Bunna Media and Communication

Bunna Media and Communication አውነተኛና ትክክለኛ መረጃ ማድረስ መሪሃችን ነው!!!

በአፋር ክልል በበራህሌ ወረዳ ከፍተኛ የሰደድ እሳት አደጋ ተከሰተ!​የአስቸኳይ ጊዜ ጥሪ!​በአፋር ክልል፣ በበራህሌ ወረዳ ስር በሚገኘው ሃለ ጉቢ ቀበሌ፤ ልዩ ስሙ በደት ጋራብ፣ አፍዓዶ ጓሎ ...
10/06/2026

በአፋር ክልል በበራህሌ ወረዳ ከፍተኛ የሰደድ እሳት አደጋ ተከሰተ!

​የአስቸኳይ ጊዜ ጥሪ!

​በአፋር ክልል፣ በበራህሌ ወረዳ ስር በሚገኘው ሃለ ጉቢ ቀበሌ፤ ልዩ ስሙ በደት ጋራብ፣ አፍዓዶ ጓሎ እና ኤሊ ጋራብ በሚባሉ አካባቢዎች ከፍተኛ የሆነ የሰደድ እሳት አደጋ ተከስቷል።

​የአካባቢው ነዋሪዎችና የአመራር አካላት እሳቱን በቁጥጥር ስር ለማዋል ሌት ተቀን እየታገሉ ቢሆንም፣ የሚከተሉት ተግዳሮቶች ሁኔታውን አስቸጋሪ አድርገውታል፦

​የመንገድና የትራንስፖርት ችግር፡ ወደ አካባቢው ለመድረስ አስቸጋሪ መሆኑ፣

​የውሃ አቅርቦት እጥረት፡ እሳቱን ለማጥፋት የሚያስችል በቂ የውሃ ግብአት አለመኖር፣

​የአካባቢው ተፈጥሮ፡ ስፍራው ጥቅጥቅ ባሉ ጫካዎችና ደኖች የተሸፈነ በመሆኑ እሳቱ በሰው ኃይል ብቻ መመከት አልቻለም።

​ይህ በቁጥጥር ስር ያልዋለው የሰደድ እሳት በአካባቢው በሚገኙ የተፈጥሮ ሀብቶች፣ በዱር አራዊትና በቤት እንስሳት ላይ እንዲሁም በአካባቢው ማኅበረሰብ ህልውና ላይ ከፍተኛ ስጋት ደቅኗል።

​ስለሆነም፣ የሚመለከታቸው የመንግስት አካላት፣ የልማት አጋሮች እና የድርጅት መዋቅሮች በሙሉ ለአደጋው ልዩ ትኩረት በመስጠት ፈጣን ድጋፍ እንዲያደርጉ ጥሪ እናቀርባለን።

​የጉዳቱን መጠን ለመቀነስ የአካባቢውን ማህበረሰብ ድምጽ እናሰማ! ይህንን መረጃ ለሚመለከተው አካል እንዲደርስ ሼር በማድረግ ይተባበሩ።

​ #የሰደድእሳት #አፋር #በራህሌ

የካፋ ዞን የማህበረሰብ አቀፍ ጤና መድህን አፈጻጸም ተጠናክሮ ቀጥሏል!​የካፋ ዞን የማህበረሰብ አቀፍ ጤና መድህን አባላት የፋይዳ መታወቂያ ትስስር እና የጤና ተቋማት የቅድመ ቁርጥ ክፍያ አፈ...
10/06/2026

የካፋ ዞን የማህበረሰብ አቀፍ ጤና መድህን አፈጻጸም ተጠናክሮ ቀጥሏል!

​የካፋ ዞን የማህበረሰብ አቀፍ ጤና መድህን አባላት የፋይዳ መታወቂያ ትስስር እና የጤና ተቋማት የቅድመ ቁርጥ ክፍያ አፈጻጸም ግምገማና የንቅናቄ መድረክ እየተካሄደ ነው።

​የዞኑ ዋና አስተዳዳሪ አቶ እንዳሻው ከበደ በዚሁ ወቅት እንደተናገሩት፤ የማህበረሰብ አቀፍ ጤና መድህን የጤና አገልግሎትን በማቀላጠፍ ረገድ ከፍተኛ አስተዋጽኦ አበርክቷል። በተለይም በጤና ተቋማት ይስተዋል የነበረውን የመድኃኒት አቅርቦት ችግር በመፍታት ረገድ የመድህኑ ሚና ጉልህ መሆኑን አጽንኦት ሰጥተዋል።

