Hiber Ethiopia

Hiber Ethiopia This page is about to inform the public on current issues, true information, and risky alerts

06/06/2026
05/06/2026
ጃፓን ለ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ አድናቆቷን መግለጻ ተሰማ*************በኢትዮጵያ የጃፓን ኤምባሲ ለሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ ለማደራጀት እና ለመምራት ላደረገው ከፍተኛ ጥረት ለብሔራዊ ምርጫ ...
03/06/2026

ጃፓን ለ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ አድናቆቷን መግለጻ ተሰማ
*************
በኢትዮጵያ የጃፓን ኤምባሲ ለሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ ለማደራጀት እና ለመምራት ላደረገው ከፍተኛ ጥረት ለብሔራዊ ምርጫ ቦርድ አድናቆቱን ገልጿል። ኤምባሲው ባወጣው ይፋዊ መግለጫ ጃፓን በምርጫ ሂደቱ ላይ ለተሳተፉት እጩ ተወዳዳሪዎች በሙሉ እንዲሁም ድምፃቸውን ለመስጠት ለቻሉ የኢትዮጵያ ዜጎች የእንኳን ደስ አላችሁ መልዕክት አስተላልፋለች።
በተጨማሪም ጃፓን የኢትዮጵያን የዲሞክራሲ ሂደት ለመደገፍ ለብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ድጋፍ በማድረጓ የተሰማትን ደስታ ገልጻለች ሲል ኢቢሲ ዘግቧል።

03/06/2026
“ከባለቤቱ የሚያውቅ ቡዳ ነው!”===================በእኛም ምርጫ ላይ አስታራቂ መሳይ ስውር የውጭ ተቀላቢዎች በየሚዲያዉ አፋቸዉን እያሞጠሞጡ ነው፡፡ እኛ ኢትዮጵያውያን 7ኛውን ጠቅ...
03/06/2026

“ከባለቤቱ የሚያውቅ ቡዳ ነው!”
===================
በእኛም ምርጫ ላይ አስታራቂ መሳይ ስውር የውጭ ተቀላቢዎች በየሚዲያዉ አፋቸዉን እያሞጠሞጡ ነው፡፡ እኛ ኢትዮጵያውያን 7ኛውን ጠቅላላ ምርጫ አካሂደናል፡፡ የራሳችን ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የመራዉ ምርጫ፡፡ ራሳችን ወጥተን በነፃ ፈቃዳችን ድምፃችንን ሰጥተናል፡፡ ሀገር በቀል የሲቪክ ማኅበራት፣ የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብት ኮሚሽን፣ የአፍሪካ ኅብረት እና ኢጋድ ምርጫዉን ታዝበዋል፡፡ የምርጫ ሂደቱ ሰላማዊ፣ ነጻ እና ሕግን የተከተለ እንደነበረ በመጀመሪያ ደረጃ ሪፖርታቸው ገልጸዋል፡፡ የመጀመሪያ ደረጃ ታዛቢዎቹ እኛ መራጮቹ እና ተፎካካሪ ፓርቲዎችም ሂደቱ ሰላማዊ፣ ዴሞክራሲያዊ፣ ሕግን የተከተለ እንደነበረ እየገለጹ ነው፡፡ ነገር ግን አንዳንድ ራሳቸዉን “ዓለማቀፍ” በሚል ቅጽል የሚገልጹ የበሬ ግንባር የምታክል ሀገር ተቋማት “እኛ አልባረክነውም” እያሉ ነው፡፡

ደግነቱ “ከባለቤቱ የሚያውቅ ቡዳ ነው!” ብሎ ጆሮ የሚሰጣቸው ሕዝብ የለም፡፡ እኛ የተሳተፍንበትን፣ በዐይናችን በብረቱ ያየነውን፣ ተቋሞቻችን ያረጋገጡትን ሀቅ ከሩቅ ባዕድ ማረጋገጫ የምንፈልግበት አንዳች ምክንያት የለም፡፡ “ምርጫዉ እንዴት ነበር?” ለሚሉን ኹሉ መልሳችን “እኛ እንደመረጥንበት ሂደት ነበር፤ ሂደቱን ደግሞ በአካል ተሳትፈን ያየነው እኛው ነን!” ነው፡፡ “ችግር የለም እንጅ ችግር እንኳ ቢኖር ቀጣይ የምናሳካዉ አጀንዳችን ምክክር ስለኾነ እኛዉ እንመክርበታለን” ነው መልሳችን፡፡

Address

Addis Ababa

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Hiber Ethiopia posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share