Balageru TV

Balageru TV Balageru television, promotes Ethiopian history, culture, tradition, lifestyle, investment, tourism..

Our Channel Frequency
NSS12 57 Degree East HD, Freq - 11105, Pol - Horizontal, S/R - 45000
or
DSTV Channel - 484

ሁለተኛ ወርቅ ሜዳሊያ ለኢትዮጵያ ተመዝግቧል !በዓለም ከ20 ዓመት በታች የአትሌቲክስ ሻምፒዮና ኦሪገን አሜሪካ በአራተኛ ቀን ውሎ ለኢትዮጵያ ሁለተኛ ወርቅ ሜዳሊያ ተገኝቷል።የሴቶች 3000 ሜ...
09/08/2026

ሁለተኛ ወርቅ ሜዳሊያ ለኢትዮጵያ ተመዝግቧል !

በዓለም ከ20 ዓመት በታች የአትሌቲክስ ሻምፒዮና ኦሪገን አሜሪካ በአራተኛ ቀን ውሎ ለኢትዮጵያ ሁለተኛ ወርቅ ሜዳሊያ ተገኝቷል።

የሴቶች 3000 ሜትር የፍፃሜ ውድድር ኢትዮጵያውያን አትሌቶች የወርቅ እና የብር ሜዳልያ አሸናፊ ሆነዋል፡፡

አትሌት ዮርዳኖስ ፅጋብ 8:43.65 ሰዓት በመግባት የወርቅ ሜዳልያ አሸናፊ ፣አትሌት ሽቶ ጉሚ በሁለተኛነት የብር ሜዳልያ አስመዝግባለች፡፡

የሴቶች 5000 ሜትር አሸናፊ ኡጋንዳዊቷ ቻሪቲ ቼሮፕ በ3ኛነት አጠናቃለች ። ኢትዮጵያ ሁለተኛ ወርቅ ማግኘቷን ተከትሎ ከአለም በደረጃ ሰንጠረዥ 3ኛ ተቀምጣለች። Balageru TV

ኮልፌ ኢንዱስትሪያል ኮሌጅ ከስልጠና ባለፈ ለአካባቢው ማህበረሰብ ጥራታቸውን  የጠበቀቁ ምርቶችን በተመጣጣኝ ዋጋ እያቀረበ መሆኑን አስታወቀ።ኮሌጁ በ2018 በጀት ዓመት ያከናወናቸውን አምስት ...
08/08/2026

ኮልፌ ኢንዱስትሪያል ኮሌጅ ከስልጠና ባለፈ ለአካባቢው ማህበረሰብ ጥራታቸውን የጠበቀቁ ምርቶችን በተመጣጣኝ ዋጋ እያቀረበ መሆኑን አስታወቀ።

ኮሌጁ በ2018 በጀት ዓመት ያከናወናቸውን አምስት ዋና ፕሮጀክቶች፣ የተለያዩ መሠረተ ልማቶችና ስማርት ማሰልጠኛ ክፍሎችን አስመርቋል።

ከተመረቁት ፕሮጀክቶች መካከል የኮሌጁን የውሃ አቅርቦት ችግር ለመፍታት የተከናወነ የከርሰ ምድር ውሃ ፕሮጀክት፣ ስማርት ማሰልጠኛ ክፍሎችና ሌሎች የስልጠና መሠረተ ልማቶች ይገኙበታል።

የኮልፌ ቀራንዮ ክፍለ ከተማ ም/ሥራ አስፈፃሚና የሥራና ክህሎት ጽ/ቤት ሃላፊ አቶ አከበርከኝ ወጋገን፣ ኮሌጁ በአጭር ጊዜ ያሳየው ለውጥ የሚያበረታታ መሆኑን ገልጸዋል።

ኮሌጁ በከተማ ግብርናና በምርት ዘርፍ በመሳተፍ የዋጋ ንረትን ለመቀነስና የአካባቢውን ማህበረሰብ ተጠቃሚ ለማድረግ እየሰራ ያለው ሥራም አበረታች መሆኑን ጠቁመዋል።

የኮሌጁ ዋና ዲን ዶ/ር ቢንያም አወቀ እንደገለጹት፣ ኮሌጁ በማምረት ዘርፍ በመሳተፍ ለአካባቢው ህብረተሰብ ዳቦ፣ ቡና፣ የለውዝ ቅቤና የወተት ተዋፅኦዎችን በተመጣጣኝ ዋጋ እያቀረበ ነው።

