EBC Fact Check

EBC Fact Check EBC Fact Check is part of Ethiopian Broadcasting Corporation a 24 hour working public media.

ፓሊስ ያጋለጠው ሀሰተኛ የአፈናና ድብደባ ውንጀላ *********የሙዚቃ ስራዎቻቸውን ለማቅረብ ወደ አዲስ አበባ የመጡት MAPARA A JAZZ የተባሉና የደቡብ አፍሪካ ዜግነት ያላቸው ሁለት ግ...
27/10/2025

ፓሊስ ያጋለጠው ሀሰተኛ የአፈናና ድብደባ ውንጀላ
*********

የሙዚቃ ስራዎቻቸውን ለማቅረብ ወደ አዲስ አበባ የመጡት MAPARA A JAZZ የተባሉና የደቡብ አፍሪካ ዜግነት ያላቸው ሁለት ግለሰቦች አዲስ አበባ ውስጥ አፈናና ድብደባ ተፈጽሞብናል ብለው በፌስ ቡክ ገፃቸው ያሰራጩት መረጃ ሀሰተኛ መሆኑን ማረጋገጡን የአዲስ አበባ ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ አስታውቋል።

የደቡብ አፍሪካ ዜግነት ያላቸው Mapara A JAZZ የተባሉት ሙዚቀኞች ወደ አዲስ አበባ የመጡት የሙዚቃ ስራቸውን ለማቅረብ እንደሆነ ፖሊስ ባሰባሰበው መረጃ ማወቅ ተችሏል።

እነዚህ ግለሰቦች ስራቸውን ጨርሰው በሠላም ወደ ሀገራቸው ከተመለሱ በኋላ አዲስ አበባ ውስጥ አፈናና ድብደባ ተፈፅሞብናል ብለው በፌስ ቡክ ገፃቸው ያሰራጩትን መረጃ መሰረት በማድረግ ፖሊስ ተገቢውን የማጣራት ተግባር አከናውኗል።

ተፈፅሞብናል ስላሉት ወንጀል ለፖሊስ መረጃ ደርሶ እንደሆነ ለማረጋገጥ በክፍለ ከተማ ፖሊስ መምሪያ እና በፖሊስ ጣቢያዎች ተጠይቆ ምንም ዓይነት የቀረበ አቤቱታ ካለመገኘቱም ባሻገር በፖሊስ ምርመራ የተሰባሰቡ የተንቀሳቃሽ ምስል፣ የፎቶና የድምጽ ማስረጃዎች እንዲሁም ከአዘጋጁ ቅሩንፉድ ኢንተርቴይመንት ጭምር እንደተረጋገጠው ግለሠቦቹ ይህን የሀሠት መረጃ የለቀቁት ብዙ ተከታዮችን ለማግኘት ሆን ብለው መሆኑን ተረጋግጧል።

ግለሰቦቹ አፈናና ድብደባ ተፈጽሞብናል ያሉት አርብ ጥቅምት 14 ቀን 2018 ዓ/ም ቢሆንም በማግስቱ ጥቅምት 15 በተጋበዙበት መድረክ ላይ ተገኝተው የሙዚቃ ስራቸውን ፍጹም ሠላማዊ በሆነ መንገድ አቅርበው ማጠናቀቃቸው እና በሠላም ወደመጡበት ሀገር መመለሳቸውን ከኢሚግሬሽንና ዜግነት አገልግሎት እንዲሁም ከአዘጋጆቹ የተረጋገጠና ሲሆን የተሰራጨውም መረጃ ሀሰተኛ መሆኑን ፖሊስ አረጋግጧል።

ከተማችን አዲስ አበባ በአስተማማኝ የፀጥታ ሁኔታ ላይ የምትገኝ ሲሆን የከተማዋን ብሎም የሀገሪቱን መልካም ገፅታ ለማጉደፍ የሚደረጉ መሠል እንቅስቃሴዎችን ህብረተሰቡ በንቃት ሊከታተልና የመረጃዎቹን ትክክለኛነት ሊያጤን እንደሚገባም የአዲስ አበባ ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ አሳስቧል።