​የጤና መምሪያ ኃላፊ አቶ አክሊሉ አሰፋ በበኩላቸው፤ በአሁኑ ወቅት የጤና መድህን አባላት ቁጥር 164,125 መድረሱንና ከ175 ሚሊዮን ብር በላይ መሰብሰቡን ገልጸዋል።

​የጤና መድህን አባላትን ከፋይዳ መታወቂያ ጋር በማስተሳሰር የአገልግሎት አድማሱን ለማስፋፋት እና የህዝቡን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ በትኩረት እየተሰራ ይገኛል።

​ #ጤና #የጤናመድህን #ካፋ #ኢትዮጵያ #ጤናአገልግሎት #ፋይዳ #ልማት

የቦንጋ ዶሮ እርባታ ማዕከል የሌማት ትሩፋት ንቅናቄን በላቀ አቅም እያገዘ ይገኛል! 🥚🐔​የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ምክትል ርዕሰ መስተዳድርና የግብርና ቢሮ ኃላፊ አቶ ማስረሻ በ...
10/06/2026

የቦንጋ ዶሮ እርባታ ማዕከል የሌማት ትሩፋት ንቅናቄን በላቀ አቅም እያገዘ ይገኛል! 🥚🐔

​የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ምክትል ርዕሰ መስተዳድርና የግብርና ቢሮ ኃላፊ አቶ ማስረሻ በላቸው እንደገለጹት፤ የቦንጋ ዶሮ እርባታ ማዕከል የክልሉን የሌማት ትሩፋት ግቦች ለማሳካት ቁልፍ ሚና እየተጫወተ ይገኛል።

​ማዕከሉ አሁን ላይ ካለፈው ውድቀት ወጥቶ፣ በቴክኖሎጂ ታግዞ ለክልሉ የተሻሻሉ የዶሮ ዝርያዎችን (እንደ "ቴትራ H" ያሉ) በማቅረብ የማህበረሰቡን የስጋና የእንቁላል ፍላጎት በማሟላት ላይ ነው።

​በማዕከሉ የተከናወኑ ዋና ዋና ስራዎች፡

✅ እስከ 78 ሺህ ጫጩት ማቀፍ የሚችል ዘመናዊ ሃቸር ማሽን ተገጥሟል።

✅ የወላጅ ዶሮዎች ቁጥር ከ4-5 ሺህ ወደ 10 ሺህ ከፍ ብሏል።

✅ የቴክኖሎጂና የምርት አቅምን ለማሳደግ የ90 ሚሊዮን ብር እና የ12 ሚሊዮን ብር ድጋፎች ተደርገዋል።

✅ በቴፒ፣ ሚዛንና ታርጫ ሳተላይት ማዕከላት የማስፋፊያ ስራዎች እየተከናወኑ ነው።

​ክልላችንን የሌማት ትሩፋት ምርቶች ማዕከል ለማድረግ እየተደረገ ያለው ጥረት ተጠናክሮ ይቀጥላል!

​ #የሌማትትሩፋት #የቦንጋዶሮእርባታ #የደቡብምዕራብኢትዮጵያ #ግብርና #ልማት

በ2019 በጀት ዓመት የገቢ አሰባሰብ መሠረቶችን በማስፋት የህዝቡን የልማት ጥያቄ ምላሽ የመስጠት ተግባር ተጠናክሮ እንደሚቀጥል የቢሮ ሀላፊ ወይዘሮ  ህይወት አሰግድ ገለፁ።​የደቡብ ምዕራብ ...
10/06/2026

በ2019 በጀት ዓመት የገቢ አሰባሰብ መሠረቶችን በማስፋት የህዝቡን የልማት ጥያቄ ምላሽ የመስጠት ተግባር ተጠናክሮ እንደሚቀጥል የቢሮ ሀላፊ ወይዘሮ ህይወት አሰግድ ገለፁ።

​የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልላዊ መንግስት የገቢ አሰባሰብ መሠረቶችን ይበልጥ በማስፋትና ፍትሃዊ አሰራርን በመዘርጋት፣ የህዝቡን የልማትና የመልካም አስተዳደር ጥያቄዎች በየደረጃው ምላሽ ለመስጠት በቁርጠኝነት እየሰራ ይገኛል።

​የክልሉ ገቢዎች ቢሮ ከፋይናንስ እና ከፕላንና ልማት ቢሮ አመራሮች ጋር በመሆን፣ በ2019 በጀት ዓመት የገቢ አሰባሰብ ዕቅድ ዙሪያ የምክክር መድረክ ማካሄድ ጀምሯል።

