ደኅንነት የነበረው ፕሮጄክት ነው” ያሉት ሳሊኒ፤ ሆኖም ግን ታላቅ ስኬቶች ዋጋ እንደሚከፈልባቸው ሁሉ በግድቡ ግንባታ ሂደት የሰው ዋጋ መከፈሉን አንስተዋል።

ፔትሮ ሳሊኒ ባለፉት 15 ዓመታት፤ 33 ሠራተኞች በመንገድ አደጋና በሌሎችም ሁኔታዎች ሕይወታቸውን እንዳጡ አስታውቀዋል። ለዚህ ስኬት ሕይወታቸውን ለሰጡ ሠራተኞች ያላቸውን ከበሬታ የገለፁት ሳሊኒ፤ ለቤተሰቦቻቸውም ትውስታቸው አይጠፋም ሲሉ መልዕክት አስተላልፈዋል።

ከ10 ሺህ በላይ ሰራተኞች ተቀይረው መስራታቸውን የጠቆሙት ሥራ አስኪያጁ፤ 250 ሺህ ሰዓታት ሠራተኞችን ስለ ደኅንነት ለማሰልጠን እንደዋለ ጠቅሰዋል። 25 ሺህ ወጣቶች በሥራ ላይ የአቅም ግንባታ ስልጠና እንደተሰጣቸው ጠቅሰው፤ ይህም ለአገሪቱ ወደፊት መሰረታዊ አበርክቶ ይኖረዋል ሲሉ በሙሉ ልብ ተናግረዋል።

የግድቡን መሠረት ካሳረፉትና በግድቡ ዙሪያ ሥማቸው በጉልህ ከሚነሳው ከቀድሞው ጠቅላይ ሚኒስትር መለስ ዜናዊ ጋር በቅርበት መስራታቸውን የተናገሩት ሳሊኒ፤ ከመለስ ዜናዊ ጋር ያደረጉትን ንግግርም ጠቅሰዋል።

“‘ለዚህ አገር ሕልም አለኝ፤ የተትረፈረፈ የኃይል ሉዓላዊነት። ዓባይ ላይ ፕሮጀክት ልትነድፍልኝ ትችላለህ? ታላቅ ፕሮጀክት፤ ቢያንስ ስድስት ሺህ ሜጋ ዋት የሚያመነጭ እፈልጋለሁ’ አለኝ። ፤በፍጥነት ስራው[አለኝ]’፤ ከአንድ ዓመት በኋላ ሕይወቱ አለፈ” በማለት የግድቡ ውጥን እንዴት እንደተጠነሰሰ ገልፀዋል።

ከኢትዮጵያ ጋር በግድብ ግንባታ እስከ ቤተሰባቸው ታሪካዊ ትስስር እንዳላቸው በስሜት የገለፁት ፔትሮ ሳሊኒ፤ ኢትዮጵያ በምን ያህል ፈተና ውስጥ ተከባ ሕዳሴን እንደገነባችም ዘርዝረዋል።

“አገሪቱ ይህን ግድብ እንድትገነባ ማንም አልፈለገም። ማንም ገንዘብ ለማቅረብ አልፈለገም። ብዙ ፖለቲካዊ ጉዳዮች፤ ብዙ ችግሮች [ነበሩ]፤ ቀላል መፍትሔ አልነበረም። ነገር ግን ኢትዮጵያዊያን ችግር ፈሪ አይደሉም። አይበገሬ ናቸው። መገዳደር ወይም ጠላት ሲገጥማቸው ጥረታቸውን በእጥፍ ይጨምራሉ፤ ማግኘት ያለባቸውን ያገኛሉ” ብለዋል።

ቢቢሲ

" ለመላው ኢትዮጵያውያን ወገኖቻችን እንኳን ለታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ምረቃ በዓል አደረሳችሁ" አሉ ቴድሮስ አድሃኖም (ዶ/ር)የዓለም ጤና ድርጅት ዋና ዳይሬክተር ቴድሮስ አድሃኖም (ዶ/...
09/09/2025

" ለመላው ኢትዮጵያውያን ወገኖቻችን እንኳን ለታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ምረቃ በዓል አደረሳችሁ" አሉ ቴድሮስ አድሃኖም (ዶ/ር)