በግጭት ወቅት የሐሰት መረጃ ስርጭት የሚያደርሰው ቀውስ ከፍተኛ መሆኑን ያውቃሉ?*******በግጭት ወቅት የሚሰራጩ የሐሰት እና የጥላቻ መረጃዎች የሚያደርሱት ቀውስ ከፍተኛ መሆኑን በጉዳዩ ላይ...
23/10/2025

በግጭት ወቅት የሐሰት መረጃ ስርጭት የሚያደርሰው ቀውስ ከፍተኛ መሆኑን ያውቃሉ?
*******

በግጭት ወቅት የሚሰራጩ የሐሰት እና የጥላቻ መረጃዎች የሚያደርሱት ቀውስ ከፍተኛ መሆኑን በጉዳዩ ላይ ጥናት ያደረጉ ባለሙያዎች ይገልፃሉ።

ኢቢሲ ያነጋገራቸው የዘርፉ ባለሙያዎች፣ በግጭት ወቅት እና ከግጭት በኋላ የሐሰት መረጃዎችን በስፋት የማጣራት መሥራት እንደሚያስፈልግ አሳስበዋል።

ባለሙያዎቹ እንዳብራሩት፣ የተሳሳተ መረጃ በሀገራት ላይ የሚያደርሰው ጉዳት ከፍተኛ ነው። በግጭት ወቅት የሚፈጸመው የሐሰተኛ መረጃ ስርጭት ዜጎችን ለከፍተኛ ችግር በመጣል ማኅበራዊ እና ኢኮኖሚያዊ ቀውሶችን እንደሚያስከትል ባለሙያዎቹ አስታውቀዋል።

የፖለቲካ ሳይንስ ምሁሩ ፕሮፌሰር ብሩክ ኃይሉ በበኩላቸው፣ አፍሪካ ግጭት በበዛባት ቁጥር በኢኮኖሚዋ እንዲሁም በሕዝቦቿ ላይ ከፍተኛ ተጽዕኖ ይፈጠራል ይላሉ።

በመላው ዓለም ሰላማዊ የመኖሪያ አካባቢን ለመፍጠር የሚደረገውን ጥረትም ሁሉም ዜጋ ሊደግፈው እንደሚገባ አንስተዋል።

በቢታኒያ ሲሳይ

የጥንቃቄ መልዕክት - ከፋይናንስ ደህንነት አገልግሎት ********************የፋይናንስ ደህንነት አገልግሎት ባሰራጨው የጥንቃቄ መልዕክት፥ አንዳንድ በማጭበርበር ድርጊት ላይ የተሰማሩ...
17/10/2025

የጥንቃቄ መልዕክት - ከፋይናንስ ደህንነት አገልግሎት
********************

የፋይናንስ ደህንነት አገልግሎት ባሰራጨው የጥንቃቄ መልዕክት፥ አንዳንድ በማጭበርበር ድርጊት ላይ የተሰማሩ ሰዎች ከግለሰቦች ፈቃድ ውጪ በሞባይሎቻቸው ውስጥ በመግባት፣ እንደ ዋትስአፕ እና ቴሌግራም የመሳሰሉ የማህበራዊ መገናኛ መተግበሪያዎችን በመጠቀም፣ ግላዊ እና ምስጢራዊ መረጃዎችን በመስረቅ የገንዘብ ማጭበርበር ድርጊት ላይ ተሰማርተው ይገኛሉ ብሏል።

እነዚህ አካላት የግለሰቦችን የማህበራዊ መገናኛ መተግበሪያዎች ከተቆጣጠሩ በኋላ እውነተኛ የአካውንት ባለቤት በመምሰል በግለሰቦቹ ስልኮች ተመዝግበው ለሚገኙ ቤተሰቦች፣ ዘመዶች፣ ጓደኞች እና የሥራ ባልደረቦች እንደተቸገሩ የሚገልፅ የፅሁፍ መልዕክት በመላክ ለዚሁ የማጭበርበር ዓላማ ወደ ተዘጋጀ የባንክ አካውንት እንዲላክላቸው ያደርጋሉ ነው ያለው።

