Bunna Media and Communication

Bunna Media and Communication Media for Unity

26/09/2025

እንኳን ለሸካ ብሄረሰብ ዘመን መለወጫ ማሽቃረ ባሮ በሰላም አደረሳችሁ እያለ የሸካ ዞን አስተዳደር መልካም ምኞቱን ገልጿል ።
በመስከረም 20 አይቀርም !!!

ቡና ሚዲያና ኮሚዩኒኬሽን

“የደምና ስጋ ተካፋይ የጎንጋ ቤተሰብ በሆነው ቦሮ ሺናሻ ወንድም/አህቶቼ ጋር ለመታደም ቤንሻንጉል ጉሙዝ አሶሳ ተገኝቻለሁ”፦ አቶ አልማው ዘውዴበደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል በምክትል...
26/09/2025

“የደምና ስጋ ተካፋይ የጎንጋ ቤተሰብ በሆነው ቦሮ ሺናሻ ወንድም/አህቶቼ ጋር ለመታደም ቤንሻንጉል ጉሙዝ አሶሳ ተገኝቻለሁ”፦ አቶ አልማው ዘውዴ

በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል በምክትል ርዕሰ-መስተዳድር ማዕረግ የማህበራዊ ክላስተር አስተባባሪና የትምህርት ቢሮ ኃላፊ አቶ አልማው ዘውዴ የሽናሻ ብሔር ዘመን መለወጫ በዓል “ጋሪ-ዎሮ”ን ለማክበር አሶሳ ገቡ።

“የወንድም ቦሮ ሺናሻ ብሔረሰብ ውብ ማንነትና ድልብ ማህበራዊ እሴት ነጸብራቅ የሆነው የዘመን መለወጫ “ጋሪ-ዎሮ” በዓል ነገ በድምቀት ይከበራል ፤ እንኳን አደረሰን አደረሳችሁ” ብለዋል።

“የደምና ስጋ ተካፋይ የጎንጋ ቤተሰብ በሆነው ቦሮ ሺናሻ ወንድም/አህቶቼ ጋር ለመታደም ቤንሻንጉል ጉሙዝ አሶሳ ተገኝቻለሁ” ሲሉ በማህበራዊ ትስስር ገፃቸው መልዕክት አስተላልፈዋል።

ጋሪ ዎሮ ቀናት ተቆጥረው ዓመት የሚለወጥበት በዓል ብቻ ሳይሆን፣ ልቦች በይቅርታ የሚታደሱበት፣ ቂምና በቀል በፍቅር የሚሸነፉበት ታላቅ የእርቅና የመተሳሰብ ኪዳን መሆኑን ገልጸዋል።

በዚህች የተቀደሰች ዕለት፣ ማህበረሰቡ ያለፈውን በይቅርታ ሸኝቶ መጪውን ዘመን በንጹሕ ልብና በአዲስ ተስፋ እንደሚቀበል አንስተዋል።

“የተጣላ የሚታረቅበት፣ የተራራቀ የሚቀራረብበት፣ የአብሮነት እሴቶቻችን ጎልተው የሚታዩበት ይህ በዓል ለሁላችንም ኢትዮጵያውያን ትልቅ ትምህርት የሚሰጥ ህያው ባህላችን ነው” ብለዋል አቶ አልማው።

ለመላው የጎንጋ ቤተሰቦች፣ የቦሮ ሺናሻ ህዝብና ለመላው ኢትዮጵያውያን በዓሉ የደስታ፣ የጤና እና የፍቅር እንዲሆን ተመኝተዋል።

የቦርሮ ሽናሻ ዘመን መለወጫ"ጋሪዎሮ"ን ከወንድም ሽናሻ ብሄር  ጋር አብሮ ለማክበር  ካፋና ሽካ  ብሄረሰብ ተወካዮች  አሶሳ ገብተዋል።ተወካዮቹ አሶሳ  አየር ማረፊያ ስደርሱ የቤንሻንጉል ጉሙ...
26/09/2025

የቦርሮ ሽናሻ ዘመን መለወጫ"ጋሪዎሮ"ን ከወንድም ሽናሻ ብሄር ጋር አብሮ ለማክበር ካፋና ሽካ ብሄረሰብ ተወካዮች አሶሳ ገብተዋል።

ተወካዮቹ አሶሳ አየር ማረፊያ ስደርሱ የቤንሻንጉል ጉሙዝ ዋና አፈጉባኤን ጨምሮ የክልሉ ከፍተኛ የስራ ሀላፊዎች አቀባበል አድርገውላቸዋል።

