Balageru TV

Balageru TV Balageru television, promotes Ethiopian history, culture, tradition, lifestyle, investment, tourism..

Our Channel Frequency
NSS12 57 Degree East HD, Freq - 11105, Pol - Horizontal, S/R - 45000
or
DSTV Channel - 484

የስልጠና ሉዓላዊነት አሁኑኑ!  በጋዜጠኛ ሀይለ እግዚአብሔር አድሀኖም ለከራረመው የአትሌክሳችን ውጤት መራቅ ምክንያት ይሆናሉ ብለን ስለ የቡድን ስራ መጥፋት: ታክቲክ፣ የአየር ሁኔታ፣ የትውል...
15/09/2025

የስልጠና ሉዓላዊነት አሁኑኑ!

በጋዜጠኛ ሀይለ እግዚአብሔር አድሀኖም

ለከራረመው የአትሌክሳችን ውጤት መራቅ ምክንያት ይሆናሉ ብለን ስለ የቡድን ስራ መጥፋት: ታክቲክ፣ የአየር ሁኔታ፣ የትውልዶች መለያየት እና ሌሎችም ማውራት እንችላለን:: ተገቢ እና ውሃ የሚያነሱ ሀሳቦችም ናቸው:: ነገር ግን ትኩረት የሚሻው ሌላውና ዋናው ችግር "የስልጠና ሉዓላዊነታችንን" ማጣታችን ነው ብዬ አምናለሁ።

እንዴት?

አሁን ላይ የስልጠና ስልቶቻችን፣ ልማዶቻችን እና አመጋገባችን፣ ሁሉንም መርሐግብር በሚያዘጋጁልን ጥቂት አውሮፓውያን እጅ ስር ጠቅልሎ ከገባ ሰነባበተ::

የአብዛኛዎቹ የሀገር ውስጥ አሰልጣኞቻችን ሚናም ከጊዜ ወደ ጊዜ በሚያሳዝን ሁኔታ ወደ ተራ ሰዓት ያዥነት እና ከሌላ ቦታ ተዘጋጅቶ የሚመጣውን የስልጠና እቅድ ሳይሸራርፉ ተግባራዊ ወደ ማድረግ እያሽቆለቆለ ይገኛል።

ይህንን በማድረጋችንም የስልጠና ሉዓላዊነታችንን ብቻ ሳይሆን የነበረንን የውጤት የበላይነታችንንም አጥተናል።

የራሳችን አሰልጣኞች ዘመናዊ ሳይንሱን: ለኢትዮጵያውያን አትሌቶች ባህርይ እንዲስማማ አድርገው ያሰለጥኑ በነበረበት ወቅት:

እኛ የበላይነት ነበረን።
ማንነት ነበረን።
ውጤትም አግኝተንበት ነበር።

አዲሱ እውነታ

አሁን አሁን፣ ከዚህ ቀደም ኢትዮጵያውያን አትሌቶች በውጤታማነት በሚታወቁባቸው የውድድር አይነቶች: ያልተለመዱ ሀገራት ሯጮች ውጤት ሲያስመዘግቡ እየተመለከትን እንገኛለን::

በተለይም በተመሳሳይ የአትሌት ማኔጅመንት ስር በሚተዳደሩ በየትኛውም የአለም ክፍል በሚገኙ አትሌቶች መካከል ያለው የአቋም እና የውጤት ልዩነት በእጅጉ እየጠበበ መምጣቱ የአደባባይ ሀቅ ከሆነ ከራረመ:: ለዚህ አዲስ እውነታ ከዋነኛ ምክንያቶቹ አንዱ ደግም የስልጠና ሂደቶቹ የሚቀዱት በአብዛኛው ከተመሳሳይ ቋት መሆኑ ነው::

ነገር ግን እንዲህ እንጠይቅ እስኪ: ለመሆኑ:

የሥልጠና ሥርዓቶቻችንን የሚያዘጋጁልን አካላት: በተለያዩ ሀገራት አትሌቶች መካከል ምንም ዓይነት አድልዎ ላለማድረጋቸው ማረጋገጫችን ምንድን ነው?

የኢትዮጵያውያን አትሌቶች የዝግጅት እና የውድድር ታክቲክ ለተፎካካሪወቻቸው ቀድሞ አለመድረሱን ማን ማስተማመኛ ይሰጠናል?

አትሌቶቻችንን ከዶፒንግ አደጋ የምንጠብቅበት የደህንነት ሁኔታስ ልብ የሚያሳርፍ ነው? ወዘተ...

