Balageru TV

Balageru TV Balageru television, promotes Ethiopian history, culture, tradition, lifestyle, investment, tourism..
(1)

Our Channel Frequency
NSS12 57 Degree East HD, Freq - 11105, Pol - Horizontal, S/R - 45000
or
DSTV Channel - 484

ዓመታዊው የቁልቢ ገብርኤል የንግስ በዓል በሰላም ተከብሮ እንዲያልፍ የምስራቅ ሐረርጌ ዞን ፖሊስ በቂ ዝግጅት ማድረጉን አስታወቀ (ባላገሩ ቴሌቪዥን ፣ሀምሌ 18 ቀን 2017 ዓ.ም)ምዕመናን ከ...
25/07/2025

ዓመታዊው የቁልቢ ገብርኤል የንግስ በዓል በሰላም ተከብሮ እንዲያልፍ የምስራቅ ሐረርጌ ዞን ፖሊስ በቂ ዝግጅት ማድረጉን አስታወቀ

(ባላገሩ ቴሌቪዥን ፣ሀምሌ 18 ቀን 2017 ዓ.ም)

ምዕመናን ከወዲሁ ለንግስ በዓሉ ወደ አካባቢው እየተጓዙ ሲሆን ነገም በስፋት ይጓዛሉ፤ ቁልቢና አካባቢው ገብተውም ያድራሉ።

ፖሊስ በዓሉ በሰላም ተከብሮ እንዲጠናቀቅ በቂ ዝግጅት መደረጉን አመልክቷል።

በአካባቢው ዳገት፣ ቁልቁለት እና ጠመዝማዛ መንገድ ስለሚበዛና ወቅቱም ደግሞ ክረምት ስለሆነ አሽከርካሪዎች ተገቢውን ጥንቃቄ በማድረግ እንዲሁም የትራፊክ ህግና ደንብ በማክበር እንዲያሽከረክሩ ማሳሰቢያ ተላልፏል።

የበዓሉ ታዳሚዎች ወደ በዓሉ ስፍራ ሲጓዙም ንብረቶቻቸውን በጥንቃቄ መያዝ አለባቸው ተብሏል።
ENA

ተዋናይት ሃረገወይን አሰፋ፣ ተዋናይ ሸዋፈራሁ ደሳለኝ እና ተዋናይ የኋላሸት ዘሪሁን የሚተውኑበት "ወደ ማዶ" የተሰኘ ትያትር በ30 የአለም ሀገራት መድረኮች ሊቀርብ ነው።(ባላገሩ ቴሌቪዥን ፣...
25/07/2025

ተዋናይት ሃረገወይን አሰፋ፣ ተዋናይ ሸዋፈራሁ ደሳለኝ እና ተዋናይ የኋላሸት ዘሪሁን የሚተውኑበት "ወደ ማዶ" የተሰኘ ትያትር በ30 የአለም ሀገራት መድረኮች ሊቀርብ ነው።

(ባላገሩ ቴሌቪዥን ፣ሀምሌ 18 ቀን 2017 ዓ.ም)

* ከትያትሩ ጎን ለጎን ለልብ ህሙማን ህፃናት መርጃ ማዕከል የገቢ ማሰባሰቢያ ይካሄዳል።

የኪነ ጥበብ ስራዎችን በአለም አቀፍ መድረኮች ይዞ የመጓዝ እና የማሳየት የረጅም ጊዜ ልምድ ያለው ዋካ ፕሮሞሽንና ኢቨንት እስካሁን ባልተለመደ መልኩ በ30 አለም አቀፍ መድረኮች የሚታይ ትያትር ፕሮዲውስ አድርጓል።

"ወደ ማዶ" የተሰኘው እና ኮሜዲ ዘውግ ያለው ትያትር በትወና ብቃቷ ከፍተኛ የተመልካች ፍቅርና አድናቆት ያላት ሃረገወይን አሰፋን ጨምሮ ሸዋፈራው ደሳለኝ እና የኋላእሸት ዘሪሁን ይተውኑበታል።

በቴዎድሮስ ተ/አረጋይ ተደርሶ በሴም አማኑኤል የተዘጋጀው "ወደ ማዶ" ትያትር ማህበራዊ ጉዳዮችን እያነሳ የሚሄስ፤ ሲሆን በህወታችን የሚገጥሙን ችግሮች ለማውጣት የሚደረግን ትንቅንቅ የሚያሳይ ሲሆን ከፍ ያለ ዝግጅትም የተደረገበት ነው።