በተለይም የዳቦ ምርቱ ጥራቱን በመጠበቅ ለማህበረሰቡ እየቀረበ መሆኑን ዶ/ር ቢንያም ገልጸዋል።

ኮሌጁ ከፍተኛ የማምረት አቅም ቢኖረውም፣ የመሸጫ ቦታ እጥረትና ከአካባቢው ፍላጎት ጋር በተያያዘ ከአቅሙ በታች እያመረተ መሆኑን ጠቁመዋል።

ምርቶቹን በሌሎች አካባቢዎችም ተደራሽ ለማድረግና የምርት አቅሙን ለማሳደግ ከሚመለከታቸው አካላት ጋር ውይይት እያደረገ መሆኑንም አስታውቀዋል።

ኮሌጁ በሙያ ስልጠና ዘርፍም ትልቅ ሥራ እየሰራ መሆኑ ተገልጿል። በኢንዱስትሪ፣ በማምረቻ፣ በኤሌክትሪክ፣ በሜካኒክ፣ በኮንስትራክሽን፣ በአይቲና በሌሎች የሙያ መስኮች ስልጠና የሚሰጥ ሲሆን፣ በአጫጭር ስልጠናዎች 50 ሺህ ሰልጣኞችን ማፍራት ችሏል።

የኮሌጁ የስልጠናና አካዳሚክ ጉዳዮች ምክትል ዲን ወ/ሮ ሳራ አበበ፣ በኮሌጁ የንድፈ ሐሳብ ትምህርትን ከተግባራዊ ስልጠና ጋር በማጣመር የሥራ ክህሎትና ፈጠራን የሚያጠናክር ስልጠና እየተሰጠ መሆኑን ገልጸዋል።

በኮሌጁ የሰለጠኑ ባለሙያዎችም በከፍተኛ ደረጃ የሥራ ዕድል ማግኘታቸውን ጠቁመዋል።

የኮልፌ ቀራንዮ ክፍለ ከተማ ምክር ቤት ዋና አፈ ጉባዔ ወ/ሮ ቦጋለች ተድላ በበኩላቸው፣ የተከናወኑት ሥራዎች የአካባቢውን ማህበረሰብ ተጠቃሚነት በተጨባጭ ያረጋገጡ መሆናቸውን ገልጸው፣ ኮሌጁ ሥራ አልባ ወጣቶችን በማሰልጠን የሥራ ዕድል እየፈጠረ መሆኑን አክለዋል።

ዋና ዲኑ ዶ/ር ቢንያም አወቀ እንደገለጹት፣ ኮሌጁ ቀደም ሲል ያጋጠሙትን የመሠረተ ልማትና የመልካም አስተዳደር ችግሮች ከባለድርሻ አካላት ጋር በመሆን በዕቅድ መፍታት ችሏል።

ኮሌጁ በ2010 ዓ.ም ከተቋቋመ ጀምሮ በርካታ ተግዳሮቶችን ቢያልፍም፣ ዛሬ ላይ ስልጠናን፣ ምርትንና ማህበረሰብን በአንድ ላይ በማስተሳሰር የሚሰራ ተቋም ለመሆን እየተሻገረ መሆኑ ተመላክቷል።

በአለታ ወንዶ በደረሱ ሁለት የትራፊክ አደጋዎች የ7 ሰዎች ሕይወት አለፈ​በሲዳማ ክልል አለታ ወንዶ ከተማ ቡልቱማ ቀበሌ ትናንት ምሽት በደረሱ ሁለት የትራፊክ አደጋዎች የሰባት ሰዎች ሕይወት ...
08/08/2026

በአለታ ወንዶ በደረሱ ሁለት የትራፊክ አደጋዎች የ7 ሰዎች ሕይወት አለፈ

​በሲዳማ ክልል አለታ ወንዶ ከተማ ቡልቱማ ቀበሌ ትናንት ምሽት በደረሱ ሁለት የትራፊክ አደጋዎች የሰባት ሰዎች ሕይወት ማለፉን የክልሉ ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ አስታወቀ።

​ከቦረና ወደ ሀዋሳ ሲጓዝ የነበረ የፌዴራል ፖሊስ ተሽከርካሪ በመገልበጡ የስድስት የፌዴራል ፖሊስ አባላት ሕይወት አልፏል።

በተመሳሳይ ስፍራ አንድ የሲኖትራክ ጭነት ተሽከርካሪ መንገድ ስቶ ወደ መኖሪያ ቤት በመግባቱ የአንድ ሰው ሕይወት ማለፉ ተገልጿል።

