09/08/2026
ሁለተኛ ወርቅ ሜዳሊያ ለኢትዮጵያ ተመዝግቧል !
በዓለም ከ20 ዓመት በታች የአትሌቲክስ ሻምፒዮና ኦሪገን አሜሪካ በአራተኛ ቀን ውሎ ለኢትዮጵያ ሁለተኛ ወርቅ ሜዳሊያ ተገኝቷል።
የሴቶች 3000 ሜትር የፍፃሜ ውድድር ኢትዮጵያውያን አትሌቶች የወርቅ እና የብር ሜዳልያ አሸናፊ ሆነዋል፡፡
አትሌት ዮርዳኖስ ፅጋብ 8:43.65 ሰዓት በመግባት የወርቅ ሜዳልያ አሸናፊ ፣አትሌት ሽቶ ጉሚ በሁለተኛነት የብር ሜዳልያ አስመዝግባለች፡፡
የሴቶች 5000 ሜትር አሸናፊ ኡጋንዳዊቷ ቻሪቲ ቼሮፕ በ3ኛነት አጠናቃለች ። ኢትዮጵያ ሁለተኛ ወርቅ ማግኘቷን ተከትሎ ከአለም በደረጃ ሰንጠረዥ 3ኛ ተቀምጣለች። Balageru TV