ወደ ማዶ" አለም አቀፍ የትያትር ጉዞ ለሚቀጥሉት ሦስት ዓመታት ትውልደ ኢትዮጵያውያን በሚገኙባቸው በአፍሪካ፣ በመካከለኛው ምስራቅ፣ በአውሮፓና በሰሜን አሜሪካ አህጉራት በሚገኙ ሀገራት እንዲሁም በኢትዮጵያ ከ30 በላይ መድረኮች ይታያል።

በተጨማሪም እስካሁን ባልተለመደ መልኩ ትያትሩ በሚታይባቸው ሀገራትና መድረኮች ከትያትሩ ጎን ለጎን ለ"የኢትዮጵያ የልብ ህሙማን ህፃናት መርጃ ማዕከል" የገቢ ማሰባሰቢያ ይካሄዳል።
ይህንንም በጎ አላማ ለማሳካት ከማዕከሉ ጋር የመግባቢያ ስምምነት ይፈረማል።

የትያትሩ ይፋዊ የመክፈቻ መርሃ ግብር ታላላቅ የኪነ ጥበብ ባለሙያዎች፣ የጥበብ ወዳጅ ኢትዮጵያውያን በተገኙበት በነሐሴ ወር በአፍሪካ የተለያዩ ሃገራት ይደረጋል።
ትያትሩን ፕሮዲውስ ያደረገው ዋካ ፕሮሞሽንና ኤቨንት በኪነ ጥበቡ ሰፊ እንቅስቃሴዎችን በማድረግ የረጅም ጊዜ ልምድ የካበተ ሲሆን ትያትርና ፊልሞችን ጨምሮ የተለያዩ ሁነቶችን በማዘጋጀት ይታወቃል።
ከዚህ ቀደም ለመጀመሪያ ጊዜ በኢትዮጵያ ብሔራዊ ሙዚየም በሙዚቃ መሳሪያ የታጀበ የስዕል አውደ ርዕይ አዘጋጅቷል። በተጨማሪ በናይጄሪያ አቡጃ እና በጣሊያን (ሮም) ከተሞች የስዕል አውደ ርዕይ ከሙዚቃ ጋር የቀረበበትን ዝግጅት ሲያካሂድ፤ በፈረንጆቹ 2023 ደግሞ አሜሪካን ሃገር ከሚገኘው ግሎባል ትሬድ ኔትወርክ ጋር በጋራ በመሆን በቤልቪው ሆቴል ትሬድ ሰሚት አካሂዷል።

ዋካ ፕሮሞሽንና ኤቨንት "ጥቅለ ኪነ ጥበባት" በሚል በተለያዩ ቦታዎች በመዘዋወር የኪነ ጥበብ ስራዎችን አቅርቧል።
በተለያዩ የክልል ከተሞች በሚገኙ ቴአትር እና ሲኒማ ቤቶች የተለያዩ የኪነ ጥበብ ስራዎችን ከመከወን ባለፈ ለኩላሊት ህመምተኞች የገቢ ማሰባሰቢያ በጎ አድራጎት ስራንም ሰርቷል።

የመጨረሻ ውሳኔ !የጋሞ ዞን ከፍተኛ ፍርድ ቤት በአለልኝ አዘነ ጉዳይ የመጨረሻ ፍርድ ዛሬ ሰጥቷል።በተከሳሽ የአለልኝ ባለቤት አደይ ጌታቸዉና በእህቷ ባል ሉንጎ ሉቃስ ላይ የ16 እና 15 ዓመ...
22/07/2025

የመጨረሻ ውሳኔ !

የጋሞ ዞን ከፍተኛ ፍርድ ቤት በአለልኝ አዘነ ጉዳይ የመጨረሻ ፍርድ ዛሬ ሰጥቷል።በተከሳሽ የአለልኝ ባለቤት አደይ ጌታቸዉና በእህቷ ባል ሉንጎ ሉቃስ ላይ የ16 እና 15 ዓመት ፅኑ እስራት ተፈርዶባቸዋል።

አለልኝ አዘነ ጋብቻውን በፈጸመ በቀናት ውስጥ ህይወቱ ሲያልፍ ራሱን እንዳጠፋ ሲነገር ቢቆይም፤ በተደረገ ምርመራ እና የፍርድ ሂደት ባለቤቱና በባለቤቱ እህት ባል በተቀነባበረ ሁኔታ መገደሉን የጋሞ ዞን ከፍተኛው ፍ/ቤት በማረጋገጡ ተከሳሾቹ የ16 እና 15 ዓመት ፅኑ እስራት ተፈርዶባቸዋል።

