A D I S M E L K

A D I S M E L K መረጃና ዜና ከተለያዩ ቦታዎች ያገኘናቸውን
በሰፌዳችን አበጥረን ለናንተ እናቀርባለን

ሚጠጠቅመንን ብቻ እንውሰድ በማይጠቅመን ጊዜ አናጥፋ

አነጋጋሪው  የጎግል ማፕ ተግባርአሰብን  የኢትዮጵያ አካል  አድርጎ  አስቀምጧል ምን ታይቶት  ነው😠?
18/11/2025

አነጋጋሪው የጎግል ማፕ ተግባር

አሰብን የኢትዮጵያ አካል አድርጎ አስቀምጧል ምን ታይቶት ነው😠?

ትራምፕ ሮናልዶን በ'ኋይት ሀውስ' ያስተናግዳሉ!ጄክ ቴይለር የአሜሪካው ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ ፖርቹጋላዊውን ኮከብ ክሪስትያኖ ሮናልዶ ተቀብለው እንደሚያስተናግዱ 3 የኋይት ሀውስ ምንጮች ...
18/11/2025

ትራምፕ ሮናልዶን በ'ኋይት ሀውስ' ያስተናግዳሉ!

ጄክ ቴይለር የአሜሪካው ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ ፖርቹጋላዊውን ኮከብ ክሪስትያኖ ሮናልዶ ተቀብለው እንደሚያስተናግዱ 3 የኋይት ሀውስ ምንጮች ነገሩኝ ሲል ዘግቧል። ቴይለር ለMSNO News የ' ኋይት ሀውስ ኮረስፖንዳንት' በመሆን እያገለገለ የሚገኝ ጋዜጠኛ ነው።

ትራምፕ ሮናልዶን የሚያገኙት የሳውዲውን ልዑል በፅህፈትቤታቸው በሚቀበሉበት በነገው እለት መሆኑም ተገልጿል። ይህ የሚሆን ከሆነም ሮናልዶ ከረጅም አመታት በኋላ ወደአሜሪካ ምድር ለመጀመሪያ ጊዜ የሚሄድ ይሆናል።

✍️ ዮናታን አየለ

20/10/2025

የተቀዳሚ ሙፍቲ ሐጂ ዑመር ኢድሪስ የሽኝት ሥነ ሥርዓት በሚኒለየም አዳራሽ ተካሄደ!

የተቀዳሚ ሙፍቲ ሐጂ ዑመር ኢድሪስ የአስከሬን ሽኝት ሥነ ሥርዓት የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት ፕሬዝደንት ሸይኽ ሀጂ ኢብራሂም ጨምሮ ከፍተኛ የመንግሥት የሥራ ኃላፊዎች በተገኙበት በአዲስ አበባ ሚኒሊየም አዳራሽ ተከናውኗል፡፡

በአስከሬን ሽኝት ሥነ ሥርዓቱ የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳይ ጠቅላይ ምክር ቤት ፕሬዚዳንት ሐጅ ኢብራሂም ቱፋ፣ የኢፌድሪ ፕሬዝደንት ታየ አጽቀ ስላሴ፣ የቀድሞው ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር አቶ ደመቀ መኮንን፣ የኢትዮጵያ ኃይማኖት ተቋማት ጉባኤ ዋና ፀሐፊ ሊቀ ትጉሃን ቀሲስ ታጋይ ታደለ፣ ከፍተኛ የመንግሥት የሥራ ኃላፊዎች፣ ኡለማዎች፣ ደረሳዎቻቸው እና ወዳጅ ዘመዶቻቸው ተገኝተዋል።

ሙፍቲ ሀጅ ዑመር እድሪስ ሥርዓተ ቀብራቸው ከቀኑ 10 ሰዓት ላይ የሚፈጸም ይሆናል።

© ሀሩን ሚዲያ

ኢና ሊላሂ ወኢና ኢለይሂ ራጂዑን እኛ የአላህ ነን! ወደ አላህም ተመላሾች ነን!የክቡር ዶ/ር ተቀዳሚ ሙፍቲ ሐጂ ኡመር ኢድሪስ ወደ ማይቀርበት አኼራ ተሻገሩተቀዳሚ ሙፍቲ ሐጂ ኡመር ኢድሪስ ባ...
19/10/2025

ኢና ሊላሂ ወኢና ኢለይሂ ራጂዑን
እኛ የአላህ ነን! ወደ አላህም ተመላሾች ነን!