አገልግሎቱ የደረሱትን ጥቆማዎች መሠረት በማድረግ በወንጀል ድርጊቱ ላይ የተሳተፉ አካላትን በመለየት እና በመከታተል በሕግ ተጠያቂ እንዲሆኑ ከሚመለከታቸው ባለ ድርሻ አካላት ጋር በቅንጅት እየሠራ መሆኑን ገልጿል።

ኅብረተሰቡ ይህን የማጭበርበር ድርጊት ለመከላከል ወደ ስልኩ ለሚደርሱ መልዕክቶች ምላሽ ከመስጠቱ አስቀድሞ በተለያዩ መንገዶች የመልዕክቱን ትክክለኛነት ደጋግሞ በማረጋገጥ ተገቢውን ጥንቃቄ እንዲያደርግ አሳስቧል።

በተጨማሪም ከሚመለከታቸው ተቋማት የሚተላለፉ የጥንቃቄ መልዕክቶችን በመከታተል ራሱን ከወንጀል ድርጊቶቹ እንዲጠብቅ እና ወንጀል ተፈፅሞ ሲገኝም ለሕግ አስከባሪ አካላት እንዲያሳውቅ መልዕክት አስተላልፏል።

ከማይታወቅ ሀገር መጣች የተባለችው ሴት ከየት መጥታ ነው? ቶሬንዛ የት ነች? *******ከሰሞኑ "ቶሬንዛ" የተባለ የማይታወቅ ሀገር ፓስፖርት ያላት አንዲት ሴት "በጆን ኤፍ ኬኔዲ" አየር ማ...
16/10/2025

ከማይታወቅ ሀገር መጣች የተባለችው ሴት ከየት መጥታ ነው? ቶሬንዛ የት ነች?
*******

ከሰሞኑ "ቶሬንዛ" የተባለ የማይታወቅ ሀገር ፓስፖርት ያላት አንዲት ሴት "በጆን ኤፍ ኬኔዲ" አየር ማረፊያ ውስጥ ተገኘች የሚል መረጃ ማህበራዊ ሚዲያው ላይ መነጋገሪያ ሆኖ ሰንብቷል።

ተንቀሳቃሽ ምስሉ እንደከዚህ ቀደም በሰውሰራሽ አስተሎት የተሰራ ባለመሆኑ እና እውነተኛ ቀረፃ መሆኑ ደግሞ ሰዎች ጉዳዩን በትኩረት እንዲመለከቱት አድርጓል።

ተንቀሳቃሽ ምስሉ ላይ እንደተባለው ካልታወቀ ሀገር ስለመጣች ሴት የተገለፀው እውነት ነው ወይ የሚል ጥያቄ ያስነሳል::

በ2000 ዎቹ አጋማሽ በአሜሪካ ውስጥ ታዋቂ ከነበረው የአየር መንገድ ሰራተኞች "ሪያሊት ቲቪ ሾው" ላይ የተወሰደ ቪዲዮ ስለመሆኑ ተገልጿል።

ይህ "ሪያሊት ቲቪ ሾው" በትልቅ አየር ማረፊያ ውስጥ የተሟላ አገልግሎት ለመስጠት የሚሞክሩ የአየር መንገዱ ሰራተኞች የእለት ተእለት ገጠመኝ የሚያሳይ ነው።

ተንቀሳቃሽ ምስሉም ግለሰቧ አረብኛ ቋንቋ ተናጋሪ በመሆኗ አረብኛ የሚናገር አስተርጓሚ እስክታገኝ በመጠባበቅ ላይ እያለች የተወሰደ ነው።

"A&E" በተሰኘ ከ11 ሚሊዮን በላይ ተከታይ ባለው የዩትዩብ ገፅ ላይ በሚለቀቀው በዚህ ሪያሊት ቲቪ ሾው" ላይ "ቶሬንዛ" ስለምትባል ሀገር የተጠቀሰ ምንም ነገር የለም።