ጥቂት የመፍትሄ ነጥቦች:

ፌዴሬሽኑ የቴክኒካል ዲፓርትመንቱን በራዕይ እና በተጠያቂነት እንዲመራ እንደገና ማዋቀር እና ማብቃት።

ከዩኒቨርሲቲዎች፣ ከምሁራን እና የዓለም አትሌቲክስ ጋር ጠንካራ ትብብር በመፍጠር: የሚገኙ አወንታዊ አቅሞችን ሁሉ አሟጦ መጠቀም።

በሁሉም የስልጠና እርከኖች የሚተገበር: ኢትዮጵያ መር: ቀጣይነት ያለው የአሰልጣኝነት የአቅም ግንባታ እና ምዘና መርሃ ግብሮችን በየደረጃው ተግባራዊ ማድረግ።

በኢትዮጵያ የአትሌቲክስ አሰልጣኝነትን ለማጥናት፣ ለማሳደግ እና አዳዲስ ፈጠራ መር የአሰለጣጠን መንገዶችን ለመማር የሚያስችል "የልህቀት ማእከል" እስከመመስረት ድረስ በትልቁ ማሰብ::

እነዚህን እና ከሌሎች ባለድርሻ አካላት የሚሰጡ ጠቃሚ ምክረሀሳቦችን ወደ ተግባር ከለወጥን: በእርግጥም: ማንነታችንን እናስከብራለን፣ አሸናፊነታችንን እናስጠብቃለን እንዲሁም ቀጣዩን ድል አድራጊ ትውልድ በሚገባ ለማዘጋጀት እንችላለን።

አዎ: የስልጠና ሉዓላዊነት አሁኑኑ !

ባላገሩ ስፖርት

ተሳፋሪ በመምሰል የማታለል (ሿሿ) ወንጀል ፈጽመዋል የተባሉ 10 ተጠርጣሪዎች በቁጥጥር ስር ኣሉተሳፋሪ በመምሰል የማታለል (ሿሿ) ወንጀል ፈጽመዋል የተባሉ 10 ተጠርጣሪዎች ከነ ተሽከርካሪያቸ...
15/09/2025