የክቡር ዶ/ር ተቀዳሚ ሙፍቲ ሐጂ ኡመር ኢድሪስ ወደ ማይቀርበት አኼራ ተሻገሩ

ተቀዳሚ ሙፍቲ ሐጂ ኡመር ኢድሪስ ባጋጠማቸው ህመም በህክምና ሲረዱ ቆይተው የአላህ ውሳኔ ሆነና ማምሻውን ወደ አኼራ ሄደዋል።

ህክምና ላይ መሆናቸውን ሰምቶ ያልምንም የእምነት ልዩነት በዱዓና በፀሎት ሲያስባቸው ለቆየው የኢትዮጵያ ህዝብ ሀዘኑ መሪር ነው።

አላህ ከእውነተኞቹ፣ ከሰማዕታቱ፣ ከደጋጎችና ከነቢያቶች ጎን እንዲቀሰቅሳቸው እየተመኘን ለመላው የኢትዮጵያ ህዝብ መፅናናትን ይመኛል።

ለበርካታ አስርት አመታት መርካቶ 'መደብ' የሚባል ሱቅ ይዘው ሲሰሩ የነበሩ ነጋዴዎች ንብረታቸውን በአስቸኳይ ይዘው እንዲነሱ ተነገራቸው(መሠረት ሚድያ)- ከደረሰኝ መቁረጥ/አለመቁረጥ ጋር በተ...
14/10/2025

ለበርካታ አስርት አመታት መርካቶ 'መደብ' የሚባል ሱቅ ይዘው ሲሰሩ የነበሩ ነጋዴዎች ንብረታቸውን በአስቸኳይ ይዘው እንዲነሱ ተነገራቸው

(መሠረት ሚድያ)- ከደረሰኝ መቁረጥ/አለመቁረጥ ጋር በተያያዘ የገቢዎች ቢሮ እና እንደ መርካቶ ባሉ ገበያዎች የሚሰሩ ነጋዴዎች አልፎ አልፎ ውዝግብ ውስጥ ሲገቡ ይታያል፣ ይህ ውዝግብ አንዳንዴም ወደ ሱቅ መዝጋት አድማ ሲሸጋገር በቅርብ ወራት ታይቷል።

በተመሳሳይ ከሰሞኑ የገቢዎች ቢሮ በመርካቶ ጠበቅ ያለ ቁጥጥር እያረገ ይገኛል።

መሠረት ሚድያ ከስፍራው የደረሰው መረጃ እንደሚያሳየው በተለይ ሸቀጦችን፣ እቃዎችን እና ምርቶችን ጭነው ወደተለያዩ ክፍለ ሀገራት የሚሄዱ ተሽከርካሪዎች ላይ ከባድ ፍተሻ እየተደረገ ነው።

ይሁንና በርካታ በመርካቶ የሚካሄዱ ጉብኝቶች ደረሰኝ የሌላቸው ከመሆኑ ጋር በተያያዘ 'መደብ' ተብለው የሚጠሩት እና ከመርካቶ ሱቆች ስር የሚሰሩ ነጋዴዎች ችግር ላይ እንዳሉ ለሚድያችን ጠቁመዋል።