ይልቁንም በአየር ማረፊያ ውስጥ ስራ ላይ ያለች አንዲት ሰራተኛ ለግለሰቧ አስተርጓሚ ስትፈልግላት ያለውን ሂደት ብቻ የሚያሳይ ነው።

በተጨማሪም ትዕይንቱ በሎስ አንጀለስ እንጂ በኒውዮርክ "ጆን ኤፍ ኬኔዲ" አውሮፕላን ማረፊያ የተቀረጸ አይደለም።

ከዚህ ባሻገር ግን ያሉ ከግለሰቧ ጋር በተያዘዘ ቃለመጠይቅ ስትደረግ ፣ ቶሬንዛ የሚል ፓስፖርት ይዛ የሚያሳይ ምስል እንዲሁም የታዋቂ ዜና ጣቢያዎች ሪፖርት ሲያደርጉ የሚያሳዩ ተንቀሳቃሽ ምስሎች በሰው ሰራሽ አስተውሎት የተሰሩ ናቸው።

በሰው ሰራሽ አስተውሎት የመነጩ ሐሰተኛ ዜናዎችን እንዴት መለየት ይቻላል?********ዛሬ ላይ በሰው ሰራሽ አስተውሎት የመነጩ ሐሰተኛ ዜናዎችን ከእውነታው ለመለየት አዳጋች እየሆነ መጥቷል።እ...
13/10/2025

በሰው ሰራሽ አስተውሎት የመነጩ ሐሰተኛ ዜናዎችን እንዴት መለየት ይቻላል?
********

ዛሬ ላይ በሰው ሰራሽ አስተውሎት የመነጩ ሐሰተኛ ዜናዎችን ከእውነታው ለመለየት አዳጋች እየሆነ መጥቷል።

እነዚህ መረጃዎች ምንም እንኳን የረቀቁ ቢሆኑም፤ በተንቀሳቃሽ ምስሎችም ሆነ በምስሎች ላይ በሚፈጥሩት ጥቃቅን ስህተት በገሀዱ ዓለም የተከሰቱ እውነተኛ መረጃዎች አለመሆናቸውን መለየት ይቻላል።

እንዴት መለየት ይቻላል ካሉ ተከታዮቹን ነጥቦች ይመልከቱ፡-

1. ዜናውን ያሰራጨው አካል ወይም የሚዲያ ተቋም ማነው የሚለው በአገባቡ ያረጋግጡ፤

ዘጋቢው ማን እንደሆነ፣ የትኛው ሚዲያ እንዳስተላለፈው ወይም ክስተቱ በትክክል እንደተከሰተ የሚያረጋግጥ ነገር ማግኘት ካልቻሉ፣ ዜናው ሀሰተኛ ወይም በሰው ሰራሽ አስተውሎት የተሰራ ነው ማለት ነው።

2.ዜናው ተአማኒ ምንጭ መጥቀሱን ይመልከቱ፤

እውነተኛ የዜና ማሰራጫዎች ብዙውን ጊዜ የታመኑ ምንጮችን፣ ኦፊሴላዊ ዘገባዎችን ወይም ቃለ-መጠይቆችን ይጠቅሳሉ። አንዳቸውንም ካልጠቀሱ ግን ተንቀሳቃሽ ምስሎችም ሆኑ ዘገባዎቹ እውነት ላይሆን ይችላሉ።

3.እንቅስቃሴዎችን በትኩረት ይመልከቱ፤

የዜና አቅራቢዎቹን በደንብ ይመልከቱ፤ ፊታቸው፣ ዓይኖቻቸው፣ ወይም የእጅ እንቅስቃሴዎችን በመመልከት ተፈጥሯዊ ያልሆኑ እንቅስቃሴዎችን (የጣት ቁጥሮች ማነስ/መብዛት፣ የአፍ እንቅስቃሴ ብዥታ፣ የእቃዎች ቀለም እና ይዘት መቀያየር) በማጤን መለየት ይቻላል።

