Bunna Media and Communication

Bunna Media and Communication Media for Unity

የተመረዘ ምግብ በልተዉ ከታመሙ 8 የአንድ ቤተሰብ አባላት  ዉስጥ የ7ቱ  ህይወት አለፈምግቡ በማንና እንዴት ተመረዘ?ሆሳዕና ህዳር 12 ቀን 2018 (ማ.ኢ.ፖ.ኮ) በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል...
21/11/2025

የተመረዘ ምግብ በልተዉ ከታመሙ 8 የአንድ ቤተሰብ አባላት ዉስጥ የ7ቱ ህይወት አለፈ

ምግቡ በማንና እንዴት ተመረዘ?

ሆሳዕና ህዳር 12 ቀን 2018 (ማ.ኢ.ፖ.ኮ) በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ምስራቅ ጉራጌ ዞን መስቃን ወረዳ በአብሮነት እራት ተመግበዉ በጠና ከታመሙ ስምንት የአንድ ቤተሰብ አባላት ዉስጥ አባወራዉ ከስድስት ልጆቹ ጋር ሰባት የአንድ ቤተሰብ አባላት ህይወታቸዉ ማለፉን ፖሊስ ገልጿል።

የክልሉ ፖሊስ የወንጀል መረጃ ኢንተለጀንስ ዳይሬክቶሬት ተወካይ ምክትል ኮማንደር ያለዉ ተመስገን እንደገለፁት በወረዳዉ መሰረተ ወገራም ቀበሌ ዳሾ ቆቶ ተብሎ በሚጠራዉ መንደር ህዳር 6 ቀን 2018 ዓ.ም ምሽት 1:00 ሰዓት ስምንቱ የቤተሰብ አባላት አብረዉ እራት ከተመገቡ በኋላ በድንገት መታመማቸዉ ተናግረዋል።

በአብሮነት እራት እንደተመገቡ ብዙም ሳይቆዩ ከፍተኛ ለሆነ ህመም መዳረጋቸዉን መረጃ የደረሳቸዉ የአካባቢዉ ነዋሪዎች የተጎጂዎችን ህይወት ለማትረፍ ተረባርበዉ ወደ ሆስፒታል ማድረሳቸዉ ነዉ የተነገረዉ።

ቢሆንም ከተጎዱ የቤተሰቡ አባላት የ5 ዓመቱ መንግስቱ ኃይሌ ፣የ7 ዓመቱ መክብነ ኃይሌ እና የ17 ዓመቱ ተክሉ ኃይሌ የተባሉት ሶስቱ ወንድማማቾች በዕለቱ ሆስፒታል እንደደረሱ ህይወታቸዉ ማለፉን ነዉ የተገለፀዉ።

የተቀሩ ተጎጂዎችን ህይወት በህክምና ለማትረፍ ሀኪሞች ያልተቋረጠ ጥረት ቢያደርጉም የ14 ዓመቷ መቅደስ ኃይሌ እና የ15 ዓመቱ ገብሬ ኃይሌ የሁለቱ እህትና ወንድም ህይወት ህዳር 7 ቀን 2018 ዓ.ም ምሽት 11:00 ሰዓት ሲያልፍ የሟቾች ቁጥር ወደ አምስት አሻቀበ።

ከተቀሩት ተጎጂዎች ደግሞ የ1ዓመት ከ7 ወሩ ህፃን ሲሳይ ኃይሌ ህዳር 9 ቀን 2018 ዓ.ም ጥዋት 2:00 ሰዓት ላይ ህይወቱ ሲያልፍ የስድስቱ ሟች ልጆች አባት የሆነዉ አቶ ኃይሌ አበራ ህዳር 10 ቀን 2018 ዓ.ም ለሊት በሰመመን ዉስጥ ሆኖ ከእንቅልፉ ሳይነቃ ህልፈቱ እዉን ሆኖ ልብ ሰባሪና አሳዛኝ የሆነ ዜና ተደመጠ።

የባለቤቷንና የስድስት ልጆችዋን ህልፈት ለማወቅ ያልታደለችዉ ወይዘሮ ዳመነች ደንበል በሚኒሊክ ሆስፒታል በከፍተኛ የጥንቃቄ ክፍል ዉስጥ ሆና በህክምና እየተረዳች በህወት መኖሯን ነዉ ፖሊስ የተገለፀዉ።

ተጎጂዋ ቤተሰቡን በጅምላ ወደ ሞት ያወረደዉን ጉዳይ ልትተርክ በህይወት ትተርፍ ይሆን?ወይስ እሷም የባለቤቷና የልጆችዋ እጣ ገጥሟት ከቤተሰቡ መሀል አንድም ለወሬ ነጋሪ ሳይተርፍ በጅምላ እቺን አለም የመሰናበታቸዉ አሳዛኝ ዜና ይደመጣል? የሚለዉን ለመገመት ይከብዳል።

