Hiber Ethiopia

Hiber Ethiopia This page is about to inform the public on current issues, true information, and risky alerts

21/10/2025

የባሌ ወግ በሶፍዑመር ዋሻ!!! ድሮና ዘንድሮ -----

እውነትና ንጋር እያደር---
20/10/2025

እውነትና ንጋር እያደር---

18/10/2025

የባሌ ተራሮችና የሶፉመር ዋሻ ዓዱሱ ገጽታ!!!

ውስጣዊ ዐቅምን ማጠናከር እና ራስን መቻል የጂኦስትራቴጂ ቁመና መሠረቶች ናቸው።ክቡር አቶ ከበደ ዴሲሳ
17/10/2025

ውስጣዊ ዐቅምን ማጠናከር እና ራስን መቻል የጂኦስትራቴጂ ቁመና መሠረቶች ናቸው።
ክቡር አቶ ከበደ ዴሲሳ

በታላቁ ህዳሴ ግድብ ዙሪያ ኢትዮጵያ ለግብጽ የሰጠችዉ ጋዜጣዊ መግለጫ ዋና ዋና ነጥቦች++++++++++++++++++++++👉 ግብፅ በዓባይ ወንዝ እና በታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ዙሪያ የም...
15/10/2025

በታላቁ ህዳሴ ግድብ ዙሪያ ኢትዮጵያ ለግብጽ የሰጠችዉ ጋዜጣዊ መግለጫ ዋና ዋና ነጥቦች
++++++++++++++++++++++
👉 ግብፅ በዓባይ ወንዝ እና በታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ዙሪያ የምታደርጋቸዉን ጸብ አጫሪ ንግግሮች ኢትዮጵያ ታወግዛለች።
👉 ኢትዮጵያ፣ ግብፅ በዓባይ ተፋሰስ ሀገራት መሰረተ ልማቶችን በመገንባት ከአፍሪካ ጋር አጋርነት እያሳየሁ ነዉ ማለቷ የትብብር ፍላጎት ማሳያ አለመሆኑና ይልቁንም በዓባይ ተፋሰስ ውስጥ ያሉ የግብፅ ፕሮጀክቶች ተምሳሌታዊና በቂ ያልሆኑና ያረጁ አስተሳሰቦችን የሚያንፀባርቁ እንደሆኑ ገልጻለች።
👉 ኢትዮጵያ የዓባይ ወንዝን ለልማት ፍላጎቷ የመጠቀም ህጋዊና የማይሻር መብት እንዳላት አጥብቃ ትገልጻለች። ይህንን መብቷን እንድትተው በማንም ጫና ሊደረግባት እንደማይገባ ታሳውቃለች።
👉 ግብፅ በዓባይ ወንዝ ላይ ታሪካዊ መብቶች የሚለውን የቅኝ ግዛት ዘመን አስተሳሰብ የሙጥኝ ብላ ብትይዝም፤ ኢትዮጵያ ለሁሉም የተፋሰሱ አገሮች ፍትሃዊና ምክንያታዊ አጠቃቀምን ትደግፋለች።
👉 ግብፅ በሶስትዮሽ የህዳሴ ግድብ ንግግሮችም ሆነ በሰፊው የዓባይ ተፋሰስ ትብብር ማዕቀፍ (CFA) ያደረገቻቸዉ ድርድሮች ታማኝነት የጎደላቸዉ ነበሩ።
👉 ግብፅ ከሌሎች የዓባይ ተፋሰስ አገሮች ጋር ያለ ምንም ምክክር የምታደርገውን ውሀውን በበላይነት የመጠቀም ልምድን ጨምሮ ህገወጥና ብክነት የተሞላበት የዉሀ አስተዳደርን ኢትዮጵያ ትቃወማለች።
👉 በዓባይ ዙሪያ መፍትሄ ሊገኝ የሚችለው በጉዳዩ በሚመለከታቸው ወገኖች መካከል በቀጥታና በእኩል ደረጃ በሚደረግ ተሳትፎ ብቻ መሆኑን ኢትዮጵያ አጥብቃ እንደምታምን ገልጻለች።
👉 ግብፅ የምትጠቀመውን ማስፈራራት፣ ሀሰተኛ ውንጀላ፣ ፈጠራ ላይ መሰረት ያደረገ ውንጀላ እና የማተራመስ ዘዴዎችን ኢትዮጵያ ትቃወማለች።
👉 ግብፅ በህዳሴ ግድብ ዙሪያ የምትሰጣቸዉ የድርቅ እና ጎርፍ ማስጠንቀቂያዎች የተፈበረኩ ናቸዉ። ይህም የጋራ ፍላጎትን መሰረት ያደረገ መፍትሔ ለመፈለግ ያለመቻሏን ያሳያል።
👉 ኢትዮጵያ የግብፅን ትርምስ የመፍጠር አጀንዳር ሙከራዎችን በመቃወም፣ በህዳሴ ግድብ ላይ ከሱዳን ጋር ውጤታማና የተቀናጀ ግንኙነት እንዳላት ትገልጻለች።
👉 ኢትዮጵያ ጉዳዩን በዲፕሎማሲያዊ መንገድ ለመፍታት ያላትን ቁርጠኝነት አረጋግጣለች። እንዲሁም በግድብ አስተዳደር እና በአካባቢ ዘላቂ ልማት ላይ ያላትን አቋም አሳይታለች።
EPA

