Balageru TV

Balageru TV Balageru television, promotes Ethiopian history, culture, tradition, lifestyle, investment, tourism..

Our Channel Frequency
NSS12 57 Degree East HD, Freq - 11105, Pol - Horizontal, S/R - 45000
or
DSTV Channel - 484

የሃይማኖት ተቋማት ጉባኤ በአርሲ በንጹሃን ላይ የተፈጸመውን ግድያና ቃጠሎ አወገዘ​ የኢትዮጵያ የሃይማኖት ተቋማት ጉባኤ በአርሲ ዞን አሰኮ፣ ሽርካ፣ ሆንቆሎ፣ ዋቤ እና ሙኔሳ ወረዳዎች በኦርቶ...
03/06/2026

የሃይማኖት ተቋማት ጉባኤ በአርሲ በንጹሃን ላይ የተፈጸመውን ግድያና ቃጠሎ አወገዘ

​ የኢትዮጵያ የሃይማኖት ተቋማት ጉባኤ በአርሲ ዞን አሰኮ፣ ሽርካ፣ ሆንቆሎ፣ ዋቤ እና ሙኔሳ ወረዳዎች በኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን አገልጋዮችና ምዕመናን ላይ የተፈጸመውን አሰቃቂ ግድያ እና የአብያተ ክርስቲያናት ቃጠሎ በጽኑ ማውገዙን አስታወቀ።

ጉባኤው በጥቃቱ የተሰማውን ጥልቅ ሃዘን ገልጾ፣ ለተጎጂ ቤተሰቦች መጽናናትን ተመኝቷል።
​ቀደም ሲል ተመሳሳይ ጥቃቶች እንዳይፈጸሙ ጥበቃ እንዲደረግ መጠየቁን ያስታወሰው ጉባኤው፣ አሁንም ችግሩ ባለመቀረፉ ተጨማሪ ጉዳት መድረሱ ሃዘኑን እጥፍ ድርብ እንዳደረገው ገልጿል።

​በመሆኑም መንግሥት የዜጎችን ደህንነት የማረጋገጥ ተቀዳሚ ኃላፊነቱን እንዲወጣ፣ ለተፈናቀሉና ስጋት ላለባቸው ዜጎች አስተማማኝ ጥበቃ እንዲያደርግ እንዲሁም ወንጀለኞችን በአፋጣኝ ለፍርድ እንዲያቀርብ በጥብቅ አሳስቧል።

አባል ተቋማት ድርጊቱን በአንድነት እንዲያወግዙና የአካባቢው ማህበረሰብም በጋራ እንዲተጋገዝ ጥሪ አቅርቧል።

ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአኵስም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለሃይማኖት በአርሲ ሀገረ ስብከት በቤተ ክርስቲያናችን እና በኦርቶዶክሳ...
03/06/2026

ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአኵስም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለሃይማኖት በአርሲ ሀገረ ስብከት በቤተ ክርስቲያናችን እና በኦርቶዶክሳውያን ላይ የደረሰውን ጥቃት በማስመልከት አባታዊ መልእክት አስተላለፉ።

ግንቦት 26 ቀን 2018 ዓ.ም.
አዲስ አበባ፣ ኢትዮጵያ

ቅዱስነታቸው ያስተላለፉት አባታዊ የኀዘን መልእክት እንደሚከተለው ነው፦

መልእክተ ብፁዕ ወቅዱስ ፓትርያርክ
በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን፡፡

‹‹ወረሰዩ አብድንቲሆሙ ለአግብርቲከ መብልዐ ለአዕዋፈ ሰማይ፣ ወሥጋሆሙኒ ለጻድቃኒከ ለአራዊተ ገዳም፦ የአገልጋዮችህንም በድኖች ለሰማይ ወፎች መብል አደረጉ፥ የቅዱሳንህንም ሥጋ ለምድር አራዊት።››
(መዝሙረ ዳዊት ፸፰፥፪)

