
14/09/2025
ተማሪ ኻሊድ በሽር የ12ኛ ክፍል ማጠቃለያ ፈተና 591 ውጤት ማምጣቱ ተገለፀ።
የትምህርት ሚኒስቴር ብርሃኑ ነጋ በዛሬው እለት በሰጡት መግለጫ በዘንድሮ ዓመት የ12ኛ ክፍል ማጠናቀቂያ ፈተና ከተፈተኑ 585 ሺህ 882 ተማሪዎች መካከል 8.4 በመቶ የሚሆኑ ተማሪዎች 50 በመቶ ውጤት ማምጣታቸው ገልፀዋል::
ከተፈጥሮ ሳይንስ ተፈታኞች 11.4 በመቶ አንዲሁም ከማኅበራዊ ሳይንስ ተፈታኞች 5.2 በመቶ ማምጣታቸውን ተናግረዋል፡፡
ከፍተኛ ውጤት ያስመዘገበው ተማሪ ካሊድ በሽር በተፈጥሮ ሳይንስ ትምህርት 591 በማምጣት ከፍተኛ ውጤት አንዳስመዘገበ ተገልፆል::
የ12ኛ ክፍል ማጠናቀቂያ ፈተና ካስፈተኑ ትምህርት ቤቶች መካከል 1 ሺህ 249 የሚሆኑት ትምህርት ቤቶች አንድም ተማሪ አለማሳለፋቸውን ተገለፀ።
በተጨማሪም 50 ትምህርት ቤቶች ሙሉ በሙሉ ተማሪዎቻቸውን ማሳለፋቸው ታውቆል።