ተሳፋሪ በመምሰል የማታለል (ሿሿ) ወንጀል ፈጽመዋል የተባሉ 10 ተጠርጣሪዎች በቁጥጥር ስር ኣሉ

ተሳፋሪ በመምሰል የማታለል (ሿሿ) ወንጀል ፈጽመዋል የተባሉ 10 ተጠርጣሪዎች ከነ ተሽከርካሪያቸው በቁጥጥር ስር ውለው ምርመራው መቀጠሉን የአዲስ አበባ ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ አስታወቀ።
*
አዲስ አበባ፤ መስከረም 5 ቀን 2018 ዓ/ም (አዲስ ፖሊስ)፦ ግለሰቦቹ ተሳፋሪ በመምሰል የማታለል (ሿሿ) ወንጀሉን ፈጽመዋል ተብለው በቁጥጥር ስር የዋሉት መስከረም ሦስት ቀን 2018 ዓ/ም በቦሌ ክ/ከተማ ልዩ ቦታው ባምቢስ ተብሎ ከሚጠራው አካባቢ ነው።
ተጠርጣሪዎቹ ኮድ 3-98351 ኦሮ በሆነ ሚኒባስ መነሻቸውን ፒያሳ ቅዱስ ጊዮርጊስ ቤተ ክርስቲያን አካባቢ በማድረግ ወደ አውቶብስ ተራ፣ አብነት፣ ጥቁር አንበሳ እና ባምቢስ አካባቢ እየተንቀሳቀሱ ወንጀሉን ሲፈጽሙ እንደነበር ታውቋል።
ግለሰቦቹ ይህንን የማታለል (ሿሿ) ወንጀል የሚፈጽሙት ተሽከርካሪውን ሞልተው ከተቀመጡ በኋላ አንድ የቀረው በማለት በማስገባትና ትራፊክ መጣ ዝቅ በል፣
አንዴ ውረድ በማለትና በማዋከብ ስልክ፣ ገንዘብ እና የተለያዩ ንብረቶችን እንደሚወስዱ የየካ ክ/ከተማ ፖሊስ መምሪያ ከግል ተበዳዮች ለመርማሪ ፖሊስ ከሰጡት ቃል ማረጋገጡን ገልጿል።
ተጠርጣሪዎቹ ከዚህ ቀደም በየካ ክ/ከተማ ወረዳ ሰባት ሲግናል ከሚባል አካባቢ ተመሳሳይ የማታለል ዘዴ ተጠቅመው የአንዲት ግለሰብን ስልኳን እንደወሰዱባት እና የተሽከርካሪውን ሠሌዳ ቁጥር መስጠቷን የጠቆመው ፖሊስ የተሽከርካሪው ሠሌዳ ቁጥር በተለያዩ ክ/ከተሞች ለሚገኙ ትራፊክ ተቆጣጣሪዎች መበተኑን አስታውሷል።
ተጠርጣሪዎቹ በተለያዩ ክ/ከተሞች እየተዘዋወሩ የተለመደ የወንጀል ተግባራቸውን ሲፈጽሙ ከቆዩ በኋላ በቦሌ ክ/ከተማ ባምቢስ አካባቢ በአዲስ አበባ ፖሊስ ትራፊክ ቁጥጥር አባላት ሊያዙም ችለዋል። ከተገኙባቸው የሞባይል ስልኮች የማረጋገጥ ስራ ሲሰራ አንደኛው የግል ተበዳይ ተጠርጣሪዎቹ በተያዙበት ዕለት አውቶብስ ተራ አካባቢ ስልኩን እና 10 ሺ ብር እንደወሰዱበት አረጋግጧል።
እስካሁን ሁለት የግል ተበዳዮች በተጠርጣሪዎቹ ንብረታቸው እንደተወሰደባቸው ያመለከቱ ሲሆን የአንደኛውን ሞባይል ስልክ ይዘውት እንደተገኙም ፖሊስ ጠቅሷል። በአጠቃላይም 10 ተጠርጣሪዎች ከነተሽከርካሪያቸውና 4 ስማርት ስልኮችን በመያዝ ምርመራው እንደቀጠለ ይገኛል።
የታክሲ ትራንስፖርት ተጠቃሚው ህብረተሠብ ለእንደዚህ አይነት የማታለል ወንጀል ተጋላጭ እንዳይሆን አጠራጣሪ ነገሮችን ሲመለከት ለፖሊስ ጥቆማ መስጠት እንደሚያስፈልግ እና በመሰል የማታለል ወንጀል ስልክ እና ሌሎች ንብረቶች የተወሰደባችሁ ግለሰቦች የካ ክ/ከተማ ፖሊስ መምሪያ በአካል በመቅረብ ተጠርጣሪዎቹን በመለየት የተሠረቀባችሁን ስልኮችም መረከብ እንደምትችሉ የአዲስ አበባ ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ ጥሪውን አስተላልፏል።

መረጃው የአዲስ አበባ ፖሊስ ፌስቡክ ገጽ ነው

የወንዶች 3000 ሜትር መሰናክል የፍፃሜ ውድድር  ዛሬ ይካሄዳል! ዛሬ ቀን 9:55 ጀምሮ ይካሄዳል🥇🥈🥉🇪🇹ለሜቻ ግርማ 🇪🇹ሳሙኤል ፍሬው🇪🇹ጌትነት ዋለ- ኢትዮጵያ በአለም ሻምፒዮና የተሳትፎ ታ...
15/09/2025

የወንዶች 3000 ሜትር መሰናክል የፍፃሜ ውድድር ዛሬ ይካሄዳል!

ዛሬ ቀን 9:55 ጀምሮ ይካሄዳል🥇🥈🥉

🇪🇹ለሜቻ ግርማ

🇪🇹ሳሙኤል ፍሬው

🇪🇹ጌትነት ዋለ

- ኢትዮጵያ በአለም ሻምፒዮና የተሳትፎ ታሪኳ በሁለቱም ፆታዎች በ3ሺ ሜትር መሰናክል የወርቅ ሜዳሊያ አግኝታ አታውቅም።

- ኬንያ በ3ሺ ሜትር መሰናክል በወንዶች 13 ጊዜ የወርቅ ሜዳሊያ በማሸነፍ ስኬታማዋ ሃገር ናት።

- የርቀቱ የወቅቱ የአለም የክብረወሰን ባለቤት 🇪🇹ለሜቻ ግርማ ዶሃ፣ዩጂን እና ቡዳፔስት ላይ ያስመዘገበውን የብር ሜዳሊያ ክብር ወደ ወርቅ ከፍ ለማድረግ ይፋለማል።