4.ስክሪፕቱን እና ምስሉን ይገምግሙ

አንባቢው እንዴት እንደሚናገር ያዳምጡ። በሰው ሰራሽ አስተውሎት የመነጩ ዜናዎች ድምፀት የታፈነ (ያልጠራ)፣ የቃላት ግድፈት ያለው እንዲሁም ንግግሩ ከተንቀሳቃሽ ምስሉ ጋር የማይናበብ መሆኑን በአስተውሎ መመልከት ያስፈልጋል።

5. የሰው ሰራሽ አስተውሎት መተግበሪያ አርማዎችን ቀድሞ መለየት፤

አንዳንድ የሰው ሰራሽ አስተውሎት ተንቀሳቃሽ ምስሎች የተሰሩበት መተግበሪያ አርማዎችን ወይም ምልክቶችን ያሳያሉ፤ በመሆኑም እነኚህን አርማዎች ቀድሞ ማወቅ ያስፈልጋ፡፡

በሴራን ታደሰ

 #ለጥንቃቄ*****በተቋማት ውስጥ የሳይበር ደህንነት ባህልን ለማጎልበት የሚረዱ መሠረታዊ ጉዳዮችየሳይበር ደህንነት ባህልን በተቋም ውስጥ ለመገንባት በሚከተሉት አራት ጉዳዮች ላይ ትኩረት ተሰ...
07/10/2025

#ለጥንቃቄ
*****

በተቋማት ውስጥ የሳይበር ደህንነት ባህልን ለማጎልበት የሚረዱ መሠረታዊ ጉዳዮች

የሳይበር ደህንነት ባህልን በተቋም ውስጥ ለመገንባት በሚከተሉት አራት ጉዳዮች ላይ ትኩረት ተሰጥቶ ሊሠራ ይገባል፡-

1 ከመሠረታዊ ጉዳዮች መጀመር

👉በተቋም ደረጃ ጠንካራ የይለፍ-ቃል አጠቃቀም ፖሊሲ መተግበር፤ ይህም አጥቂዎች ወደ ሥርዓቶቻችን በቀላሉ እንዳይገቡ ያደርጋቸዋል፤

👉ለሰራተኞች የደህንነት ፍተሻ ማድረግ፤ አንድ ሠራተኛ ከስራው በሚለቅበት ወቅት ወዲያውኑ ወደ መረጃ ቋቱ ወይም ሥርዓቱ የመግባት ፈቃድን ማቋረጥ እና አጠቃላይ የደህንነት ፍተሻ ማድረግ፤

2_ከሳይበር ጋር የተገናኙ ሥልጠናዎችን መከታተል

👉ሰራተኞች ቀጣይነት ባለው አግባብ የሳይበር ደህንነት ሥልጠናዎች እንዲያገኙ ማድረግ፤

👉 ከሠራተኞች የህይወት ዘይቤ ጋር የተያያዙ ምሣሌዎችን በመጠቀም የሳይበር ጥቃት ሊያስከትል የሚችለውን ጉዳት ማስገንዘብ፤

👉ሠራተኞች በሳይበር ደህንነት ዙሪያ ራሳቸውን ብቁ ማድረጋቸው ተቋሙ ለሚያደርገው የስኬት ጉዞ የጎላ አስተዋፅዖ የሚያበረክት መሆኑን እንዲገነዘቡት ማድረግ፤

3_ከሥልጠና በኋላ ሠራተኞች ያላቸውን ባህሪ መከታተል

👉ሰራተኞች በስልጠና ያገኙትን የደህንነት ማስጠበቂያ ምክረ ሀሳቦች ተግባራዊ እያደረጉ መሆኑን መፈተሽና ማረጋገጥ፤

👉የሳይበር ደህንነት ጉዳይ በተቋሙ ሠራተኞች መካከል ባህል እስከሚሆን ድረስ ተከታታይ ክትትልና ድጋፍ ማድረግ፤

4_ሠራተኞች የጥቃት ሙከራዎችን ሪፖርት እንዲያደርጉ ቀላል ሥርዓት መዘርጋት

👉ሠራተኞች በሚጠቀሟቸው ኮምፒውተሮችም ይሁን ሌሎች ከኢንተርኔት ጋር የተቆራኙ ሲስተሞች ላይ የሳይበር ጥቃት ምልክቶች ሲያጋጥማቸው በቶሎ ሪፓርት አንዲያደርጉ ማስገንዘብ፤