"በአዳራሽ ዙሪያ ያለን 15 አመት በላይ የቆየን ነጋዴዎችን መነሳት አለባችሁ ተብለናል። ከባለፈው ቅዳሜ ጀምሮ ተነሱ የሚል መረጃ ይዘው መጡ፣ የሚገርመው ይህ የሆነው ከሰሞኑ ግብር ከፍለን ከጨረስን በኋላ ነው" የሚሉት አንድ የመደብ ሱቅ ባለቤት ናቸው።

"በዛሬው እለት ደግሞ ስማችንን እየፃፉ ማስፈራሪያ ሲሰጡን ውለዋል። ቦታ ሳይዘጋጅ እንዲህ ማለት ተገቢ አይደለም፣ እቃዎቻችንን እያነሱ ውለዋል። ነገ አዲስ ሀይል ይመጣል የሚል ማስፈራሪያ ስጥተውን ሄደዋል" በማለት አክለዋል።

ሌላኛው የመርካቶ ነጋዴ ደግሞ "መርካቶ ለረጅም አመታት ስንሰራ የነበርን ነጋዴዎች ንግድ ፍቃድ ያለን እና ለመንግሥት ግብር ስንከፍል የቆየን ነን። እኛ በዚህ ስራ ስንት ቤተሰብ እንደምናስተዳደር አያውቁ ይሆን? ቦታ ሳይዘጋጅ ተነስ ማለት ምን ማለት ነው? ግብር ከፍለን ከጨረስን በኋላ አጠቃላይ መርካቶ መደብ ተነሱ የሚል ትዕዛዝ መጥቷል፣ ለምን" ብለው ጥያቄ ሰንዝረዋል።

የዛሬ አመት ገደማ በመርካቶ ገበያ የተጀመረው ሱቅ የመዝጋት አድማ መነጋገርያ ሆኖ ነበር። መንግሥት እያካሄደ በነበረው የደረሰኝ ቁጥጥርና ቅጣት ምክንያት ነጋዴዎች መደብሮቻቸውን በመዝጋት አድማ ላይ ነበሩ።

በወቅቱ ከአድማው በተጨማሪ ከመጋዘን እቃ የማሸሽ ተግባርም መኖሩን የገለፁት ነጋዴዎቹ በዚህም ምክንያት ገበያ መቀዛቀዙን ገልፀዋል። የአዲስ አበባ ከተማ ከንቲባ አዳነች አበቤ በበኩላቸው፣ “ቁጥጥሩ የተጀመረው በርካታ ሕገ ወጥ አሠራሮች ስላሉ ነው” ሲሉ ተናግረዋል፡፡

-መሠረት ሚድያ-

ከ20 በላይ ዘርፎችን ያካተተ የኢትዮጵያ  ሙስሊም አዋርድ ሊዘጋጅ ነው። ጥቅምት 3 ቀን 2018"በኢስላማዊ እሴት ኢትዮጵያዊ መልክ” በሚል መሪ ቃል፣ የሚዘጋጀው የኢትዮጵያ  የሙስሊም አዋርድ...
13/10/2025

ከ20 በላይ ዘርፎችን ያካተተ የኢትዮጵያ ሙስሊም አዋርድ ሊዘጋጅ ነው።

ጥቅምት 3 ቀን 2018

"በኢስላማዊ እሴት ኢትዮጵያዊ መልክ” በሚል መሪ ቃል፣ የሚዘጋጀው የኢትዮጵያ የሙስሊም አዋርድ በሀገራችን ለመጀመሪያ ጊዜ እንደሚካሄድ አዘጋጆቹ ዛሬ በሰጡት መግለጫ አስታውቋል።

ለህዝባቸው እና ለሀገራቸው ዘመን ተሻጋሪ የሆነ የላቀ አሰተዋጽኦ ያበረከቱ ሙስሊሞች ከዚህ በፊት ተገቢ የሆነ ክብርና እውቅና እንዳልተሰጣቸው አዘጋጆች ገልፀው።