የዓለም ጤና ድርጅት ዋና ዳይሬክተር ቴድሮስ አድሃኖም (ዶ/ር ) የዚህ አስደናቂ ክስተት አካል በመሆኔ ኩራት ይሰማኛል ብለዋል በመልዕክታቸው ።

የቀድሞ ጠቅላይ ሚኒስትር መለስ ዜናዊ ፕሮጀክቱን ለመጀመር ባሳዩት ራዕይ እና ድፍረት እናስታውሳቸዋለን፤ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐብይም ፕሮጀክቱን ስላጠናቀቁ እናመሰግናለን። "ሲሉ የእንኳን ደስ አላችሁ መልዕክት አስተላልፈዋል፡፡

ጳጉሜ 4/2017 ዓ.ም

ደቡብ ሱዳን ከሕዳሴ ግድብ ኃይል ለማግኘት በቅርቡ ስምምነት ትፈፅማለች - ፕሬዚዳንት ሳልቫ ኪር    ደቡብ ሱዳን ከታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ኃይል ለማግኘት የሚያስችል ስምምነት በቅርቡ ...
09/09/2025

ደቡብ ሱዳን ከሕዳሴ ግድብ ኃይል ለማግኘት በቅርቡ ስምምነት ትፈፅማለች - ፕሬዚዳንት ሳልቫ ኪር

ደቡብ ሱዳን ከታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ኃይል ለማግኘት የሚያስችል ስምምነት በቅርቡ ትፈፅማለች አሉ የሀገሪቱ ፕሬዚዳንት ሳልቫ ኪር ማያርዲት፡፡

ፕሬዚዳንቱ በሕዳሴ ግድብ የምረቃ ሥነ ሥርዓት ላይ ባስተላለፉት መልዕክት÷ በአፍሪካ የመጀመሪያ የሆነው ታላቅ የሀይድሮ ኤሌክትሪክ ግድብ ተገንብቶ በመጠናቀቁ እንኳን ደስ አላችሁ ብለዋል፡፡

ግድቡ ከኢትዮጵያ አልፎ የቀጣናውን ሀገራት የኤሌክትሪክ ኃይል ተጠቃሚ እንደሚያደርግ ጠቅሰው፤ በቅርቡ ሀገራቸው የኤሌክትሪክ ኃይል ማግኘት የሚያስችላትን ስምምነት ከኢትዮጵያ ጋር እንደምትፈፅም ጠቁመዋል።

ይህም በደቡብ ሱዳን ትምህርት ቤቶች፣ ሆስፒታሎች እና ከተሞች ያለውን የኤሌክትሪክ ኃይል እጥረት እንደሚፈታ ገልጸው÷ ግድቡ ለደቡብ ሱዳን ህዝብ አዲስ ምዕራፍን የሚከፍት ነው ብለዋል፡፡

የህዳሴ ግድቡ ሁለቱን ሀገራት በኃይል መሰረተ ልማት የሚያስተሳስር እና የሀገራቱን ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት የሚያሳድግ መሆኑን ተናግረዋል፡፡

በሚኪያስ አየለ

ሰበር ዜና  በቀጣይ ሳምንታት የመጀመሪያው የተፈጥሮ ጋዝ ፋብሪካ ይመረቃል  በተመሳሳይ ቀን ከተመረቀው የጋዝ ፋብሪካ በ10 እጥፍ ሚበልጥ  የጋዝ ፋብሪካ  ስራ ይጀመራል ።  ጠ/ሚ  ዶ/ር አ...
09/09/2025

ሰበር ዜና
በቀጣይ ሳምንታት የመጀመሪያው የተፈጥሮ ጋዝ ፋብሪካ ይመረቃል በተመሳሳይ ቀን ከተመረቀው የጋዝ ፋብሪካ በ10 እጥፍ ሚበልጥ የጋዝ ፋብሪካ ስራ ይጀመራል ። ጠ/ሚ ዶ/ር አብይ አህመድ