​በአደጋዎቹ ጉዳት የደረሰባቸው አምስት ሰዎች ለህክምና ወደ ሀዋሳ ሪፈራል ሆስፒታል የተወሰዱ ሲሆን፣ የሁለቱም አደጋዎች መንስኤ በፖሊስ እየተጣራ እንደሚገኝ የትራፊክ አደጋ መከላከልና ምርመራ ኃላፊ ኢንስፔክተር መለሰ ቡኑራ አስታውቀዋል።

የወርቅ ሜዳሊያ  ተመዝግቧል !ከ20 ዓመት በታች የአለም አትሌቲክስ ሻምፒዮና በኦሪገን አሜሪካ ቀጥሏል ። የመጀመሪያ ወርቅም ተመዝግቧል ።አትሌት አልማዝ ዮሐንስ በ3ሺ ሜ  በ09:15.81  ...
08/08/2026

የወርቅ ሜዳሊያ ተመዝግቧል !

ከ20 ዓመት በታች የአለም አትሌቲክስ ሻምፒዮና በኦሪገን አሜሪካ ቀጥሏል ። የመጀመሪያ ወርቅም ተመዝግቧል ።

አትሌት አልማዝ ዮሐንስ በ3ሺ ሜ በ09:15.81 ምርጥ ሰዓት በማስመዝገብ አሸንፋለች።አትሌት ወሰኔ አሰፋ ብር ሜዳሊያ አስመዝግባለች።

የግራንድ አፍሪካ ራን አዘጋጆች "ከሩጫም በላይ ነው!" በሚል መርሃ ግብር 10 የበጎ አድራጎት አጋሮችን አስተዋወቁ  | ዋሽንግተን ዲሲ - የግራንድ አፍሪካ ራን አዘጋጆች በዋሽንግተን ዲሲ ባ...
07/08/2026

የግራንድ አፍሪካ ራን አዘጋጆች "ከሩጫም በላይ ነው!" በሚል መርሃ ግብር 10 የበጎ አድራጎት አጋሮችን አስተዋወቁ

| ዋሽንግተን ዲሲ - የግራንድ አፍሪካ ራን አዘጋጆች በዋሽንግተን ዲሲ ባካሄዱት ጋዜጣዊ መግለጫ፣ በዘንድሮው ዝግጅት አብረዋቸው የሚሠሩ 10 የበጎ አድራጎት ድርጅቶችን በይፋ አስተዋውቀዋል።

" ከሩጫም በላይ ነው!" በሚለው መርሃ ግብር፣ አዘጋጅ አካሉ በኢትዮጵያ፣ በአሜሪካና በሌሎች የአፍሪካ ሀገራት ድጋፍ የሚሹ ማኅበረሰቦችን ከሚያገለግሉ ተቋማት ጋር በቅንጅት እንደሚሠራ ገልጻል።

እነዚህ አጋር ድርጅቶች በካንሰር ግንዛቤና ሕሙማን ድጋፍ፣ ልዩ ፍላጎት ያላቸውን ወገኖች በማገዝ፣ የሕፃናት ትምህርትን በመደገፍ፣ ድህነትን በመቀነስ፣ የነርሶችና የሌሎች ባለሙያዎችን አቅም በማጎልበት እንዲሁም ንጹሕ የመጠጥ ውኃ በማቅረብ ዘርፍ የተሰማሩ ናቸው።

በጋዜጣዊ መግለጫው የተወከሉት የየተቋማቱ ተወካዮች ማኅበረሰቡ በዝግጅቱ እንዲሳተፍ ጥሪ ያቀረቡ ሲሆን፣ ተሳታፊዎችም የመረጡትን የበጎ አድራጎት ድርጅት በመደገፍ ተሳትፏቸውን ትርጉም ያለው እንዲያደርጉ ጠይቀዋል።

በምዕራቡ ዓለም የበጎ አድራጎት ድርጅቶች የሩጫ ዝግጅቶችን ለገቢ ማሰባሰቢያነት ይጠቀሙበታል። በተመሳሳይ መልኩ እነዚህ 10 ድርጅቶች ግራንድ አፍሪካ ራንን እንደ መድረክ በመጠቀም፣ ተሳታፊዎች ከወዳጅ ዘመዶቻቸውና ከሥራ ባልደረቦቻቸው ገቢ እንዲያሰባስቡ ዕድል ያመቻቻሉ። ተሳታፊዎች የአምስት ኪሎ ሜትር ርቀቱን በመክፈል ወዳጆቻቸው ለእያንዳንዱ ርቀት ድጋፍ እንዲያደርጉ በኢሜይል፣ በአጭር ጽሑፍ፣ በስልክ ወይም በማኅበራዊ ሚዲያ መጠየቅ ይችላሉ።