13/10/2025
ስኬቶቻችን የሰንደቃችን ከፍታ የሚጨምሩ ናቸው (GCS)**********************************ኢትዮጵያ ባለፉት ጥቂት የለውጥ ዓመታት እመርታዊ ስኬቶችን እያስመዘገበች የሚመጥናት...
13/10/2025

ስኬቶቻችን የሰንደቃችን ከፍታ የሚጨምሩ ናቸው
(GCS)
**********************************
ኢትዮጵያ ባለፉት ጥቂት የለውጥ ዓመታት እመርታዊ ስኬቶችን እያስመዘገበች የሚመጥናትን ከፍታ እየያዘች ትገኛለች። ለዘመናት የቁጭት እና እንጉርጉሮ ትርክት ምንጭ የነበረዉን ዓባይን ገርታ የኃይል እና ብርሃን ምንጭ አድርጋለች፡፡
በንጋት ኃይቅ በምግብ ሉዓላዊነቷ ላይ ጉልህ ሚና የሚጫወት የዓሣ ምርት ማግኘት ችላለች፤ ዐዲስ የቱሪዝም መዳረሻ ደሴቶችንና ከተሞችን ፈጥራለች፡፡ የዓባይን የቁጭት ትርክት ወደ ድል እና አሸናፊነት ብስራት ቀይራለች፡፡
ተጨማሪ የኃይል ምንጮችን ከውኃ እስከ እንፋሎት፣ ከፀሐይ ብርሃን እስከ ኑውክሊየር ኃይል እና ነፋስ በመገንባት ላይ ናት፡፡ እነዚህ ሁሉ የሰንደቋን ከፍታ እና ተምሳሌትነት የሚያጎሉ ናቸው፡፡
ኢትዮጵያ ከገጸ ምድር ባሸገር በከርሰ ምድር ያሉ ሀብቶቿን ወደመጠቀም ተሸጋግራለች፡፡ በተፈጥሮ ጋዝ ማውጣት የታየዉን ስኬት ለማላቅ፣ በነዳጅ ዘይትም ለመድገም ግዙፍ ፕሮጀክቶችን ጀምራለች፡፡ የግብርና ዘርፉን ውጤታማነት ለማሳደግ የዐፈር ማዳበሪያ በራሷ ለማምረት ወሳኝ ምዕራፍ ላይ ደርሳለች፡፡ ይህም የምግብ ሉዓላዊነታችንን ለማረጋገጥ የተጀመረውን ሥራ ይበልጥ የሚጠናክር ሆኗል።
የሕዝቧን የአኗኗር ዘይቤ ለመቀየር ከቢሮ እስከ ግቢ በሚል ጀምራ፣ ከከተማ እስከ ገጠር ወደሚል ተሸጋግራለች፡፡ በአዲስ አበባ የተጀመረዉ የከተሞችን ገጽታ የመቀየር ንቅናቄ ዘመናዊነትን፣ የስማርት ሲቲ ጽንሰ ሐሳብን እና ሰውን ከተፈጥሮ የማስማማት ልምምድን ያስተዋወቀ ነው፡፡ ይህም የዲፕሎማሲ ማእከል የሆነችውን መዲናችንን በዓለማቀፍ ደረጃ ያላትን ገጽታ የሚያጎላ፣ የሰንደቃችንን ከፍታ የሚጨምር ነው፡፡