አዳዲስ መልቲሚዲያ ከኮማንደር ሚዲያና ኮሚዩኒኬሽን ጋር በመተባበር የተዘጋጀው የኢትዮጵያ ሙስሊሞች አዋርድ ለወገናቸው እና ለሀገራቸው የማይተካ ሚና ላበረከቱ ሙስሊም ባለውለታዎች ተገቢውን ክብርና እውቅና እንዲያገኙ ለማድረግ የተዘጋጅ የመጀመሪያው የኢትዮጵያ ሙስሊሞች አዋርድ መሆኑ ተጠቅሷል።

በሀገራችን ኢትዮጵያ ሙስሊሙ ማህበረሰብ በማህበራዊ፣ በኢኮኖሚያዊ እና በሌሎችም ዘርፎች እያበረከተ ያለውን አዎንታዊ አስተዋፅኦ እውቅና መስጠት፣ የመልካም ስራ ባህልን ማዳበርና ለቀጣዩ ትውልድ በኢስላማዊ እሴት የታነፁና አርአያ የሚሆኑ የልህቀት ተምሳሌቶችን ከፊት ማውጣት የአዘጋጆቹ ዋነኛ አለማ እንደሆነም ተገልጿል።

ዝግጅቱ መልካም ስነ ምግባርን የሚያስፋፉ፣ በትውልዱ ላይ በጎ ተፅዕኖ የሚያሳድሩ፣ ኢስላማዊና ኢትዮጵያዊ እሴቶችን የሚያጎለብቱ ግለሰቦችንና ስራዎችን ለክብር፣ ለእውቅናና ለሽልማት ማብቃት እንደሆነም አዘጋጆቹ ተናግረዋል።

ዝግጅቱ ከ20 በላይ ዘርፎችን ያካተተ መሆኑ ተነግሯል።

ዘርፎቹ በውድድር የሚለዩ እና ያለውድድር ተመርጠው እውቅና የሚሰጥበት ዘርፎች እንዳሉ አዘጋጆች አስታውቀዋል።

ከጥቅምት 3 ጀምሮ ለ21 ተከታታይ ቀናት የዕጩ ተመራጮችን በተለያዩ የሶሻል ሚዲያ አማራጮች መቀበል እንደሚጀመር እና ጥቅምት 24 የዕጩ ተመራጮችን መቀበል እንደሚቆም ተገልጿል።

የኢትዮጵያ ሙስሊም አዋርድ ፍፃሜውን በታህሳስ ወር እንደሚያደርግም ዛሬ ከተሰጠው መግለጫ ለማወቅ ተችሏል።

በሙስጦፋ ሙሀመድ

የዘንድሮው የዓለም የኖቤል የሰላም ሽልማት ለቬኔዙዌላዊቷ የተቃዋሚ ፓርቲ መሪ ማሪያ ኮሬና ተሰጥቷል።   የአሜሪካው ፕሬዝዳንት የሆኑት ዶናልድ ትራንፕ የዘንድሮውን ሽልማት ለመውሰድ የሽልማት ...
10/10/2025

የዘንድሮው የዓለም የኖቤል የሰላም ሽልማት ለቬኔዙዌላዊቷ የተቃዋሚ ፓርቲ መሪ ማሪያ ኮሬና ተሰጥቷል።
የአሜሪካው ፕሬዝዳንት የሆኑት ዶናልድ ትራንፕ የዘንድሮውን ሽልማት ለመውሰድ የሽልማት ኮሚቴው ላይ ጫና ከመፍጠር አልፎ ኖርዌይን በከፍተኛ የጉምሩክ ቀረጥ ማስፈራራት የደረሰ ጫና ሲያሳደር ነበር።
እንዲሁም የጋዛን ጦርነት ጨምሮ 8 ዓለም ላይ የነበሩ ጦርነቶችን አስቁምያለው ሲል የነበረ ቢሆንም
በመጨረሻም ሽልማቱ ወደ ቬንዙዌላ ሄድዋል።