የሚሰበሰበው ገቢ በቀጥታ ወደ ተመረጠው ድርጅት የሚገባ ሲሆን፣ ተሳታፊዎችም በድረ ገጹ ላይ የተሰበሰበውን መጠንና የደጋፊዎችን ማንነት መከታተል ይችላሉ። የኖቫ ኮኔክሽንስ፤ የዝግጅቱ ዳይሬክተር ዶክተር ጋሻው አብዛ እንደገለጹት፣ ይህ መርሃ ግብር የማኅበረሰብ ግንኙነትን ከማጠናከሩም በላይ እያንዳንዱ እርምጃ ለበጎ ዓላማ እንዲውል መንገድ ይከፍታል።

በተጨማሪም የዘንድሮው 8ኛው ግራንድ አፍሪካ ራን ልዩ ገጽታ በአሌክሳንድሪያ ቶዮታ ስፖንሰርነት የቀረበው የ2026 ሞዴል ቶዮታ ኮሮላ የመኪና ዕጣ ሽልማት ነው። ለሽልማቱ ብቁ ለመሆን ፈጣን ሯጭ መሆን አያስፈልግም፤ ለተመዘገቡ ተሳታፊዎች ሁሉ እኩል ዕድል የሚሰጥ ሲሆን አሸናፊው በመዝጊያ ፕሮግራሙ ላይ ይፋ ይደረጋል።

8ኛው ዓመታዊ ግራንድ አፍሪካ ራን ቅዳሜ፣ ጥቅምት 10 ቀን 2026፣ በአሌክሳንድሪያ፣ ቨርጂኒያ "አብሮነት መሻል ነው!" በሚል መርህ ይካሄዳል። Balageru TV

የኢትዮጵያ ከ20 ዓመት በታች አትሌቲክስ ልዑክ ቡድን ወደ አሜሪካ አመራ!በአሜሪካ ኦሪገን ግዛት፣ ዩጂን ከተማ ከሐምሌ 29 እስከ ነሐሴ 3/2018 ዓ.ም. በሚካሄደው 21ኛው የዓለም ከ20 ዓ...
02/08/2026

የኢትዮጵያ ከ20 ዓመት በታች አትሌቲክስ ልዑክ ቡድን ወደ አሜሪካ አመራ!

በአሜሪካ ኦሪገን ግዛት፣ ዩጂን ከተማ ከሐምሌ 29 እስከ ነሐሴ 3/2018 ዓ.ም. በሚካሄደው 21ኛው የዓለም ከ20 ዓመት በታች (World Athletics U20 Championships) አትሌቲክስ ሻምፒዮና የሚሳተፈው የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ልዑክ ቡድን ዛሬ ምሽት ወደ ውድድሩ ስፍራ አቅንቷል።

ሻምፒዮናው በዓለም አቀፍ የአትሌቲክስ ታሪካዊ መድረክ በሆነው በሄይዋርድ ፊልድ ስታዲየም የሚካሄድ ሲሆን፣ ከዓለም ዙሪያ የተውጣጡ ወጣት አትሌቶች ለዓለም ክብር በከፍተኛ ፉክክር ይሳተፋሉ።

በ2024 በፔሩ ሊማ በተካሄደው 20ኛው የዓለም ከ20 ዓመት በታች ሻምፒዮና ኢትዮጵያ 6 የወርቅ፣ 1 የብር እና 2 የነሐስ በድምሩ 9 ሜዳሊያዎችን በማሸነፍ በዓለም 2ኛ ደረጃ ማጠናቀቋ ይታወሳል።

በዘንድሮው ሻምፒዮና ኢትዮጵያ በ5000 ሜትር፣ 3000 ሜትር፣ 1500 ሜትር፣ 800 ሜትር (በሁለቱም ፆታዎች)፣ 3000 ሜትር መሰናክል (በሴቶች)፣ 400 ሜትር (በሴቶች) እንዲሁም በርምጃ ውድድር (በሁለቱም ፆታዎች) በመሳተፍ የተሻለ ውጤት ለማስመዝገብ በተጠናከረ ዝግጅት ቀርባለች።

የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን ፕሬዚዳንት ኮማንደር አትሌት ስለሺ ስህን፣ የፌዴሬሽኑ ጽሕፈት ቤት ኃላፊ ዶክተር አመንሲሳ ከበደ እና የፌዴሬሽኑ የስልጠና፣ ጥናትና ምርምር ዳይሬክተር አቶ አሰፋ በቀለ ቦሌ ዓለም አቀፍ አየር ማረፊያ በመገኘት ልዑክ የቡድኑን አሸኛኘት አድርገዋል።

የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን Balageru TV

''ስዊድን የጠፉት የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድንን የወከሉ አይደሉም'' ፌዴሬሽኑ በዓመታዊው የጎቲያ ካፕ ውድድር ላይ ለመካፈል ወደ ስዊድን ያመሩ ታዳጊዎች እና የቡድን አባላት በስዊድን መጥፋታቸው...
29/07/2026

''ስዊድን የጠፉት የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድንን የወከሉ አይደሉም'' ፌዴሬሽኑ

በዓመታዊው የጎቲያ ካፕ ውድድር ላይ ለመካፈል ወደ ስዊድን ያመሩ ታዳጊዎች እና የቡድን አባላት በስዊድን መጥፋታቸውን የስዊድን ፖሊስ ይፋ ካደረገ ጀምሮ በርካታ መገናኛ ብዙሀን ጉዳዩን እየዘገቡት ነው።

በጉዳዩ ዙርያ ማብራርያ የተጠየቀው ኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን የቡድኑ አባላት መጥፋት ያሳዘነው መሆኑን ገልፆ ቡድኖች በራሳቸው ጥረት በሚያገኙት እድል ወደ ውድድሩ የሚያመሩ እንጂ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድንን የወከሉ አለመሆኑን ገልጿል።

በአንዳድ አካላት የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን አባላት እንደሆኑ እየተገለጸበት ያለው መንገድ ትክክል አለመሆኑን እናሳውቃለን ብሏል።

በስዊድን ጎቲያ ካፕ ባልተለመደ መልኩ ሙሉ ቡድን አባላት 20 ተሳታፊዎች መጥፋታቸው ተረጋግጧል። የስዊድኑ ሎካል ኒውስ አዘጋጆቹን አናግሮ እንደዘገበው :- እንደዚህ አይነት የቁጥር ብዛት ከአንድ ቡድን መጥፋት ያለተለመደ እና አስደንጋጭ እንደሆነ ፅፏል። Balageru TV

ግብፆች ደገሙት ?  😮🇪🇬 ግብፆች በዘንድሮ አለም ዋንጫ ማሊያቸው ላይ 7 ኮከብ አርማ አድርገው ሊገቡ ሲሉ በፊፋ ውሳኔ ኮከቡን አጥፍተው እንዲጫወቱ ማድረጉ ይታወሳል። ኮከቦቹ  አለም ዋንጫ ...
28/07/2026

ግብፆች ደገሙት ? 😮🇪🇬

ግብፆች በዘንድሮ አለም ዋንጫ ማሊያቸው ላይ 7 ኮከብ አርማ አድርገው ሊገቡ ሲሉ በፊፋ ውሳኔ ኮከቡን አጥፍተው እንዲጫወቱ ማድረጉ ይታወሳል።

ኮከቦቹ አለም ዋንጫ ያሸነፈ ብሄራዊ ቡድን ባሸነፈው ቁጥር መጠን የሚያደርገው ቢሆንም ግብፆች 7 ጊዜ አፍሪካ ዋንጫ ያሸነፉበትን አድርገው ሊገቡ ሲል እንዲቀይሩ ተደርገዋል።

በተመሳሳይ የግብፅ ሴቶች ብሔራዊ ቡድን ወደ ሞሮኮ ለአፍሪካ ዋንጫ ሲጎዙ የወንዶች ቡድን ያሸነፋቸውን ሰባት የአፍሪካ ዋንጫ ኮከቦች በደረት ላይ ማድረጋቸው አነጋጋሪ ሀኗል።

በጉዳዩ ሁለት ተቃራኒ አመለካከቶች እየተንፀባረቁ ነው ። ኮከቦቹ የአንድን የተወሰነ ጾታ ቡድን ሳይሆን አጠቃላይ የግብፅ እግር ኳስ የጋራ ታሪክ እና ብሔራዊ ኩራት የሚወክሉ በመሆናቸው ሴቶቹም ይህንን ታሪክ የመጋራት መብት አላቸው የሚል አቋም አለ።

በሌላ በኩል ስኬቶቹ በሜዳ ላይ ልፋት የተገኙ በመሆናቸው እያንዳንዱ ቡድን የራሱን ኮከብ ማግኘት እንዳለበት እና የወንዶችን ስኬት የሆነውን መልበስ የሴቶቹ ቡድን ማንነት በወንዶቹ ጥላ ስር እንዲሸሸግ ያደርገዋል የሚሉ ትችቶች እየቀረቡ ነው።