​የቢሮው ኃላፊ ወ/ሮ ህይወት አሰግድ እንደገለጹት፤ በዘንድሮው በጀት ዓመት በፈቃደኝነት ላይ የተመሰረተ የግብር የመክፈል ባህልን በማዳበርና ዘመናዊ የገቢ አሰባሰብ ስርዓትን በመተግበር፣ የክልሉን የውስጥ አቅም ለማሳደግ ልዩ ትኩረት ይሰጣል።

​ይህ ጥረት ክልሉ የልማት ፕሮጀክቶቹን በራሱ አቅም ለመደገፍ የሚያደርገውን ጉዞ ስኬታማ ለማድረግ ትልቅ ሚና ይኖረዋል።

​ #ደቡብምዕራብኢትዮጵያ #ገቢዎችቢሮ #የልማትጉዞ #ግብር #የኢትዮጵያልማት

በምዕራብ ኦሞ ዞን፣ መኒት ጎልዲያ ወረዳ የተገኘ ስኬት፡ የተራቆቱ መሬቶች በልማት እየታደሱ ነው! 🌱🌾​በምዕራብ ኦሞ ዞን፣ መኒት ጎልዲያ ወረዳ አርሶ አደሮች በአፈር እና ውሃ ጥበቃ ስራዎች ...
10/06/2026

በምዕራብ ኦሞ ዞን፣ መኒት ጎልዲያ ወረዳ የተገኘ ስኬት፡ የተራቆቱ መሬቶች በልማት እየታደሱ ነው! 🌱🌾

​በምዕራብ ኦሞ ዞን፣ መኒት ጎልዲያ ወረዳ አርሶ አደሮች በአፈር እና ውሃ ጥበቃ ስራዎች ላይ ያላቸው ተሳትፎ እየጨመረ መምጣቱ ርዕሰ መስተዳድር ዶክተር ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ በግል ማህበራዊ ሚዲያቸው ባስተላለፉት መልዕክት አስታውቀዋል ።

​በኢትዮጵያ የጋራ መሬት አያያዝ (GLI) ፕሮግራም ማዕቀፍ እየተከናወነ ያለው ይህ የተቀናጀ የአፈር እና ውሃ ጥበቃ ስራ፡

✅ ለረጅም ጊዜ የተራቆቱ መሬቶችን በፍጥነት ወደ ቀድሞ ምርታማነታቸው እንዲመለሱ አግዟል ነው ያሉት።

✅ የአፈር መሸርሸርን በመከላከል የሰብል ምርታማነት እንዲሻሻል መሰረት ጥሏል።

✅ የአርሶ አደሩን ተሳትፎ በማሳደግ የዘላቂ ልማት ተምሳሌት ሆኗል።

​የአካባቢውን የተፈጥሮ ሃብት በመንከባከብ ምርታቸውን እያሳደጉ የሚገኙትን የመኒት ጎልዲያ ወረዳ አርሶ አደሮች ጥረት እናደንቃለን!ስሉም ማስታወቃቸውን ቡና ሚዲያና ኮሚዩኒኬሽን ዘግቧል።

​ #የአፈርናውሃጥበቃ #ምዕራብኦሞ #መኒትጎልዲያ #ግብርና

የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ክልል ለዘመናዊ የፈተና አስተዳደር ሥርዓት ዝግጅቱን አጠናቀቀ! 📝✅​በቦንጋ ከተማ በ"የዘመነ ፈተና አስተዳደር ስርዓት፤ ለላቀ የትምህርት ጥራት!" መሪ ቃል የ2018...
10/06/2026

የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ክልል ለዘመናዊ የፈተና አስተዳደር ሥርዓት ዝግጅቱን አጠናቀቀ! 📝✅

​በቦንጋ ከተማ በ"የዘመነ ፈተና አስተዳደር ስርዓት፤ ለላቀ የትምህርት ጥራት!" መሪ ቃል የ2018 ዓ.ም ሀገራዊና ክልላዊ ፈተና አስተዳደር ምክክር መድረክ እየተካሄደ ነው።

​የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ (ዶ/ር) በተገኙበት በተካሄደው በዚህ መድረክ፡-