'እኔ እንግዲህ ከሀገሬም አልፌ በመላው አለም በደንብ የታወቅሁ ሰው ነኝ። በአለም ደረጃ ዝነኛ ነኝ። ይሁን እንጂ ከሀገሬ ወጥቼ ሰው ሀገር ስሄድና አውሮፕላን ልሳፈር ስሰለፍ " ኢትዮጵያ " ...
09/10/2025

'እኔ እንግዲህ ከሀገሬም አልፌ በመላው አለም በደንብ የታወቅሁ ሰው ነኝ። በአለም ደረጃ ዝነኛ ነኝ። ይሁን እንጂ ከሀገሬ ወጥቼ ሰው ሀገር ስሄድና አውሮፕላን ልሳፈር ስሰለፍ " ኢትዮጵያ " የሚለውን ፓስፓርቴን አውጥቼ ሳሳይ ወደ መጨረሻው ረድፍ ሂድ ነው የሚሉኝ። መጀመርያ አሜሪካኖቹን፣ እንግሊዞቹን፣ የበለጸጉትን ሀገራት ዜጎች አስገብተው ሲጨርሱ ነው እኔ ምገባው። ድሮ ከመጀመሪያው ሰልፍ የነበረችው ሀገራችን አሁን መጨረሻ ቀርታለች። ከሀገር ስንወጣ ያው የዚችው የደሀዋ ሀገር ዜጎች ነን። የኛ አማራ ነኝ፣ ኦሮሞ ነኝ ወላይታ ነኝ ፉክክር ምንም አይፈይደንም። ይህን የሚያውቅልንም የለም። ይልቅ ቶሎ ቶሎ በርትተን ሰርተን ተለውጠን በአለም ፊት የቆሸሸውን የሀገራችንን ስም ብናጸዳ ነው የሚጠቅመን።'

© ሻለቃ ሀይሌ ገብረስላሴ

ብስራት ስፖርት ላልተወሰነ ጊዜ በሬድዮ እንደማይቀርብ መንሱር አብዱልቀኒ አስታወቀ!"የብስራት ኤፍ ኤም 101.1 ፓርትነር በመሆን ከጣቢያው ጋር በትብብር "ብስራት-ስፖርት” የተሰኘውን ፕሮግራ...
09/10/2025

ብስራት ስፖርት ላልተወሰነ ጊዜ በሬድዮ እንደማይቀርብ መንሱር አብዱልቀኒ አስታወቀ!

"የብስራት ኤፍ ኤም 101.1 ፓርትነር በመሆን ከጣቢያው ጋር በትብብር "ብስራት-ስፖርት” የተሰኘውን ፕሮግራም ለ12 ዓመታት ሳቀርብ መቆየቴ ይታወቃል።

ይሁንና በእነዚህ ሁለት ቀናት (ረቡዕ እና ሐሙስ መስከረም 28 እና 29) ከእኔ የስራ ትጋት ጋር ባልተያያዘ (በግሌ ልፈታው በማልችለው ምክንያት) ከጣቢያው ጋር ያልተግባባንባቸው ጉዳዮች ተፈጥረዋል።

እነዚህ ልዩነቶች መፍትሔ እስኪያገኙ ድረስ (ዛሬ በማለዳ ያስተዋወቅኳችሁን ፕሮግራም ጨምሮ) "ብስራት-ስፖርት" ከሬድዮ አየር ላይ እንደወረደ ስገልጽላችሁ ከታላቅ ይቅርታ ጋር ነው" ሲል መንሱር አብዱልቀኒ በይፋዊ ቴሌግራም ገፁ አስታውቋል።

ከሐማስ ጋዜጣዊ መግለጫ የተወሰደ ፦-ሐማስ በጋዛ ላይ የተከፈተውን ጦርነት የሚያስቆም፤ወራሪው ኃይል ከጋዛ ለቆ እንዲወጣ የሚያደርግ፤ ዕርዳታ እንዲገባ የሚፈቅድና የእስረኞች መለዋወጥን የሚያካ...
09/10/2025