ከተማችንን የማዘመኑን ጅማሮ ወንዞቻችን በማከም የተፋሰሶችን ደኅንነት የሚያረጋግጥ ሆኗል፡፡ ከእንጦጦ ጀምሮ እየተሠራ ያለዉ የወንዞች ዳርቻ ልማት የአዋሽ ተፋሰስን ሥነ ምኅዳር ጭምር የሚያክም ለአካባቢ ጥበቃ አብነት ነው፡፡ የገጠር አኗኗር ዘይቤያችንን በማዘመን ኢትዮጵያን በበጎ የምትመሰል ሀገር የማድረግ ጥረታችንም ፍሬው እየታየ ነው፡፡ እነዚህ ሁሉ የሰንደቃችንን በኩራት መውለብለብ የሚያጎሉ የትጋታችን ውጤቶች ናቸው፡፡
ዛሬ የምናከብረው የሰንደቅ ዓላማ ቀን በነፃነት ቀን የተገኘ አይደለም፤ ነፃ ሆኖ ለሌሎች ነፃነት ከፍ ብሎ ሲውለበለብ የታየ የነፃነት ምልክት እንጅ፡፡ ነፃነቱን ለማስከበር ግን ቀደምቶቻችን ደም፣ ሥጋ እና ዐጥንት ገብረዋል፡፡ ኢትዮጵያን የዓለም የነፃነት ቀንዲል አድርገዉ አስረክበውናል፡፡
ዛሬም እንደትናንቱ የኢትዮጵያን ሉዓላዊነት በደም እና በዐጥንት ለማስበር የቆረጡ ጀግኖች አሉን፡፡ በምድር፣ በአየር፣ በባሕር እና በሳይበር የኢትዮጵያን ሉዓላዊነት በማስከበር ሰንደቋ የነፃነት ተምሳትነቱ እንዲቀጥል የሚተጉ ጀግኖቻችን አሉ፡፡
የሰንደቅ ዓላማ ቀንን የምናከብረዉ በሁሉም ግንባር፣ በሁሉም ዓውድ ስለኢትዮጵያ ዋጋ የሚከፍሉ ጀግኖቻችን በማመስገን፣ ሰንደቃችንም በክብር ከፍ አድርገን በማውለብለብ፣ ለላቀ ከፍታዉ እንደምንተጋ ቃል በመግባት ነው፡፡ የተጀመሩ ትልልቅ የሰንደቅ ዓላማ ፕሮጀክቶች ለማሳካት ደግሞ ያለስስት በጋራ መጣር፣ የኢትዮጵያን ብልጽግና እውን ለማድረግ ማናቸዉንም ዋጋ መክፈል ከዜጎች ይጠበቃል፡፡
እንኳን ለሰንደቅ ዓላማ ቀን አደረሳችሁ!
የመንግሥት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት
ጥቅምት 3/2018 ዓ/ም

18ኛው ቤሔራዊ የሰንደቅ ዓላማ ቀን በተለያዩ ተቋማትና የሀገራችን ክፍሎች ተክብሯል፡፡03/02/2018 ዓ.ም *******************************************18ኛው የሰን...
13/10/2025