- ሞሮኳዊው ሶፊያን ኤል ባካሊ የዩጂን እና ቡዳፔስት አለም ሻምፒዮና ክብሩን ለማስጠበቅ ይወዳደራል።

ልዩ ስፖርት

15/09/2025

የ2018 ዓ.ም የመማር ማስተማር ሂደት በዛሬው ዕለት ተጀምሯል

የ2018 ትምህርት ዘመን የመማር ማስተማር ሥራ በዛሬው ዕለት በሁሉም ክልሎችና ከተማ አስተዳደሮች ተጀምሯል፡፡

በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር በዛሬው ዕለት የመማር ማስተማር ሥራ በሁሉም ት/ቤቶች መጀመሩን የከተማዋ ትምህርት ቢሮ ገልጿል፡፡

በተመሳሳይ በኦሮሚያ ክልል የ2018 ትምህርት ዘመን የመማር ማስተማር ሥራ በዛሬው ዕለት ተጀምሯል፡፡

የኢትዮጵያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ሆነው ያገለገሉት ዶክተር ምናሴ ኃይሌ  ከዚህ ዓለም በሞት ተለዩየኢትዮጵያ ንጉሠ ነገሥት መንግሥት የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር፣ አገራቸውን ብሎም አሕጉራቸውን አፍሪ...
15/09/2025

የኢትዮጵያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ሆነው ያገለገሉት ዶክተር ምናሴ ኃይሌ ከዚህ ዓለም በሞት ተለዩ

የኢትዮጵያ ንጉሠ ነገሥት መንግሥት የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር፣ አገራቸውን ብሎም አሕጉራቸውን አፍሪካን ያገለገሉት ዶክተር ምናሴ ኃይሌ በተወለዱ በ95 ዓመታቸው መስከረም 1 ቀን 2018 ዓ.ም. በሚኖሩበት አገረ አሜሪካ ከዚህ ዓለም ድካም ማረፋቸው ታውቋል።
ዶክተር ምናሴ ኃይሌ ከአባታቸው ከባላምባራስ ኃይሌ ድብነህ ከእናታቸው ወይዘሮ ኢሌኒ ኃይሌ ታኅሣሥ 24 ቀን 1922 ዓ.ም. ሐረር ከተማ የተወለዱት ሲሆን ከማንም በላይ የለፋላትን አገራቸውን ከኀምሳ አመታት በላይ ሳያዩ በስደት እንዳሉ በአሜሪካን አገር በኒውጀርሲ ጠቅላይ ግዛት ሕይዎታቸው አልፏል።

በንጉሰ ነገስት መንግስት ዘመን ሀገራቸው ኢትዮጵያን በማስታወቂያ እና በውጭ ጉዳይ ሚኒስትርነት ያገለገሉት ታላቁ ዲፕሎማት ዶ/ር ምናሴ ኃይሌ ዩናይትድ ስቴትስ ውስጥ በ95 ዓመታቸው ማረፋቸውን ተሰምቷል።
እኚህ አንጋፋ ዲፕሎማት ብዙዎቻችን የምናውቃቸው በዘመነ ቀኃሥ የሊቢያው ተወካይ የአፍሪካ አንድነት ድርጅት ዋና መዲናውን ከአዲስ አበባ ወደ ሌላ የአፍሪካ ከተማ እንዲዘዋወር ትእቢትና ንቀት በታከለበት ሁኔታ ለጠየቀው ጥያቄ በሰጡት አስደናቂ መልስ ነበር።

ዶ/ር ምናሴ በ1922 ዓ.ም(እኢአ)የተወለዱ ሲሆን የከፍተኛ ትምህርታቸውን የመጀመሪያ ዲግሪያቸው እ.አ.አ 1946 - 1950 በአሜሪካ በሚገኘው ዊስኮሲን ማዲሰን ዩኒቨርሲቲ ካገኙ በኋላ በተጨማሪም ዶክትሬታቸዉን እ.አ.አ 1954 - 1961 ድረስ በኮሎምቢያ የህግ ዩኒቨርስቲ አግኝተዋል።
ዶ/ር ምናሴ በግርማዊ ሃይለስላሴ አስተዳደር ዉስጥ ከ 1971 - 1973 ዓ.ም(እኢአ) የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ሆነው ያገለገሉ ሲሆን በደርግ አብዮት ዘመን በህይወት ከተረፉ ጥቂት የቀ.ኃ.ስ ባለስልጣናት አንዱ ናቸው።
ዶ/ር ምናሴ በሙሉ የፕሮፌሰር ማዕረግ በተለያዩ የአሜሪካ ዩኒቨርስቲ ውስጥ የህግ መምህር ሆነዉ አገልግለዋል።