ከሐማስ ጋዜጣዊ መግለጫ የተወሰደ ፦

-ሐማስ በጋዛ ላይ የተከፈተውን ጦርነት የሚያስቆም፤ወራሪው ኃይል ከጋዛ ለቆ እንዲወጣ የሚያደርግ፤ ዕርዳታ እንዲገባ የሚፈቅድና የእስረኞች መለዋወጥን የሚያካትት ስምምነት ላይ መደረሱን ያውጃል።

-የኳታር፣ግብፅ እና ቱርክ ወንድሞቻችን የአደራዳሪነት ጥረትን እጅግ አድርገን እናደንቃለን።በተጨማሪም ጦርነቱን በዘላቂነት ለማስቆም እና ወራሪው ኃይል ከጋዛ ሰርጥ ሙሉ በሙሉ እንዲወጣ የሚያደርገውን የአሜሪካው ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕን ጥረት እናደንቃለን።

-ፕሬዝዳንት ትራምፕን፣የስምምነቱ ዋስትና ሰጪ የሆኑ አደራዳሪ ሀገሮችን እንዲሁም የተለያዩ የዐረብ፣የኢስላማዊ እና ዓለም አቀፍ አካላትን ወራሪው መንግስት የስምምነቱን መስፈርቶች ሙሉ በሙሉ እንዲተገብር እንዲያስገድዱትና ከተስማማበት ነጥቦች እንዲያፈነግጥ ወይም እንዲያጓትት እንዳይፈቅዱለት እንጠይቃለን።

-በጋዛ ሰርጥ፣ በቅድስቱ ከተማ (አል-ቁድስ) እና በዌስት ባንክ፣ እንዲሁም በሀገር ውስጥና ከሀገር ውጪ የሚገኙ የታላቁ ሕዝባችን ክፍልን እናደንቃለን።ይህ ሕዝብ ተወዳዳሪ የማይገኝላቸው የክብር፣ የጀግንነትና የሐቀኝነት አቋሞችን በመመዝገብ መብቱንና የሀገራዊ ጥቅሙ ላይ ያነጣጠሩ የፋሺስት ወራሪዎችን ዕቅዶች ተጋፍጧል።እነዚህ ታላቅ መስዋዕትነቶችና ፅኑ አቋሞችም የእስራኤል የወረራ ኃይሎችን የማስገበርና የማፈናቀል ሴራዎች እንዲከሽፉ አድርገዋል።

-የሕዝባችን መስዋዕትነት በከንቱ እንደማይቀርና ቃል ኪዳናችንን እንደምንጠብቅ እንዲሁም ነፃነታችንና ራስን በራስ የማስተዳደር መብታችን እስኪረጋገጥ ድረስ ከሕዝባችን ብሔራዊ መብቶች ከማስከበር ወደኃላ እንደማንመለስ እናረጋግጣለን።

አዲሱ የተሽከርካሪ ሰሌዳ (ታርጋ) ዛሬ ይፋ ሆኗል።" ነባሩ ታርጋ በአዲስ በሚቀየርበት ወቅት የሰሌዳ ማስቀየር ስራው የሚጠይቀውን ሁሉንም ወጪ የመኪናው ባለንብረት ይሸፍናል " - የትራንስፖር...
08/10/2025

አዲሱ የተሽከርካሪ ሰሌዳ (ታርጋ) ዛሬ ይፋ ሆኗል።

" ነባሩ ታርጋ በአዲስ በሚቀየርበት ወቅት የሰሌዳ ማስቀየር ስራው የሚጠይቀውን ሁሉንም ወጪ የመኪናው ባለንብረት ይሸፍናል " - የትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ ሚኒስቴር