18ኛው ቤሔራዊ የሰንደቅ ዓላማ ቀን በተለያዩ ተቋማትና የሀገራችን ክፍሎች ተክብሯል፡፡

03/02/2018 ዓ.ም
*******************************************
18ኛው የሰንደቅ ዓላማ ቀን “ሰንደቅ ዓላማችን ለኢትዮጵያ ታላቅ የከፍታ ዘመን ብስራት፤ ለብሔራዊ አንድነታችን፣ ለሉዓላዊነታችንና ለኢትዮጵያ ሕዳሴ” በሚል መሪ ሐሳብ በተለያዩ የሀገራችን ክፍሎች ተከብሯል፡፡ የተለያዩ ተቋማትና ክልሎች 18ኛውን የሰንደቅዓላማ ቀን ከኢትዮጵያ መንሰራራት ጅምሮ ጋር በማያያዝ ማክበራቸውን መረጃዎች ያሳያሉ፡፡ በዚህም ሰንደቅ ዓላማችን የኢትዮጵያ የከፍታ ዘመን ማሳያ ተደርጎ መወሰድ እንዳበለት ከተላለፉ መልዕክቶች ለመረዳት ተችሏል፡፡

የቬንዙዌላዋ ተቃዋሚ ማሪያ ኮሪና ማቻዶ የ2025 የኖቤል የሰላም ሽልማት አሸነፉ፡፡**************************30/01/2018 ዓ.ም****************የኖርዌይ የኖቤል ኮ...
10/10/2025

የቬንዙዌላዋ ተቃዋሚ ማሪያ ኮሪና ማቻዶ የ2025 የኖቤል የሰላም ሽልማት አሸነፉ፡፡
**************************30/01/2018 ዓ.ም****************
የኖርዌይ የኖቤል ኮሚቴ ሰብሳቢ ጆርገን ዋትነ ፍሬድነስ እንዳሉት በቬንዙዌላ የቀድሞ የተቃዋሚ ፕሬዚዳንታዊ እጩ ተወዳዳሪ በፖለቲካ ተቃዋሚዎች ውስጥ ቁልፍ እና አንድነት ያለው ሰው በመሆን አሸንፋለች ሲል አሶሸትድ ፕሬስ ዘግቧል።

የኖርዌይ የኖቤል ኮሚቴ የ2025 የኖቤል የሰላም ሽልማትን ለቬንዙዌላ ሕዝቦች ዲሞክራሲያዊ መብቶችን በማስተዋወቅ እንዲሁም ከአምባገነን ሥርዓት ወደ ዲሞክራሲ ለመሸጋገር ባደረጉት ያላሰለሰ ጥረት ማሪያ ኮሪና ማቻዶ ሊሸልም ውሳኔ ማሳለፋቸው ታውቋል።

“የታላቁ ሕዳሴ ግድብ ስኬት የመደመር ፍልስፍና ውጤት ነው” ሲሉ ፕሮፌሰር ሳሊም አሊ መግለጻቸዉ ተጠቆመ፡፡29/01/2018 ዓ.ም***************************************...
09/10/2025

“የታላቁ ሕዳሴ ግድብ ስኬት የመደመር ፍልስፍና ውጤት ነው” ሲሉ ፕሮፌሰር ሳሊም አሊ መግለጻቸዉ ተጠቆመ፡፡
29/01/2018 ዓ.ም
****************************************
ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብን አስመልክቶ በታዋቂው ፎርብስ መጽሔት ላይ ላይ ሰፊ ሀተታ ያወጡት አሜሪካ በሚገኘው ደላዌር ዩኒቨርሲቲ ሊቀመንበር እና የጂኦግራፊ ፕሮፌሰር የሆኑት ሳሊም አሊ፥ "ግድቡ የተቀናጀ አመራር የታየበት ውጤታማ ፕሮጀክት ነው" ብለውታል።

