A D I S M E L K

A D I S M E L K መረጃና ዜና ከተለያዩ ቦታዎች ያገኘናቸውን
በሰፌዳችን አበጥረን ለናንተ እናቀርባለን

ሚጠጠቅመንን ብቻ እንውሰድ በማይጠቅመን ጊዜ አናጥፋ

የቀድሞው የኢራን ፕሬዝዳንት ማህሙድ አህመዲነጃድ በሕይወት መኖራቸው ተረጋገጠየቀድሞው የኢራን ፕሬዝዳንት ማህሙድ አህመዲነጃድ ደህንነታቸው የተጠበቀና በሕይወት እንደሚገኙ የቅርብ አማካሪያቸው ...
03/03/2026

የቀድሞው የኢራን ፕሬዝዳንት ማህሙድ አህመዲነጃድ በሕይወት መኖራቸው ተረጋገጠ

የቀድሞው የኢራን ፕሬዝዳንት ማህሙድ አህመዲነጃድ ደህንነታቸው የተጠበቀና በሕይወት እንደሚገኙ የቅርብ አማካሪያቸው ለአናዶሉ የዜና ወኪል ገለጹ።

አሜሪካና እስራኤል በጋራ በመሆን የኢራንን ከፍተኛ አመራሮችና ወታደራዊ መሠረተ ልማቶችን ኢላማ ባደረገ ጥቃት መክፈታቸውን ተከትሎ አህመዲነጃድ ተገድለዋል የሚሉ ዘገባዎች ተሰራጭተው ነበር። ሆኖም ስማቸው እንዳይጠቀስ የፈለጉት አማካሪያቸው “ከእሳቸው ጋር ተገናኝቻለሁ ሁሉም ነገር ሰላም ነው” ሲሉ ወሬውን አስተባብለዋል።
እንደ አማካሪው ገለጻ ትናንት በተሰነዘረው ጥቃት ከአህመዲነጃድ የደህንነት ጥበቃ ጋር ግንኙነት ያለው ሕንፃ ተመትቷል በጥቃቱም
የኢራን አብዮታዊ ዘበኛ (IRGC) አባል የሆኑ ሦስት የግል ጠባቂዎቻቸው ተገድለዋል የፕሬዝዳንቱ መኖሪያ ቤት ጥቃቱ ከፈጸመበት ሕንፃ 100 ሜትር ያህል ርቀት ላይ የሚገኝ ቢሆንም ቤቱ ኢላማ አልተደረገም እንዲሁም ምንም ዓይነት ጉዳት አልደረሰበትም።

ማህሙድ አህመዲነጃድ ከ2005 እስከ 2013 እ.ኤ.አ. ድረስ በፕሬዝዳንትነት ያገለገሉ ሲሆን ይህ ማረጋገጫ የተሰጠው በእስራኤልና አሜሪካ የአየር ድብደባ ተገድለዋል የሚለው መረጃ በስፋት ከተሰማ በኋላ ነው።

በመካከለኛው ምስራቅ የአሜሪካ የሆነው ግዙፉ ራዳር በኢራን ጥቃት በዛሬው እለት ወድሞል  :: ==========================በመካከለኛው ምስራቅ ቀጠና የአሜሪካ የሚሳይል መከላከያ ...
03/03/2026

በመካከለኛው ምስራቅ የአሜሪካ የሆነው ግዙፉ ራዳር በኢራን ጥቃት በዛሬው እለት ወድሞል ::
==========================
በመካከለኛው ምስራቅ ቀጠና የአሜሪካ የሚሳይል መከላከያ ሥርዓት ዋልታና ማገር እንደሆነ የሚነገርለት ግዙፉ የቅድመ ማስጠንቀቂያ ራዳር፣ በኢራን በሚሰነዘሩ የሚሳይል ጥቃቶች ኢላማ መሆኑ ተዘገበ። ይህ ክስተት በቀጠናው ያለውን ወታደራዊ ሚዛን በእጅጉ ሊቀይረው እንደሚችል ተገምቷል።

AN/FPS-132 የተሰኘው ይህ እጅግ ዘመናዊ ራዳር፣ አሜሪካ በመካከለኛው ምስራቅ ካሏት ወታደራዊ ቁሶች መካከል በግንባር ቀደምትነት የሚጠቀስ ነው።

