09/03/2026
ቻይና ለኢራን የባሊስቲክ ሚሳኤሎችን ማስተላለፏ ተነገረ‼
📌 ፕሬዝዳንት ዢም ለምዕራባውያን ማስጠንቀቂያ ሰጡ‼
ቻይና DF-21D የተሰኙ መርከብ አውዳሚ የባሊስቲክ ሚሳኤሎችን ለኢራን በምስጢር ሳታስተላልፍ እንዳልቀረች የሚጠቁሙ መረጃዎች መውጣታቸውን ተከትሎ በቀጠናው ያለው ውጥረት አይሏል።
ምንም እንኳን መረጃው በይፋ ባይረጋገጥም፣ የመከላከያ ተንታኞች ጉዳዩን በስጋት እየተከታተሉት ይገኛሉ።
ይህ በእንዲህ እንዳለ፣ የቻይናው ፕሬዝዳንት ዢ ጂንፒንግ "ዓለም የማንም የግል ንብረት አይደለችም" በሚል ለምዕራባውያን ጠንካራ ማስጠንቀቂያ አስተላልፈዋል።
ፕሬዝዳንቱ ዓለምን "የእኛ ናት" ከሚሉ ኃይሎች ነፃ ለማውጣት እንደሚሰሩ የገለጹ ሲሆን፣ ይህም የቻይናን ወታደራዊ ግስጋሴና አዲስ የኃይል ሚዛን ፍለጋን የሚያመላክት መሆኑ ተነግሯል።