ፖሊስ ተጎጂዎች የተመገቡት ምግብ የተመረዘዉ በማንና እንዴት?የሚለዉን እዉነታ ለማረጋገጥና የተፈፀመዉን ድርጊት አጣርቶ እዉነታዉ ለማረጋገጥ ከምስራቅ ጉራጌ ዞን እና ከመስቃን ወረዳ የተወጣጣ የምርመራ አጣሪ ግብረ ኃይል አዋቅሮ ምርመራ የማጣራቱን ስራ መጀመሩን የተናገሩት ኮማንደር ያለዉ ተመስገን የምርመራ ግብረ ኃይሉ በድርጊቱ የሌሎች እጅ ሊኖር ይችላል በሚል ጥርጣሬ አስር ሰዎችን በቁጥጥር ስር አዉሎ ምርመራ እያጣራ መሆኑን ገልፀዋል።
ተጎጂዎች በዳግማዊ ምንሊክ ሆስፒታል ህክምና ተከታትለዋል ያለዉ ፖሊስ የሟቾች የአስክሬን ምርመራ ዉጤት እየተጠበቀ መሆኑንና ስለጉዳዩ የተሻለ ፍንጭ ሊሰጥ እንደሚችል መረጃ ሊገኝ እንደሚችል ይገመታል። የክልሉ ፖሊስ ሚድያ ክፍል ይህ ዜና በሚድያ ይፋ እስካደረገበት ሰዓት ድረስ ከስምንቱ ተጎጂዎች ዉስጥ አንዷ የሆነችዉ የቤቱ እማወራ በአዲስ አበባ ምንሊክ ሆስፒታል በህክምና እየተረዳች መሆኑን አረጋግጧል።መረጃው የክልሉ ፓሊስ ነው ። ታጁ ነጋሽ።

በአስገድዶ መድፈር ወንጀል የተከሰሰው ግለሰብ በ17 ዓመት ፅኑ እስራት መቀጣቱን የሺሾ እንዴ ወረዳ ፍትህ ፅህፈት ቤት ገለፀ።የወረዳው ፍትህ ፅህፈት ቤት ኃላፊ አቶ ናትናኤል ገዛኸኝ እንደገለ...
21/11/2025

በአስገድዶ መድፈር ወንጀል የተከሰሰው ግለሰብ በ17 ዓመት ፅኑ እስራት መቀጣቱን የሺሾ እንዴ ወረዳ ፍትህ ፅህፈት ቤት ገለፀ።

የወረዳው ፍትህ ፅህፈት ቤት ኃላፊ አቶ ናትናኤል ገዛኸኝ እንደገለፁት በወረዳው ዋና ቦላ ቀበሌ ልዩ ስሙ ኤጂቲ ተብሎ በሚጠራ አካባቢ ነዋሪ የሆነው ተከሳሽ መለሰ መይሱ በቀን 27/10/2017 ዓ/ም ከቀኑ 11 ሰዓት በሚሆን ጊዜ የ17 ዓመት ተበዳይ የሆነችውን እንጨት እየለቀመች እያለ በሀይል በማፈን አስገድዶ መድፈሩን ገልፀዋል።

ተበዳይዋም ባሰማችው የይድረሱልኝ ጩኸት የአካባቢ ሰዎች ሲደርሱ ግለሰቡ ድርጊቱን ከፈፀመ በኃላ በወቅቱ ያመለጠ ቢሆንም ፖሊስ ተከታትሎ በመያዝ በቁጥጥር ስር አውሎ ምርመራ ስያጣራ ከቆየ በኃላ የምርመራ መዝገቡን ለወረዳው ፍትህ ፅህፈት ቤት ዐቃቤ ህግ መላኩን ጠቁመዋል።

መዝገቡ የደረሰው የወረዳው ፍትህ ፅህፈት ቤት ዐቃቤ ህግ መዝገቡን ከመረመረ በኇላ በግለሰቡ ላይ የኢፌዴሪ ወንጀል ህግ አንቀጽ 620 (2) (ሀ) ላይ የተደነገገዉን በመተላለፍ የአስገድዶ መድፈር ወንጀል ፈፅሟል የሚል: እንዲሁም ይህንን ድርጊት የፈፀመው የወንድሙ ልጅ ላይ በመሆኑ በመካከላቸው የስጋ ዝምድና መኖሩን እያወቀ የግብረስጋ ግንኙነት ያደረገ በመሆኑ የኢፌዴሪ ወንጀል ህግ አንቀጽ 655 ላይ የተደነገገዉን በመተላለፍ በዘመዳሞች መካከል የሚፈፀም ለመልካም ፀባይ ተቃራኒ የሆነ የብልግና ወንጀል ፈፅሟል የሚሉ ሁለት ክሶችን በመመስረት ለሺሾ-እንዴ ወረዳ ፍርድ ቤት ያቀረበ መሆኑንም አቶ ናትናኤል ገልፀዋል።

ጉዳዩን ስያከራክር የቆየው የሺሾ እንዴ ወረዳ ፍርድ ቤትም ተከሳሹ ወንጀል መፈፀሙን በሰውና በሰነድ ማስረጃ በማረጋገጡ እንዲከላከል ብይን የሰጠ ቢሆንም መከላከል ባለመቻሉ በቀን 10/3/2018 ዓ.ም በዋለው የወንጀል ችሎት ግለሰቡን ያርማል ሌሎችን ያስተምራል ባለው 17 ዓመት ፅኑ እስራት እንዲቀጣ መወሰኑን አስታውቀዋል።

አቶ ናትናኤል በመልዕክታቸው የአስገድዶ መድፈር ወንጀል ባልተለመደ ሁኔታ እየተስፋፋ በመሆኑ ማህበረሰቡ ለጉዳዩ ትኩረት ልሰጥና ሊያወግዘው ይገባል ብለዋል ሲል፠የሺሾ እንዴ ወረዳ መንግስት ኮሙኒኬሽን ነው

የትምህርት ቤቶችን የውስጥ ገቢ ማሳደግ ለትምህርት የልማት ዘርፍ ሥራዎች አጋዥ መሆኑ ተገለጸየትምህርት ቤቶችን የውስጥ ገቢ ማሳደግ ለትምህርት የልማት ዘርፍ አጋዥ መሆኑን የደቡብ ምዕራብ ኢት...
20/11/2025