ጥቃት የደረሰበት ራዳር
======================

🔹 1.1 ቢሊዮን ዶላር የሚገመት ሲሆን፣ ከፍተኛ መዋዕለ ንዋይ የፈሰሰበት ፕሮጀክት ነው።

🔹 እስከ 5,000 ኪሎ ሜትር ርቀት ድረስ ማንኛውንም የሚሳይል እንቅስቃሴ መከታተል የሚችል ሲሆን፣ ይህም መላውን መካከለኛው ምስራቅና ከዚያም በላይ ያለውን ቀጠና ለመሰለል ያስችለዋል።

🔹 ባሊስቲክ ሚሳይሎች ሳይወነጨፉና ከተወነጨፉም በኋላ ያሉበትን ትክክለኛ ቦታ በመለየት ለቅድመ ማስጠንቀቂያና ለመከላከያ እርምጃ መረጃ መስጠት ይችላል።

እንደ ፕሬስ ቲቪ (PressTV) ዘገባ ከሆነ፣ ኢራን ሰንዝራዋለች በተባለው ጥቃት ይህ እጅግ ውድ የሆነ ራዳር ወድሟል።

ጥቃቱ የተፈጸመው በኳታር በሚገኘውና የአሜሪካ ወታደራዊ ማዕከል በሆነው አል ኡዴይድ አየር ኃይል ጣቢያ አቅራቢያ ነው።

ኢራን ይህንን እርምጃ የወሰደችው አሜሪካና አጋሮቿ በቀጠናው ለሚያደርጉት እንቅስቃሴ ምላሽ ለመስጠት እንደሆነ ተገልጿል።

የራዳሩ መውደም አሜሪካ በኢራን የሚሰነዘሩ የሚሳይል ጥቃቶችን አስቀድሞ የመለየት አቅሟን (Early Warning System) ክፉኛ እንደሚጎዳው ተነግሯል።

ይህ ክስተት በመካከለኛው ምስራቅ ያለውን ጂኦ-ፖለቲካዊ ውጥረት ወደ አዲስ ምዕራፍ ያሸጋገረው ሲሆን፣ የአሜሪካ የቴክኖሎጂ የበላይነት በኢራን ድንገተኛ ጥቃት መፈተኑን ያሳያል። ራዳሩ ከአገልግሎት ውጭ መሆኑ የቀጠናውን የአየር ክልል ደህንነት ለከፍተኛ ስጋት አጋልጦታል።

ኢራን በሆርሙዝ ጉዳይ የመጨረሻ ውሳኔ አስተላለፈች​አስቸኳይ ዜና፦ ኢራን የሆርሙዝ ስትሬትን መዝጋቷን አስታወቀችየኢራን አብዮታዊ ዘበኛ ኃይል (IRGC) በዓለም አቀፍ የንግድ እንቅስቃሴ ውስጥ...
03/03/2026

ኢራን በሆርሙዝ ጉዳይ የመጨረሻ ውሳኔ አስተላለፈች

​አስቸኳይ ዜና፦ ኢራን የሆርሙዝ ስትሬትን መዝጋቷን አስታወቀች

የኢራን አብዮታዊ ዘበኛ ኃይል (IRGC) በዓለም አቀፍ የንግድ እንቅስቃሴ ውስጥ እጅግ ወሳኝ የሆነውን የሆርሙዝ ስትሬት ለማንኛውም የባህር ላይ ትራፊክ ዝግ ማድረጉን በዛሬው እለት አስታወቀ።

​የአብዮታዊ ዘበኛው ዋና አዛዥ ከፍተኛ አማካሪ የሆኑት ኢብራሂም ጃባሪ ለሀገሪቱ የመንግስት መገናኛ ብዙኃን በሰጡት መግለጫ ማንኛውም የውሃ መንገዱን ለመሻገር የሚሞክር መርከብ ጥቃት እንደሚሰነዘርበት አስጠንቅቀዋል።

​የሆርሙዝ የውሃ መንገድ ተዘግቷልለማለፍ የሚሞክር ማንኛውም አካል ካለ የአብዮታዊ ዘበኛው ጀግኖች እና መደበኛው የባህር ኃይል መርከቦቹን በእሳት ያጋያሉ ብለዋል አማካሪው።

