Balageru TV

Balageru TV Balageru television, promotes Ethiopian history, culture, tradition, lifestyle, investment, tourism..

Our Channel Frequency
NSS12 57 Degree East HD, Freq - 11105, Pol - Horizontal, S/R - 45000
or
DSTV Channel - 484

"ግብፅ ከጠብ አጫሪ ልትቆጠብ  ይገባል"ሲል -የውኃ እና ኢነርጂ ሚኒስቴር አሳሰበ::ግብፅ በዓባይ ወንዝ እና በታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ዙሪያ ዛሬም ‘እኔ ከሞትኩ ሰርዶ አይብቀል’ ትርክ...
13/10/2025

"ግብፅ ከጠብ አጫሪ ልትቆጠብ ይገባል"ሲል
-የውኃ እና ኢነርጂ ሚኒስቴር አሳሰበ::

ግብፅ በዓባይ ወንዝ እና በታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ዙሪያ ዛሬም ‘እኔ ከሞትኩ ሰርዶ አይብቀል’ ትርክቷን መቀጠሏን የውኃ እና ኢነርጂ ሚኒስቴር ባወጣው መግለጫ አስታውቋል።

ሚኒስቴር መሥሪያ ቤቱ በመግለጫው የግብፅ ጠብ አጫሪ አካሄድ መቀጠሉን አንስቶ፤ ሀገሪቱ ያወጣችው የቅርብ ጊዜ መገለጫ ግብፅ በዓባይ ወንዝ ተፋሰስ ላይ አለኝ በምትለው የተለመደ ታሪካዊ መብት የተቃኘ እንደሆነም ጠቁሟል።

የግብፅ የቅኝ ግዛት ዘመን አስተሳሰብ፤ ከትብብር ይልቅ የኢትዮጵያን አቅም ዝቅ አድርጎ የመመልከት የከሸፈ እና የተሳሳተ ፖሊሲ እንድትከተል አድርጓል ሲል ጠቅሷል።

የታላቁ የዓባይ ወንዝ መነሻ እና 85 በመቶ የዓባይ ውኃ ምንጭ የሆነችው ኢትዮጵያ ግን በአንፃሩ የብልፅግና ጎዳና ላይ ነች ይላል መግለጫው።

ኢትዮጵያ የዓባይን ወንዝ በመጠቀም የመልማት ፍላጎቷን ለመገደብ የሚደረግ የትኛውም ጫና ከልማት ጉዞዋ አያስቆማትም ያለው መግለጫው፤ የኢትዮጵያ ብልፅግና ምንም ዓይነት ትንኮሳ እና የእጅ አዙር ጦርነት ወደ ኋላ የማይመለሰው እንደሆነም አፅንኦት ሰጥቷል።

ኢትዮጵያ እና ሌሎች የዓባይ ተፋሰስ ሀገራት ለአሥርተ ዓመታት በዓለም አቀፍ ሕግጋት መሰረት የድንበር ተሻጋሪ ትብብርን እውን ለማድረግ ከግብፅ ጋር ለመስራት መሞከራቸውን የጠቀሰው መግለጫው፣ የትኛውም የትብብር ጥያቄ ግን በግብፅ የተሳሳተ አካሄድ ሲደናቀፍ መቆየቱን አስታውሷል።

መግለጫው አክሎም ግብፅ በታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የመጀመሪያ ሙሌት፤ ዓመታዊ ሥራ ግምገማ እና በዓባይ ወንዝ ተፋሰስ የትብብር ማዕቀፍ ላይ፣ እንዲሁም በግድቡ ዙሪያ በተደረገው የሦስትዮሽ ድርድር በቅን ልቦና ተወያይታ አታውቅም ብሏል።

ከዚህም ባለፈ ግብፅ የሌሎችን የተፋሰሱ ሀገራት ፍላጎትና መብት በመዘንጋት፤ የሙጥኝ ብላ ከያዘችው የቅኝ ግዛት ዘመን የመነጨ “ታሪካዊ መብት” አስተሳሰቧን ለመጫን ጥረቷን መቀጠሏንም ሚኒስቴሩ በመግለጫው ጠቅሷል።