የትምህርት ቤቶችን የውስጥ ገቢ ማሳደግ ለትምህርት የልማት ዘርፍ ሥራዎች አጋዥ መሆኑ ተገለጸ

የትምህርት ቤቶችን የውስጥ ገቢ ማሳደግ ለትምህርት የልማት ዘርፍ አጋዥ መሆኑን የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል በምክትል ርዕሰ መስተዳድር ማዕረግ የማኅበራዊ ክላስተር አስተባባሪና የትምሀርት ቢሮ ኃላፊ አቶ አልማው ዘውዴ ገለጹ፡፡

የክልሉ ትምህርት ቢሮ ከፍተኛ አመራሮች በዳውሮ ዞን የዋካ ሁለተኛ ደረጃና መሰናዶ ት/ቤት በአካል ተገኝተው ጎበኝተዋል።

የቢሮ ኃላፊ አቶ አልማው ዘውዴ እንደገለጹት የትምህርት ልማት ሥራዎችን ለማሳደግ የት/ቤት የውስጥ ገቢ ማሳደግ ላይ ትኩረት ተሰጥቶ ሊሠራ እንደሚገባ ጠቁመው÷ እንደ ሀገር የተቀመጠውን ትምህርት ለትውልድ ንቅናቄ ዓላማ ለማሳካት ክልሉ በትምህርት ቤቶች የልማት ስራዎች ላይ ቅድሚያ ሰጥቶ እየሰራ ይገኛል ብለዋል።

ከጉብኝቱ በኋላ የቢሮ ኃላፊው ከትምህርት ቤት ኃላፊዎችና መምህራን ጋር የጋራ ውይይት አድርገዋል።

በውይይት ወቅትም ከመምህራን የተለያዩ ጥያቄዎች እና አስተያየቶች የተነሱ ሲሆን በዋናነት በደመወዝ እና ጥቅማጥቅም ዙሪያ የሚስተዋሉ ክፍተቶች በትምህርት ሥራ ላይ አሉታዊ ተጽዕኖ እያሳደረ እንደሚገኝ ከትምህርቱ ቤቱ መምህራን መካከል መምህር ሠላም ተስፋዬና ወርቁ ወላንቾ አንስተዋል።

በተጨማሪም የመምህራን ደረጃ ዕድገትና የእርከን ውዝፍ ክፍያ በተመለከተ ያልተመለሰ ጥያቄ መሆኑን በማስረዳት ችግሮቹ መቀረፍ እንደሚገባቸውም መምህራኑ ጠይቀዋል።

የቢሮ ኃላፊው ከመምህራንና ከትምህት ቤት ኃላፊዎች ለተነሱ ጥያቄዎች ምላሽና ማብራሪያ የሰጡ ሲሆን ለቀጣይ ክልሉ ወስዶ የሚያከናውናቸው በርካታ የቤት ሥራዎች መኖራቸውንም ጠቁመው÷ እነዚህን የተስተዋሉ ችግሮችን ከመቅረፍ በተጨማሪ በትምህርት ቤቶች የውስጥ ገቢ ለማሳደግ የልማት ሥራ ትኩረት የሚሻ በመሆኑ ሁሉም በጋራ ተጋግዞ መስራት እንዳለባቸውም አሳስበዋል።

በጉብኝቱ ላይ የትምህርት ቤት ርዕሰ መምህራን፣ የዞኑ ትምህርት መምሪያ የሥራ ሂደት አስተባባሪዎችን ጨምሮ የዋካ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ጽ/ቤት ኃላፊ የጉብኝቱ ተሳታፊዎች መሆናቸውን ደሬቴድ ዋካ ቅርንጫፍ ዘግቧል።

በክልሉ የግብርና ሥራዎችን የሚያጠናክር የአከባቢ ሥነ-ምህዳር ያገናዘቡ ዘመናዊ የእርሻ ማሽነሪዎች ድጋፍ ይደረጋል ፦ ዶክተር መለስ መኮንን በግብርና ሚኒስቴር የእርሻና ሆርቲካልቸር ልማት ዘር...
20/11/2025

በክልሉ የግብርና ሥራዎችን የሚያጠናክር የአከባቢ ሥነ-ምህዳር ያገናዘቡ ዘመናዊ የእርሻ ማሽነሪዎች ድጋፍ ይደረጋል ፦ ዶክተር መለስ መኮንን

በግብርና ሚኒስቴር የእርሻና ሆርቲካልቸር ልማት ዘርፍ ሚኒስትር ዴኢታ መለሰ መኮንን (ዶ/ር) እና የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ምክትል ርዕሰ መስተዳድርና የግብርና ቢሮ ኃላፊ አቶ ማስረሻ በላቸው በካፋ ዞን የተለያዩ የግብርና ልማት ሥራዎችን ምልከታ አድርገዋል።

በክልሉ ካፋ ዞን አዲዮ ወረዳ ቦቃ ቀበሌ በክላስተር የለማ የ2017/2018 መኸር ስንዴ ልማት እና በዞኑ ዴቻ ወረዳ በFSPR በጀት ድጋፍ የተቋቋመ ዲንቻ የመንግስት ሻይ ችግኝ ብዜት ጣቢያ ተዘዋውረው ተመልክተዋል።

በመስክ ምልከታው በግብርና ሚኒስቴር የእርሻና ሆርቲካልቸር ልማት ዘርፍ ሚኒስትር ዴኢታ መለሰ መኮንን (ዶ/ር) በአካባቢው በግብርና ልማት ሥራ አበረታች ውጤት እንዳለ በጉብኝት ወቅት መመልከታቸውን ገልጸዋል።