ማንኛውም የአፍሪካ ሀገር የካፍ ዋና ውድድር የሆነውን የአፍሪካ ዋንጫን ሲያሸንፍ ያገኘውን የዋንጫ ብዛት የሚወክል ኮከብ በማሊያው ላይ የማድረግ መብት እንዳለው የካፍ ህግ ይፈቅዳል ።

ካፍ በሚያዘጋጀው ውድድር ስር ስለሆነ ኮከቡ ማድረጋቸውን ህጉ ቢፈቅድም ፤የተነሱት የተለያዩ አመለካከቶች ስፖርት ቤተሰቡን ለ2 ከፍለውታል .። እርስዎ ምን ይላሉ .?

የኢትዮጵያ ሴቶች ብሄራዊ ቡድን የወንዶች ቡድን ያሳኩትን አፍሪካ ዋንጫ 1 ኮከብ አድርገው መጫወት ቢችሉስ ምን ያስባሉ ? Balageru TV

ሴናፍ ዋቁማ !የኢትዮጵያ ብሄራዊ ቡድን አጥቂ ሴናፍ ዋቁማን የታንዛኒያው ሲምባ ኩዊንስ  እግር ኳስ ክለብ ማስፈረሙን  ይፋ አድርጓል።ከጥሩነሽ ዲባባ ስፖርት አካዳሚ ከወጣች በኋላ በአዳማ ከተ...
27/07/2026

ሴናፍ ዋቁማ !

የኢትዮጵያ ብሄራዊ ቡድን አጥቂ ሴናፍ ዋቁማን የታንዛኒያው ሲምባ ኩዊንስ እግር ኳስ ክለብ ማስፈረሙን ይፋ አድርጓል።

ከጥሩነሽ ዲባባ ስፖርት አካዳሚ ከወጣች በኋላ በአዳማ ከተማ፣ በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ እና በመቻል እግር ኳስ ክለቦች በከፍተኛ ብቃት ተጫውታለች።

በጥቅምት ወር ለአሜሪካው ዲሲ ዩናይትድ የሙከራ ዕድል አግኝታ ወደ አሜሪካ አምርታ ነበር። በመጨረሻ በታንዛኒያ ፕሪምየር ሊግ ለሲምባ ኪዊንስ ለ1 አመት ለመጫወት ፈርማለች። Balageru TV

የግል ሀሳብ...  በኢንስትራክተር ሰላም ዘርዓይ...የተጫዋቾች የዝውውር ዋጋ መጨመር በራሱ ችግር አይደለም፤ ችግሩ ዋጋው ከተጫዋቹ እውነተኛ ብቃት፣ ከክለቡ አቅም እና ከሊጉ እድገት ጋር ሲለ...
25/07/2026

የግል ሀሳብ... በኢንስትራክተር ሰላም ዘርዓይ...

የተጫዋቾች የዝውውር ዋጋ መጨመር በራሱ ችግር አይደለም፤ ችግሩ ዋጋው ከተጫዋቹ እውነተኛ ብቃት፣ ከክለቡ አቅም እና ከሊጉ እድገት ጋር ሲለያይ ነው። በኢትዮጵያ ዛሬ የምናየው ሁኔታ ይህንኑ ያሳያል፤ የተጫዋቾች ዋጋ ከዓመት ወደ ዓመት እየጨመረ ሲሄድ፣ የሊጉ ጥራት፣ የተጫዋቾች ግለሰባዊ ብቃት እና የአለም አቀፍ ተወዳዳሪነታችን ግን በተመሳሳይ ፍጥነት ሲያድግ አይታይም።

የክለቦች ውድድር በዋጋ ብቻ ሲመራ የሚጎዳው በመጨረሻ ክለቡን ራሱን ነው። ዛሬ ተጫዋች ለማስፈረም የሚወጣ ብዙ ገንዘብ ነገ ለወጣት ልማት፣ ለአካዳሚ፣ ለአሰልጣኞች እድገት፣ ለስፖርት ሳይንስ፣ ለህክምና፣ ለመረጃ ትንተና እና ለመሠረተ ልማት መዋል የሚገባውን በጀት ሊያሳጣ ይችላል።