በተጨማሪም ግብፅ ከሌሎች የተፋሰሱ ሀገራት ጋር ምንም ዓይነት ምክክር ሳታደርግ ከተፋሰሱ ውጭ ውኃ መቀልበስን ጨምሮ በርካታ ሕገወጥ እና ግዴለሽነት በተሞላባቸው ድርጊቶቿ የውኃ ብክነት ላይ ተሰማርታለችም ብሏል መግለጫው።

የዓባይ ጉዳይ መፍትሔ የሚያገኘው ከሚመለከታቸው አካላት ጋር በቀጥታ በመወያየት መሆኑንም የተነሳ ሲሆን፤ የውኃ ደኅንነት የሚረጋገጠው ሁሉም የተፋሰሱ ሀገራት የዓባይን ወንዝ ፍትሐዊ እና ምክንያታዊ በሆነ መንገድ ሲጠቀሙ ብቻ መሆኑንም ነው መግለጫው የጠቆመው።

የግብፅ እጣ ፈንታ ከሌሎች የተፋሰሱ ሀገራት ጋር የተቆራኘ በመሆኑ፤ ብቸኛው ምክንያታዊ አማራጭ ግብፅ ከላይኛው የተፋሰሱ ሀገራት ጋር ያላታን ግንኙነት ከዛቻ፣ ዘለፋ እና ሌሎች ያልተገቡ ድርጊቶች አፅድታ ከሌሎች የተፋሰሱ ሀገራት ጋር በእኩልነት ስትወያይ ብቻ ነውም ብሏል ሚኒስቴር መሥሪያ ቤቱ።

የግብፅ "ድርቅ ገጠመኝ" ስሞታ በፍጥነት ወደ "በጎርፍ ተጥለቅልቄጣለሁ" ጽንፍ መቀየሩ ግብፅ የጋራ ጥቅምን ማዕከል ያደረገ መፍትሄ የማግኘት መንገድ አለመፈለጓን ማሳያ እንደሆነ ያነሳው መግለጫው፤ ግብፅ ሱዳንንም ወደ ፈጠረችው ቀውስ ለመጎተት እየሞከረች ነው ብሏል።

ኢትዮጵያ እና ሱዳን በሕዳሴ ግድብ ላይ ውጤታማ ቅንጅት እንዳላቸውም የተጠቀሰ ሲሆን፤ ይህን ወንድማዊ ትስስራቸውን ወደ ሕዝባቸው የጋራ ልማት ማሸጋገር እንደሚቀጥሉም ነው የተገለፀው።

ኢትዮጵያ የረጅም ጊዜ የሃይድሮ ኤሌክትሪክ ግድቦችን የመገንባት እና የማንቀሳቀስ ልምድ ያላት ሀገር እንደመሆኗ፤ ታላቁን የሕዳሴ ግድብን ጨምሮ በግድቦቿ አስተዳደር ላይ በከፍተኛው የሙያ ብቃት እየሠራች ትገኛለችም ብሏል የውኃ እና ኢነርጂ ሚኒስቴር በመግለጫው።

ከዚህም ባለፈ የኢትዮጵያ አረንጓዴ ዐሻራ ንቅናቄ የደን ልማት ዘመቻ፤ የሕዳሴ ግድብን የሚጠብቅ የተፈጥሮ ጥበቃ ሥራ እንደሆነ አንስቶ ግብፅ ከዚህ ልትማር ይገባል ብሏል።

መግለጫው በማጠቃለያው ኢትዮጵያ በዓባይ ጉዳይ ላይ ካልተገቡ መግለጫዎችን እና ጠብ አጫሪ ድርጊቶች በመቆጠብ ለዲፕሎማሲያዊ መንገዶች እና የወዳጅነት አካሄዶች የቅድሚያ ቅድሚያ መስጠቷን እንደምትቀጥል አጽንኦት ሰጥቷል።
(ኢቢሲ)

