10/06/2026
በአፋር ክልል በበራህሌ ወረዳ ከፍተኛ የሰደድ እሳት አደጋ ተከሰተ!
የአስቸኳይ ጊዜ ጥሪ!
በአፋር ክልል፣ በበራህሌ ወረዳ ስር በሚገኘው ሃለ ጉቢ ቀበሌ፤ ልዩ ስሙ በደት ጋራብ፣ አፍዓዶ ጓሎ እና ኤሊ ጋራብ በሚባሉ አካባቢዎች ከፍተኛ የሆነ የሰደድ እሳት አደጋ ተከስቷል።
የአካባቢው ነዋሪዎችና የአመራር አካላት እሳቱን በቁጥጥር ስር ለማዋል ሌት ተቀን እየታገሉ ቢሆንም፣ የሚከተሉት ተግዳሮቶች ሁኔታውን አስቸጋሪ አድርገውታል፦
የመንገድና የትራንስፖርት ችግር፡ ወደ አካባቢው ለመድረስ አስቸጋሪ መሆኑ፣
የውሃ አቅርቦት እጥረት፡ እሳቱን ለማጥፋት የሚያስችል በቂ የውሃ ግብአት አለመኖር፣
የአካባቢው ተፈጥሮ፡ ስፍራው ጥቅጥቅ ባሉ ጫካዎችና ደኖች የተሸፈነ በመሆኑ እሳቱ በሰው ኃይል ብቻ መመከት አልቻለም።
ይህ በቁጥጥር ስር ያልዋለው የሰደድ እሳት በአካባቢው በሚገኙ የተፈጥሮ ሀብቶች፣ በዱር አራዊትና በቤት እንስሳት ላይ እንዲሁም በአካባቢው ማኅበረሰብ ህልውና ላይ ከፍተኛ ስጋት ደቅኗል።
ስለሆነም፣ የሚመለከታቸው የመንግስት አካላት፣ የልማት አጋሮች እና የድርጅት መዋቅሮች በሙሉ ለአደጋው ልዩ ትኩረት በመስጠት ፈጣን ድጋፍ እንዲያደርጉ ጥሪ እናቀርባለን።
የጉዳቱን መጠን ለመቀነስ የአካባቢውን ማህበረሰብ ድምጽ እናሰማ! ይህንን መረጃ ለሚመለከተው አካል እንዲደርስ ሼር በማድረግ ይተባበሩ።
#የሰደድእሳት #አፋር #በራህሌ