ወደ አሶሳ የተጓዘው ልዑክ የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ክልል በምክትል ርዕሰ መስተዳድር ማዕረግ የማህበራዊ ክላስተር አስተባባና የክልሉ ትምህርት ቢሮ ሀላፊ አቶ አልማው ዘውዴና በፌደራል ተቋም በሃላፊነት የሚሰሩት አቶ ክፍለ ገብረማሪያም የተመራ ነው።

ቡና ሚዲያና ኮሚዩኒኬሽን ኹኔቱን እየተከታተለ ለመላው አለም የሚያደርስ ይሆናል!!

ቡና ሚዲያና ኮሚዩኒኬሽን

26/09/2025

እንኳን ለቦሮ ሽናሻ ጋሪዎሮ በዓል በሰላም አደረሳችሁ!
ቡና ሚዲያና ኮሚዩኒኬሽን ከበዓሉ አዘጋጅ ኮሚቴ ጋር በመተባበር
#

የደመራና መስቀል በዓል ከኃይማኖታዊ ይዘቱ ባሻገር ኢትዮጵያውያን የጋራ መስተጋብርን የሚያድሱበት፣ አብሮነትንና አንድነትን የሚያጠናክሩበት በዓል ነው፦አቶ አበበ ማሞ‎የሸካ ዞን ዋና አስተዳዳሪ...
26/09/2025

የደመራና መስቀል በዓል ከኃይማኖታዊ ይዘቱ ባሻገር ኢትዮጵያውያን የጋራ መስተጋብርን የሚያድሱበት፣ አብሮነትንና አንድነትን የሚያጠናክሩበት በዓል ነው፦አቶ አበበ ማሞ

‎የሸካ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ አበበ ማሞ ለመላው የክርስትና እምነት ተከታዮች ለ2018 ዓ.ም የደመራና መስቀል በዓል የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት አስተላልፈዋል።

በመልዕክታቸውም የደመራና መስቀል በዓል ከኃይማኖታዊ ይዘቱ ባሻገር ኢትዮጵያውያን የጋራ መስተጋብርን የሚያድሱበት፣ አብሮነትንና አንድነትን የሚያጠናክሩበት በዓል መሆኑን ገልጸዋል።

መስቀል ሰውን ከአምላኩ ጋር ያገናኘ የሰላም ተምሳሌት በመሆኑ በዓሉን ስናከብርም ቂም በቀልን ትተን በይቅርታ ልብ መሆን እንዳለበት ዋና አስተዳዳሪው አሳስበዋል።

​ በዓሉን ስናከብር ለሀገራችን ሰላም ፣ አንድነት እና ልማት በጋራ መቆም አስፈላጊ መሆኑን እና የተቸገሩ ወገኖችን በመርዳት መከበር እንዳለበት ገልጸዋል።

​በመጨረሻም የመስቀል በዓል ለኢትዮጵያ ፍቅርን፣ ሰላምን እና ይቅርታን የሚያድል እንዲሆን አቶ አበበ መልካም ምኞታቸውን ገልጸዋል።

እንኳን ለሸካቾ ብሔረሰብ ዘመን መለወጫ"ማሽቃሬ ባሮ" በሠላም አደረሳችሁ!
26/09/2025

እንኳን ለሸካቾ ብሔረሰብ ዘመን መለወጫ"ማሽቃሬ ባሮ" በሠላም አደረሳችሁ!

በተፈጥሮ ሀብቷ የታደለችው የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ክልል አካል የሆነችውን ዳውሮ በቅርቡ ተገኝቼ እንድጎበኝ የዞኑ ዋና አስተዳዳሪ ጋብዘውኛል።ለማሽቃሮ ቦንጋ በሄድኩበት ክቡር ዋና አስተዳዳሪ...
26/09/2025

በተፈጥሮ ሀብቷ የታደለችው የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ክልል አካል የሆነችውን ዳውሮ በቅርቡ ተገኝቼ እንድጎበኝ የዞኑ ዋና አስተዳዳሪ ጋብዘውኛል።

ለማሽቃሮ ቦንጋ በሄድኩበት ክቡር ዋና አስተዳዳሪ ስለሰጡኝ ክብርና ፍቅር እጅግ አመሰግናለሁ ።

በቅርቡ እጅግ የሚወዳትን ዳውሮን እጎበኛታለሁ።
የዳውሮን ማህበረሰብ እምቅ ሀብቶችንና የተፈጥሮ ፀጋዎችን እንዲሁም የፍቅር ህዝብ መሆኑን በጉዞ ማስታወሻዬ አስቃኛችኋላሁ።