ሐማስ የእስራኤል ታጋቾችን ለቀቀየእስራኤል መከላከያ ሰባት በሕይወት ያሉ ታጋቾች መለቀቃቸውን እና መረከቡን አስታወቀ።የእስራኤል ጦር ዛሬ ማለዳ እንዳስታወቀው የመጀመርያዎቹን ሰባት ታጋቾች ተ...
13/10/2025

ሐማስ የእስራኤል ታጋቾችን ለቀቀ

የእስራኤል መከላከያ ሰባት በሕይወት ያሉ ታጋቾች መለቀቃቸውን እና መረከቡን አስታወቀ።
የእስራኤል ጦር ዛሬ ማለዳ እንዳስታወቀው የመጀመርያዎቹን ሰባት ታጋቾች ተረክቦ ቤተሰቦቻቸውን ወደሚያገኙበት ስፍራ እየወሰደ ነው።
ጦሩ ባወጣው መግለጫ ላይ "የእስራኤል ጦር እና ደህንነት ኤጀንሲዎች ተመላሾቹን ወደ እስራኤል አጅበው እያመጧቸው ነው" ብሏል።
ወደ እስራኤል ከተመለሱ በኋላ "የመጀመርያ የሕክምና ምርምራ ይደረግላቸዋል" ያለው መግለጫው፣ በኋላ ላይ ለቀይ መስቀል ተላልፈው የሚሰጡ ተጨማሪ ታጋቾችን ለመረከብ መዘጋጀቱን አስታውቋል።
ሐማስ ተጨማሪ 13 ተጋቾች በሚቀጥሉት ሰዓታት ውስጥ ይለቅቃል ተብሎ ይጠበቃል።

ሰበር ዜና!የቀድሞ የኢትዮጵያ ብሄራዊ ቡድን ግብ ጠባቂ ተካበ ዘውዴ ፕሬዝዳንት ሆኖ ተመረጠ !የሰሜን አሜሪካ ኢትዮጵያዊያን ስፖርት ፌዴሬሽን ባደረገው ጉባኤ አዲስ ስራ አመራር ቦርድና አዘጋጅ...
13/10/2025

ሰበር ዜና!

የቀድሞ የኢትዮጵያ ብሄራዊ ቡድን ግብ ጠባቂ ተካበ ዘውዴ ፕሬዝዳንት ሆኖ ተመረጠ !

የሰሜን አሜሪካ ኢትዮጵያዊያን ስፖርት ፌዴሬሽን ባደረገው ጉባኤ አዲስ ስራ አመራር ቦርድና አዘጋጅ ከተማ መምረጡን አስታውቋል ።

የቀድሞ የኢትዮጵያ ብሄራዊ ቡድን ግብ ጠባቂ ጀግናው ተካበ ዘውዴ በሰሜን የኢትዮጵያዊያን የሰሜን አሜሪካ ስፖርት ፌዴሬሽን ESFNA ፕሬዝዳንት ሆኖ ተመርጧል።

ሙላት መለሰ ከላስ ቬጋስ አዲሱ የቢዝነስ ማናጀር ፤ዳግም ፀጋዬ የውስጥ ኦዲተር ፤ መንግስቱ ሁሴን የውድድር አስተባባሪ ፣ያሬድ ነጋሽ ህዝብ ግንኙነት በመሆን ተመርጠዋል።

43ኛው አመት የዘንድሮ ውድድር የሚደረግበት ቦታም ሜኒሶታ በመሆን ተመርጧል ከ June 27 – July 4, 2026 እንደሚካሄድ ታውቋል።

ባላገሩ ስፖርት

ጊፍት ሪል እስቴት የአፍሪካ ኢምፓክት ዋና አጋር ነው!ዛሬ ምሽት በሲልቨር ስፕሪንግ ሜሪላንድ ታላላቅ ሰዎች እውቅና ያገኛሉ።ስኬትን እና የላቀ ስራን ተከብሮ በሚሸለምበት  ፕሮግራም  አቶ መስ...
12/10/2025

ጊፍት ሪል እስቴት የአፍሪካ ኢምፓክት ዋና አጋር ነው!

