15/10/2025
በታላቁ ህዳሴ ግድብ ዙሪያ ኢትዮጵያ ለግብጽ የሰጠችዉ ጋዜጣዊ መግለጫ ዋና ዋና ነጥቦች
++++++++++++++++++++++
👉 ግብፅ በዓባይ ወንዝ እና በታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ዙሪያ የምታደርጋቸዉን ጸብ አጫሪ ንግግሮች ኢትዮጵያ ታወግዛለች።
👉 ኢትዮጵያ፣ ግብፅ በዓባይ ተፋሰስ ሀገራት መሰረተ ልማቶችን በመገንባት ከአፍሪካ ጋር አጋርነት እያሳየሁ ነዉ ማለቷ የትብብር ፍላጎት ማሳያ አለመሆኑና ይልቁንም በዓባይ ተፋሰስ ውስጥ ያሉ የግብፅ ፕሮጀክቶች ተምሳሌታዊና በቂ ያልሆኑና ያረጁ አስተሳሰቦችን የሚያንፀባርቁ እንደሆኑ ገልጻለች።
👉 ኢትዮጵያ የዓባይ ወንዝን ለልማት ፍላጎቷ የመጠቀም ህጋዊና የማይሻር መብት እንዳላት አጥብቃ ትገልጻለች። ይህንን መብቷን እንድትተው በማንም ጫና ሊደረግባት እንደማይገባ ታሳውቃለች።
👉 ግብፅ በዓባይ ወንዝ ላይ ታሪካዊ መብቶች የሚለውን የቅኝ ግዛት ዘመን አስተሳሰብ የሙጥኝ ብላ ብትይዝም፤ ኢትዮጵያ ለሁሉም የተፋሰሱ አገሮች ፍትሃዊና ምክንያታዊ አጠቃቀምን ትደግፋለች።
👉 ግብፅ በሶስትዮሽ የህዳሴ ግድብ ንግግሮችም ሆነ በሰፊው የዓባይ ተፋሰስ ትብብር ማዕቀፍ (CFA) ያደረገቻቸዉ ድርድሮች ታማኝነት የጎደላቸዉ ነበሩ።
👉 ግብፅ ከሌሎች የዓባይ ተፋሰስ አገሮች ጋር ያለ ምንም ምክክር የምታደርገውን ውሀውን በበላይነት የመጠቀም ልምድን ጨምሮ ህገወጥና ብክነት የተሞላበት የዉሀ አስተዳደርን ኢትዮጵያ ትቃወማለች።
👉 በዓባይ ዙሪያ መፍትሄ ሊገኝ የሚችለው በጉዳዩ በሚመለከታቸው ወገኖች መካከል በቀጥታና በእኩል ደረጃ በሚደረግ ተሳትፎ ብቻ መሆኑን ኢትዮጵያ አጥብቃ እንደምታምን ገልጻለች።
👉 ግብፅ የምትጠቀመውን ማስፈራራት፣ ሀሰተኛ ውንጀላ፣ ፈጠራ ላይ መሰረት ያደረገ ውንጀላ እና የማተራመስ ዘዴዎችን ኢትዮጵያ ትቃወማለች።
👉 ግብፅ በህዳሴ ግድብ ዙሪያ የምትሰጣቸዉ የድርቅ እና ጎርፍ ማስጠንቀቂያዎች የተፈበረኩ ናቸዉ። ይህም የጋራ ፍላጎትን መሰረት ያደረገ መፍትሔ ለመፈለግ ያለመቻሏን ያሳያል።
👉 ኢትዮጵያ የግብፅን ትርምስ የመፍጠር አጀንዳር ሙከራዎችን በመቃወም፣ በህዳሴ ግድብ ላይ ከሱዳን ጋር ውጤታማና የተቀናጀ ግንኙነት እንዳላት ትገልጻለች።
👉 ኢትዮጵያ ጉዳዩን በዲፕሎማሲያዊ መንገድ ለመፍታት ያላትን ቁርጠኝነት አረጋግጣለች። እንዲሁም በግድብ አስተዳደር እና በአካባቢ ዘላቂ ልማት ላይ ያላትን አቋም አሳይታለች።
EPA