4ኛው የአፍሪካ ፋክትስ ሳሚት በሴኔጋል እየተካሄደ ነው****************ከ20 የአፍሪካ ሀገራት የተወጣጡ ከ200 በላይ ተሳታፊዎች የተገኙበት 4ኛው የአፍሪካ ፋክትስ ሳሚት በዳካር፣ ሴ...
02/10/2025

4ኛው የአፍሪካ ፋክትስ ሳሚት በሴኔጋል እየተካሄደ ነው
****************

ከ20 የአፍሪካ ሀገራት የተወጣጡ ከ200 በላይ ተሳታፊዎች የተገኙበት 4ኛው የአፍሪካ ፋክትስ ሳሚት በዳካር፣ ሴኔጋል እየተካሄደ ይገኛል።

በአፍሪካ ቼክ አዘጋጅነት ለሁለት ቀናት በሚካሄደው ጉባዔ ጋዜጠኞች፣ ተመራማሪዎች፣ የሲቪል ማህበረሰብ መሪዎች እና ፖሊሲ አውጭዎች ተገኝተዋል።

በእውነታ ላይ የተመሠረተ አስተማማኝ መረጃ፣ የሰው ሰራሽ አስተውሎት ተፅዕኖ፣ የተቀናጀ አሠራር አማራጮች እና የሐሰተኛ ዜና ተጋላጭነት የጉባኤው ዋነኛ አጀንዳዎች ናቸው።

በጉባዔው በአፍሪካ ውስጥ የሐሰተኛ መረጃ ስርጭትን በመከላከል ረገድ ያሉ ዕድሎች እና ፈተናዎችን በተመለከተ ውይይቶች ይደረጋሉ ተብሎ ይጠበቃል።

በተጨማሪም ጉባዔው በአህጉሪቱ ባለው የመረጃ ታማኝነት ሥነ-ምህዳር ውስጥ ያሉ የተለያዩ ባለድርሻ አካላትን በማሰባሰብ ፕሮጀክቶችን እና በእውነታ ማጣራት ሂደት ውስጥ ያሉ ዕድገቶችን የሚዳስስ ይሆናል።

ጉባዔው በፋክት ቼክ ለውድድር ከቀረቡ የዓመቱ የሐሰተኛ መረጃ ማጣራት ሥራዎች መካከል ለአሸናፊዎች እውቅና እና ሽልማት በመስጠት ይጠናቀቃል።

በሴራን ታደሰ

እንደ ወረርሽኝ እየተስፋፋ ያለውን የሃሰተኛ መረጃ ስርጭት እንዴት መከላከል ይቻላል?*******በየጊዜው ሃሰተኛ መረጃዎች ከአንዱ የዓለም ጫፍ ወደ ሌላኛው የዓለም ጫፍ በቀላሉ እየተሰራጩ በመ...
29/09/2025

እንደ ወረርሽኝ እየተስፋፋ ያለውን የሃሰተኛ መረጃ ስርጭት እንዴት መከላከል ይቻላል?
*******

በየጊዜው ሃሰተኛ መረጃዎች ከአንዱ የዓለም ጫፍ ወደ ሌላኛው የዓለም ጫፍ በቀላሉ እየተሰራጩ በመሆኑ ማኅበራዊ እና ስነ-ልቦናዊ ጉዳት እያስከተሉ ይገኛል ይላል ተመድ፡፡

በመሆኑም ማንኛውም ግለሰብ በማኅበራዊ ሚዲያ የሚያገኘውን መረጃ ከማጋራቱ በፊት 5 ጉዳዮችን ማጣራት እንደሚገባውም ተመድ ያሳስባል፡፡

