
25/07/2025
ዓመታዊው የቁልቢ ገብርኤል የንግስ በዓል በሰላም ተከብሮ እንዲያልፍ የምስራቅ ሐረርጌ ዞን ፖሊስ በቂ ዝግጅት ማድረጉን አስታወቀ
(ባላገሩ ቴሌቪዥን ፣ሀምሌ 18 ቀን 2017 ዓ.ም)
ምዕመናን ከወዲሁ ለንግስ በዓሉ ወደ አካባቢው እየተጓዙ ሲሆን ነገም በስፋት ይጓዛሉ፤ ቁልቢና አካባቢው ገብተውም ያድራሉ።
ፖሊስ በዓሉ በሰላም ተከብሮ እንዲጠናቀቅ በቂ ዝግጅት መደረጉን አመልክቷል።
በአካባቢው ዳገት፣ ቁልቁለት እና ጠመዝማዛ መንገድ ስለሚበዛና ወቅቱም ደግሞ ክረምት ስለሆነ አሽከርካሪዎች ተገቢውን ጥንቃቄ በማድረግ እንዲሁም የትራፊክ ህግና ደንብ በማክበር እንዲያሽከረክሩ ማሳሰቢያ ተላልፏል።
የበዓሉ ታዳሚዎች ወደ በዓሉ ስፍራ ሲጓዙም ንብረቶቻቸውን በጥንቃቄ መያዝ አለባቸው ተብሏል።
ENA