ባላገሩ ስፖርት

ትራምፕ ለሶስተኛ ጊዜ አሜሪካ ለታላቁ የ ኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ግንባታ የገንዘብ ድጋፍ አድርጋለች ሲሉ በአንድ መድረክ ላይ ተናገሩ(ባላገሩ ቴሌቪዥን ፣ሀምሌ 14 ቀን 2017 ዓ.ም)የአሜሪካው...
21/07/2025

ትራምፕ ለሶስተኛ ጊዜ አሜሪካ ለታላቁ የ ኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ግንባታ የገንዘብ ድጋፍ አድርጋለች ሲሉ በአንድ መድረክ ላይ ተናገሩ

(ባላገሩ ቴሌቪዥን ፣ሀምሌ 14 ቀን 2017 ዓ.ም)

የአሜሪካው ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ ባሳለፍነው ሳምንት አርብ ዕለት የሪፐብሊካን ሴናተሮችን በዋይት ሀውስ ተቀብለው ባስተናገዱበት ወቅት ባደረጉት ንግግር፤ ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ በአሜሪካ የገንዘብ ድጋፍ እንደተደረገለት ሲናገሩ ተደምጠዋል።

“ኢትዮጵያ ግድቡን የገነባችው በአብዛኛው በአሜሪካ ገንዘብ ነው” ሲሉ በአንድ ወር ውስጥ ለሶስተኛ ጊዜ ተናግረዋል።

እውነታው ግን ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ የተገነባው ሙሉ በሙሉ በኢትዮጵያ ህዝብ በህዝባዊ መዋጮ እና በአገር ውስጥ ሀብት መሆኑ ነው። በተጨማሪም ግድቡ ለግብፅ የውሃ ደህንነት ምንም አይነት ስጋት አይፈጥርም።

በድጋሜ አዲስ ስታንዳርድ የኢትዮጵያ መንግስት ከአሜሪካ ጋር ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነቱን እንዲያጠናክር እና እነዚህን አሳሳች ትርክቶች ለመመከት እና ማስተካከያ ለማድረግ ጠንካራ አቋም እንዲይዝ በድጋሚ ጥሪ ያቀርባል።

የአንጋፋው ስፖርት ጋዜጠኛ ጥሩነህ ካሳ መፅሀፍ ለህትመት ሊበቃ ነው። በኢትዮጵያ ስፖርት ጋዜጠኝነት ከ30 አመታት በላይ በስፖርት ህትመት ሚዲያው ዘርፍ በታታሪነት የሰራው  ጥሩነህ ካሳ መፅሀ...
21/07/2025

የአንጋፋው ስፖርት ጋዜጠኛ ጥሩነህ ካሳ መፅሀፍ ለህትመት ሊበቃ ነው።

በኢትዮጵያ ስፖርት ጋዜጠኝነት ከ30 አመታት በላይ በስፖርት ህትመት ሚዲያው ዘርፍ በታታሪነት የሰራው ጥሩነህ ካሳ መፅሀፍ ለህትመት ሊበቃ መሆኑን ሰምተናል።

''ከኢትዮጵያ ሻምፒዮና እስከ ቤትኪንግ ፕሪሚየር ሊግ''80 አመታት ከኢትዮጵያ እግር ኳስ ጋር በሚል አርዕስት የተዘጋጀው መፅሀፉ ፤ ጋዜጠኛውን ለማበረታታትና እውቅና ለመስጠት በኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ሙሉ ወጪ መፅሀፉ እንደሚታተም አውቀናል።

መፅሀፉ ባለሙሉ ቀለም 316 ገፆች ያሉት፣ በሶስት ምዕራፍ የተከፈለ ፣ የ80 ዓመት የሊግ ታሪክ። 23 ታሪካዊ የስፖርት ሰዎች ቃለ ምልልሶች ፣ ቁጥሮች ፣እውነታዎች ፣ አስገራሚ ታሪኮች፣ የ80 ዓመት 50 እውነታዎች ተካተውበታል።

አንጋፋው ስፖርት ጋዜጠኛ ጥሩነህ ካሳ ስፖርት ጋዜጦች ወርቃማ ዘመን ዝነኛ የሆነው የወርልድ ስፖርት ጋዜጣ ዋና አዘጋጅ በመሆን ከ26 አመታት በላይ ሰርቷል።

በቅርብ ጊዜ በሸገር ኤፍኤም፣በብስራት ሬዲዮ በተለያዩ የስፖርት ፕሮግራሞች በማገልገል፣ያካበተውን እውቀት በተለያዩ የመገናኛ ብዙሀን መንገዶች ለአድማጭ ተመልካች መረጃ እያደረሰ ይገኛል ።

ባላገሩ ስፖርት

ኢትዮጵያ ቡና ወጣቱን አብይ ካሳሁንን ዋና አሰልጣኝ አድርጎ ሾመ!ኢትዮጵያ ቡና እግር ክለብ ወጣቱን አሰልጣኝ አብይ ካሳሁንን የዋናው ቡድን ዋና አሰልጣኝ አድርጎ መሾሙ ታውቋል።አሰልጣኝ አብይ...
21/07/2025

ኢትዮጵያ ቡና ወጣቱን አብይ ካሳሁንን ዋና አሰልጣኝ አድርጎ ሾመ!