✅ የፈተና ምዘናና አስተዳደር ሥርዓትን ማዘመን ለትምህርት ጥራት ቁልፍ መሆኑ ተመላክቷል።

✅ በዘንድሮው ዓመት ከ89 ሺህ በላይ የ6ኛ እና 8ኛ ክፍል ተማሪዎችን በብቃት ለማስፈተን ቅድመ ዝግጅት መጠናቀቁ ተገልጿል።

✅ ፈተናዎችን ከኩረጃ የጸዳ እና ታማኝ እንዲሆኑ በትኩረት እየተሰራ እንደሚገኝ ተገልጿል።

​በመድረኩ ላይ የክልሉ፣ የዞን እና የከተማ አስተዳደር አመራሮች እንዲሁም የዩኒቨርሲቲ አመራሮች እና ባለድርሻ አካላት ተገኝተዋል።

​ #ትምህርት #ቦንጋ

የ2019 ረቂቅ በጀት ከ2.3 ትሪሊዮን ብር በላይ ሆኖ እንዲቀርብ የሚኒስትሮች ምክር ቤት ወሰነ  የሚኒስትሮች ምክር ቤት በዛሬው ዕለት ባካሄደው 56ኛ መደበኛ ስብሰባ በተለያዩ ጉዳዮች ላይ ...
10/06/2026

የ2019 ረቂቅ በጀት ከ2.3 ትሪሊዮን ብር በላይ ሆኖ እንዲቀርብ የሚኒስትሮች ምክር ቤት ወሰነ

የሚኒስትሮች ምክር ቤት በዛሬው ዕለት ባካሄደው 56ኛ መደበኛ ስብሰባ በተለያዩ ጉዳዮች ላይ ተወያይቶ ውሳኔ አሳልፏል።

ምክር ቤቱ የ2019 በጀት ዓመት የፌዴራል መንግሥት የበጀት ረቂቅ አዋጅ ላይ ተወያይቷል።

የ2019 የፌዴራል መንግሥት በጀት የዐሥር ዓመቱ መሪ የልማት ዕቅድ አካል የሆነው የ2019-2021 የልማት እና ኢንቨስትመንት ዕቅድ ላይ የተቀመጡ ግቦችን እና የመካከለኛ ዘመን (2019-2023) የማክሮ ኢኮኖሚ እና የፊሲካል ማዕቀፍን መሠረት በማድረግ፣ የ2018 በጀት ዓመት የፕሮግራም በጀት አፈጻጸም መነሻ በማድረግ፣ በቀጣይ ሊኖር የሚችለውን የማኅበራዊ እና የኢኮኖሚ ትራንስፎርሜሽን አቅጣጫዎች እና ዓላማዎች እንዲሁም በመንግሥት የተቀመጡ ግቦችን ለማሳካት የመንግሥትን የፋይናንስ አቅም እና አስፈጻሚ መሥሪያ ቤቶች ከተሰጣቸው ተልዕኮ እና ኃላፊነት አንጻር የሚያስፈልገውን ወጪ በመገምገም ተዘጋጅቶ ቀርቧል።

በዚሁ መሠረትም ለመደበኛ ወጪዎች፣ ለካፒታል ወጪዎች፣ ለክልል መንግሥታት ድጋፍ፣ ለዘላቂ የልማት ግቦች ማስፈጸሚያ ድጋፍ የሚውል 2 ትሪሊዮን 339 ቢሊዮን 268 ሚሊዮን 126 ሺህ 738 (ሁለት ትሪሊዮን፣ ሦስት መቶ ሠላሳ ዘጠኝ ቢሊዮን፣ ሁለት መቶ ስድሳ ስምንት ሚሊዮን፣ አንድ መቶ ሀያ ስድስት ሺህ፣ ሰባት መቶ ሰላሳ ስምንት) ብር በጀት ለምክር ቤቱ ቀርቧል።

ምክር ቤቱም በቀረበው የፌዴራል መንግሥት የ2019 ረቂቅ በጀት አዋጅ ላይ በሰፊው ከተወያየበት በኋላ ግብአቶችን በማከል ወደ ሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት እንዲተላለፍ በሙሉ ድምፅ መወሰኑን የጠቅላይ ሚኒስትር ጽ/ቤት አስታውቋል።

ዘገባው የኢቢሲ ነው፡፡

በኮንታ ዞን ገቢዎች መምሪያ የሰው ሀብት ልማትና ስምሪት ስልጠና እየተሰጠ ነው!​የክልሉን ገቢዎች አቅም ለማሳደግና የህዝቡን የልማት ጥያቄዎች በብቃት ለመመለስ እንዲቻል፣ በኮንታ ዞን ገቢዎች...
09/06/2026

በኮንታ ዞን ገቢዎች መምሪያ የሰው ሀብት ልማትና ስምሪት ስልጠና እየተሰጠ ነው!