ከዚህ በላይ የሚያሳስበው ጉዳይ ግን የክለቦቻችን መሠረታዊ መዋቅር ነው። አሁንም የራሳቸው የልምምድ ሜዳ የሌላቸው፣ የተሟላ የአስተዳደር ቢሮ የሌላቸው፣ የወጣት አካዳሚ በሚገባ ያልገነቡ፣ የስፖርት ሳይንስ እና የመረጃ ትንተና ስርዓት ያልፈጠሩ በርካታ ክለቦች አሉ። በተመሳሳይ ጊዜ የሊጉ የሽልማት ገንዘብም ከክለቦች ወጪ ጋር ሲነፃፀር በቂ አይደለም።

ይህን ስንናገር የተጫዋቾች ዋጋ መጨመር አይገባቸውም ወይም ጥሩ ክፍያ ማግኘት የለባቸውም ማለት አይደለም። ተጫዋቾች በሙያቸው ተገቢውን ዋጋ ማግኘታቸው ተፈጥሯዊ ነው። የሚነሳው ጥያቄ ግን ይህ ወጪ ከክለቡ አጠቃላይ የእድገት እቅድ ጋር የተመጣጠነ ነው ወይ? የሚለው ነው።

መፍትሄው ምንድን ነው?

የተጫዋቾች ዋጋን በህግ ወይም በትዕዛዝ መቆጣጠር አስቸጋሪ ነው። ግን ክለቦች የክፍያ ውድድሩን ከማባባስ ወጥተው ዘላቂ ስኬት የሚያመጣ መንገድ መምረጥ ይችላሉ።

1. ግልጽ የጨዋታ ፍልስፍና (Game Model) መገንባት

እያንዳንዱ ክለብ እንዴት መጫወት እንደሚፈልግ ግልጽ ማንነት ሊኖረው ይገባል። ተጫዋቾች መመልመል ያለባቸው በዋጋቸው ሳይሆን ከጌም ሞዴሉ ጋር በሚጣጣሙ ባህሪያት መሰረት ነው።

2. በኢንፍራስትራክቸር ላይ ቅድሚያ መስጠት

የልምምድ ሜዳ፣ የአካዳሚ ማዕከል፣ የህክምና ክፍል፣ የጂምናዚየም ቦታ፣ የቪዲዮ ትንተና ክፍል እና የተሟላ የክለብ ቢሮ የረጅም ጊዜ ንብረት ናቸው። ውድ የዝውውር ክፍያ በአንድ ወቅት ያልፋል፤ ጠንካራ ኢንፍራስትራክቸር ግን ለብዙ ዓመታት ውጤት ያመጣል።

3. በወጣት ተጫዋቾች ልማት ላይ ኢንቨስትመንት

አካዳሚ ወጪ ሳይሆን ኢንቨስትመንት ነው። ከራስ አካዳሚ የሚወጡ ተጫዋቾች የዝውውር ወጪን ይቀንሳሉ፣ የክለቡን ማንነት ያጠናክራሉ፣ ወደፊትም የዝውውር ገቢ ምንጭ ሊሆኑ ይችላሉ።

4. በመረጃ የተደገፈ ምልመላ (Data-driven Recruitment)

የተጫዋች ምርጫ በስም ወይም በግምት ሳይሆን በቴክኒካል፣ ታክቲካል፣ አካላዊ እና ስነ-ልቦናዊ መረጃዎች ላይ መመስረት አለበት።

5. ጠንካራ የፋይናንስ አስተዳደር

ክለቦች የተጫዋች ደመወዝና የዝውውር ወጪ ከአመታዊ ገቢያቸው ጋር የተመጣጠነ መሆኑን ሊያረጋግጡ ይገባል። በስሜት ሳይሆን በሚያስገኘው ገቢ ላይ እንዲሁም ባለን በጀት ላይ ተመርኩዞ ውሳኔ መወሰን ያስፈልጋል።

በመጨረሻ፣ ክለቦች ራሳቸውን አንድ ጥያቄ ሊጠይቁ ይገባል፦ "ዛሬ የከፈልነው ገንዘብ ከአምስት ዓመት በኋላ የተሻለ ክለብ ይፈጥራል፣ ወይስ የዛሬን የዝውውር ገበያ ብቻ ያሸንፋል?" የኢትዮጵያ እግር ኳስ የሚፈልገው የዝውውር ገበያን ማሸነፍ ሳይሆን፣ ዘላቂ እና ተወዳዳሪ ክለቦችን መገንባት ነው።