ኢትዮጵያ ቡና እግር ክለብ ወጣቱን አሰልጣኝ አብይ ካሳሁንን የዋናው ቡድን ዋና አሰልጣኝ አድርጎ መሾሙ ታውቋል።

አሰልጣኝ አብይ ካሳሁን ከ20 ዓመት በታች ኢትዮጵያ ቡናን ቡድን አምና የሊግ ዋንጫን ካሳካ በኋላ ፤ በዘንድሮ ውድድር አመት ከድሬድዋ ጨዋታዎች መልስ የዋናውን ቡድን በምክትል አሰልጣኝ ሚና እንዲቀላቀል የክለቡ ቦርድ ማድረጉ ይታወሳል።

አሰልጣኝ አብይ ካሳሁን በኢትዮጵያ እግር ኳስ አሰልጣኘነት በቅርብ አመታት አቅም ካላቸው ወጣት አሰልጣኞች ውስጥ አንዱ እንደሆነ ይነገርለታል።

አሰልጣኝ አብይ ፣ ካሳዪ አራጌ በ1995 ቡናን ካሰለጠነ በኋላ በእድሜ ትንሹ የክለቡ አሰልጣኝ በመሆን ታሪካዊ ሆኗል ። አንዋር ያሲን ፣እድሉ ደረጄ በወጣትነታቸው ኢትዮጵያ ቡናን ካሰለጠኑት ውስጥ ይጠቀሳሉ።

አሰልጣኝ አብይ በርካታ ታዳጊዎችን በሀሌታ አካዳሚ በማፍራት ፣ ከስኮትላንድ የአውሮፖ የUAFA ''C'' ፣ ከኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን የCAF ''B'' ላይሰንስ ወስዷል። ከ20 ፣ ከ17 አመት በታች የኢትዮጵያ ብሄራዊ ቡድን በምክትል አሰልጣኝነትም ማገልገሉ ይታወሳል።

አሰልጣኝ አብይ በሶስት አመት ውል ከክለቡ ጋር ሲቆይ ከ20 አመት በታችና ከ17 አመት በታች ቡድንን እንደሚቆጣጠር የወጣት ተጨዋቾች እድገት ላይ ቀጥተኛ ሚና እንደተሰጠው ለማውቅ ተችሏል።

ባላገሩ ስፖርት

እንደርታ ፣ሀማሴን፣ አካለጉዛይ፣ የሶዶ ምንጭ ...... በታሪክ ለ3ኛ ጊዜ የኢትዮጵያ እግር ኳስ ክለቦች ስም እንዲቀይሩ ይገደዱ ይሆን? ! የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን  ክለቦች የብሄር ...
18/07/2025

እንደርታ ፣ሀማሴን፣ አካለጉዛይ፣ የሶዶ ምንጭ ......

በታሪክ ለ3ኛ ጊዜ የኢትዮጵያ እግር ኳስ ክለቦች ስም እንዲቀይሩ ይገደዱ ይሆን? !

የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ክለቦች የብሄር ስም ያላቸውን ቀይረው እንደዲመዘገቡ ቅድመ ሁኔታ አስቀምጧል። እኛም እንደመነሻ የ4 የክለብ አመራሮችን በማናገር መቼ ለመቀየር እንዳሰቡ ጠይቀናል ። ተቀራራቢ መልስ የሰጡን ክለቦቹ በቅርቡ በይፋ ሂደቱን እንደሚያሳውቁና ለጊዜው መረጃ ለመስጠት እንደሚቸገሩ ነው የነገሩን ። እኛም እየተከታተልን እናቀርባለን።

ይህ በታሪክ ለሶስተኛ ጊዜ ነው ። ከተፈፀመ.......