በአርሲ ሀገረ ስብከት በአሰኮ፣ በሽርካ፣ በሆንቆሎ፣ በዋቤ እና በሙኔሳ ወረዳዎች በመንፈስ ቅዱስ ልጆቻችንና በቅድስት ቤተ ክርስቲያን ላይ ስለደረሰው አሰቃቂ ጥቃት የሰማነው በተሰበረ ልብ ነው።
የእምነት ነፃነት ተደፍሮ መቶ ዓመታት ያስቆጠረው የጠላታ ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን በተቃጠለበት፣ እንዲሁም የካራ ኩፍቴና መድኃኔ ዓለም ቤተ ክርስቲያን በተዘረፈበት በዚህ ክፉ ቀን፤ በርካታ ምእመናን በግፍ መሰዋታቸውና በመቶዎች የሚቆጠሩ ወገኖቻችን ከቀዬአቸው መፈናቀላቸው ቤተ ክርስቲያናችንን በእጅጉ ያሳዘነ ክስተት ነው።

የሰላም፣ የፍቅርና የታሪክ ማህደር የሆነችው ቤተ ክርስቲያን በምድራዊ መከራ ውስጥ ያሉትን ምእመናን በምታጽናናበት በዚህ ወቅት ራሷ በፈተና ውስጥ ሆና ከመቸገሯም በላይ በአርሲ ምድር በተደጋጋሚ የሚስተዋለው በደልና ግፍ በሁላችንም ልቡና ውስጥ "እስከ መቼ?" የሚል የቁጭት እና የኀዘን ጥያቄን ፈጥሯል።

በመሆኑም ይህ መከራ እያበቃ ሳይሆን እየሰፋ በመምጣቱ የዜጎችን ደኅንነት የመጠበቅና ሰላምን የማስፈን አደራ የተጣለባችሁ የጸጥታ አካላትና በየመዋቅሩ ያላችሁ ሓላፊዎች ከምንም በላይ ታሪክ የሚጠይቃችሁ በሥልጣን ዘመናችሁ ለዜጎች ደኅንነት በምትከፍሉት ዋጋ ነውና ይህንን የጥቃት ሰንሰለት በማስቆምና ወንጀለኞችን ለሕግ በማቅረብ ከታሪክ ባለዕዳነት ትድኑ ዘንድ በቤተ ክርስቲያናችን ስም አበክረን እናሳስባለን።

በየአካባቢው የምትገኙ ምእመናንና መላው ኢትዮጵያውያንም በወንድማማችነት መንፈስ ተጋግዛችሁ፣ የተፈናቀሉ ወገኖችን በመደገፍና በጸሎት ከቤተክርስቲያናችን ጎን እንድትሆኑ ጥሪያችንን እናቀርባለን።

በመጨረሻም ቤተ ክርስቲያናችን ለሰላም፣ ለይቅርታና ለሰው ልጆች ክብር ሁል ጊዜ የምትቆም መሆኑን በመግለጽ ይህንን የኀዘን ሰዓት አምላካችን በምሕረቱ ያሳልፍልን፣ የሞቱትን ነፍሶቻቸውን በመንግሥቱ ይቀበልልን፣ የተጎዱትንም በቸርነቱ ያጽናናልን በማለት አባታዊ የኀዘን መልእክታችንን በእግዚአብሔር ስም እናስተላልፋለን።

እግዚአብሔር አምላክ ኢትዮጵያንና ሕዝቦችዋን ይባርክ!!