የትራንስፖርት እና ሎጂስቲክስ ሚኒስቴር በሀገር አቀፍ ደረጃ ነባሩን የተሽከርካሪ መለያ ሰሌዳ ቁጥር በአዲስ ለመተካት የሚያስችል አዲስ የተሽከርካሪዎች የመለያ ቁጥር ሰሌዳ አይነቶችና ምልክቶች መወሰኛና የአገልግሎት አሰጣጥ መመሪያ ቁጥር 1050/2017 ማውጣቱ ይታወቃል።

ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ መመሪያውን አዘጋጅቶ ተግባራዊ ለማድረግ የሚያስችል ስራዎችን እየሰራ መሆኑን ገልጿል።

በ2018 ዓም ሙሉ በሙሉ ተሽከርካሪዎችን በአዲስ ታርጋ የመቀየር ስራ እንደሚሰራ የትራንስፖርት እና ሎጂስቲክስ ሚኒስቴር ሚኒስትር አለሙ ስሜ (ዶ/ር) ተናግረዋል።

በአገልግሎት ላይ ያለውን ነባሩን የተሽከርካሪ መለያ ስሌዳ ቁጥር በአዲስ ለመተካት ካስፈለገበት ምክንያቶች ውስጥ ቀደም ሲል የነበረው የተሽከርካሪ መለያ ቁጥር ስሌዳ አመራረትና አሰረጫጨት የአሰራር ክፍተት እና የሃብት ብክነት ሲስተዋልበት የቆየ በመሆኑ ያንን ለመቅረፍ የሚያስችል ስርዓት መዘርጋት በማስፈለጉ ነው ተብሏል።

አሽከርካሪዎች እየተጠቀሙበት የሚገኘው በስራ ላይ ያለው ታርጋ ከ1994 ዓም በኋላ ምንም አይነት ማሻሻያ ሳይደረግበት የቆየ ነው።

አለሙ ስሜ (ዶ/ር) ፥ " ነባሩ ታርጋ በአዲስ በሚቀየርበት ወቅት የሰሌዳ ማስቀየር ስራው የሚጠይቀውን ሁሉንም ወጪ የመኪናው ባለንብረት ይሸፍናል " ብለዋል።

" ከእዚህ ቀደም የነበረው ታርጋ 9 ሚሊየን መኪኖችን ብቻ መዝግቦ የሚያበቃ ውስን ታርጋ ነበር እስካሁን ባለው መረጃም 1.6 ሚሊየን የሚሆኑ ተሽከርካሪዎች ተመዝግበዋል የአሁኑ ታርጋ ግን 121 ሚሊየን ታርጋዎችን መመዝገብ ያስችልናል " ሲሉም አክለዋል።

ሁለት ሚሊየን የሚሆን የተሽከርካሪ ታርጋ ለማሳተም በእቅድ ተይዞ የመጀመሪያ 50 ሺ የተታተመ ታርጋ ወደ ሃገር ስለመግባቱ የተናገሩት ሚኒስትሩ " ታርጋውን አድሎ ስራ ላይ ለማዋል የዲጂታል ስርዓት መዘርጋት ይጠበቅብናል " ብለዋል።

ስርአቱን ከሚዘረጋው አካል ጋር እየተነጋገሩ እና በአንዳንድ ጉዳዮች ላይ ድርድር እየተካሄደ መሆኑን አክለው በ 2018 ዓም ሙሉ በሙሉ ተሽከርካሪዎችን በአዲስ ታርጋ የመቀየር ስራ ይሰራል ተብሎ መታቀዱን ገልጸዋል።

አዲሱ ታርጋ ቅየራ ስለሚከናወንበት ጊዜም " መሰራት ያለባቸው ቅድመ ሁኔታዎች መሰራት ስላለባቸው አዲሱ ታርጋ ቅየራ አልተጀመረም ከሁለት ወር ባጠረ ጊዜ አዲሱን ታርጋ መቀየር እንጀምራለን በያዝነው 2018 ዓም ሙሉ በሙሉ አዲሱን ታርጋ ቀይረን እንጨርሳለን " ሲሉ ገልጸዋል።

08/10/2025

ዜና ከአዲስ አበባ ፖሊስ!