ታላቁ የአፍሪካ የእግር ኳስ አባት አቶ ይድነቃቸው ተሰማ ኢትዮጵያን በካፍና በፊፋ ወክለው አስገዳዳጅ አንቀፅ እንዲገባ ታሪካዊ ትግሎች ካደረጉበት ውሳኔዎች አንዱ የዘረኝነት ጉዳይ ነው።

ደቡብ አፍሪካን በካፍ መስራች እንዳትሆን ብቻ ሳይሆን የአለም ዋንጫ ለአፍሪካ በተሰጠው ኮታ እንዳትወዳደር አስከማድረግ የደረሰ ታሪካዊ ስራ ሰርተዋል።

ይህም የሆነው ለንደን 1951 የፊፋ ጉባኤ ጀምሮ ስራ አስፈፃሚ ሆነው ኢትዮጵያን በመወከል እልህ አስጨራሽ ጥረት በማድረግ በ1961 ጓዳላሃራ ላይ በተደረገ የፊፋ ጉባኤ የፊፋ በዘር ሀይማኖት ፖለቲካ ልዩነትን የሚያወግዝውን አንቀፅ ጥረታቸው ፍሬ አፍርቶ እንዲካተት አድርገዋል። ከሴኔጋሉ ከሪቶ አልካንትራ ጋር ተጨማሪ ስራ አስፈፃሚ አፍሪካ ያገኘችበት ወቅትም ትልቅ ታሪክ ሆኖ አብረው በአለም አቀፉ እግር ኳስ ማህበር (ፊፋ) የኢትዮጵያና የአፍሪካን ስም ከፍ አድርገዋል።

ለእግር ኳሱ እድገት አብዘተው የለፉት ታላቁ ይድነቃቸው ተሰማ በካፍ እና በፊፋ የታገሉለት ነፃ እግር ኳስ በኢትዮጵያውያን ፈተና የሆነባቸውን ወቅቶችንም በመረዳት ጠቃሚ ውሳኔዎች ለትውልድ አስተላልፈዋል። የአፍሪካ ክለቦች የጎሳ ስያሜ ያሳስባቸውም ነበር ።
በፋሺስት ጣሊያን ዘመን በአዲስ አበባ ቅዱስ ጊዮርጊስ በግድ ወደ ሊቶሪዮ ውቤ ሰፈር ስሙ እንዲባል ሲያደርጉ ፤ በድኖችን ፖለቲካዊና የጎሳ የሀይማኖት ስም እንዲይዙ ፋሺስቶቹ ትዕዛዝ ይሰጡ ነበር ።በከፋፍለህ ግዛ የፖለቲካ መመሪያ በመከተል ልዩ ልዩ ስሞች ለክለቦች እንዲወጣ ያስገድዱ ነበር ።

ይህን በደንብ የተረዱት ታላቁ ይድነቃቸው ተሰማ የፈሩት ደርሶ በኢትዮጵያ የጨዋታ ውጤቶች ከሜዳ አልፈው ሌላ መልክ በመያዛቸው በማሳሰቡ አስገዳጅ ለውጥ ያደረጉበት ዘመን ነበር ።

የኢትዮጵያ ስፖርት ክለቦች በጎሳ በሀይማኖት ስሜት እንዳይመሩ ማድረግ የፌዴሬሽኑ ዋና ተግባር ነው በማለት 1958 ዓ.ም የሚከተሉት ክለቦች ስም እንዲቀይሩ አስደረጉ።

ሐማሴን ቡድን -----------------አስመራ ።
አካለ ጉዛይ-------------------እምባሶራይ።
የሰራዬ ቡድን---------------- መንደፈራን ።
የሎጎጭዋ ቡድን-------------- ማይለሃም ።
የሶዶ ምንጭ ቡድን --------------አዋሽ ምንጭ ።
የእንደርታ ቡድን ------------------በራሃሌይ.. ። እንዲባሉና ስማቸው የጎሳና የሀይማኖት መልክ የያዘ ሁሉ እንዲለወጥ አድርገዋል ።

የመቀሌ 70 እንደርታ እግር ኳስ ክለብ ዘንድሮ ከቀየረ ለሁለተኛ ጊዜ እንደርታ የሚለውን ስሙን ሊለውጥ እንደሚችል ታሪክ ይመሰክራል።

ሀማሴን በ1947 የኢትዮጵያ ሻምፒዮና ካሸነፈ በኋላ ስሙን ቀይሮ በተከታታይ በ1964/65 የኢትዮጵያ ሻምፒዮን ሆኗል። በቀጣይ አመት በ66 እምቧይሰራም ስም ቀይሮ ዋንጫ በልቷል...።