ወስብሐት ለእግዚአብሔር!!!
አሜን።

አባ ማትያስ ቀዳማዊ
ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ
ሊቀ ጳጳስ ዘአኵስም ወዕጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት
ግንቦት 26 ቀን 2018 ዓ.ም.
አዲስ አበባ፣ ኢትዮጵያ

© የብፁዕ ወቅዱስ ፓትርያርክ ልዩ ጽሕፈት ቤት

የአፍሪካ ኅብረት የታዛቢዎች ቡድን በአዲስ አበባ የምርጫ ጣቢያዎች ጊዜያዊ ውጤቶችን እየተመለከተ ይገኛል
02/06/2026

የአፍሪካ ኅብረት የታዛቢዎች ቡድን በአዲስ አበባ የምርጫ ጣቢያዎች ጊዜያዊ ውጤቶችን እየተመለከተ ይገኛል

ድምጽ የመስጠት ሒደቱ እስከ ዕኩለ ሌሊት 6 ሰዓት ድረስ ይቆያልየ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ድምጽ የመስጠት ሒደት እስከ ዕኩለ ሌሊት 6 ሰዓት ድረስ ተራዝሟል አለ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ፡፡...
01/06/2026

ድምጽ የመስጠት ሒደቱ እስከ ዕኩለ ሌሊት 6 ሰዓት ድረስ ይቆያል

የ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ድምጽ የመስጠት ሒደት እስከ ዕኩለ ሌሊት 6 ሰዓት ድረስ ተራዝሟል አለ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ፡፡

ምርጫ ቦርድ ጉዳዩን አስመልክቶ ባወጣው መግለጫ÷ ዛሬ ሰኞ ግንቦት 24 ቀን 2018 ዓ.ም ከማለዳ 12 ሰዓት ጀምሮ እስከ ምሽት 12 ሰዓት የ7ኛውን ጠቅላላ ምርጫ ድምፅ የማስፈጸም ሒደት ላይ እንደነበር ጠቅሷል፡፡

ቦርዱ በሥምሪት ላይ ያለው የክትትል ቡድኑ ያቀረበለትን ሪፖርት ተመልክቶ ውሳኔ ማሳለፉን አመልክቷል፡፡

በኢትዮጵያ የምርጫ፣ የፖለቲካ ፓርቲዎች ምዝገባና የምርጫ ሥነ ምግባር ዐዋጅ 1162/2011 አንቀጽ 49(4) መሠረት ቦርዱ የምርጫው ነፃና ፍትሐዊነት ይበልጥ ያሰፍናል ብሎ ካመነ የድምፅ መስጫ ሰዓቱን ሊያራዝም እንደሚችል በግልጽ ይደነግጋል።

በዚህ መሰረትም የድምጽ መስጫ ሒደት ባልተጠናቀቀባቸው የምርጫ ጣቢያዎች ላይ ድምጽ የመስጠት ሒደቱ እስከ ዕኩለ ሌሊት 6 ሰዓት ድረስ የተራዘመ መሆኑን ነው ቦርዱ ያስታወቀው፡፡

የተመዘገቡ መራጮች መርጠው የተጠናቀቁባቸው ጣቢያዎች ላይ አስፈጻሚዎች የድምፅ ቆጠራ ሒደቱን እንዲያከናውኑም ቦርዱ አሳስቧል፡፡

የኢፌዴሪ ፕሬዝዳንት አምባሳደር ታዬ አጽቀሥላሴ በ7ተኛው ጠቅላላ ምርጫ በአራዳ ምርጫ ክልል 1/9 ወጣት ማዕከል ምርጫ ጣቢያ የመራጭነት ድምፃቸውን ሰጥተዋል፡፡ፕሬዝዳንቱ ለመገናኛ ብዙሃን በሰ...
01/06/2026

የኢፌዴሪ ፕሬዝዳንት አምባሳደር ታዬ አጽቀሥላሴ በ7ተኛው ጠቅላላ ምርጫ በአራዳ ምርጫ ክልል 1/9 ወጣት ማዕከል ምርጫ ጣቢያ የመራጭነት ድምፃቸውን ሰጥተዋል፡፡

ፕሬዝዳንቱ ለመገናኛ ብዙሃን በሰጡት መግለጫ የመረጥኩት ለሀገሬ ፣ ቤተሰቤ እና እንደ ግለሰብ ለራሴም ነው ሲሉ ገልጸዋል፡፡

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በበሻሻ ድምፅ ሰጡ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ በትውልድ ቀያቸው በሻሻ ጎማ ሁለት ሀሮ ምርጫ ጣቢያ ድምፅ ሰጥተዋል...
01/06/2026