ዘላቂ ስኬት የሚመጣው በአንድ ወቅት ውድ ተጫዋቾችን በማሰባሰብ ሳይሆን በጠንካራ የክለብ መዋቅር ነው። ጠንካራ ክለብ ማለት ግልጽ ራዕይ ያለው፣ የራሱ መሠረተ ልማት ያለው፣ የወጣት ልማትን የሚያስቀድም፣ በመረጃ ላይ የተመሠረተ ምልመላ የሚያደርግ፣ ፋይናንሱን በስርዓት የሚያስተዳድር እና ለረጅም ጊዜ የሚያስብ ክለብ ነው።

ስለዚህ የኢትዮጵያ እግር ኳስ የሚያስፈልገው የተጫዋቾችን ዋጋ ማሳደግ ሳይሆን የተጫዋቾችን ብቃት ከክለቦች መዋቅራዊ እድገት ጋር በአንድነት ማሳደግ ነው። ብቃት ሲጨምር ዋጋው በራሱ ይጨምራል፤ ጠንካራ ክለብ ሲገነባ ደግሞ ያ እድገት ዘላቂ ይሆናል።

6. የአሰልጣኞች ቅጥር

የኢትዮጵያ ክለቦች ሊያስቡበት የሚገባው ሌላ ጉዳይ የቡድን ቀጣይነት (Continuity) ነው። ብዙ ጊዜ ክለቦች ሚሊዮኖችን አውጥተው ተጫዋቾችን ያስፈርማሉ፤ ከአንድ ወይም ከሁለት ዓመት በኋላ ግን ቡድኑ ይፈርሳል፣ ተጫዋቾቹ ወደ ገበያ ይመለሳሉ፣ ክለቡም እንደገና ከዜሮ ይጀምራል። ይህ ዑደት በየዓመቱ ሲደጋገም ክለቡ እውነተኛ እድገት ማሳየት አይችልም።
ከዚህ ጋር ተያይዞ የአሰልጣኞች ቅጥርም በረጅም ጊዜ እቅድ ላይ ሳይሆን በአፋጣኝ ውጤት ላይ ያተኮረ ነው። ብዙ ክለቦች አሰልጣኝ ሲቀጥሩ "ዋንጫውን ታመጣልናለህ" ብለው ይጀምራሉ፤ ነገር ግን "ጠንካራ ቡድን ትገነባለህ፣ የክለቡን የጨዋታ ማንነት ታስፈጽማለህ፣ ወጣቶችን ታሳድጋለህ" የሚለው አላማ ብዙ ጊዜ ግምት ውስጥ አይገባም።

ከዚህም የባሰው፣ በአንዳንድ የአሰልጣኞች ውል ውስጥ "ሶስት ተከታታይ ጨዋታ ከተሸነፍክ ውሉ ይቋረጣል" የሚል አንቀጽ ይካተታል። እንዲህ ዓይነት የአጭር ጊዜ ግፊት አሰልጣኙን የረጅም ጊዜ ቡድን ከመገንባት ይልቅ የቀጣዩን ጨዋታ ብቻ እንዲያስብ ያደርገዋል።
በእግር ኳስ ግን ሶስት ተከታታይ ሽንፈት የወቅቱን ስኬት ወይም ውድቀት አይወስንም፤ በታሪክ ብዙ ቡድኖች አስቸጋሪ ወቅት አልፈው በመጨረሻ ዋንጫ አንስተዋል።

ስለዚህ ክለቦች የሚያወዳድሩትን ሰው ብቻ ሳይሆን የሚያስፈጽመውን ስርዓት መምረጥ አለባቸው። አሰልጣኞች በክለቡ የጨዋታ ፍልስፍና (Game Model) መሰረት መቀጠር አለባቸው፤ ከዚያም ያንን ፍልስፍና ለመተግበር በቂ ጊዜ፣ ድጋፍ እና መረጋጋት ሊሰጣቸው ይገባል።

በመጨረሻም፣ ዋንጫ የጠንካራ አደረጃጀት ውጤት ነው፤ የጠንካራ አደረጃጀት ምክንያት አይደለም። ውጤት ዘላቂ የሚሆነው ክለቡ ግልጽ ራዕይ፣ የጨዋታ ሞዴል፣ ጠንካራ ኢንፍራስትራክቸር፣ የወጣት ልማት፣ ቀጣይነት ያለው የአሰልጣኝ ፕሮጀክት እና ጠንካራ አስተዳደር ሲኖረው ነው። Balageru TV

Address

Lancha Infront Of Global Hotel Meaza Desalegn Building 14th Floor
Addis Ababa
1000

Opening Hours

Monday 02:30 - 11:30
Friday 02:30 - 01:45

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Balageru TV posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to Balageru TV:

Shortcuts

Share

Category