አማኑኤል ሀይሌ(ጋዜጠኛ)

25/09/2025

ትንሿ ኢትዮጵያ የፍቅር ከተማ ጅማን በጣም እወዳታለሁ!! በዓመት ብዙ ጊዜ እመላለስባታለሁ።

ያገኘኝ ሁሉ ወዳጀ ነው። በክብር ተቀብሎ ፍቅሩን ሰጥቶ ይሸኘኛል።
ይመቻችሁ ጅማዎች ።

ስለ ጅማ ከተማ በጉዞ ማስታወሻዬ በስፋት እመለሳለሁ።

ዛሬ ጅማ በነበረኝ ቆይታዬ የሚዲያችን ቤተሰብ ያለውን አድናቆት ገልፆልኛል። አመሰግናለሁ ።
አማኑኤል ሀይሌ(ጋዜጠኛ)

ጅማን የማውቃት ከልጅነቴ ጀምሮ ነው። ትንሿ ኢትዮጵያ ናት! ጅማ የበርካታ ከተሞች መገናኛ መስመር ናት።ብዙዎች ነግደው ያተርፉባታል።የተለያዩ ብሄር ብሄረሰቦች ተዋደውና ተከባብረው የሚኖሩባት ...
25/09/2025

ጅማን የማውቃት ከልጅነቴ ጀምሮ ነው።
ትንሿ ኢትዮጵያ ናት!
ጅማ የበርካታ ከተሞች መገናኛ መስመር ናት።
ብዙዎች ነግደው ያተርፉባታል።

የተለያዩ ብሄር ብሄረሰቦች ተዋደውና ተከባብረው የሚኖሩባት ድንቅ ህብረብሄራዊት ከተማ ነች ጅማ።
በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ክልል የነበረኝን ቆይታ አጠናቅቀ ወደ መኖሪያዬ አዲስ አበባ እየሄድኩ ከባልደረቦቼ ጋር ቆንጆ ምሳን በፍቅር ተመግበ ቆይታዬን ጅማ አድርገአለሁ።
አማኑኤል ሀይሌ(ጋዜጠኛ)
ቀናችሁ ያማረ ይሁን

ማሽቃሮ በድንቅ ትዕይንት ተጠናቋል። የዓመቱ ሰው ይበለን።ቡና ሚዲያና ኮሚዩኒኬሽን አረንጓዴ ምድር ደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያን ተፈጥሮ ከንፁህ አየር ጋር እያጣጣመ ጉዞ ወደ አዲስ  አበባ እያደረ...
25/09/2025

ማሽቃሮ በድንቅ ትዕይንት ተጠናቋል። የዓመቱ ሰው ይበለን።

ቡና ሚዲያና ኮሚዩኒኬሽን አረንጓዴ ምድር ደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያን ተፈጥሮ ከንፁህ አየር ጋር እያጣጣመ ጉዞ ወደ አዲስ አበባ እያደረግን ነው።

በፍቅርና በአክብሮት የተቀበላችሁኝ ውድ አብሮ አደጎቸና ወዳጅ ዘመዶቼ እንዲሁም ከክልል ጀምሮ ያላችሁ አመራሮች ስለተቀበላችሁኝ አመሰግናለሁ ።

አማኑኤል ሀይሌ(ጋዜጠኛ) እንደልማዴ አረንጓዴው የልምላሜ ተምሳሌት የሆነን ክልል በጉዞ ማስታወሻዬ ዘጋቢ ቅንብር ይዠላችሁ እመጣለሁ! ጠብቁኝ!