የኢራን ውሳኔ በተግባር ላይ የሚውል ከሆነ በዓለም አቀፍ የነዳጅ ንግድ ላይ ከፍተኛ ቀውስ ያስከትላል ተብሏል።

በዓለም ላይ ለገበያ ከሚቀርበው የነዳጅ ምርት ውስጥ ሲሶው (1/5ኛው) የሚያልፈው በዚህ ጠባብ የውሃ መንገድ በኩል ነው።

ሳዑዲ አረቢያ፣ ኩዌት፣ ኢራቅ፣ ኳታር፣ ባህሬን እና የተባበሩት አረብ ኤምሬትስ ነዳጅና ጋዝ ወደ ውጭ የሚልኩት በዚህ መስመር ነው።

​ዜናው ከተሰማ በኋላ የነዳጅ ዋጋ በዓለም ገበያ ላይ ከፍተኛ ጭማሪ ሊያሳይ እንደሚችል የኢኮኖሚ ባለሙያዎች በመተንበይ ላይ ናቸው።

​ኢራን ይህን እርምጃ የወሰደችው ከሰሞኑ በእስራኤል እና በአሜሪካ ተሰነዘረ የተባለውን ጥቃት ተከትሎ በወሰደችው የአጸፋ እርምጃ እንደሆነ መረጃዎች ይጠቁማሉ።

​ #የሆርሙዝስትሬት​ #ኢራን​ #የነዳጅዋጋ​ #ሰበርዜና
​ #ዓለምአቀፍዜና​ ​ ​ ​
​ ​

ኢራን ለአረብ ሀገራት የላከችው ጠንካራ መልዕክትየኢራን ከፍተኛ ብሔራዊ ደህንነት ምክር ቤት ጸሐፊ ለአረብ ሀገራት መልዕክት አስተላልፏል።ኢራን ለአረብ ሀገራት አስጠንቅቃ መልዕክት አስተላልፋለ...
03/03/2026

ኢራን ለአረብ ሀገራት የላከችው ጠንካራ መልዕክት

የኢራን ከፍተኛ ብሔራዊ ደህንነት ምክር ቤት ጸሐፊ ለአረብ ሀገራት መልዕክት አስተላልፏል።

ኢራን ለአረብ ሀገራት አስጠንቅቃ መልዕክት አስተላልፋለች። በአካባቢው ያሉ የአየር እና የባህር ቦታዎች በአሜሪካና በእስራኤል ጥቃት ላይ እንደ መነሻ ከተጠቀሙባቸው እነዚያ ቦታዎች እንደ አሜሪካ መሠረት ይቆጠራሉ ብላለች።

“በእናንተ ላይ ለመዝመት አሳብ የለንም፤ ነገር ግን በመሬታችሁ ውስጥ ያሉ ቦታዎች በእኛ ላይ ጥቃት ለመፈጸም ከተጠቀሙባቸው እንመልሳለን።"

በተደጋጋሚ አስጠንቅቀናችኋል፣ ጆሮ ካልሰጣችሁ በኋላ እርምጃ ወስደናል ብሏል። የአየርና የባህር ቦታዎቻችሁን እንደ አካባቢ ሳይሆን እንደ አሜሪካ መሠረት እንመለከታቸዋለን ብሏል። እናንተ ደግሞ አሜሪካ እንዳትጠቀምባችሁ የማታግዱ መሆናችሁን ተረድተናል፤ ስለዚህ ያ ቦታ ለእኛ ጥቃት እንደ መነሻ ሆኖ ከተጠቀሙት እንመታዋለን።

እስካሁን ድረስ አስጠንቅቆ መግለጫ ማውጣት ካልተቋረጠ እና አሜሪካ ጎን መቆም ከቀጠለ እርምጃ ይቀጥላል።
“አሜሪካን ብንቃወም እንሞታለን” ብላችሁ የምትፈሩ ከሆነ፣ ኢራንን ብትቃወሙም ሞት እንዳለ እናሳያችኋለን።