የተጀመረውን የግብርና ልማት ሥራዎችን አጠናክሮ ማስቀጠል እንዲያስችል ሚኒስትር መስሪያ ቤቱ ከተለያዩ ልማት አጋሮች ጋር በመቀናጀት የአከባቢ ሥነ-ምህዳር ያገናዘቡ ዘመናዊ የእርሻ ማሽነሪዎችን ድጋፍ ያደርጋል ብለዋል ዶክተሩ።

የክልሉ ምክትል ርዕሰ መስተዳድር እና የግብርና ቢሮ ኃላፊ አቶ ማስረሻ በላቸው፤ በክልሉ የግብርና ምርትና ምርታማነት በማሳደግ የምግብ ዋስትና እና ሉዓላዊነት ማረጋገጥ የሚያስችል የተቀናጀና የተጠናከረ የግብርና ልማት ሥራ እየተከናወነ ይገኛል።

ምርታማነትን በማሳደግ ከውጭ የሚገባውን ምርት በማስቀረት በሀገር ውስጥ ምርት ለመተካትና ወደ ውጪ የሚላከውን የኤክስፖርት ምርት ለማሳደግ እየተሰራ መሆኑንም ጠቅሰዋል።

በክልሉ በ2017/18 ምርት ዘመን 29 ሺህ 172 ሄክታር መሬት በመኸር ስንዴ የለማ መሆኑን ጠቁመው ከዚህም መካከል ከ9 ሺህ ሄክታር በላይ ማሳ በኩታገጠም ለምቷል ነው ያሉት።

አጠቃላይ ከለማው ማሳ አንድ ሚሊዮን 44 ሺህ ኩንታል ምርት እንደሚጠበቅም ምክትል ርዕሰ መስተዳድሩ አስረድተዋል።

የካፋ ዞን አዲዮ ወረዳ ግብርና፣ አከባቢ ጥበቃና ህብረት ሥራ ጽ/ቤት የእርሻና ህብረት ሥራ ዘርፍ ኃላፊ አቶ እሸቱ ገበየሁ በበኩላቸው በወረዳዉ 23 ሺህ 223 ሄክታር መሬት በአምስት ዋና ዋና ሰብሎች እየለማ መሆኑን ተናግረዋል።

ከዚህ መካከል 5 ሺህ 780 ሄክታር መሬት በመኸር ስንዴ በኩታገጠም የለማ መሆኑን የጠቀሱት አቶ እሸቱ፣ ምርትና ምርታማነት ለማሳደግ የአሲዳማ አፈር በኖራ በማከም እና ሙሉ የቴክኖሎጂ ፓኬጅ መጠቀም በመቻሉ ምርቱ በጥሩ ደረጃ ላይ እንደሚገኝ ነዉ ያብራሩት።

በጉብኝቱ ያነጋገርናቸው አርሶ አደሮች ቀደም ሲል መሬታቸው የምርታማነት ችግር እንደነበረው ገልጸዉ ከግብርና ባለሙያዎች ባገኙት ምክር ሀሳብ በግብርና ኖራ ማሳቸውን በማከም እና ሌሎች ምርት ማሳደጊያ ግብዓቶችን በሙሉ ፓኬጅ መጠቀም በመቻላቸው ከማሳው የተሻለ ምርት እንደሚጠበቁና የሰብሉ ቁመና ተስፋ ሰጪ እንደሆነም አንስተዋል።

አርሶ አደሮቹ ምርትና ምርታማነት አስጠብቆ ለማስቀጠል ዘመናዊ የግብርና ማሽነሪዎች እና ሌሎች አስፈላጊ ግብዓት አቅርቦት በቀጣይነትም እንዲሟሉላቸው ጠይቀዋል።

የክልሉ መንግስት ኮሚዩኒኬሽን ያገኘነው መረጃ እንዳመለከተው በጉብኝቱ የክልሉ ምክትል ርዕሰ መስተዳድርና የግብርና ቢሮ ኃላፊ አቶ ማስረሻ በላቸው፣ በግብርና ሚኒስቴር የእርሻና ሆርቲካልቸር ልማት ዘርፍ ሚኒስትር ድኤታ መለሰ መኮንን (ዶ/ር)፣ የክልሉ የመንግስት ረዳት ተጠሪ አቶ በላይ ተሰማ፣ የካፋ ዞንና የወረዳ አመራሮች ተሳትፈዋል።

በማንሰራራት ላይ ያለችው ጥንታዊቷ የማጂ ከተማ።በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል በምዕራብ ኦሞ ዞን የሚትገኘው የማጂ ከተማ፣ ከኢትዮጵያ ጥንታዊ ከተሞች አንዷ ናት።የማጂ ከተማ የቀድሞው...
20/11/2025

በማንሰራራት ላይ ያለችው ጥንታዊቷ የማጂ ከተማ።

በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል በምዕራብ ኦሞ ዞን የሚትገኘው የማጂ ከተማ፣ ከኢትዮጵያ ጥንታዊ ከተሞች አንዷ ናት።

የማጂ ከተማ የቀድሞው የካፋ ክፍለ ሀገር የአውራጃ ከተማ ሆኖ ከማገልገሏ ባሻገር ኢትዮጵያ እና አፍሪካ ያገናኘው የኢንግሊዝ ቆንሲላ ጽ/ቤት የነበራት፣ ቀድማ የነቃች ከተማም ነበረች።

ከተማዋ በዕድሜዋ ልክ ያልለማች በዙሪያውም በማስተዋለው የፀጥታ ችግር ልማትና ዕድገቷ ተገተው እንደቆየ ነው የማጂ ቱም ከተማ አስተዳደር ካንትባ አቶ እሸቴ አየለ የሚገለጹት።