በታሪክ የመጀመሪያዋ ኢትዮጵያዊት ወደ ህዋ ልትጓዝ ነው  ኢትዮጵያዊቷ  የኤሮስፔስ መሀንዲስ እመቤት በአሜሪካ መቀመጫውን  ባደረገው የህዋ ምርምር ኩባንያ ቲታንስ ስፔስ ኢንደስትሪ ለቀጣዩ 20...
15/09/2025

በታሪክ የመጀመሪያዋ ኢትዮጵያዊት ወደ ህዋ ልትጓዝ ነው

ኢትዮጵያዊቷ የኤሮስፔስ መሀንዲስ እመቤት በአሜሪካ መቀመጫውን ባደረገው የህዋ ምርምር ኩባንያ ቲታንስ ስፔስ ኢንደስትሪ ለቀጣዩ 2029 ህዋ ተልእኮ ከተጓዥ ተመራማሪዎች መካከል አንዷ አድርጎ መርጧታል።

የእመቤት በዚህ መስክ መመረጥ በህዋ ሳይንስ ዘርፍ አዲስ ምዕራፍ መከፈቱንና ለኢትዮጵያም ሆነ ለአፍሪካ ታሪካዊ ምዕራፍ ነው ተብሎለታል።

የእመቤት መሃባው የጠፈር ሳይንስ ፍቅር የጀመረው ገና በልጅነቷ ሰለ መሆኑ ገልጻለች።

በአዲስ አበባ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ እየተማረች በህዋ ሳይንስ ዘርፍ ከፍተኛ የሆነ የትምህርት እድል አግኝታ በህንድ ትምህርቷን እንድትቀጥል እድል አግኝታለች።

የእሷ ቁርጠኝነት እና የአካዳሚክ ልህቀት ከጊዜ በኋላ መቀመጫውን አሜሪካ ባደረገው ቲታንስ የጠፈር ኢንዱስትሪ ውስጥ እንድትቀላቀል እድል ፈጥሮላታል። በአሁኑ ጊዜም በተለያዩና እጅግ በገዘፉ የምርምር ፕሮጀክቶች ውስጥ እንደ ኤሮስፔስ መሐንዲስ ትሰራለች።

ለ2029 የጠፈር ተልዕኮ ምርጫ የበቃችውም በጠንካራ የግምገማ ሂደት አልፋ እንደሆነ መረጃዎች ያሳያሉ።

እንደ ሪፖርቶች ከሆነ አስደናቂ የአካል ብቃቷ፣ የስነ ልቦና ዝግጅቷ እና ልዩ የምርምር አቅሟ ለዚህ ከፍተኛ ክብር እንድትመረጥ ካደረጉት ቁልፍ ነገሮች መካከል ናቸው።

እመቤት በአሁኑ ወቅት ለተልዕኮው ቅድመ ዝግጅት እያደረገች ሲሆን የሙሉ የቡድን ስልጠና በ2026 አካባቢ እንደሚጀመር ተገልጿል።

በተልዕኮዋ እና ምድርን በምትዞርበት ወቅትም ሳይንሳዊ ሙከራዎችን በማድረግ ኢትዮጵያን በኩራት ለመወከል ማቀዷን አስታውቃለች።

የኢትዮጵያን ባንዲራ ተሸክማ ወደ ህዋ የመጓዝ ፍላጎት እንዳላት የገለጸችው እመቤት ይህም ብሄራዊ ኩራት እና ኢትዮጵያ ለአለም አቀፍ የሳይንስ እድገት የምታበረክተውን አስተዋፅዖ ለማስተዋወቅ መሆኑን ነው የተናገረችው።

እመቤት መሃባው በታይታንስ ስፔስ ኢንደስትሪ ካበረከተችው ሚና በተጨማሪ በህዋ ዘርፍ ያሉ ወጣት ባለሙያዎችን በሚደግፈው አለም አቀፍ የስፔስ ጄኔሬሽን አማካሪ ምክር ቤት የኢትዮጵያ ተወካይ በመሆን አገልግላለች። ስኬቶቿም አለም አቀፍ እውቅናን ማትረፍ ጀምረዋል።
እ.ኤ.አ. በ2024 የአፍሪካ የጠፈር መሪዎች ሽልማት ከአራቱ አፍሪካውያን ተሸላሚዎች መካክል አንዷ ነበረች።

በተጨማሪም እ.ኤ.አ. በ2025 የአለም አቀፉ የስነ ፈለክ ፌደሬሽን “በአለም ላይ ካሉት እጅግ በጣም ተስፋ ሰጭ ወጣት የጠፈር ሳይንቲስቶች አንዷ”ሲል እውቅና ሰጥቷታል።