በአንድ ጊዜ የእስላም ህዝብ ክብርን ታጠፋላችሁ ፣ የራሳችሁንም ክብር ትነካላችሁ — ይላል የኢራን ከፍተኛ ባለስልጣን መግለጫ።

ዳዬ ሙስሊም ሚድያ Daye Muslim Media

የኢራን ጥቃት በኔታናሁ የፀጥታ ስብሰባ ላይ​በእየሩሳሌም ላይ የተሰነዘረው የኢራን ሚሳኤል ጥቃት የኔታንያሁ የጸጥታ ስብሰባን ኢላማ ማድረጉ ተገለጸ​ትላንት እሁድ ማምሻውን ኢራን በእየሩሳሌም ...
02/03/2026

የኢራን ጥቃት በኔታናሁ የፀጥታ ስብሰባ ላይ

​በእየሩሳሌም ላይ የተሰነዘረው የኢራን ሚሳኤል ጥቃት የኔታንያሁ የጸጥታ ስብሰባን ኢላማ ማድረጉ ተገለጸ

​ትላንት እሁድ ማምሻውን ኢራን በእየሩሳሌም ላይ በከፈተችው የሚሳኤል ናዳ ጠቅላይ ሚኒስትር ቤንያሚን ኔታንያሁ የሚመሩትን አነስተኛ የጸጥታ ስብሰባ ኢላማ ማድረጓ ተዘግቧል።

​ኢራን በትላንትናው ዕለት በመቶዎች የሚቆጠሩ የባለስቲክ ሚሳኤሎችንና ድሮኖችን ወደ እስራኤል ያስወነጨፈች ሲሆን በእየሩሳሌም ሰማይ ላይ በርካታ ፍንዳታዎች ተሰምተዋል።

ጥቃቱ በተለይ ጠቅላይ ሚኒስትር ኔታንያሁ የመከላከያ ሚኒስትር ኢስራኤል ካትዝ እና ሌሎች ከፍተኛ የደህንነት ባለስልጣናት በምስጢራዊ ጉዳይ ላይ ሲመክሩበት የነበረውን ስብሰባ ለማስተጓጎል የታለመ ነበር ተብሏል።

እስካሁን ባለው መረጃ ጥቃቱ በስብሰባውና በባለስልጣናቱ ላይ ያደረሰው ጉዳት የለም።
ይሁን እንጂ ከእየሩሳሌም በቅርብ ርቀት ላይ በሚገኘው ቤት ሼሜሽ አካባቢ በደረሰ የሚሳኤል ጥቃት ዘጠኝ ሰዎች መገደላቸውና አንድ ምኩራብ መውደሙ ተረጋግጧል።

​ጠቅላይ ሚኒስትር ኔታንያሁ ከጥቃቱ በኋላ በሰጡት መግለጫ ኢራን በታሪኳ ትልቁን ስህተት መፈጸሟን ገልጸው እስራኤል ሊገመት በማይችል ኃይል ምላሽ እንደምትሰጥ ዝተዋል።

በሌላ በኩል በደረሰው የኢራን ጥቃት ኔታናሁ መሞታቸው እየተነገረ ነው

ሰበር ዜና!  የዓለምን የፖለቲካ ውጥረት የሚያረግብ አስደሳች ዜና፦ የአሜሪካው ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ ከአዲሶቹ የኢራን መሪዎች ጋር ለመነጋገር ተስማሙ!የአሜሪካው ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራም...
01/03/2026

ሰበር ዜና! የዓለምን የፖለቲካ ውጥረት የሚያረግብ አስደሳች ዜና፦ የአሜሪካው ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ ከአዲሶቹ የኢራን መሪዎች ጋር ለመነጋገር ተስማሙ!

የአሜሪካው ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ፣ ከአዲሶቹ የኢራን መሪዎች ጋር ቀጥታ ንግግር ለማድረግ መስማማታቸውን ለ"ዘ አትላንቲክ" (The Atlantic) በሰጡት መግለጫ አስታውቀዋል።

በሁለቱ አገራት መካከል የነበረውን ከፍተኛ የዲፕሎማሲ ውጥረት ለማርገብ፣ አዲሶቹ የኢራን መሪዎች የውይይት ጥሪ ማቅረባቸውን ተከትሎ፣ ፕሬዚዳንት ትራምፕ
ንግግሩን ለመቀበል ፈቃደኛ መሆናቸውን ገልጸዋል።