ዛሬ ምሽት በሲልቨር ስፕሪንግ ሜሪላንድ ታላላቅ ሰዎች እውቅና ያገኛሉ።

ስኬትን እና የላቀ ስራን ተከብሮ በሚሸለምበት ፕሮግራም አቶ መስፍን ጣሰው፣ አትሌት መሰረት ደፋር፣ ጋሽ መሀሙድ አህመድ፣ አቶ ጆ ማሞ እና ሰይፉ ፋንታሁን የዘንድሮ ተሸላሚዎች ናቸው።

🎶 በዕለቱ ልዩ የበጎ አድራጎት የሙዚቃ ፕሮግራም ይቀርባል

🎤 የአሜሪካ ሴናተሮች፣ ከንቲባዎች እና የልዑክ ቡድኖች ይገኛሉ

በየአመቱ ልዩ ተሸላሚዎች ከስፖርት፣ ከኪነጥበብ ፣ቢዝነስ ዘርፍ ተመርጠው ላደረጉት በጎ አስተዋፅኦ ሽልማት ይበረከትላቸዋል፣ ለስራቸውም ይመሰገናሉ።

በቅርብ በአዲስ አበባ እግር ኳስ አካዳሚ ለመክፈት እቅድ የያዘውና ኢትዮጵያን ተጨዋቾች በሜጀር ሊግ ሶከር እንዲጫወቱ ኢንቨስት በማድረግ እየተንቀሳቀሰ የሚገኘው ባለሀብቱ አቶ እዮብ ማሞ ( የዝነኛው የማሞ ካቻ ልጅ)፣ በኦሎምፒክና በአለም አትሌቲክስ ሻምፒዮና ኢትዮጵያን ያኮራችው የአሁኑ የፌዴሬሽኑ ስራ አስፈፃሚ አትሌት መሰረት ደፋር ስፖርት ዘርፍ ላይ እየተንቀሳቀሱ ከሚገኙ ተሸላሚዎች ውስጥ ናቸው ።

📍 ቦታ: Civic Building, 1 Veteran Plaza, Silver Spring, Maryland

🗓️ ቀን እና ሰዓት: ኦክቶበር 12, 5:30 PM

ይህን ኢትዮጵያን የሚሰባሰቡበትን ታላቅ ዝግጅት ጊፍት ሪል እስቴት ዋና አጋር በመሆን እውቅና ለሚሰጣቸው ታላላቅ ሰዎች ሽልማቶቹን በማበርከቱ ደስታ ይሰማዋል።

በታማኝነት ከ25 አመታት በላይ የቤት ባለቤት ያደረገው ጊፍት የዲያስፖራውን የሀገር ቤት የቤት ፍላጎት ለመሙላት በታማኝነት አብረን እንስራ ይላል።

አብይ ዘላለም ከሲልቨር ስፕሪንግ

ፈረሰኞቹ የሲቲ ካፕ ዋንጫን አሸነፉ!በአዲስ አበባ ከተማ ሲቲ ካፕ ''ህዳሴ ዋንጫ'' ቅዱስ ጊዮርጊስ መቻልን በማሸነፍ የዋንጫ አሸናፊ ሆኗል።በ19ኛው ሲቲ ካፕ ፈረሰኞቹ  መቻልን  2ለ1 ሲያ...
12/10/2025

ፈረሰኞቹ የሲቲ ካፕ ዋንጫን አሸነፉ!

በአዲስ አበባ ከተማ ሲቲ ካፕ ''ህዳሴ ዋንጫ'' ቅዱስ ጊዮርጊስ መቻልን በማሸነፍ የዋንጫ አሸናፊ ሆኗል።

በ19ኛው ሲቲ ካፕ ፈረሰኞቹ መቻልን 2ለ1 ሲያሸንፉ ለቅዱስ ጊዮርጊስ አሸናፊ ጌታቸው ፣ አዲሱ አቱላ ግቦቹን አስቆጥረዋል።

የመቻልን ብቸኛ ግብ ቻርልስ ሙስጌ አስቆጥሯል ። የአዲስ አበባ ስታዲየም በተመልካች ተሞልቶ በተደረገው ጨዋታ ግሩም ሀጎስና በቀይ ካርድ ከሜዳ ወጥቷል። አዲሱ አቱላ የጨዋታው ኮከቦ ሆኗል። የሲቲ ካፑን ዋንጫ ፈረሰኞቹ ሲያነሱ ፣መቻል ሁለተኛ ፣ ኢትዮጵያ ቡና 3ኛ ደረጃ ይዘው አጠናቀዋል።

