ክብር ለኢየሱስ ይሁን

ክብር ለኢየሱስ  ይሁን ✍️ “የጽድቅም ሥራ ሰላም፥ የጽድቅም ፍሬ ለዘላለም ጸጥታና መታመን ይሆናል።”🙏
✍️ኢሳይያስ 32፥17
Thank you God 🙏🔥

04/08/2025

ቸሩ መድኃኒአለም የቀራንዮ ንጉስ የድንግል ማርያም ልጅ ከኃጢያት በቀር የልባችን መሻት ይፈጽምልን!!!
==============/////==============
በመለኮቱ ሕያው ሲሆን በስጋው ግን ሞትን ቀመሰ፡፡

የአዳምን ሞት በሞቱ ሊሽር መድኃኔ ዓለም ኢየሱስ ክርስቶስ ነፍሱን በገዛ ፈቃዱ አሳልፎ ሰጠ፡፡ ቅዱስ ጳውሎስም ለኤፌሶን ክርስቲያኖች ሲጽፍ “ከወደደን ከትልቅ ፍቅሩ የተነሣ በበደላችን ሙታን እንኳ በሆንን ጊዜ ከክርስቶስ ጋር ሕይወት ሰጠን… አስቀድሞ ያዘጋጀውን መልካሙን ሥራ ለማድረግ በክርስቶስ ኢየሱስ ተፈጠርን” ይላል፡፡ ካሕናት አባቶቻችን የስቅለተ ዕለተ የዘጠኝ ሰዓት ስግደት ሲሰገድ “ኦ ዘጥዕመ ሞተ በስጋ” “በስጋው ሞትን የቀመሰ ኢየሱስ ክርስቶስ” እያሉ ልብን በሚያሳዝን ዜማ ያዜማሉ፡፡ የእስክንድርያው ሊቀ ጳጳስ ቅዱስ ቄርሎስም “ለቤተ ክርስቲያን ስትል በአደባባይ በጥፊ የተመታህ አቤቱ ይህን ማድረግህ እርስዋን በከበረ ደምህ ትቀድሳት ዘንድ ነው፡፡ ለእርስዋ ሲል ታሥሮ መጎተት የቻለ የበደለውም በደል ሳይኖር፣ ርኩስ ምራቅን ሲተፋበት የታገሠ መድኃኔ ዓለም በእንጨት መስቀል ላይ ተሰቀለ” በማለት ገለጸው፡፡

አምላካችን እግዚአብሔር ሰው ሆኖ እንደሚያድነን በመጀመሪያ ለአዳም ቃል ገባለት፡፡ ከዚያም በነቢያት ትንቢት አስነገረ፡፡ በስጋ በተገለጠ ጊዜም የሰቀሉትና የገደሉት አይሁድ ሳይቀሩ እንዲናገሩ አፋቸውን አስከፈታቸው፡፡ አልአዛርን ለአራት ቀናት በመቃብር ከቆየ በኋላ ከሙታን ሲያስነሳው ከአይሁድ ወገን ብዙዎች አመኑ፡፡ አንዳንዶች ግን ወደ ፈሪሳውያን ሄደው ኢየሱስ ያደረገውን ነገሯቸው፡፡ በዮሐንስ 11 እንደተጻፈው ከተአምራቱና ከትምህርቱ የተነሳ ሕዝቡ ሁሉ ትቷቸው እንዳይሔድ የፈሩት አይሁድ ሲማከሩ በዚያች ዓመት ሊቀ ካህናት የነበረ ቀያፋ የሚሉት ከእነርሱ አንዱ፡- “እናንተ ምንም አታውቁም፤ ሕዝቡም ሁሉ ከሚጠፋ አንድ ሰው ስለ ሕዝቡ ይሞት ዘንድ እንዲሻለን አታስቡም” አላቸው።

ይህንም የተናገረ ከራሱ አይደለም፤ ኢየሱስ ስለ ሕዝቡ ሊሞት እንዳለው እግዚአብሔር መንፈስ ቅዱስ ትንቢት አናገረው፡፡ “ስለ ሕዝቡም ሁሉ አይደለም፣ ነገር ግን የተበተኑትን የእግዚአብሔርን ልጆች በአንድነት እንዲሰበስባቸው ነው እንጂ።” ተብሎ ተጽፏልና፡፡ የቀድሞው የግብጽ ኦርቶዶክሳውያን ሊቀ ጳጳስ አቡነ ሺኖዳ “እኛ ወደ እርሱ መውጣት ሲያቅተን መድኃኔ ዓለም ወደኛ ወረደ” በማለት ይገልጹታል፡፡ የማዳኑ ስራ ለሰው ልጅ ቤዛነት የተደረገ፣ ፍጹም ፍቅሩ የታየበት ከሰው ሕሊና በላይ የሆነ አባትነቱን ያሳየበት ነው፡፡ አምላክነትን ሲሻ የወደቀው የሰው ልጅ፣ የወደደውን አምላክነት ያገኝ ዘንድ የሰውን ባሕርይ ተዋህዶ ከቅድስት ድንግል ማርያም ተወለደ፡፡ በድንቅ ተዋህዶ አምላክ ሰው፣ ሰውም አምላክ ሆኗልና ከኛ በነሳው ስጋም ወደ ሰማይ አረገ፡፡

ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ “ሔዋንን ዲያብሎስ አሳታት የሞት ምክንያት የሚሆን ቃየልን ወለደች፡፡ ድንግል ማርያም ግን መልአክ በአበሠራት ጊዜ ሁሉን ወደ ዘለዓለም ሕይወት የሚመራ አካላዊ ቃልን በሥጋ ወለደች፡፡” ይለናል፡፡ በማዳኑ ስራ ውስጥ የቅድስት ድንግል ማርያም ድርሻ ታላቅ ነው፡፡ ቅዱስ ጳውሎስም በገላ 4÷4 “የዘመኑ ፍጻሜ በደረሰ ጊዜ እግዚአብሔር ከሴት የተወለደውን ልጁን ላከ፡፡” ሲል ጽፏል፡፡ ስለፍጹም የሰው ልጆች ፍቅር መድኃኔ ዓለም ተላልፎ ተሰጠ፡፡ ለዚህም ነው በፊልጵ 2÷8 “በምስሉም እንደ ሰው ተገኝቶ ራሱን አዋረደ፣ ለሞትም ይኸውም የመስቀል ሞት እንኳ የታዘዘ ሆነ” ተብሎ የተጻፈው፡፡

ዛሬ እሁድ በአሶሳ ክርስቶስ አንድነት ቤተ-ከርስቲያን አጥቢያ ከጠዋቱ ጀመረው እሰከ ከሠዓት ፕሮግራም እንዲህ ይመስላል። ያገለግሉልን አገለጋይዎች እግዚአብሔር አብዝቶ ይባረካችሁ!!  በእግዚአ...
03/08/2025

ዛሬ እሁድ በአሶሳ ክርስቶስ አንድነት ቤተ-ከርስቲያን አጥቢያ ከጠዋቱ ጀመረው እሰከ ከሠዓት ፕሮግራም እንዲህ ይመስላል። ያገለግሉልን አገለጋይዎች እግዚአብሔር አብዝቶ ይባረካችሁ!! በእግዚአብሔር ክበር ተጀምሮ በክብር ተጠናቀዋል።❤🙏

አሶሳ ክርስቶስ አንድነት ቤተ-ክርሰቲያን አጥቢያ የከሰዓት ፕሮግራም በዚህ መልክ ተጠናቀዋል። ነገ ደገሞ 3:00 የጀመራል። እግዚአብሔር በስራ ላይ ነው።👑👑❤🙏
02/08/2025

አሶሳ ክርስቶስ አንድነት ቤተ-ክርሰቲያን አጥቢያ የከሰዓት ፕሮግራም በዚህ መልክ ተጠናቀዋል። ነገ ደገሞ 3:00 የጀመራል። እግዚአብሔር በስራ ላይ ነው።👑👑❤🙏

ዛሬ ቀዳሜ 26/11/2017ዓ/ም  በአሶሳ ክርስቶስ  አንደነት ቤተ ከርስቲያን አጥቢያ የመነቃቃት ኮንፈረንስ ላይ ተጋባዥ እንገዳ  #ወ/ዊ/ገመዳ ተስማ እና  #ዘማሪ/ማፖ ፍቃዱ እግዚአብሔር ...
02/08/2025

ዛሬ ቀዳሜ 26/11/2017ዓ/ም በአሶሳ ክርስቶስ አንደነት ቤተ ከርስቲያን አጥቢያ የመነቃቃት ኮንፈረንስ ላይ ተጋባዥ እንገዳ #ወ/ዊ/ገመዳ ተስማ እና #ዘማሪ/ማፖ ፍቃዱ እግዚአብሔር በሰጣቸው የጸጋን ቀባት አገለግሎልናል።❤🙏

የእግዚአብሔር መላዓከት በክብሩ ያጀባችሁ!!
26/07/2025

የእግዚአብሔር መላዓከት በክብሩ ያጀባችሁ!!

24/07/2025

ስማ ወንድም! /ስምኝ እህተ
በቅርቡ የናቁህ ሁሉ እስከሚፈልጉህ ድረስ አምላክህ እግዚአብሔር የክብር ምዕራፍ ይከፍትልሃል።
Christ army Tv world wide

21/07/2025

“እኔም በልቤ፦ በዚያ ለነገር ሁሉና ለሥራ ሁሉ ጊዜ አለውና በጻድቅና በኃጢአተኛ ላይ እግዚአብሔር ይፈርዳል አልሁ።”
መክብብ 3፥17

20/07/2025

👑👑👑
መልካም ዜና
አትጨነቁ እግዚአብሔር
ሁሉን ያዘጋጃል።
Christ Army Tv Worldwide

17/07/2025

🗣“እግዚአብሔር ብርሃኔና መድኃኒቴ ነው፤ የሚያስፈራኝ ማን ነው? እግዚአብሔር የሕይወቴ መታመኛዋ ነው፤ የሚያስደነግጠኝ ማን ነው።🔥
መዝሙር 27፥1

በአምልኮና በዝማሬ ምርኮ ይመለሳል!!❤🙏
13/07/2025

በአምልኮና በዝማሬ ምርኮ ይመለሳል!!❤🙏

11/07/2025

በዚህ ወር ሴጣን የቀዶ የፈረስ ይሁን!!

Address

Assosa
Addis Ababa

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when ክብር ለኢየሱስ ይሁን posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to ክብር ለኢየሱስ ይሁን:

Share