ከክልሉ መመሥረት በፊት በከተማውና አከባቢው በማስተዋል የሠላም መደፍረስ የማጂ ከተማ ኢኮኖሚ ተቀዛቅዞ፣ አጠቃላይ እንቅስቃሴ ተዳክሞ እንደነበረ የሚገለጹት አቶ እሸቱ በአንድ ወቅት በአስፓልት ሰው መመልከት ናፍቆን ነበረ ይላሉ።

የክልሉ መንግሥት በቆራጥነት የፀጥታ ችግሩን ኅብረሰብን በማሳተፍ መፍታት በመቻሉ እንዲሁም በጠንካራ የህግ ማስከበር ስራ አውንታዊ ለውጥ መመዝገቡን በማንሳት በዚህም ኢንቨስትመንት እየተስፋፋ እንደኾነ ጠቁመዋል።

በተገኘው ሠላም በከተማው የኢኮኖሚ መነቃቃት እየተፈጠረ፣ማኅበራዊና ኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴዎች እያንሰራራ መኾኑንም የክልሉ የመንግሥት ኮሙኒኬሽን በአከባቢው በነበረው ቅኝት መታዘብ ችሏል።

የመሠረተ ልማት ዝርጋታዎች በከተማ አስተዳደሩ እየተከናወነ የሚገኝ ሲሆን፥ በተማው ለኢንቨስትመንት ምቹ ሁኔታዎች መኖሩንም ካንቲባ እሸቱ ተናግረዋል።

የማጂ ከተማ የ10 ዓመት መሪ የከተማ ፕላን ያላት፣ በዙሪያው በማይነጥፉ ወንዞች የተከበበች በውሃ ሀብት የታደለች ከተማ መኾኑን ያመለከቱት አቶ እሸቱ በከተማው ለማልማት ለሚመጡ አልሚዎች በሩ ክፍት ነው ብለዋል።

የክልሉ መመሥረት ለማጂና አከባቢ ካስገኙት ትሩፋቶች ቀዳሚው የአከባቢውን ሠላም ማስፈስን እንደኾነ ያነሱት አቶ እሸቱ በዚህም በአከባቢው ከ30 ዓመታት በላይ የመልካም አስተዳደር ጥያቄ ሆኖ የሰነበተውን የኮሉ ወርቅ ማዕድን ጉዳይ ምላሽ አግኝተው ወደ ምርት መግባቱን አስታውቀዋል።

በዚህም በርካታ የአከባቢው ወጣቶች እና አልሚ ባለሀብቶች የወርቅ ማዕድን መሬት ተረክበው ምርት ማምረት መጀመራቸውን በመጥቀስ አጠቃላይ ሂዴቱ ለማጂ ከተማ ተጨማሪ ዕድል ይዞ የመጣ ነው ብለዋል።

ከክልሉ መንግስት ኮሚዩኒኬሽን ጉዳዮች ቢሮ ያገኘነው መረጃ እንዳመለከተው በከተማው አዳዲስ የንግድና የአግልግሎት ሰጪ ተቋማት ህንጻዎች በስፋት እየተገነቡ መኾናቸውን መመልከት ተችሏል።
@ Bonga Town Government Communication Affairs Office

"ቢስት ባር" -   ያንዱ ላንዱ የመተሳሰብ ስብዕና መገለጫ    | ታላቅ የሚከበርበት፣ ፍቅር ለምልሞ አብሮነትን የሚደምቅበት፣ በዝናብ አብቅሎ ቤታቸውን በእህል ለሞላው ፈጣሪ ቤንቾች ምስጋና...
20/11/2025

"ቢስት ባር" - ያንዱ ላንዱ የመተሳሰብ ስብዕና መገለጫ

| ታላቅ የሚከበርበት፣ ፍቅር ለምልሞ አብሮነትን የሚደምቅበት፣ በዝናብ አብቅሎ ቤታቸውን በእህል ለሞላው ፈጣሪ ቤንቾች ምስጋና የሚያቀርቡበት በዓል- "ቢስት ባር"።

"ቢስት" ማለት የመጀመሪያ ወይም በኩር ማለት ሲሆን በክረምቱ የተዘራ እህል ደርሶ የመጀመሪያውን ፍሬ የሚቀምሱበት መሆኑን ያመለክታል። "ባር" ማለት ደግሞ በዓል የሚል ቀጥተኛ ትርጉም አለው።

ታዲያ ይህ የመጀመሪያ እህል ከመቅመስ ጋር ተያይዞ የሚከበረው በዓል ከዛም ከፍ ያለ ትርጉም ያለው ነው። በቤንቾች ዘንድ ለሰው ልጅ ተገቢውን ክብር መስጠት ባህል ነው። ክብር ሲሰጥ ከጣት እንኳን ረጅምና አጭር አለ የሚል ብሂልን አስደግፈው ታላቅን እንደ ታላቅነቱ ከፍ የማድረግ ልምዳቸው የጎላ ነው።

በ"ቢስት ባር" ከመጀመሪያው እህል የተዘጋጀውን ምግብም ሆነ መጠጥ የመጀመሪያ ልጅ ወይም ታላቅ ሳይቀምስ ሌሎች ታናናሾች ወደ አፋቸው አያደርሱም። የ"ቢስት" በዓል ለልጆች መከባበርን በማስተማርና የሥርዓቱ ሰንሰለትን ከቀጣይ ትውልድ ጋር በማስተሳሰር የሚከበር በዓል ነው።