ይህ ውሳኔ በዓለም አቀፍ ደረጃ ያለውን የፖለቲካ ውጥረት ለማርገብ ትልቅ ተስፋ የተጣለበት በመሆኑ በአለም አቀፍ መድረኮች ከፍተኛ ትኩረት ስቧል። ዘገባው የReuters ነው::

©️Reuters

ሲያልቅ አያምር ‼️  ድሮ ታላቋ አሜሪካ እንኳን ራሷን ይቅርና ትንንሾቹን ግልገል ወዳጆቿን እዳፈራለሁ ብሎ የሚያስብ አካልን "ዋ "የሚል ድምፅ በመናገር ብቻ በቁሙ ታሸናው ነበር።     ምክ...
01/03/2026

ሲያልቅ አያምር ‼️

ድሮ ታላቋ አሜሪካ እንኳን ራሷን ይቅርና ትንንሾቹን ግልገል ወዳጆቿን እዳፈራለሁ ብሎ የሚያስብ አካልን "ዋ "የሚል ድምፅ በመናገር ብቻ በቁሙ ታሸናው ነበር።

ምክንያቱም የገነባችው የሶፍት ፓወር ትርክት እንኳን የራሷን ይቅርና የአሜሪካ ፕሬዝዳንት ጋር ተሳስቆ ፎቶ የተነሳን ሁሉ ያስከብር ነበር።

የራሷን የተሰሚነት አቅምና ትርክት በራሷ ማፈራረስና መብላት ከጀመረች በሗላ ግን እንኳን ሶፍት ፓዎሯን ይቅርና ጠጠር አቅሞቿን ካልተለካካሁ የሚል አድስ ሀይል ተፈጠረባት።አሁን ላይ እንኳን ወዳጆቿን መጠበቅ ይቅርና የራሷን የተሰሚነት አለም አቀፍ ይዞታ እያጣች ትገኛለች ።

አሁን ታላቋ አሜሪ እንደ አበደ ውሻ በየቦታው የምታደርገው ንክሻ ከዚህ በፊት የነበራት ተሰሚነት ጠፍቶ እየተናቀች መሄዷና ሌሎች ተቀናቃኞች ለዘመናት የገነባችውን አሜሪካ መር የዓለም ዓቀፍ ስርአት ሊያፈርሱባት መሆኑ ስላሳሰባት ነው።

ሁሉም ነገር በትክክለኛውና በአግባቡ ካልተያዘ የሚፈርስበትና የሚያረጅበት የራሱ ልክና ገደብ አለው ‼️

የኢራን እስላማዊ ሪፐብሊክ መንግሥታዊ የሳተላይት ቴሌቪዥን ፕሬስ ቲቪ፣ አያቶላህ ሰይድ ዓሊ ኻመነዪ በሰማዕትነት ማለፋቸውን ይፋ አድርጓል። ከእርሳቸውም ጋር ጥቂት የቤተሰባቸው አባላት፣ አሜሪ...
01/03/2026

የኢራን እስላማዊ ሪፐብሊክ መንግሥታዊ የሳተላይት ቴሌቪዥን ፕሬስ ቲቪ፣ አያቶላህ ሰይድ ዓሊ ኻመነዪ በሰማዕትነት ማለፋቸውን ይፋ አድርጓል። ከእርሳቸውም ጋር ጥቂት የቤተሰባቸው አባላት፣ አሜሪካና እስራኤል በፈፀሙት የሚሳኤል ጥቃት መገደላቸው ተነግሯል።

ይህን ተከትሎ በኢራን የ40 ቀናት የሐዘን ወቅት ታውጇል።

የአያቶላህ ኻመነዪ መሰዋት፣ በትናንትናው ዕለት በአሜሪካና በእስራኤል የተለኮሰውን ጦርነት በቀላሉ ወደማይበርድበት ደረጃ እንደሚያሳድገው ይታመናል።

ኢራን የመካከለኛው ምሥራቅ ዋነኛ የነዳጅ መተላለፊያ የኾነውን የሆርሙዝ የባህር ሰርጥ መዝጋቷ ተሰምቷል። ይህ በዓለም ኢኮኖሚ ላይ ከፍተኛ ቀውስ ሊፈጥር እንደሚችል አስቀድሞም ሲነገር ሰንብቷል።