ባላገሩ ስፖርት

በትራፊክ አደጋ የ10 ሰዎች ሕይወት አለፈበአማራ ክልል ኦሮሞ ብሔረሰብ አስተዳደር ዞን ጨፋ ሮቢት ከተማ በደረሰ የትራፊክ አደጋ የ10 ሰዎች ሕይወት አለፈ፡፡አደጋው 60 ሰዎችን አሳፍሮ ሲጓዝ...
12/10/2025

በትራፊክ አደጋ የ10 ሰዎች ሕይወት አለፈ

በአማራ ክልል ኦሮሞ ብሔረሰብ አስተዳደር ዞን ጨፋ ሮቢት ከተማ በደረሰ የትራፊክ አደጋ የ10 ሰዎች ሕይወት አለፈ፡፡

አደጋው 60 ሰዎችን አሳፍሮ ሲጓዝ የነበረ የሕዝብ ማመላለሻ ተሽከርካሪ ልዩ ስሙ ጃራ ድልድይ ከተባለ ቦታ ላይ ከከባድ ጭነት ተሽከርካሪ ጋር በመጋጨቱ ነው የተከሰተው፡፡

በአደጋውም እስካሁን የ10 ሰዎች ሕይወት ማለፉን የከተማው ከንቲባ አቶ ሰይድ መሃመድ ለፋና ዲጀታል ገልጸዋል፡፡

በተጨማሪም በርካታ ሰዎች ላይ ከባድ ጉዳት መድረሱን ጠቁመው ÷ የሟቾች ቁጥር ሊያሻቅብ እንደሚችል አመልክተዋል፡፡

ጉዳት የደረሰባቸው ተሳፋሪዎች አቅራቢያ በሚገኘው ጨፋ ሮቢት ሆስፒታል ሕክምና እየተከታተሉ እንደሚገኙም ጠቁመዋል፡፡

የመሬት መንቀጥቀጥ በትግራይ ክልል ዛሬ ቅዳሜ ጥቅምት 1፤ 2018 ምሽት፤ ለሁለት ጊዜያት የመሬት መንቀጥቀጥ መከሰቱን የአሜሪካ የጂኦሎጂካል ሰርቬይ መስሪያ ቤት ገለጸ። ከምሽቱ 1፡01 ላይ ...
11/10/2025

የመሬት መንቀጥቀጥ
በትግራይ ክልል ዛሬ ቅዳሜ ጥቅምት 1፤ 2018 ምሽት፤ ለሁለት ጊዜያት የመሬት መንቀጥቀጥ መከሰቱን የአሜሪካ የጂኦሎጂካል ሰርቬይ መስሪያ ቤት ገለጸ። ከምሽቱ 1፡01 ላይ የደረሰው ርዕደ መሬት በሬክተር ስኬል 5.3 መለካቱን የገለጸው መስሪያ ቤቱ፤ ከ17 ደቂቃ በኋላ የተከሰተው በሬክተር ስኬል 5.3 መድረሱን አስታውቋል።

ከእነዚህ ክስተቶች አራት ሰዓት አስቀድሞ፤ በሬክተር ስኬል 4.2 የተላከ ሌላ የመሬት መንቀጥቀጥ ከመቐለ ከተማ በሰሜን ምስራቅ አቅጣጫ 47 ኪሎ ሜትር ርቀት ባለ ቦታ ላይ መድረሱን መስሪያ ቤቱ መዝግቧል። ዛሬ ምሽት ከደረሱት ርዕደ መሬቶች የመጀመሪያው የተመዘገበው ከመቐለ ከተማ 58 ኪሎ ሜትር ርቀት ባለ ቦታ ላይ መሆኑንም ከተቋሙ የተገኘው መረጃ ያመለክታል።