የደረሰውን እህል የበኩር ልጅ እንደቀመሰ በእድሜ ደረጃ ከታላቅ እስከ ታናሽ በተራ ይደርሳል። ከዚህ በኋላ የተዘጋጀው ምግብ ከቤተሰብ አልፎ ለጎረቤት ተዳርሶ ሐሴት ይደርግበታል። በቤንች የመጀመሪያን እህል ለብቻ መቅመስ ነውር ነው። ይህም ህዝቡ ለአብሮነት ቦታ እንዲሰጥ ያስቻለ ቱባ ባህል ነው።

የ"ቢስት ባር" ሌላኛው ደማቅ ገጽታ መደማመጥ ነው። ሰው ካልተደማመጠ አይከባበርም፤ ካልተከባበረ ደግሞ አብሮነት አይዘልቅም፤ አብሮነት ከሌለ በመራራቅ ውስጥ በሚፈጠር ክፍተት ሰላም ይደፈርሳል።

ለዚህም ቤንቾች ለመደማመጥ ትልቅ ቦታ ይሰጣሉ። ባላባቶች በቢስት ባር የልማት ሥራና ሌሎች ጉዳዮች ላይ መመሪያዎችን በምርቃት አዋዝተው ያስተላልፋሉ። ሌሎች ጆሮ ሰጥተው ያዳምጣሉ ድርጊቱን ተቀብለው በነጋታው ይተገብራሉ።

ለ"ቢስት" በዓል የተጣላን ሊያስታርቅ የተቀመጠ ሽማግሌ ብዙ አይደክምም። በሁለቱ ጠበኞችና በሽማግሌዎች መካከል መከባበርን መሠረት ያደረገ መደማመጥ አለና። የተደማመጠ ደግሞ መግባባቱ ስለማይቀር በሽማግሌ ምክር ራሳቸውን በፍቅር ያድሳሉ። ወዲያው ታርቀው አንድ ይሆናሉ፤ "ቢስት ባር"ን በወንድማማችነት ያከብራሉ።

የቤንች ልጆች በዓመት አንድ ጊዜ ከሌሊት ጨረቃና ከዋክብት ጋር ደስታቸውን የሚጋሩበት ልዩ ቀን "ቢስት ባር" ነው። ለቢስት ባር የተዘጋጀውን ምግብ ቀምሰው ቦርዴውን ፉት እያደረጉ ከባላባቶች ጋር የምስጋና ሥነ ሥርዓትን እንዳከናወኑ ወደ ውጭ ወጥተው በጨረቃ ብርሃን ይጨፍራሉ። በፍጹም ልብ ተዋደው በአንድ ቀዬ ተሰበስበው ያለ ልዩነት ፌሽታ የሚያደርጉበት የአብሮነት በዓል ነው- ቢስት ።

የ2018 ዓ.ም በደማቅ ሁኔታ ይከበራል መለወጫና የምስጋና በዓል በሰላም አደረሳችሁ !!

Digám Benć Bíst Báreśhn Yínť Hátsaśise !!

ሚዛን ሚዲያና ኮሙኒኬሽን

ውድ የሚዲችን  ቤተሰቦች እንደት ናችሁ? ዛሬ ላጋራችሁ የፈለኩት ጉዳይ ከሚዲያችን ተከታይ አንዱ የሆነ የላከልኝ የስዕል ስጦታ ደርሶኛል። ሰዓልውን እያመሰገንኩኝ አስካሁን የሰራሁት ስራ የሚያ...
20/11/2025

ውድ የሚዲችን ቤተሰቦች እንደት ናችሁ? ዛሬ ላጋራችሁ የፈለኩት ጉዳይ ከሚዲያችን ተከታይ አንዱ የሆነ የላከልኝ የስዕል ስጦታ ደርሶኛል። ሰዓልውን እያመሰገንኩኝ አስካሁን የሰራሁት ስራ የሚያሳይና የኔን ምስል የሳለበት አሳሳል እጅግ ደስ የሚልና የሚያስመሰግን በመሆኑ በሚዲያችን ቤተሰቦች ስም አመሰግናለሁ ።
የምስሉ ይዘት ስታይ መድረክን እየመራሁ የተነሳሁት ፎቶን አስታወሰኝ! ለሰዓልው ከልቤ የመነጨ ምስጋናና አክብሮት እየቸርኩኝ ውድ ሰዓልያችን በሌላም የስዕል ስራ እንደምንገናኝ ጭምር ተስፋ አደርጋለሁ።

ይህ የተሳለው ስዕል ወይም ምስል የዘንድሮን የካፋ ማሽቃረ "ባሮ"ን አዲስ አበባ እያስተባበርኩና እየመራሁ በነበርኩበት ወቅት የነበረ ሰው ነው።

ሰዓልው የምስሉን ስጦታ ከሰጠኝ በኋላ የካፋን ባህል ብሎም የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያን በመላው አለም የሚታስተዋውቅ በመሆኑ ይህንን ተጠብቤ የሳልኩትን ምስል አበርቻለሁ ብሎኛል።
እኔም በዚህ ታላቅ መድረክ እንዲህ ዓይነት የጥበብ ሰው በማግኘቴ እጅግ ደስ ያለኝ ሲሆን በቀጣይ በተለያዩ መድረኮች እንደማገኘው ሙሉ ተስፋ አለኝ ።
መልካም ቀን
ቡና ሚዲያና ኮሚዩኒኬሽን (አማኑኤል ሀይሌ)ጋዜጠኛ
Bonga Town Government Communication Affairs Office Kaffa Community Television Gaaki Yoodo Bonga FM 97.4 Southwest Communications South Ethiopia Regional Prison Police Commission Geech Bichegna

20/11/2025

እኛ ኢትዮጵያዊያን ጀግኖች ነን!! የሀገራችን ክብር ልነካ የሚፈልግ ካለ ወደኋላ አንልም!! ብሄራዊ ጥቅማችንን የሚነካ ካለም ቁጭ ብለን አናይም!!