​የክልሉን ገቢዎች አቅም ለማሳደግና የህዝቡን የልማት ጥያቄዎች በብቃት ለመመለስ እንዲቻል፣ በኮንታ ዞን ገቢዎች መምሪያ የሁለት ቀናት ስልጠና በአመያ ከተማ እየተካሄደ ይገኛል።

​ይህ ስልጠና ለዞኑ ገቢዎች መምሪያ ባለሙያዎች፣ እንዲሁም ለወረዳና ከተማ አስተዳደር የሰው ሀብት ባለሙያዎች የተዘጋጀ ሲሆን ዋና ዓላማውም፡-

​✅ የተዋጣለት የሰው ሀብት ስምሪትን በመፍጠር የገቢ አሰባሰብ አቅምን ማሳደግ፣

✅ በዘርፉ በስራ ሂደት የሚያጋጥሙ ክፍተቶችን መቅረፍ፣

✅ የሰራተኞች ዲሲፕሊን አጠባበቅ፣ የሰው ሀብት ሟሟላትና የአገልግሎት ማቋረጥ መመሪያዎችን በጋራ መገምገም ነው።

​የስልጠናውን አስፈላጊነት የገለጹት የክልሉ ገቢዎች ቢሮ የሰው ሀብት ልማት ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አቶ መስፍን ዳይኖ፤ ስልጠናው የተቋማትን አቅም በመገንባት የላቀ አገልግሎት ለመስጠት ወሳኝ ሚና እንዳለው አስገንዝበዋል።

​የሰው ሀብት አቅማችንን በማሳደግ የተሻለ ገቢ እንሰብስብ!

​ #አመያ

የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ቦንጋ ቅርንጫፍ ዘመናዊ ሕንፃ የመሠረተ ድንጋይ ተቀመጠ​የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ በቦንጋ ከተማ ለሚገነባው ዘመናዊ ሕንፃ የመሠረተ ድንጋይ የማስቀመጥ ሥነ-ሥርዓት በደቡብ...
09/06/2026

የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ቦንጋ ቅርንጫፍ ዘመናዊ ሕንፃ የመሠረተ ድንጋይ ተቀመጠ

​የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ በቦንጋ ከተማ ለሚገነባው ዘመናዊ ሕንፃ የመሠረተ ድንጋይ የማስቀመጥ ሥነ-ሥርዓት በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ርዕሰ መስተዳድር ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ(ዶ/ር) እና ሌሎች ከፍተኛ የመንግሥት የሥራ ኃላፊዎች በተገኙበት ተከናወነ።

​ስለ ፕሮጀክቱ ዋና ዋና ነጥቦች፡

​የሕንፃው ይዘት፡ ሁለት ቤዝመንት (ምድር ቤት)፣ ሚዛኔን እና አስር ወለል ያለው።

​በጀት፡ ከ1.2 ቢሊዮን ብር በላይ።

​የግንባታ ጊዜ፡ በ900 ቀናት ውስጥ የሚጠናቀቅ።

​ኮንትራክተር፡ ዮሐንስ ኃይሌ ኮንስትራክሽን።

​በሥነ-ሥርዓቱ ላይ ንግግር ያደረጉት የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ(ዶ/ር)፣ የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ለኢኮኖሚ እንቅስቃሴ ያለው ሚና ወሳኝ መሆኑን ገልጸው፤ የካፋ ዞን ያለውን እምቅ አቅም በኢንቨስትመንት ለመቀየር የዚህ የፋይናንስ ተቋም መኖር ጉልህ ድርሻ እንደሚኖረው ተናግረዋል።

​የካፋ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ እንዳሻው ከበደ በበኩላቸው፣ ፕሮጀክቱ የከተማዋን ገጽታ ከመቀየሩ ባሻገር ለህብረተሰቡ የሚሰጠውን አገልግሎት ጥራት እንደሚያሳድግ ገልጸዋል። የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ጅማ ዲስትሪክት ዳይሬክተር አቶ ሳዲቅ አብዱም ፕሮጀክቱ የባንኩን ዘመናዊ አገልግሎት ለደንበኞች ለማድረስ የሚደረግ ጥረት አካል መሆኑን አስረድተዋል።

​ይህ ፕሮጀክት መጠናቀቁ ለቦንጋ ከተማ ሁለገብ ልማት እና ለባንኩ ደንበኞች የላቀ አገልግሎት አሰጣጥ ትልቅ እመርታ እንደሚሆን ታምኖበታል።

​ #ኢትዮጵያንግድባንክ #ቦንጋ #ልማት #ኢትዮጵያ

Address

Addis Ababa

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Bunna Media and Communication posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share