በመጀመሪያ የመረጃ አዘጋጁ ማን ነው? የሚለውን ማጣራት የሚገባ ሲሆን፤ ይህም የመረጃውን አዘጋጅ እና ባለቤት ማንነት ለማወቅ እንደሚረዳ ተመድ ያመላክታል።

በሁለተኛ ደረጃ የመረጃ ምንጩ ማን ነው? የሚለውን ማጣራት ይገባል፤ ይህም የመረጃ ምንጩን ትክክለኛነት ለማረጋገጥ እንደሚረዳ ተመድ ያስቀምጣል።

በሶስተኛ ደረጃ መረጃው ከየት? እንደተገኘ ማወቅ ይገባል ይላል። መረጃው በትክክል ከየት እንደተነሳ መረዳትም አስፈላጊ መሆኑን ተመድ ይገልጻል።

በአራተኛ ደረጃ መረጃውን ለማጋራት ዓላማ ሊኖረን እንደሚገባ ማስታወስ እንደሚያስፈልግ ይጠቁማል።

በአምስተኛ ደረጃ ደግሞ መረጃው የተለቀቀው መቼ? እንደሆነ በተለያዩ መንገዶች ማረጋገጥ ይገባል ሲል አመላክቷል።

እነዚህን መረጃዎች በማጣራት የማኅበራዊ ሚዲያ አጠቃቀምን ማጎልበት እና ሃሰተኛ መረጃዎችን ከማሰራጨት መቆጠብ እንደሚገባም ተመድ አስገንዝቧል።

በላሉ ኢታላ

 #ለጥንቃቄ አንድን መረጃ በግል ማህበራዊ ሚዲያዎት ላይ ከማጋራትዎት በፊት ሊጠይቋቸው የሚገቡ 5ቱ ወሳኝ ጥያቄዎች*************1ኛ - መረጃውን ማን አቀናበረው?2ኛ - የመረጃው ምንጭ...
29/09/2025

#ለጥንቃቄ

አንድን መረጃ በግል ማህበራዊ ሚዲያዎት ላይ ከማጋራትዎት በፊት ሊጠይቋቸው የሚገቡ 5ቱ ወሳኝ ጥያቄዎች
*************

1ኛ - መረጃውን ማን አቀናበረው?

2ኛ - የመረጃው ምንጭ ማነው?

3ኛ - የመረጃው ከየት ተገኘ?

4ኛ - መረጃውን ለምንድን ነው የምናጋራው?

5ኛ - መረጃው መቼ የተለጠፈ ነው?

#ለምን

እንኳን ለመስቀል በዓል አደረሳችሁ
26/09/2025

እንኳን ለመስቀል በዓል አደረሳችሁ

ከስትራቴጂያዊ ጂኦፖለቲካዊ አቀማመጥ እስከ ከፍተኛ ተራሮች ተሞልታለች። ከታሪክ እስከ ቅርስ፣ ከኅብረ ብሔራዊነት እስከ ብዝኃ እምነት ተትረፍርፋለች። ኢትዮጵያ ከስጦታዎች ይህ አጠራት የምትባል...
25/09/2025

ከስትራቴጂያዊ ጂኦፖለቲካዊ አቀማመጥ እስከ ከፍተኛ ተራሮች ተሞልታለች። ከታሪክ እስከ ቅርስ፣ ከኅብረ ብሔራዊነት እስከ ብዝኃ እምነት ተትረፍርፋለች። ኢትዮጵያ ከስጦታዎች ይህ አጠራት የምትባል አይደለችም።

(የመደመር መንግሥት መጽሐፍ ገጽ 41)

ፍጥነትን እውን የማድረጊያ መንገዶች (ከመደመር መንግሥት መጽሐፍ ገጽ 88 ላይ የተወሰደ)
25/09/2025

ፍጥነትን እውን የማድረጊያ መንገዶች

(ከመደመር መንግሥት መጽሐፍ ገጽ 88 ላይ የተወሰደ)

Address

Shegole, Addisu Gebeya
Addis Ababa
1000

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when EBC Fact Check posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share