ታላቁ ይድነቃቸው ተሰማ በመጀመሪያዎቹ የኢትዮጵያ እግር ኳስ የክለቦች ውድድር አጀማመር ስም የመቀየር ትልቅ ፈተናም ነበር። የወታደሩና የፖሊስ ቡድኖች ፈተና በሆኑባቸው አመታት ነበር.. መሸናነፉ መሳሪያ እያከመማዘዝ ደርሶ የሰው ህይወት አደጋ መሆኑ ያሰጋቸው በ1947 ዓም የሰራዊት ቡድኖች እንዲወዳደሩ ሲደረግ ስማቸውን እንዲቀይሩና ጤናማ የፉክክር መንፈስ እንዲፈጠር ተደርጓል። ...በዚህም

የጦር ሰራዊት ቡድን -- መቻል
የክብሩ ዘበኛ ቡድን...... መኩሪያ
አየር ሀይል ............ንብ
የፖሊስ ቡድን ...... ኦሜድላ ተብለው እንዲቀየሩ ተደርጓል።

ለዘላቂ መፍትሄ ...

የጎሳ ስሜት፣ የአካባቢው ስሜት ለእግር ኳስ አስፈላጊ ነው። ጤነኛ መንገድ ሆኖ ብንጠቀም ነበር ትክክል የሚሆነው። ህዝባዊ መሰረት ያለው ከማንነት ጋር አስተሳስሮ እድገት እንዲያመጣ ወደ ጤናማ የእግር ኳሱ ኢንዱስትሪ እንዲያያድግ የሚያደርግ ክለቦች መፍጠር ይቻል ነበር። የሀገራችን ተጨባጭ ሁኔታ ይህን ባለመፍቀዱ... ፌዴሬሽኑ የእግር ኳሳዊ ውሳኔዎቹ በሌላ መልክ መታየታቸው አሳስቦት ..በታሪክ ለ3ኛ ዘመን ክለቦች ስም እንዲቀይሩ ተጠይቋል ....

ክለቦች የመጨረሻ ግባቸው የሀገር እግር ኳስ እድገት በመሆኑ በበጎ ውሳኔውን ተመልክተው መቀየር እንደሚመከር ታሪክ ያሳየናል ።
የፌዴሬሽኑ የማስፈፀም አቅም ታላቁ ይድነቃቸው ተሰማ በነበሩበት ዘመን አይነት ነው ወይ? የሚለው የሚለካበት ውሳኔ እንደሚሆን ይጠበቃል ....

በጋዜጠኛ አብይ ዘላለም (ባላገሩ ስፖርት አዘጋጅ ) ።

የታላቁ ሩጫ በኢትዮጵያ ሀያ አምስትኛ አመት የውድድር ምዝገባ በይፋ ተጀመረ!ታላቁ ሩጫ በኢትዮጵያ 25ኛ አመቱ 10 ኪ.ሜ የሩጫ ውድድርን አስመልክቶ ዛሬ ከሰአት በሀያት ሪጀንሲ ሆቴል በልዩ ...
17/07/2025

የታላቁ ሩጫ በኢትዮጵያ ሀያ አምስትኛ አመት የውድድር ምዝገባ በይፋ ተጀመረ!

ታላቁ ሩጫ በኢትዮጵያ 25ኛ አመቱ 10 ኪ.ሜ የሩጫ ውድድርን አስመልክቶ ዛሬ ከሰአት በሀያት ሪጀንሲ ሆቴል በልዩ የመድረክ በይፋ ምዝገባ አስጀምሯል።

በመድረኩ በታላቁ ሩጫ በኢትዮጵያ ንቁ ተሳትፎ በማድረጋቸው የተለያዩ ተቋማት በሰራተኞቻቸው ስም እውቅና ከክብር እንግዶች ተበርክቶላቸዋል።

የሴቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ሚኒስትሯ ኤርጎጌ ተስፋዬ ፣ ቱሪዝም ሚኒስቴር ዴኤታ ዶ/ር እንደገና አበበ የመክፈቻ ንግግር በማድረግ የታላቁ ሩጫ በኢትዮጵያ እንደሀገር እያደረገ ያለውን አስተዋፅኦ በመጥቀስ አበረታተዋል።

በዛሬው መርሀ ግብር የመገናኛ የብዙሀን ባለሙያዎች ፣ ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች በተገኙበት 25ኛ አመትን አስመልክቶ ልዩ ልዩ ትውስታዎች በቪዲዮና በመድረክ ስራ ቀርበዋል።

55ሺ ተሳታፊዎች እንደሚወዳደሩ ሲጠበቅ ፤ የውድድሩ ምዝገባ ከነገ ጀምሮ በቴሌብር ሱፐር አፕ ፣በዳሽን ባንክ አፕ በኦንላይን ምዝገባው እንደሚጀመር ይፋ ሆኗል ።

ባላገሩ ስፖርት

‎ሲዳማ ቡና ክለብ ለCAS ይግባኝ  ማስገባቱን አረጋግጧል !‎የሲዳማ ቡና እግር ኳስ ክለብ ለአለም አቀፉ የስፖርት ግልግል ይግባኝ ማስገባቱና ተቀባይነት ማግኘቱን የክለቡ ስራ አመራር ቦርድ ...
17/07/2025

‎ሲዳማ ቡና ክለብ ለCAS ይግባኝ ማስገባቱን አረጋግጧል !