ሁለተኛው የመሬት መንቀጥቀጥ የተከሰተው ከውቅሮ ከተማ 32 ኪሎ ሜትር በሚርቅ ቦታ ላይ እንደሆነ በዓለም አቀፍ ደረጃ የሚከሰቱ ርዕደ መሬቶችን የሚመዘግበው “ቮልካኖ ዲስከቨሪ” በድረ ገጹ ላይ አስፍሯል።

2026  የአሌክሳንድሪያ ቶዮታ መኪና አሸናፊዋ ታዳጊ!7ኛው ግራንድ አፍሪካ ረን ሰሜን አሜሪካ ቨርጂኒያ አሌክሳንድሪያ  ዛሬ በሺዎች የሚቆጠሩ ተሳታፊዎች በተገኙበት 5ኬ ሜ የሩጫ ውድድር  ተ...
11/10/2025

2026 የአሌክሳንድሪያ ቶዮታ መኪና አሸናፊዋ ታዳጊ!

7ኛው ግራንድ አፍሪካ ረን ሰሜን አሜሪካ ቨርጂኒያ አሌክሳንድሪያ ዛሬ በሺዎች የሚቆጠሩ ተሳታፊዎች በተገኙበት 5ኬ ሜ የሩጫ ውድድር ተካሂዷል።

በጉጉት የተጠበቀውን የአሌክሳንድሪያ ቶዮታ 2026 መኪና አሸናፊ ያብስራ ዘውድነህ ሆናለች ::ታዳጊዋ እድለኛ የአትሌት አየለች በቀለ ልጅ ናት ።

ግራንድ አፍሪካ ረን በአሌክሳንድሪያ ተካሂዷል!7ኛው ግራንድ አፍሪካ ረን ሰሜን አሜሪካ ቨርጂኒያ አሌክሳንድሪያ  ዛሬ በሺዎች የሚቆጠሩ ተሳታፊዎች በተገኙበት የሩጫ ውድድር  ተካሂዷል። በወንዶ...
11/10/2025

ግራንድ አፍሪካ ረን በአሌክሳንድሪያ ተካሂዷል!

7ኛው ግራንድ አፍሪካ ረን ሰሜን አሜሪካ ቨርጂኒያ አሌክሳንድሪያ ዛሬ በሺዎች የሚቆጠሩ ተሳታፊዎች በተገኙበት የሩጫ ውድድር ተካሂዷል።

በወንዶች የ5ኪሜ አሸናፊ ግርማ በዳዳ ፣ ዋሌ ዮሀንስ2ኛ ፣ ነጋ አበበ በቀዳሚነት አጠናቀዋል 250 ዶላር አሸናፊ ሆኗል ።

ከመዝናኛ ውድድሩ ተጨማሪ በአጋር ድርጅቶች የተዘጋጁ ሽልማቶችን ተሳታፊዎች ሲያሸንፉ ፋስት ፔይ ፣ አሪፍ ፔይ ፣ቴሌብር ለእድለኞች ወደ ሀገር ቤት የሚላክ 100ሺ ፣15ዐሺ ብር ሽልማት ለእድለኞ ሰጥተዋል።

በጉጉት የተጠበቀውን የአሌሳንድሪያ ቶዮታ 2026 መኪና አሸናፊ ከደቂቃዎች በኋላ ይታወቃል።

አብይ ዘላለም ከአሌክሳንድሪያ

የፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤቶች የ2018 ዓ.ም መደበኛ የችሎት ማስጀመሪያ ስነ ስርዓት ተካሄደ።በዚሁ ወቅት የፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ፕሬዚዳንት ቴዎድሮስ ምህረት እንደገለፁት፤ ባለፈው በጀት...
11/10/2025

የፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤቶች የ2018 ዓ.ም መደበኛ የችሎት ማስጀመሪያ ስነ ስርዓት ተካሄደ።