የእመቤት ጉዞ ግላዊ ስኬት ብቻ ሳይሆን በመላው አፍሪካ ለሚገኙ ወጣት ሳይንቲስቶች በተለይም ወደ ኤሮስፔስ ኢንደስትሪ ለመግባት ለሚመኙ ሴቶች የመነሳሳት ምንጭ ተደርጎ ተወስዷል።።

የኢትዮጵያ ማራቶን አትሌቶች ውድድሩን አቋረጡ!በቶኪዮ አለም ሻምፒዮና የወንዶች ማራቶን በአሁን ሰአት እየተካሄደ ይገኛል።  አትሌት ደሬሳ ገለታ ፣አትሌት ታደሰ ታከለ  ውድድሩን ከ25 ኪሎ ሜ...
15/09/2025

የኢትዮጵያ ማራቶን አትሌቶች ውድድሩን አቋረጡ!

በቶኪዮ አለም ሻምፒዮና የወንዶች ማራቶን በአሁን ሰአት እየተካሄደ ይገኛል። አትሌት ደሬሳ ገለታ ፣አትሌት ታደሰ ታከለ ውድድሩን ከ25 ኪሎ ሜትር በላይ በብቃት ቢጎዙም አቋርጠዋል።

መጀመሪያ አትሌት ታደሰ ቀጥሎ ብርቱ ፍክክር እስከ 35 ኪሜ ያደረገው ደሬሳ ገለታም በተመሳሳይ ውድድሩን አቋርጧል።

ያልተለመደ የማራቶን አጨራረስ በታየበት ውድድር የታንዛኒያው አትሌት ሲምቡ አሸንፏል። በተመሳሳይ ተስፋዬ ድሪባም የውድድሩ መጀመሪያ ኪሜ አቋርጧል።

Tanzania's Alphonce Felix Simbu and Germany's Amanal Petros are rewarded the same time at Japan's National Stadium (2:09:48) 🤯

It's Tanzania's first ever gold medal at the championships and it was decided by just hundredths of a second 🇹🇿

ባላገሩ ስፖርት

አትሌት ዮሚፍ ቀጀልቻ ራሱን ከትራክ ውድድር ማግለሉን አስታወቀ! በቶኪዮ አለም ሻምፒዮና በ10 ሺ ሜትር የብር ሜዳሊያ ለኢትዮጵያ ያመጣው አትሌት ዮሚፍ ከትራክ ውድድር ራሱን ማግለሉን ከደቂቃ...
15/09/2025

አትሌት ዮሚፍ ቀጀልቻ ራሱን ከትራክ ውድድር ማግለሉን አስታወቀ!

በቶኪዮ አለም ሻምፒዮና በ10 ሺ ሜትር የብር ሜዳሊያ ለኢትዮጵያ ያመጣው አትሌት ዮሚፍ ከትራክ ውድድር ራሱን ማግለሉን ከደቂቃዎች በፊት በይፋ ማህበራዊ ገፁ አስታውቋል።

ሁሌም በአለም የውድድር መድረክ ለሀገሬ ሜዳሊያ ለማምጣት ህልም ነበረኝ የምችለውን ተዘጋጅቼ ነበር ወርቅ ለማምጣት፤ አሁን ግን የብር ሜዳሊያ ማሳካት ችያለው ለዚህም ደስተኛ ነኝ ሲል አትሌት ዮሚፍ ስለ ዛሬው ውጤት ፅፏል።

አሁን ወደ አዲስ ምዕራፍ ተሸጋግሪያለው ከትራክ ውድድር ወደ ጎዳና ላይ ሩጫ ትኩረቴ ይሆናል። ህልሜ አንድ ቀን በማራቶን ድል ወርቅ ለሀገሬ ማምጣት ነው ሲልም አትሌቱ ግቡን አሳውቋል።

ለአሰልጣኞቼ ፣ለቤተሰቤ ፣ለአዲዳስ ፣ ለአድናቂዎቼ፣ ሁሌም ብርታት ለሆናችውኝ ደጋፊዎቼ አመሰግናዋለሁ በማለት መልዕክት አስተላልፏል።

ባላገሩ ስፖርት

በ2017 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ማጠናቀቂያ ፈተና  8.4 በመቶ ተማሪዎች 50 በመቶ እና ከዚያ በላይ አምጥተዋል - ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋበ2017 ዓ.ም ትምህርት ዘመን የ12ኛ ክፍል ማጠናቀቂያ...
14/09/2025