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በበሻሻ ድምፅ ሰጡ

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ በትውልድ ቀያቸው በሻሻ ጎማ ሁለት ሀሮ ምርጫ ጣቢያ ድምፅ ሰጥተዋል።

ራይድ ትራንስፖርት በአፍሪካ ከፍተኛ ሽልማት አሸነፈ!ራይድ ትራንስፖርት (RIDE) በAfrica's Best Brands Award ላይ Most Admired Ethiopian Brand በመሆን ለከፍ...
31/05/2026

ራይድ ትራንስፖርት በአፍሪካ ከፍተኛ ሽልማት አሸነፈ!

ራይድ ትራንስፖርት (RIDE) በAfrica's Best Brands Award ላይ Most Admired Ethiopian Brand በመሆን ለከፍተኛ ሽልማት በቅቷል::

በአዲስ አበባ United Nations Economic Commission for Africa (ECA) በተደረገው የሽልማት ስነ-ስርዓት ላይ ድርጅቱ ይህንን ታላቅ ክብርና ሽልማት በማግኘቱ የተሰማውን ደስታ ለመላው የራይድ ቤተሰብ ገልጿል።

ድርጅቱ በ2006 ዓ.ም "RIDE" የተሰኘውን የንግድ ስም እና ምልክት በኢትዮጵያ አዕምሮአዊ ንብረት ጥበቃ በማስመዝገብ በኢትዮጵያ የመጀመርያውን የኤሌክትሮኒክ ታክሲ አገልግሎት ዘርፍ ፈር - ቀዳጅ ሲሆን በአሁን ወቅት በስፋት አገልግሎቱን እያቀረበ ይገኛል:: በተጨማሪም በFood Delivery እና ተዛማች አገልግሎቶች ላይ በመሪነት እያገለገለ ይገኛል::

ድርጅቱ እንዳለው "ይህንን ትልቅ ብራንድ ስንገነባ በነበረው ሂደት ከጎናችን ለነበራችሁ አሽከርካሪዎች ÷ ደንበኞቻችን እና መላው የራይድ ቤተሰቦች በቀጣይም ከኢትዮጵያ አልፎ በአፍሪካ በምናደርገው ጉዞ አብራችሁን በዘላቂ ወዳጅነት እንደምትቀጥሉ እንተማመናለን ብሏል።

ታዳጊዎቹ ለዓለም ዋንጫ  ለማለፍ ተቃርበዋል  !የኢትዮጵያ ሴቶች ታዳጊ ብሄራዊ ቡድን የዓለም ዋንጫ ማጣርያሁለተኛ ዙር የመልስ ጨዋታ ብሩንዲን በሜዳዋ ቡጁቡራ ላይ 2ለ1 አሸንፈዋል። ለኢትዮጵ...
30/05/2026

ታዳጊዎቹ ለዓለም ዋንጫ ለማለፍ ተቃርበዋል !

የኢትዮጵያ ሴቶች ታዳጊ ብሄራዊ ቡድን የዓለም ዋንጫ ማጣርያ
ሁለተኛ ዙር የመልስ ጨዋታ ብሩንዲን በሜዳዋ ቡጁቡራ ላይ 2ለ1 አሸንፈዋል።

ለኢትዮጵያ ሴቶች ታዳጊ ቡድን ጎሎቹን ምኅረት አየለ ፣ልዲያ ኢያሱ አስቆጥረዋል ።በመጀመሪያ ዙር ጨዋታ በአዲስ አበባ አበበ ቢቂላ ላይ በትንንሾቹ ሉሲዎች አሸናፊነት 2ለ1 መጠናቀቁ ይታወሳል ።

በድምር ውጤት ጨዋታው :2ለ 4 ተጠናቋል ።ኢትዮጵያ ሴቶች ታዳጊ ቡድን በቀጣይ የዛምቢያን ታዳጊ ቡድን በደርሶ መልክ ካሸነፉ በቀጥታ የአለም ዋንጫ. ለመሳተፍ የሞሮኮ ትኬት ይቆርጣሉ ።