የሲዳማ ቡና እግር ኳስ ክለብ ለአለም አቀፉ የስፖርት ግልግል ይግባኝ ማስገባቱና ተቀባይነት ማግኘቱን የክለቡ ስራ አመራር ቦርድ ዛሬ ለባላገሩ ስፖርት ማረጋገጫ ሰጥቷል።

‎CAS ጉዳዩን መቀበሉን ለኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን በላከው ኢሜል መግለፁን ክለቡ ሲገልፅ ፤ ትናንት የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን የህዝብ ግንኙነት ባለሙያ አቶ አብርሀም ማረጋገጫ አልደረሰንም ማለታቸውን መረጃ ማቅረባችን ይታወሳል።

ለፊፋ ፣ ለካፍ በግልባጭ ይግባኙ ተቀባይነት ማግኘቱን ክለቡ በይፋ ማረጋገጡን አስታውቋል።


ባላገሩ ስፖርት

የኢትዮጵያ አየር መንገድ አዉሮፕላን በመቐለ አሉላ አባነጋ አውሮፕላን ማረፊያ  መጠነኛ እክል አጋጠመው (ባላገሩ ቴሌቪዥን ፣ሀምሌ 10 ቀን 2017 ዓ.ም) የኢትዮጵያ አየር መንገድ የበረራ ቁ...
17/07/2025

የኢትዮጵያ አየር መንገድ አዉሮፕላን በመቐለ አሉላ አባነጋ አውሮፕላን ማረፊያ መጠነኛ እክል አጋጠመው

(ባላገሩ ቴሌቪዥን ፣ሀምሌ 10 ቀን 2017 ዓ.ም)

የኢትዮጵያ አየር መንገድ የበረራ ቁጥር ET-298 የሆነ አውሮፕላን በዛሬው ዕለት በመቐለ አሉላ አባነጋ አውሮፕላን ማረፊያ ካረፈ በኋላ ከመንደርደሪያው መጠነኛ የመንሸራተት እክል አጋጥሞታል።

አየር መንገዱ ባወጣው መግለጫ አውሮፕላኑ ከአዲስ አበባ ተነስቶ ወደ መቐለ በመብረር አሉላ አባነጋ አውሮፕላን ማረፊያ ሲደርስ ዝናብ እየዘነበ ነበር ብሏል።

እስካሁን ባለው መረጃ በመንገደኞች ላይ ምንም አይነት ጉዳት ያልደረሰና በሰላም ከአውሮፕላኑ እንዲወርዱ መደረጉን ገልጿል።

በሁለት የበረራ ሰራተኞቻችን ላይ መጠነኛ ጉዳት በማጋጠሙ ለተጨማሪ የህክምና ዕርዳታ በአቅራቢያ ወደሚገኝ የህክምና መስጫ ተቋም ተወስደው ከታከሙ በኋላ ወደ ሆቴል እንዲሄዱ ተደርጓል ሲል አስታውቋል።

አየር መንገዱ ለተፈጠረው መጉላላት ይቅርታ በመጠየቅ ተጨማሪ መረጃ ሲኖር የሚያሳውቅ መሆኑን ጠቁሟል።

ሰበር ዜና !የብሄር ስያሜ የያዘ እግር ኳስ ክለብ በሚቀጥለው አመት አይወዳደርም!ክለቦች ለአዲሱ የውድድር ዘመን ምዝገባ ሊያሟላቸው የሚገቡ መስፈርቶች በሚል የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ቅ...
16/07/2025

ሰበር ዜና !

የብሄር ስያሜ የያዘ እግር ኳስ ክለብ በሚቀጥለው አመት አይወዳደርም!