የኢትዮጵያ ሕዝብ በአፍሪካ ትልቅ የሃይድሮ ኤሌክትሪክ ፕሮጀክት የሆነውን ታላቁን የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ በማስመረቅ አስደናቂ ስኬት አስመዝግቧል ይላሉ ሀተታቸውን ሲጀምሩ ፕሮፌሰር ሳሊም አሊ።

"የታችኛው የዓባይ ተፋሰስ ሀገራት ባደረጉት ጫና ዓለም አቀፍ የፋይናንስ ተቋማት እና ለጋሽ ሀገራት የገንዘብ ድጋፍ የነፈጉት ግድብ፤ በኢትዮጵያ ሕዝብ ርብርብ በድል ተጠናቅቋል" በማለት ነው ኢትዮጵያውያን ግድቡን እንዴት ስኬታማ እንዳደረጉት ያወሱት።

ግብፅ በፕሮጀክቱ ላይ እንቅፋት ለመሆን መጣሯን የሚጠቅሱት ፕሮፌሰሩ፥ የኖቤል የሰላም ተሸላሚው ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የሚመሩት መንግሥት ግን በጽናት ፕሮጀክቱን ማጠናቀቁን አስታውሰዋል።

በግድቡ ጉዳይ ሁሉም ፊቱን ሲያዞር ኢትዮጵያውያን ግን እጃቸውን አጣጥፈው ከመቀመጥ ይልቅ ራሳቸው የገንዘብ ምንጭ በመሆን ይህን ስኬት ማስመዝገባቸውንም ያትታሉ በጽሑፋቸው።

ኢትዮጵያውያን በቦንድ ግዢ፣ በዘመቻ፣ በስፖርታዊ ዝግጅቶች፣ በዳያስፖራው ማኅበረሰብ ንቅናቄ እና የተለያዩ የዕጣ ሽልማቶችን በማዘጋጀት ለግድቡ ግንባታ የሚውል ገንዘብ በማሰባሰብ ረገድ ያሳዩት ኅበረት የሚደንቅ ነው ይላሉ ፕሮፌሰር አሊ።

የግድቡ በስኬት መጠናቀቅ የኤሌክትሪክ ኃይል ለማያገኘው ከግማሽ በላይ የሆነ የኢትዮጵያ ሕዝብ ብሩህ ተስፋን እንደፈነጠቀም በጽሑፋቸው ተጠቅሷል።

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ለዚህ ግድብ ልዩ ትኩረት ሰጥተው ሲሰሩ እንደነበርም ነው ፕሮፌሰሩ ያወሱት።

በኢትዮጵያም ሆነ በውጪ ያሉ ኢትዮጵያዊያን እና ትውልደ ኢትዮጵያዊያን ከመሰረቱ ማንቀሳቀስ ባይቻል ኖሮ፤ ግድቡን ከፍጻሜው ማድረስ ከባድ እንደነበርም አስታውሰዋል ጸሐፊው።

ግድቡ የአመራር ቅብብሎሽ ውጤት መሆኑንም ጠቅሰ ይህ ዓይነቱ ግድቡ ስኬታማ የሆነበት አመራር ውጤታማ የሚሆነው አጀንዳውን የጋራ በማድረግ፤ ኅብረተሰቡን ማንቀሳቀስ ሲቻል እንደሆነ የራሳቸውን ልምድ አክለው ጽፈዋል።

የኢትዮጵያ መንግሥት በየደረጃው ያሉ አመራሮች ወደ ሕዝብ በመውረድ እና በማስተባበር ፕሮጀክቱን የጋራ አጀንዳ የሚያደርጉበት አካሄድ መከተሉን ያወሱት ጸሐፊው፣ ግድቡ በስኬት እንዲጠናቀቅ ያደረገው እንዲህ ዓይነቱ አሳታፊ አመራር እንደሆነ ጠቁመዋል።