ባላገሩ ስፖርት

ለ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ከ64 ሺህ በላይ የሀገር ውስጥ እና የዓለም አቀፍ ታዛቢዎች ይሰማራሉተባለየኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ሰብሳቢዋ እንዳሉት 55 የሀገር ውስጥ የሲቪል ማኅበረሰብ ድርጅቶ...
30/05/2026

ለ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ከ64 ሺህ በላይ የሀገር ውስጥ እና የዓለም አቀፍ ታዛቢዎች ይሰማራሉተባለ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ሰብሳቢዋ እንዳሉት 55 የሀገር ውስጥ የሲቪል ማኅበረሰብ ድርጅቶች የምርጫ ታዛቢነት ዕውቅና ማግኘታቸውን አስታውቀዋል።

እነዚህ ድርጅቶች 1 ሺህ 572 አስተባባሪዎችን እንዲሁም 64 ሺህ 770 ቋሚ እና ተዘዋዋሪ ታዛቢዎችን በምርጫው ዕለት እንደሚያሰማሩ የገለጹት ሰብሳቢዋ፣ ለሁሉም ታዛቢዎች የሚሆን አስፈላጊው የባጅ ዝግጅት መደረጉን አመልክተዋል።

ከሀገር ውስጥ ታዛቢዎች በተጨማሪ የተለያዩ ዓለም አቀፍ ተቋማት ምርጫውን ለመታዘብ ዝግጅታቸውን ማጠናቀቃቸው ተገልጿል።

በዚህም መሠረት የአፍሪካ ኅብረት በቀድሞው የኬንያ ፕሬዚዳንት ኡሁሩ ኬንያታ የሚመራ 59 አባላት ያሉት የታዛቢ ቡድን ያሰማራል።

በተመሳሳይ የምሥራቅ አፍሪካ የልማት በይነ መንግሥታት ባለሥልጣን (ኢጋድ) በቀድሞዋ የኡጋንዳ ምክትል ፕሬዚዳንት ስፔሲዮሳ ዋንዲራ ካዚብዌ (ዶ/ር) የሚመራ የታዛቢ ቡድን ያሳማራል፡፡

26 አባላት ያሉት የኢጋድ ዓለም አቀፍ ታዛቢዎች ቡድን ምርጫውን እንደሚታዘቡ የጠቀሱት ሰብሳቢዋ፣ በአጠቃላይ 64 ሺህ 855 ታዛቢዎች ምርጫውን እንደሚታዘቡ አረጋግጠዋል።

''ሴቶች  ካመኑብህ ገደል ግቡ ብትላቸው ይገቡልሀል'' አሰልጣኝ ሰለሞን ገለታ ...ከግል እስከ ቡድን በቀላሉ የማይሰበር  ፣ 90 ደቂቃ ትኩረት ያለው ጠንካራ በራስ መተማመን ያለው  ተከላካ...
29/05/2026

''ሴቶች ካመኑብህ ገደል ግቡ ብትላቸው ይገቡልሀል'' አሰልጣኝ ሰለሞን ገለታ ...

ከግል እስከ ቡድን በቀላሉ የማይሰበር ፣ 90 ደቂቃ ትኩረት ያለው ጠንካራ በራስ መተማመን ያለው ተከላካይ ክፍል ለመስራት አሞክራለው ። ቡድኔ ሲያጠቃ አግሬሲቭ እንዲሆን እፈልጋለው ይላል...ጥሩነሽ ዲባባ አካዳሚን በሴቶች ወደ ፕሪሚየር ሊግ ያሳደገው አሰልጣኝ ሰለሞን ገለታ ።