ክለቦች ለአዲሱ የውድድር ዘመን ምዝገባ ሊያሟላቸው የሚገቡ መስፈርቶች በሚል የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ቅድመ ሁኔታ አስቀምጧል።

ማንኛውም ኢትዮጵያዊ ክለብ በሚቀጥለው አመት በየትኛውም የእርከን ውድድሮች የብሄር ስያሜ ያለውን ስያሜ በመቀየር በአዲስ ስም እንዲመዘገብ ቅድመ ሁኔታ ተቀምጧል።

ከክለቦቹ የብሄር ስያሜ ጋር ተያይዞ መለያ(አርማ) የፖለቲካ ወይም የብሄር ይዘቶች ያላቸው መልዕክት ወይም ምስል መጠቀም እንደማይቻልም ተገልጿል።

ባላገሩ ስፖርት

ወላይታ ዲቻ በካፍ ኮንፌዴሬሽን ዋንጫ ኢትዮጵያን ይወክላል?(ባላገሩ ቴሌቪዥን ፣ሐምሌ 9 ቀን 2017 ዓ.ም)የወላይታ ዲቻ እግር ኳስ ክለብ በአፍሪካ የክለቦች ኮንፌዴሬሽን ዋንጫ  ለመሳተፍ የ...
16/07/2025

ወላይታ ዲቻ በካፍ ኮንፌዴሬሽን ዋንጫ ኢትዮጵያን ይወክላል?

(ባላገሩ ቴሌቪዥን ፣ሐምሌ 9 ቀን 2017 ዓ.ም)

የወላይታ ዲቻ እግር ኳስ ክለብ በአፍሪካ የክለቦች ኮንፌዴሬሽን ዋንጫ ለመሳተፍ የሚያስችሉ ቅድመ ሁኔታዎችን በማሟላት ምዝገባ መፈፀሙ ታውቋል።

የክለቡ ስራ አስኪያጅ አቶ አሰፋ ሆሲሶ ዛሬ በወላይታ ወጌታ 96.6 ሬዲዮ ቀርበው ስለ ጉዳዩ ማብራሪያ ከሰጡ በኋላ ባላገሩ ስፖርት ባደረገው የማረጋገጫ ማጣራት ፣ከኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ፣ ከክለቡ ስራ አስኪያጅ አቶ አሰፋ ሆሲሶ ምዝገባው መከናወኑን አረጋግጠናል ።

የኢትዮጵያ ዋንጫ ውጤት ተሰርዞ ለወላይታ ዲቻ ክለብ ዋንጫው እንዲሆን ከተወሰነ በኋላ ሲዳማ ቡና እግር ኳስ ክለብ ለአለም አቀፉ የስፖርት ግልግል ይግባኝ አስገብቶ ጉዳዩ እየታየለት መሆኑን ሰሞኑን በማህበራዊ ትስስር ገፆች ቢፃፍም የክለቡ ስራ አስኪያጅ ወ/ሮ ከነአን በተደጋጋሚ ማረጋገጫ እንዲሰጡን ብንሞክርም ሊሰጡ አልቻሉም።

የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ህዝብ ግንኙነት ባለሙያ አቶ አብርሀም ለባላገሩ ስፖርት ሲናገሩ:- ጉዳዩ CAS ስለመድረሱ የሚያውቁት የተረጋገጠ መረጃ አለመኖሩን ፤ በ ሂደቱ CAS ውሳኔ መሀል ላይ ቢመጣ የወላይታ ተሳትፎ እንዴት ሊሆን ነው ብለን ላነሳው ጥያቄ :-የግልግል ፍርድ ቤቱ ጉዳይ ሲታይ ባለው ተሞክሮ ቅደመ ሁኔታዎችና የማጣራት የጊዜ ገደብ የኮንፌዴሬሽን ጨዋታዎች ከተደረጉ በኋላ የሚደርስ እንደሚሆን ያላቸውን እምነት በመናገር እስከዛ በውሳኔ ወላይታ ዲቻ እንደሚሳተፍ ተናግረዋል።

ጉዳዩን አስመልክቶ በተደጋጋሚ የሲዳማ ቡና ክለቡ ማረጋገጫ እንዲሰጡ ፣ ዋንጫ ስላልተመለሰበት ሁኔታ፣ ጉዳዩ ከስፖርት አልፎ የፖለቲካ አመራሮች ጭምር ጣልቃ እንዲገቡ ስለተደረገበት ሁኔታ ተጨማሪ ማብራሪያ ለስፖርት ቤተሰቡ፣ ለሲዳማ ቡና ደጋፊ እንዲያሳውቁ ያደረግነው ጥረት ለጊዜው አልተሳካም ።

አብይ ዘላለም

Address


Opening Hours

Monday 02:30 - 11:30
Friday 02:30 - 01:45

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Balageru TV posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to Balageru TV:

Shortcuts

  • Address
  • Opening Hours
  • Alerts
  • Contact The Business
  • Claim ownership or report listing
  • Want your business to be the top-listed Media Company?

Share

Balageru TV

Balageru television, Television programming that promotes Ethiopian history, culture, tradition, lifestyle, investment, tourism, current affairs, sports, and entertainment.