ኢራን ሁለቱ አገራት በጥምረት ለከፈቱባት ጥቃት፣ በቀጠናው የሚገኙ የአሜሪካ የጦር ሠፈሮችን እንዲሁም ቴል አቪቭን ጨምሮ የተለያዩ የእስራኤል ከተሞችን የሚሳኤል እና የድሮን ጥቃቶች ዒላማ በማድረግ የአፀፋ ጥቃት ፈጽማለች።

በርካታ የኢራን ሚሳኤሎች የእስራኤልን የአየር መቃወሚያ ሥርዓቶች ጥሰው ዒላማዎቻቸውን እንደመቱ ተዘግቧል።

በፅናት እየመሩ ነው “ - ለኢራን መንግሥት ቅርበት ያላቸው ሚዲያዎችከኢራን መንግስት ጋር ቅርበት ያላቸው ታስኒም እና መሄር የዜና ወኪሎች የሀገሪቱ የበላይ መሪ አያቶላ አሊ ኻሜኒ በህይወት ...
28/02/2026

በፅናት እየመሩ ነው “ - ለኢራን መንግሥት ቅርበት ያላቸው ሚዲያዎች

ከኢራን መንግስት ጋር ቅርበት ያላቸው ታስኒም እና መሄር የዜና ወኪሎች የሀገሪቱ የበላይ መሪ አያቶላ አሊ ኻሜኒ በህይወት እንዳሉና “ በፅናት እየመሩ መሆናቸውን “ ዘግበዋል።

የኢራን ባለስልጣናት የእስራኤል ዘገባዎችን “ የስነ-ልቦና ጦርነት “ ሲሉ አጣጥለውታል።

የሀገሪቱ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አባስ አራቅቺ ካሜኒም ሆኑ ፕሬዝዳንቱ በጥሩ ጤንነት ላይ እንደሚገኙ ተናግረዋል።

በኢራን መዲና ቴህራን በሺዎች የሚቆጠሩ ሰልፈኞች ለመንግሥት ያላቸውን ድጋፍ ለመግለጽ አደባባይ መውጣታቸውን ተገለፀ ይህ ሰልፍ የተካሄደው በአካባቢው ከፍተኛ ወታደራዊ ውጥረትና ጂኦፖለቲካዊ እ...
28/02/2026

በኢራን መዲና ቴህራን በሺዎች የሚቆጠሩ ሰልፈኞች ለመንግሥት ያላቸውን ድጋፍ ለመግለጽ አደባባይ መውጣታቸውን ተገለፀ

ይህ ሰልፍ የተካሄደው በአካባቢው ከፍተኛ ወታደራዊ ውጥረትና ጂኦፖለቲካዊ እንቅስቃሴዎች ባሉበት ወቅት መሆኑ ተገልጿል።

ሰልፈኞቹ የኢራንን ሰንደቅ ዓላማ በመያዝ እና ለመንግሥት አመራሩ ያላቸውን አንድነት የሚገልጹ መፈክሮችን በማሰማት በቴህራን ጎዳናዎች ላይ ተመልክተዋል።

ይህ መጠነ ሰፊ የድጋፍ ሰልፍ በሀገሪቱ ላይ ሊሰነዘሩ የሚችሉ ውጫዊ ጫናዎችን ለመቋቋም ያለመ የብሔራዊ አንድነት ማሳያ ተደርጎ ተወስዷል

ሰበር ዜና :- በኩዌት ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ላይ ጥቃት ተፈጸመየኩዌት ሲቪል አቪዬሽን ባለሥልጣን የደረሰውን የድሮን ጥቃት ማረጋገጡን አስታውቋል።የባለሥልጣኑ ኦፊሴላዊ ቃል አቀባይ ...
28/02/2026

ሰበር ዜና :- በኩዌት ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ላይ ጥቃት ተፈጸመ

የኩዌት ሲቪል አቪዬሽን ባለሥልጣን የደረሰውን የድሮን ጥቃት ማረጋገጡን አስታውቋል።

የባለሥልጣኑ ኦፊሴላዊ ቃል አቀባይ አቶ አብደላ አል-ራጂህ ባወጡት መግለጫ፣ ድሮኑ ያነጣጠረው በኩዌት ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ላይ ነው።