በኢትዮጵያውያን ባለቤትነት የተያዙ ታላላቅ የግል ድርጅቶችም ለግድቡ ግንባታ የበኩላቸውን አስተዋጽኦ ማድረጋቸውን አስታውሰው፣ እንደ ኢትዮጵያ አየር መንገድ ያሉ ስኬታማ የመንግሥት ተቋማትም ለግንባታው የድርሻቸውን መወጣታቸው ሌላው የግድቡ ስኬት ምስጢር እንደሆነ ተጠቅሷል።

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) የኖቤል ሽልማታቸውን ሲቀበሉ ባደረጉት ንግግር ትብብር እና ውህደትን ማዕከል ባደረገው የ"መደመር" ፍልስፍና እንደሚመሩ መጥቀሳቸውን የሚያስታውሱት ጸሐፊው፣ የሕዳሴ ስኬትም ከዚሁ የአመራር ፍልስፍናቸው እንደመነጨ ጠቅሰዋል።

ሕዳሴ ሀገሪቱ አሁን የጀመረችውን የዘላቂ ልማት እንቅስቃሴ እና የቀጣናው የኃይል ሚዛን ለመሆን ያየዘችውን ዓላማ ለማሳካት አቅም እንዳላት ማሳያ እንደሆነም ፕሮፌሰሩ ጠቁመዋል።

ግድቡ በዋነኛነት የተሠራው ለኤሌክትሪክ ኃይል ማመንጫ መሆኑ የሥነ-ምህዳር ተጽዕኖውን አነስተኛ ያደርገዋል የሚሉት ፕሮፌሰር አሊ፥ ይህ ደግሞ የታችኛው የዓባይ ተፋሰስ ሀገራት ያላቸውን የውኃ እጥረት ስጋት በማቃለል ቀጣናዊ መረጋጋትን እንደሚፈጥር ያነሳሉ።

ኢትዮጵያ የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት የአፍሪካ ኮሚሽን እና የአፍሪካ ሕብረት መቀመጫ መሆኗን የጠቀሱት ፕሮፌሰሩ፣ ይህ ደግሞ ሀገሪቱ በኃይል እና በውኃ አቅርቦት ረገድ ትብብርን እንድታስቀድም ተጨማሪ ኃላፊነት እንደሰጣት ጠቁመዋል።

የሕዳሴ ግድብ ለታችኛው ተፋሰስ አገራት ጉዳት እንደማያደርስ የሶማሊያ ፕሬዝዳንተ ሼህ ሐሰን ገለጹ፡፡****************29/01/2018 ዓ.ም*********************የሶማሊያ ...
09/10/2025

የሕዳሴ ግድብ ለታችኛው ተፋሰስ አገራት ጉዳት እንደማያደርስ የሶማሊያ ፕሬዝዳንተ ሼህ ሐሰን ገለጹ፡፡
****************29/01/2018 ዓ.ም*********************
የሶማሊያ ፕሬዝዳንት ሼክ ሐሰን ሙሐመድ ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የታችኛውን ተፋሰስ አገራት ማለትም ግብፅም ሆነ ሱዳንን የሚጎዳ እንዳልሆነ አል አረቢያን ዜና አውታር ዘግቧል፡፡ ፕሮጀክት የጋራ ተጠቃሚነትን የሚያመጣ ነው ያሉት ፕሬዝዳንቱ በታችኛው ተፋሰስ አገራት መካከለ የሚያቃቅር ነገር እንደሌለውም ተዘግቧል፡፡

ቀይ በህርን በተመለከተ የቀጠናዉ አገራት ሰላማዊ ውይይቶችን ማዕከል ባደረገ ሁኔታ በትብብርና በጋራ ተጠቃሚነት መርህ ላይ ቆሞ መሥራት ይኖርባቸዋል ሲሉ ፕሬዝዳንቱ አክለው ገልጸዋል፡፡ ኢትዮጵያ ሕጋዊ መንገድን ተከትላ እያቀረበቸው ያለውችሁ የባህር በር ጥያቄም የሚደገፍ መሆኑን ተጠቁሟል፡፡

Address

Addis Ababa

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Hiber Ethiopia posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to Hiber Ethiopia:

Share