በ2017 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ማጠናቀቂያ ፈተና 8.4 በመቶ ተማሪዎች 50 በመቶ እና ከዚያ በላይ አምጥተዋል -
ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ

በ2017 ዓ.ም ትምህርት ዘመን የ12ኛ ክፍል ማጠናቀቂያ ፈተና 8.4 በመቶ ተማሪዎች 50 በመቶ እና ከዚያ በላይ ውጤት ማስመዝገባቸውን የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ ገለጹ፡፡

50 በመቶ እና ከዚያ በላይ ውጤት ካስመዘገቡት መካከል የማኅበራዊ ሳይንስ ተፈታኞች 5.2 በመቶ፣ ተፈጥሮ ሳይንስ ተፈታኞች ደግሞ 11.4 በመቶ የ እንደሆኑ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ጠቅሰዋል፡፡

የዘንድሮው 12ኛ ክፍል ማጠናቀቂያ ፈተና ከፍተኛ ውጤት በተፈጥሮ ሳይንስ 591 ሆኖ ተመዝግቧል።

ውጤቱ የተመዘገበው ከዶዶላ ኢፈ ቦሩ ትምህርት ቤት መሆኑም ተመላክቷል።

በማኅበራዊ ሳይንስ የዘንድሮው ከፍተኛ ውጤት 562 መሆኑንም ጠቅሰዋል፡፡

የ2017 ዓ.ም ትምህርት ዘመን የ12ኛ ክፍል ማጠናቀቂያ ፈተናን አስመልክቶ መግለጫ እየተሰጠ ይገኛል።

585 ሺህ 882 ተማሪዎች ፈተናውን ተፈትነዋል፡፡

የ12ኛ ክፍል ማጠናቀቂያ ፈተና ውጤት ነገ ከ 6:00 ሰዓት ጀምሮ ይፋ ይሆናል

''አሰልጣኜ ገመዶ ያለኝን አለመስማቴ ዋጋ አስከፈለኝ'' አትሌት ዮሚፍ ቀጀልቻበጃፓን ቶኪዮ የአለም አትሌቲክስ ሻምፒዮና 10ሺ ሜትር ወንዶች የፍፃሜ ውድድር ዮሚፍ ቀጀልቻ የብር ሜዳልያ ቢያሳ...
14/09/2025

''አሰልጣኜ ገመዶ ያለኝን አለመስማቴ ዋጋ አስከፈለኝ'' አትሌት ዮሚፍ ቀጀልቻ

በጃፓን ቶኪዮ የአለም አትሌቲክስ ሻምፒዮና 10ሺ ሜትር ወንዶች የፍፃሜ ውድድር ዮሚፍ ቀጀልቻ የብር ሜዳልያ ቢያሳካም የመጨረሻው ትንቅንቅ ላይ ስለተፈጠረው ጉዳይ አነጋጋሪ አስተያየት ሰጥቷል።

በጃፓን ቶኪዮ ለተገኙ ኢትዮጵያውያን ጋዜጠኞች ከውድድሩ በኋላ አስተያየት የሰጠው አትሌት ዮሚፍ :-ቆንጆ ነበር ውድድሩ ሙቀቱ ግን አሰቸገረኝ በመሀል አፌ ደርቆ እያስቸገረኝ ውሀ እየጣጠው ነበር ። ነገር ግን ገመዶ ነግሮኛል 200ሜ ሲቀር ጠብቅ ብሎኛል ግን ከኋላ ሳይ ግር ብለው ሲከተሉኝ ፈርቼ ከ300ሜትር ፊኒሽንግ ተነሳው ያ ዋጋ አስከፈለኝ ሲል አነጋጋሪ አስተያየት ሰጥቷል።

በትክክል ገመዶ ኮቹ ያለኝን ጠብቄ ባደረግ ኖሮ ከ200 ብነሳ ልጁን አሸንፈው ነበር ሲል አሰልጣኜን ትዕዛዝ አለማክበሬ ወርቅ ለኢትዮጵያ አሳጥቶኛል ሲል ቁጭቱን ተናግሯል።

ባላገሩ ስፖርት

ከፍተኛ ትንቅንቅ በነበረው 10 ሺ ሜትር ዮሚፍ ቀጀልቻ ብር ሜዳሊያ አስመዝግቧል!በጃፓን ቶኪዮ የአለም አትሌቲክስ ሻምፒዮና ተጠባቂው 10 ሺ ሜትር የወንዶች ውድድር አትሌት ዮሚፍ ቀጀልቻ ሁለ...
14/09/2025

ከፍተኛ ትንቅንቅ በነበረው 10 ሺ ሜትር ዮሚፍ ቀጀልቻ ብር ሜዳሊያ አስመዝግቧል!