🏅 🇪🇹 በታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ግንባታ ላይ ጉልህ ሚና የነበራቸው አመራሮች ከጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር አብይ አህመድ ታላቁን የሀገሪቱን የክብር ኒሻን ተሸለሙ።የታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ...
09/09/2025

🏅 🇪🇹

በታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ግንባታ ላይ ጉልህ ሚና የነበራቸው አመራሮች ከጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር አብይ አህመድ ታላቁን የሀገሪቱን የክብር ኒሻን ተሸለሙ።

የታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ የምረቃ ስነ ስርዓት ላይ፣ ለግድቡ ግንባታ መሳካት ከፍተኛ አስተዋጽኦ ያበረከቱ አመራሮች የክብር ኒሻን ተበርክቶላቸዋል። እነዚህም፦

* ኢንጂነር ኤፍሬም ወልደኪዳን አማካለኝ፦ ከህዳር 2004 ዓ.ም እስከ ጥር 14 ቀን 2017 ዓ.ም የፕሮጀክቱ ምክትል ስራ አስኪያጅ በመሆን ያገለገሉ ናቸው።

* ኢንጂነር ከማል አህመድ ሱሌይማን፦ ከሚያዝያ 2013 ዓ.ም ጀምሮ እስከ አሁን ድረስ የፕሮጀክቱ የኦፕሬሽን ስራ አስኪያጅ ሆነው እያገለገሉ ይገኛሉ።

* አቶ በላቸው ካሳ ወልዴ፦ በምክትል ስራ አስኪያጅ ማዕረግ የፕሮጀክቱ ሳይት አስተባባሪ ነበሩ።

* ኢንጂነር ክፍሌ ሆሮ፦ የፕሮጀክቱ ስራ አስኪያጅ በመሆን ግድቡን በስኬት እንዲጠናቀቅ መርተዋል።
እነዚህ አመራሮች የክብር ሽልማቱን የተረከቡት በጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር አብይ አህመድ እጅ ነው።

ጉርሻ Page

በ2014ቱ የፊፋ ዓለም ዋንጫ፣ ክርስቲያኖ ሮናልዶ በ'Z' ቅርጽ የተቆረጠ ፀጉር ይዞ ብቅ ብሎ ነበር። የዚህን ትርጉም የማያውቁ ብዙ ደጋፊዎች ያፌዙና ይሳለቁበት ነበር።በርካቶች ያላወቁት ነገ...
07/09/2025

በ2014ቱ የፊፋ ዓለም ዋንጫ፣ ክርስቲያኖ ሮናልዶ በ'Z' ቅርጽ የተቆረጠ ፀጉር ይዞ ብቅ ብሎ ነበር። የዚህን ትርጉም የማያውቁ ብዙ ደጋፊዎች ያፌዙና ይሳለቁበት ነበር።

በርካቶች ያላወቁት ነገር ቢኖር፣ ይህ የፀጉር ቅርጽ በኮርቲካል ዲስፕላሲያ (የአእምሮ ህመም) ለሚሰቃየው የ10 ወር ህፃን ኤሪክ ኦርቲዝ ክሩዝ የተደረገ ልብ የሚነካ ድጋፍ መሆኑ ነው። ህፃኑ ለመዳን 83,000 ዶላር የሚያስወጣ ቀዶ ሕክምና ያስፈልገው ነበር።

ሮናልዶ የበኩሉን አስተዋጽኦ እንዲያደርግ የተጠየቀው ለጨረታ የሚሆን ፊርማ ያለበት ማሊያ እንዲለግስ ቢሆንም፣ እርሱ ግን ለቀዶ ህክምናው የሚያስፈልገውን ሙሉ ወጪ ራሱ ከፍሏል ተብሏል።

በፀጉሩ ላይ ያለው 'Z' ቅርጽ፣ ህፃኑ ኤሪክ ከቀዶ ህክምና በኋላ የሚኖረውን ጠባሳ የሚያሳይ ምልክት እንደሆነ ይነገራል። ይህም ከቃል በላይ የሆነ የትብብር እና የርህራሄ ምልክት ነው።

እውነተኛ ክብር። አድናቆት ❤️
(C) fb

Address

Addis Abeba
Addis Ababa
TODAY2020

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when A D I S M E L K posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share

Category