አሰልጣኝ ሰለሞን ገለታ ..በአትሌት ጥሩነሽ ዲባባ ስፖርት ማሰልጠኛ ማዕከል ለ 10 አመታት በሁለቱም ፆታ እግር ኳስ አሰልጥኗል። በአንቦ ጎል ፊፋ ፕሮጀክት የእግር ኳስ ማሰልጠኛ ውስጥም ለ 2 አመት ሰርቷል ።

የዘንድሮ ሴቶች ከፍተኛ ሊግ ፈታኙን ውድድር ነበር ፣ የቡድኖች ተቀራራቢ አቋም የመጀመሪያው ዙር ሀዋሳ ላይ ፋሲል በ27 ነጥብ አንደኛ ሆኖ ቢጨርስም ከሱ በታች በ4 ነጥብ ዝቅ ብለው በ23 ነጥብ አዲስ ከተማ , ጥሩነሽ እና ጉለሌ በእኩል ነጥብ በጎል ተበላልጠው ይከተሉ ነበር.... ከሌሎችም ቡድኖች የበዛ የነጥብ ልዩነት የሌለበት ጠንካራ ፉክክር የነበረበት ነበረ።

በሁለተኛው ዙር የዠግጅት ግዜ የነበሩብን ክፍተቶች ላይ በደንብ በመስራት በሁለተኛው ዙር ላይ ያለምንም ሽንፈት 11 ጨዋታ በማሸነፍ 1 ብቻ አቻ በመውጣት 2 ጨዋታዎች እየቀሩን ሻንፒዮን መሆናችንን አረጋገጥን .ይህ የ4አመት የስልጠና ጉዞ ልፋት ውጤት ነው ይላል አሰልጣኝ ሰለሞን አመቱን ሲገልፀው ።

ሴቶች ላይ መስራት ትግስት ይጠይቃል በደንብ መከታተል እና እነሱን መረዳት ይጠበቅብሀል በተለይ ቲም ስፕሪት ላይ በጣም ትቸገራለህ ይላል ።

በትንሹ ተኳርፈው ግሩፕ ይዘው ልታገኛቸው ትችላለህ ባጠቃላይ የምትቸገረው ከስልጠና ውጪ ያሉ ነገሮችን ማኔጅ ማድረግ በጣም ከባድ ነው ። ከዛ ውጪ ካመኑብህ ገደል ግቡ ብትላቸው ይገቡልሀል ሲል በግልፅ ሴቶች ላይ መስራት ያለውን ፈተና እና መልካም ነገር አሰልጣኙ ይናገራል።

ታዛሽ ናቸው ሰአት አክባሪ ናቸው ያላቸውን ለመስጠት ወደኋላ የማይሉ ናቸው በአጠቃላይ ሴቶች ላይ ሞር ሜንታል ላይ መስራት በጣም በጣም አስፈላጊ ነው ።

ጥሩነሽ ዲባባ ማሰልጠኛ በርካታ ኮከቦችን እያፈራ ነው .አሁን ከ 17 አመት በታች ብሄራዊ ቡድን ውስጥ 8ቱ ልጆች የጥሩነሽ ዲባባ ናቸው ..ሊዲያ እያሱ ፣ሊዲያ ሰለሞን ፣ ኛገዋ ማኔ ጌጤነሽ ለምለም ኮከብ ,አጁሉ እመቤት ..እና ሌሎችን እያፈራ ነው።

የወደፊት እቅዴ የማሰልጠን ልምድ እያገኘው ስለሆነ የኮቺንግ ላይሰንሴን አሳድጌ ያለኝን እውቀት ለሀገር እና ለክለቦች ማበርከት መቻል ነው ሲል ምኞት እና እቅዱን ይገልፃል... ባለትዳር የአንድ ወንድ ልጅ አባት የሆነው ሻምፒዮኑ አሰልጣኝ ሰለሞን ገለታ።

ባላገሩ ስፖርት

Address

Lancha Infront Of Global Hotel Meaza Desalegn Building 14th Floor
Addis Ababa
1000

Opening Hours

Monday 02:30 - 11:30
Friday 02:30 - 01:45

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Balageru TV posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to Balageru TV:

Share

Category