በጃፓን ቶኪዮ የአለም አትሌቲክስ ሻምፒዮና ተጠባቂው 10 ሺ ሜትር የወንዶች ውድድር አትሌት ዮሚፍ ቀጀልቻ ሁለተኛ ደረጃ አጠናቋል። ፈረንሳዊው ጂሚ ግሬሰር አንደኛ በመውጣት ወርቅ ሜዳሊያ ፣ስዊድናዊ አልሜግሬን ሶስተኛ ነሀስ ሜዳሊያ ለሀገራቸው በማስገኘት አጠናቀዋል።

Full results

1 – 🇫🇷 Jimmy Gressier – 28:55.77 SB
2 – 🇪🇹 Yomif Kejelcha – 28:55.83 SB
3 – 🇸🇪 Andreas Almgren – 28:56.02
4 – 🇰🇪 Ishmael Rokitto Kipkurui – 28:56.48
5 – 🇺🇸 Nico Young – 28:56.62 SB
6 – 🇪🇹 Selemon Barega – 28:57.21

ባላገሩ ስፖርት

በአለም አቀፉ ኢንተርቪዥን የሙዚቃ ውድድር ላይ የሚሳተፉ  የባላገሩ ምርጥ ኢትዮጵያውያን ታሪካዊውን የሩሲያ የድል  ሙዚየም ጎበኙ::ኢትዮጵያን ጨምሮ 23 ሃገሮች የሚሳተፉበት ኢንተርቪዥን ሶን...
14/09/2025

በአለም አቀፉ ኢንተርቪዥን የሙዚቃ ውድድር ላይ የሚሳተፉ የባላገሩ ምርጥ ኢትዮጵያውያን ታሪካዊውን የሩሲያ የድል ሙዚየም ጎበኙ::

ኢትዮጵያን ጨምሮ 23 ሃገሮች የሚሳተፉበት ኢንተርቪዥን ሶንግ ኮንቴስት ውድድር ላይ የሚገኙት ኢትዮጵያውያን ተወካዮች ታሪካዊውን የሩሲያ ሙዚየም በትላንትናው እለት ጎብኝተዋል::

የድል ሙዚየም በመባል የሚታወቀው የታላቁ የአርበኞች ሙዚየም በሁለተኛው የዓለም ጦርነት የሩሲያ ተሳትፎን የሚያሳይ የታሪክ ማህደር ነው።

በሩሲያ የሚገኘው ይህ ትልቁ የውትድርና ታሪክ ሙዚየም በአውሮፓ ውስጥ ትልቁ የሁለተኛው የዓለም ጦርነት ወታደራዊ መሣሪያዎች ስብስብ መኖሪያ ነው::

በታላቁ የድል ሙዚየም ውስጥ ፣ጎብኚዎች ሩሲያ በግጭቱ ውስጥ መሳተፉን የሚገልጽ አሳዛኝ ፣ ደብዳቤዎች ፣ የጦር መሳሪያዎች ፣ የደንብ ልብስ ፣ ፎቶግራፎች ፣ ጋዜጦች እና የተለያዩ ሰነዶች ያገኛሉ ።

በባላገሩ ምርጥ አስተባባሪነት በአንጋፋዋ ጋዜጠኛ ሮማን ተገኝ እየተመሩ ኢንተርቪዥን ሶንግ ኮንቴስት 2025 ላይ ለመሳተፍ ሩሲያ የሚገኙት ኢትዮጵያውያንም ይህንኑ ታሪካዊ ስፍራ ጎብኝተዋል::

ኢንተርቪዥን ሶንግ ኮንቴስት 2025("Intervision Song Contest 2025" )የመክፈቻ ስነስርአት ከትላንት በስቲያ በሩሲያ ዋና ከተማ በሞስኮ በደመቀ ስነስርአት መካሄዱ ይታወሳል::

Address

Lancha Infront Of Global Hotel Meaza Desalegn Building 14th Floor
Addis Ababa
1000

Opening Hours

Monday 02:30 - 11:30
Friday 02:30 - 01:45

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Balageru TV posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to Balageru TV:

Share

Category

Balageru TV

Balageru television, Television programming that promotes Ethiopian history, culture, tradition, lifestyle, investment, tourism, current affairs, sports, and entertainment.