* በጥቃቱ በርካታ የጽዳት/የደህንነት ሰራተኞች ላይ ቀላል የአካል ጉዳት ደርሷል።

* በዋናው የተሳፋሪዎች ማረፊያ ህንጻ (T1) ላይ መጠነኛ የንብረት ውድመት ተመዝግቧል።

የሚመለከታቸው የመንግስት አካላት ወዲያውኑ የአስቸኳይ ጊዜ አሰራሮችን በመተግበር ቦታውን ደህንነቱ የተጠበቀ አድርገውታል።

በአሁኑ ወቅት የጉዳት ግምገማ እና የጥገና ስራዎች በጥንቃቄ እየተከናወኑ ይገኛሉ።

የአውሮፕላን ማረፊያው ደህንነት ሙሉ በሙሉ በተቆጣጠሩ አካላት ስር መሆኑን የገለጹት ቃል አቀባዩ፣ የተሳፋሪዎችና የሰራተኞች ደህንነት ቀዳሚ ተግባራቸው መሆኑን አረጋግጠዋል።

Via Ayman Mat ከስፍራው

ፕሬዝዳንት ኤርዶጋን ኢራን በገልፍ ሀገራት ላይ የሰነዘረችውን ጥቃት ኮነኑ የቱርክ ፕሬዝዳንት ረሲፕ ጣይፕ ኤርዶጋን ኢራን በገልፍ ሀገራት ላይ የፈጸመችው የሚሳኤልና የድሮን ጥቃት "ተቀባይነት...
28/02/2026

ፕሬዝዳንት ኤርዶጋን ኢራን በገልፍ ሀገራት ላይ የሰነዘረችውን ጥቃት ኮነኑ

የቱርክ ፕሬዝዳንት ረሲፕ ጣይፕ ኤርዶጋን ኢራን በገልፍ ሀገራት ላይ የፈጸመችው የሚሳኤልና የድሮን ጥቃት "ተቀባይነት የሌለው" ተግባር መሆኑን ገለጹ።

ፕሬዝዳንት ኤርዶጋን ዛሬ በኢስታንቡል ባደረጉት ንግግር፥ በክልሉ እየተባባሰ የመጣው ውጥረት በእጅጉ እንዳሳሰባቸው ገልጸዋል።

ፕሬዝዳንቱ አክለውም፣ ኢራን "ወንድም" ባሏቸው የገልፍ ሀገራት ላይ የፈጸመችው ጥቃት የትኛውንም ምክንያት ቢቀርብለት ተቀባይነት የሌለውና ቀጣናውን ወደ ከፋ ግጭት የሚያመራ መሆኑን አስገንዝበዋል።

በተጨማሪም ፕሬዝዳንቱ አሜሪካና እስራኤል በኢራን ላይ የሰነዘሩትን የአየር ጥቃት የኮነኑ ሲሆን፥ ይህም የኢራንን ሉዓላዊነት የሚጋፋና የክልሉን ሰላም የሚያናጋ ነው ብለዋል።

ፕሬዘዳንቱ እስላማዊው ዓለም አፋጣኝ እርምጃ እንዲወስድ አሳስበዋል።

ፕሬዝዳንት ሬሲፕ ጣይብ ኤርዶጋን በመካከለኛው ምሥራቅ የተከሰተውን የከፋ ግጭት ለመከላከል እስላማዊው ዓለም አፋጣኝ እርምጃ እንዲወስድ አሳስበዋል።

“በኔታንያሁ ቅስቀሳ በኢራን ላይ የተጀመረው” የአሜሪካ እና የእስራኤል ጥቃት “በጣም ያሳስበኛል” ብለዋል።

ቱርክ ሁኔታው በዲፕሎማሲያዊ መንገድ እንዲፈታ ጥረት እንደምታደርግና ለድርድር ዝግጁ መሆኗንም ኤርዶጋን አረጋግጠዋል።

ልዑል ወልዴ

የካቲት 21/2018

Address

Addis Abeba
Addis Ababa
TODAY2020

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when A D I S M E L K posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share

Category