በዚሁ ወቅት የፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ፕሬዚዳንት ቴዎድሮስ ምህረት እንደገለፁት፤ ባለፈው በጀት ዓመት የዳኝነትን ግልጽነት እና ተጠያቂነትን ለማረጋገጥና የተገልጋዩን ፍላጎት ያሟላ እንዲሆን ስራዎች ተሰርተዋል።

እንዲሁም የዳኝነትን አገልግሎት ነፃነትን ለማረጋገጥ የሚያግዙ የህግ ማዕቀፎች ፀድቀው ወደስራ ገብተዋል ብለዋል።

በዚህም የ2017 ዓ.ም በጀት ዓመትን በጥሩ አፈጻጸም ማጠናቀቅ መቻሉን ያነሱት ፕሬዚዳንቱ፤ ምንም እንኳን ቀሪ በርካታ ስራዎች ቢኖሩም በአዲሱ በጀት ዓመትም የጀመርናቸውን ጥረቶች በማስቀጠል በትኩረት ይሰራል ብለዋል።

በዚህም የተጀመረውን የዲጂታል አሰራር በማጠናከር ተገልጋዮች ባሉበት ሆነው አገልግሎት እንዲያገኙ የማድረጉ ተግባር እንደሚቀጥል አመላክተዋል።

ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ  የጓጉለትን የሰላም የኖቤል ሽልማት ሳያሸንፉ ቀሩቬንዙዌላዊቷ ፖለቲከኛ ማሪያ ኮሪና ማሻዶ የ2025 የሰላም ኖቤል ሽልማትን አሸንፈዋል።ማሪያ ኮሪና ማሻዶ የዴሞክራሲ...
10/10/2025

ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ የጓጉለትን የሰላም የኖቤል ሽልማት ሳያሸንፉ ቀሩ

ቬንዙዌላዊቷ ፖለቲከኛ ማሪያ ኮሪና ማሻዶ የ2025 የሰላም ኖቤል ሽልማትን አሸንፈዋል።

ማሪያ ኮሪና ማሻዶ የዴሞክራሲ አቀንቃኝ በመሆን በሀገራቸው ዴሞክራሲ እንዲሰፍን ለማስቻል ብርቱ ትግል በማድረግ ይታወቃሉ።

እስራኤል የጋዛ የተኩስ አቁም ስምምነትን አፀደቀችየጠቅላይ ሚኒስትር ቤኒያሚን ኒታንያሁ ጽ/ቤት እንዳስታወቀው÷ በፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ የቀረበው የተኩስ አቁም ስምምነት ቀሪ የእስራኤል ታ...
10/10/2025

እስራኤል የጋዛ የተኩስ አቁም ስምምነትን አፀደቀች

የጠቅላይ ሚኒስትር ቤኒያሚን ኒታንያሁ ጽ/ቤት እንዳስታወቀው÷ በፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ የቀረበው የተኩስ አቁም ስምምነት ቀሪ የእስራኤል ታጋቾችን የሚያስለቅቅና ዘላቂ ሰላምን የሚያመጣ እንደሆነ ታምኖበታል፡፡

በስምምነቱ መሰረት እስራኤል 53 በመቶ ከሚሆነው የጋዛ ክፍል ጦሯን የምታስወጣ ሲሆን፥ ሀማስ በበኩሉ 20 የእስራኤል ታጋቾችን በ72 ሰዓታት ውስጥ የሚለቅ ይሆናል፡፡

በተመሳሳይ እስራኤል 250 እስረኞችንና በጋዛው ዘመቻ በቁጥጥር ስር ያዋለቻቸውን ከ1 ሺህ 700 በላይ ሰዎች እንደምትለቅ ቢቢሲ ዘግቧል፡፡

Address

Lancha Infront Of Global Hotel Meaza Desalegn Building 14th Floor
Addis Ababa
1000

Opening Hours

Monday 02:30 - 11:30
Friday 02:30 - 01:45

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Balageru TV posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to Balageru TV:

Share

Category

Balageru TV

Balageru television, Television programming that promotes Ethiopian history, culture, tradition, lifestyle, investment, tourism, current affairs, sports, and entertainment.