ልገዳደረን የሚሞክር ካለም ከታርካችን እንደምንረዳው በሀገራችን ጉዳይ የማንደራደር ነን

ርዕሰ መስተዳድር ዶ/ር ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ በክልሉ ፓሊስ ኮሚሽን በተዘጋጀ ስልጠና ላይ ያስተላለፉት መልዕክት!!
Bonga Town Government Communication Affairs Office ゚viralシfypシ゚viralシalシ ゚viralシfypシ゚ Kaffa Community Television Ethiopia Regional Prison Police Commission FM 97.4 Communications Yoodo Haile Hibo #

ከምዕራብ ኦሞ ዞን ከፍተኛ የበቆሎ ምርት ወደ ማዕከላዊ ገበያ እየተላከ መሆኑ ተመላከተበምዕራብ ኦሞ ዞን ጀሙ ገበያ ከፍተኛ የሆነ የበቆሎ ምርት አቅርቦት  እና የግብይት ሥራዓት መኖሩን ከጀሙ...
20/11/2025

ከምዕራብ ኦሞ ዞን ከፍተኛ የበቆሎ ምርት ወደ ማዕከላዊ ገበያ እየተላከ መሆኑ ተመላከተ

በምዕራብ ኦሞ ዞን ጀሙ ገበያ ከፍተኛ የሆነ የበቆሎ ምርት አቅርቦት እና የግብይት ሥራዓት መኖሩን ከጀሙ ከተማ አስተዳደር የተገኘ መረጃ ያሳያል፡፡

አሁን የበቆሎ ምርት በከፍተኛ ሁኔታ ወደ ማዕከላዊ ገበያ እየተጫነ መሆኑን የጀሙ ከተማ አስተዳደር የኢኮኖሚ ክላስተር አስተባባሪና ኢንተርፕራይዝ፣ ግብርና፣ ትራንስፖርትና መንገድ ልማት ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ወርቁ ኮርዲ ተናግሯል።

ከተማ አስተዳደሩ የበቆሎ ምርት ግብይት ሰንሰለቱን ይበልጥ በማጠናከር የአርሶአደሩን ብሎም አቅራቢ ነጋዴዎችን ተጠቃሚ እንዲሆኑ ትኩረት ተሰጥቶ እየተሰራ መሆኑን ገልፀዋል፡፡

በባለፈው ዓመትም ከፍተኛ የሰብል ምርት በበቆሎ እና በማሽላ ምርት የገበያ ትስስር ተፈጥሮላቸዉ ወደ ተለያዩ ማዕከላዊ ገበያ ማዕከላት ተጭኖ ማውጣቱን ገልጿል።

በዘንድሮው የበቆሎ እና የማሽላ ምርት በከፍተኛ ሁኔታ ወደ ገበያ እየቀረበ መሆኑንና አሁን ላይ በቀን ከ10 ተሳቢ መኪና በላይ የበቆሎ ምርት ተጭኖ ወደ ማዕከላዊ ገበያ እየወጣ ያለ መሆኑን ነው አቶ ወርቁ የጠቀሱት።

ከማዕከሉ በከፍተኛ ደረጀ እየወጣ ያለው የበቆሎ ምርት ህጋዊ የግብይት ሰንሰለቱን በጠበቀ መልኩ እንዲከናወን ከተማ አስተዳደሩ ከባለድርሻ አካላት ጋር በቅንጅት እየሰራ መሆኑን አቶ ወርቁ ጠቁመዋል፡፡

አማራጭ አነስተኛ ግብርህዳር 10/2018 (የደምኢህክመ ገቢዎች ቢሮ) ያስተላለፈው  መልዕክት1/ በገቢ ግብር ማሻሻያ አዋጅ ቁጥር 1395/2017  በሌላ በማናቸውም ህግ የተደነገገው ቢኖርም ...
20/11/2025

አማራጭ አነስተኛ ግብር

ህዳር 10/2018 (የደምኢህክመ ገቢዎች ቢሮ) ያስተላለፈው መልዕክት

1/ በገቢ ግብር ማሻሻያ አዋጅ ቁጥር 1395/2017 በሌላ በማናቸውም ህግ የተደነገገው ቢኖርም ማናቸውም ድርጅት ወይም ሰው ግብር በሚወሰንበት የግብር አመት ከሁሉም ንግድ ስራ የገቢ ምንጮች ባገኘው ትርፍ ላይ ሊከፍል የሚገባውን ግብር በዚሁ የግብር አመት ካገኘው ጠቅላላ ገቢ ከ2.5%(ሁለት ነጥብ አምስት በመቶ ) በታች ከሆነ ግብር ከፋዩ በተመለከተው የማስከፈያ ምጣኔ መሰረት አማራጭ አነስተኛ ግብር መክፈል አለበት፡፡

2/ አማራጭ አነስተኛ ግብር የሚከፈለው በሚከተለው የማስከፈያ ምጣኔ ይሆናል፡-

ሀ) ማናቸውም ድርጅት ወይም ሰው አመታዊ ጠቅላላ ገቢ2.5%፤ወይም
ለ) ባንኮችን በሚመለከት ከባንክ ስራ የተገኘ የተጣራ ገቢ2.5%፤
ሐ) የኢንሹራንስ ኩባንያዎችን በሚመለከት ከህይወት እና ከህይወት ውጪ ከሆነ ኢንሹራንስ የተገኘው ጠቅላላ አርቦን2.5% ፤
መ) ዋጋቸው የተወሰነ ዕቃዎችን አቅራቢ ሰው ወይም ድርጅትን በሚመለከት የኮሚሽን ገቢው 2.5%