ለምለምቷ ክልል ደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ

የታክስ ማጭበርበርን ውጤታማ በሆነ መንገድ ለመዋጋት በተቋማት መካከል በተጠናከረ መልኩ መተባበር እና በቁርጠኝነት መንቀሳቀስ እንደሚገባ ተጠቆመየደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ገቢዎች ...
24/09/2025

የታክስ ማጭበርበርን ውጤታማ በሆነ መንገድ ለመዋጋት በተቋማት መካከል በተጠናከረ መልኩ መተባበር እና በቁርጠኝነት መንቀሳቀስ እንደሚገባ ተጠቆመ

የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ገቢዎች ቢሮ እና የኢፌዴሪ ገቢዎች ሚኒስቴር በጋራ በመሆን በታክስ ህግ ተገዢነት ዙሪያ ከዞን ገቢዎች መምሪያ ፣ከ6ቱም የዞን ማዕከል ከተማ አስተዳደር ገቢዎች ጽ/ቤት ኃላፊዎች እና ከባለድርሻ አካላት ጋር የምክክር መድረክ በቦንጋ ከተማ ተካሄደ።

የውይይት መድረኩ ዓላማ የግብር ማጭበርበር እና ስወራ ወንጀሎችን በትብብር በመግታት የውስጥ ገቢ አቅም እንዲጨምር ለማስቻል ፍትሐዊ የገቢ አሰባሰብ ሥርዓት ለመዘርጋት ያለመ እንደሆነም ተጠቅሷል።

በመድረኩም የክልሉ የ2017 ዓ.ም በህግ ተገዥነት ዙሪያ የተሰሩ አፈጻጸም ሪፖርት እና የ2018 በጀት ዓመት የታክስ ህግ ተገዢነት ጠቋሚ ዕቅድ ቀርበው ማብራሪያ እና ውይይት የተደረገባቸው ሲሆን የታክስ ማጭበርበርን ለመዋጋት የባለድርሻ አካላት ሚና ዙሪያም ገለጻ ተደርጓል።

የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ገቢዎች ቢሮ ኃላፊ ወ/ሮ ህይወት አሰግድ፣የክልሉ የገቢ አሰባሰብ አቅም ከጊዜ ወደ ጊዜ እየተሻሻለ መምጣቱን በመግለፅ ይህ መድረክ የገቢ አሰባሰብ ሂደቱን በተቀመጠው የአሰራር ስርዓት ለማከናወን የሚያስችል ግብዓት የተገኘበት እንደሆነም ጠቁመዋል።

የታክስ ማጭበርበር እና የግብር ስወራን ውጤታማ በሆነ መንገድ ለመዋጋት በተቋማት መካከል በተጠናከረ መልኩ መተባበር እና በቁርጠኝነት መንቀሳቀስ እንደሚገባም አክለዋል።

የኢፌዴሪ ገቢዎች ሚኒስቴር የታክስ ማጭበርበር ምርመራ ጽ/ቤት ሀላፊ አቶ ሲሳይ ገዙ፣ በታክስ ህግ ተገዥነት ዙሪያ የክህሎት ስልጠና በሰጡበት ወቅት እንዳብራሩት፣ታክስ በተገቢው መንገድ መሰብሰብ የኢኮኖሚ ሉዓላዊነት ለማረጋገጥ ፣ብሔራዊ ዕቅድ ለማጠናከር፣እንዲሁም ጠንካራ እና ቅቡልነት ያለው ሀገረ መንግስት ለመገንባት ወሳኝ ነው ብለዋል።

የታክስ ማጭበርበርን መዋጋት ከጠንካራ ህጎች የበለጠ ጠንካራ አጋርነትን የሚጠይቅ ስለሆነ ውጤታማ ትብብር እና ቅንጅት መፍጠር እንደሚገባም አቶ ሲሳይ ገዙ አስረድተዋል።

በ2018 የበጀት ዓመት የታክስ ህግ ለማስከበር የክልሉ ገቢዎች ቢሮ ከክልሉ ፖሊስ ኮሚሽን እና ፍትህ ቢሮ ጋር በቅርበት እንደሚሰራም ተመላክቷል።

በመጨረሻም የግብር ስወራንና የገቢ ማጭበርበርን በትብብር ለመከላከል በሚቻልባቸው ነጥቦች ላይ ውይይት የተደረገ ሲሆን ከቤቱ ለተነሱ ጥያቄዎች እና አስተያየቶችም ከመድረኩ ምላሽ ተሰጥቶባቸዋል

24/09/2025

የካፋ ብሄር ማሽቃሮ ትልቅ እሴት ያለው የዘመን መለወጫ ነው።
ክቡር ርዕሰ መስተዳድር ዶ/ር ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ ዋማ ድጎና ሻግቶቴ በማለት የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት አስተላልፈዋል ።

በስፋት እንመለሳለን ጠብቁን!
ቀጥታ ከቦንጌ ሻንባቶ
በስፈ

ቡና ሚዲያና ኮሚዩኒኬሽን

Address

Addis Ababa

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Bunna Media and Communication posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share