ከባድ የህፃናት ጉልበት ብዝበዛ ወንጀል ተጋለጠ፡
18 ህፃናት ነጻ ወጡ!
Serious Child Labor Exploitation Crime Exposed: 18 Children Freed!)

አዲስ አበባ፤ መስከረም 28 ቀን 2018 ዓ/ም – የአዲስ አበባ ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ ባወጣው መረጃ መሰረት፣ 18 ህፃናትና ታዳጊዎች ከባድ የጉልበት ብዝበዛ ሲፈጸምባቸው ከነበሩ ሁለት ተጠርጣሪዎች ጋር በቁጥጥር ስር ውለዋል። ፖሊስም በጉዳዩ ላይ ሰፊ ምርመራ እያደረገ ይገኛል።

* ወንጀሉ የተጋለጠው በአዲስ ከተማ ክፍለ ከተማ፣ ወረዳ 5፣ ኦ አቤም ሆቴል አካባቢ ነው።

* አንድ የሰባት ዓመት ታዳጊ በመንገድ ላይ እያለቀሰ ሳለ፣ ፖሊስ ለምን እንደሚያለቅስ ሲጠይቀው ለሥራ የተሰጠው ሚዛን እንደጠፋበት እና አሰሪዎቹ ቤት እንደማያስገቡት በመናገሩ ነው።

* ይህን መረጃ ተከትሎ የአዲስ ከተማ ፖሊስ ባደረገው ፈጣን ክትትል፣ ወንጀሉ በኮልፌ ቀራንዮ ክ/ከተማ፣ ወረዳ 1፣ ቻይና ካምፕ አካባቢ በሚገኝ አንድ መኖሪያ ቤት ውስጥ ተደረሰ።

በቁጥጥር ስር የዋሉት 18 ህፃናትና ታዳጊዎች ዕድሜያቸው ከ7 እስከ 13 ዓመት መካከል ነው። ተጠርጣሪዎቹ እነዚህን ህፃናት፡-

* "እናስተምራለን" በሚል ሽፋን ከክልል ቤተሰቦቻቸው ላይ ወስደው ማምጣት።

* ቆሎ፣ ሶፍት እና ሚዛን በመሸጥ እንዲሰሩ ማድረግ።
* ከእያንዳንዳቸው በቀን ከ150 እስከ 300 ብር ገቢ እንዲያስገቡ ማስገደድ።

* የወንጀል አፈጻጸሞችን (እንደ የመኪና ስፖኪዮ መስታወት ማንኳት የመሰሉ ድርጊቶችን) ጭምር ያስተምሯቸው እንደነበር የምርመራ መዝገቡ ያመለክታል።

የፖሊስ የማስጠንቀቂያ መልዕክት

ፖሊስ በሁለቱ ተጠርጣሪዎች ላይ ተገቢው ምርመራ ከተጠናቀቀ በኋላ በዐቃቤ ሕግ ክስ እንደተመሠረተባቸው ገልጿል።

የአዲስ አበባ ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ በሕፃናት ላይ ለእድሜያቸው የማይመጥን እና ጤናቸውን፣ እድገታቸውን፣ ማኅበራዊና ስነ-ልቦናዊ ደህንነታቸውን የሚጎዳ የጉልበት ብዝበዛ ሕግ የሚጠይቅ ወንጀል መሆኑን አሳስቧል።

ለሕብረተሰቡ የቀረበ ጥሪ፡
መሰል የጉልበት ብዝበዛ ድርጊቶች ሲያጋጥሙ፣ በአቅራቢያዎ ለሚገኝ የጸጥታ አካል አስቸኳይ መረጃ በመስጠት ወንጀሉን ለመከላከል ትብብር ያድርጉ!

Via AAP

Address

Addis Abeba
Addis Ababa
TODAY2020

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when A D I S M E L K posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share

Category