3/ አማራጭ አነስተኛ ግብር ከሚከፈለው የንግድ ትርፍ ግብር ላይ ተቀናሽ ይደረጋል፡፡

4/ ይህ ግብር በጠቅላላ ገቢው ላይ ግብር በሚከፍል ግብር ከፋይ ላይ ተፈጻሚ አይሆንም፡፡

5/ ግብር ከፋዩ የከፈለው ግብር ሊከፍል ከሚገባው የንግድ ትርፍ ላይ የሚቀነሰው በሚከተለው አኳኋን ይሆናል፡-
ሀ) እስከ 5(አምስት ) አመታት ድረስ፤
ለ) ሊከፍል ከሚገባው የንግድ ትርፍ ግብር ላይ የሚቀነስው ሂሳብ ሊከፍል እስከሚገባው አማራጭ አነስተኛ ግብር ድረስ ሆኖ የተከፈለውን ተቀናሽ የተደረገበት የንግድ ትርፍ ግብር ሳይጨምር ይሆናል፡፡

6/ ከላይ የተገለጸው እንደተጠበቀ ሆኖ የሚከተሉት ከአማራጭ አነስተኛ ግብር ነጻ ተደረገዋል፡-
ሀ) በኪሳራ ምክንያት መፍረስ ላይ ያለ ድርጅት፤ እና
ለ) በእዳ ማሸጋሸግ ላይ ያለ ድርጅት፡፡

7/ አማራጭ አነስተኛ ግብር በኢንቨስትመንት ማበረታቻ ህግ መሰረት የግብር እፎይታ በተሰጠው ሰው ላይም ተፈጻሚ ይሆናል፡፡ስለሆነም አማራጭ አነስተኛ ግብሩ የተሰጠው ማበረታቻ ተቀንሶ ሊከፈል በሚገባው የገቢ ግብር ላይ ተፈጻሚ ይሆናል፡፡

8/ አመታዊ ጠቅላላገቢ፡- ማለት በግብር አመቱ ከተከናወነ የዕቃ ሽያጭ እና አገልግሎት የመስጠት ተግባር የተገኘ ተቅላላ ገቢ ነው፡፡
ከባንክ ስራ የተገኘ ገቢ፡- ማለት ከሚከተሉት ምንጮች የተገኘ ገቢ ነው፡-

1) ብድርን ከመሳሰሉት የባንኩ ሃብቶች በሚገኝ ወለድ እና ተቀማጭ ሂሳብን ለመሳሰሉት የባንኩ እዳዎች በሚከፈል ወለድ መካከል ያለው ልዩነት፤
2) ግብይትን ፤ሂሳብ ማሰተዳደርን እና የምክር አገልግሎትን ከመሳሰሉት አገልግሎቶች የሚገኝን ገቢ ጨምሮ ከክፍያዎች እና ከኮሚሽኖች የሚገኝ ገቢ፤
3) በፋይናንስ ሰነዶች በመገበያየት የሚገኝ ትርፍ እና የሚያጋጥም ኪሳራን ጨምሮ ከግብይት የሚገኝ የተጣራ ገቢ፤
4) ለግብይት ወይም ለኢንቨስትመንት አላማ ከተያዙ የፋይናንስ ሰነዶች የሚገኝ ጠቅላላ ገቢ፤ እና

5) አስቀድሞ ከሂሳብ መዝገብ የተሰረዙ ሂሳቦችን ከማስመለስ እና ከመሳሰሉት የተለያዩ ገቢዎች የተገኘ የሌሎች የስራ እንቅስቃሴዎች ገቢ፡፡

የኮሚሽን ገቢ፡- ማለት በህግ ወይም በተዋዋዮች መካከል በተደረገ ውል በተወሰነው መሰረት ከአንድ ዕቃ ወይም አገልግሎት ዋጋ ላይ ለአገልግሎት ሰጪው የሚከፈል ገንዘብ ነው፡፡

ዋጋው የተወሰነ ድርጅት፡- ማለት ዕቃዎችን የሚሸጥበት ወይም አገልግሎትን የሚያቀርብበት ዋጋ በውል ወይም በመንግስት አካል የተወሰነ ወይም ቁጥጥር ሚደረግበት ድርጅት ነው፡፡

20/11/2025

ዕለተ ሀሙስ ሀገራዊና ክልላዊ ዜናዎች
የሀገራችንን ክብር እናስጠብቃለን!! ርዕሰ መስተዳድር ዶ/ር ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ

በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ክልል ለፓሊስ አመራሮች ስሰጥ የነበረው ስልጠና ተጠናቋል።
የጋምቤላ ክልል ፓሊስ ስልጠናቸውን አጠናቀው ተቋማትን ጎበኙ
ስለ አዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ መረጃ ይዘናል።
የፋና ላምሮት በመጪው ምዕራፍ 21ይጀምራል

ቡና ሚዲያና ኮሚዮኒኬሽን@topfans Bonga Town Government Communication Affairs Office Kaffa Community Television Gaaki Yoodo Bonga FM 97.4 Southwest Communications South Ethiopia Regional Prison Police Commission

20/11/2025

ታርካችን የአሸናፍነት ታርክ ነው። ታርካችን የጀግንነት ታርክ ነው። የሀገራችን ክብር እናስጠብቃለን!!ዶክተር ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ

ቡና ሚዲያና ኮሚዩኒኬሽን@buna media and communication Kaffa Community Television Bonga Town Government Communication Affairs Officee@@ Gaaki Yoodo

Address

Addis Ababa

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Bunna Media and Communication posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share