Hiber Ethiopia

Hiber Ethiopia This page is about to inform the public on current issues, true information, and risky alerts

09/06/2025

ውጭ ሀገር ስንሄድ "መቼ ነው ኢትዮጵያስ እንደዚህ ውብ እና ምርጥ ከተማ የምትሆነው?" እያልን የምንቀና ሰዎች ግን ለምንድነው የእኛ ሀገር ሲሰራና ሲለማ አይሆንም የምንለው?
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ከኢቲቪ ጋር በነበራቸው ልዩ ቆይታ የ ኢትዮጵያ ከተሞች ከአለም ከተሞች ጋር የተወዳሪ ከተማ የመሆን ሂደት ላይ እንዳሉ ከራሳቸው እና ከሀገር ወዳድ ዜጎች ፍላጎት በመነሳት እንዲህ ገልጸውታል፡፡
ውጭ ሀገር ሲሄድ ስለ ኢትዮጵያ የማይቀና ሰው የለም፤ ሁላችንም "መቼ ነው ኢትዮጵያስ እንደዚህ የምትሆነው?" እያልን እንቀናለን
የዛሬ 20 ዓመት ሻንጋይ ሄደው እንደነበር ያስታወሱት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ፤ በወቅቱ ካየሁት የህንፃው እና የመንገዱ ብዛት፣ የከተማው ስፋት አንፃር መቼ ነው ሀገሬ እንደዚህ ዓይነት መልክ የምትይዘው? ይህ እንዲያውስ ይቻላል ወይ? የሚለውን ሳስበው ነገሩ ተስፋ አስቆራጭ መስሎኝ ስጋት ነበረኝ ብለዋል።
በቅርቡ ሻንጋይ በድጋሚ ሲሄዱ ግን ሀገሬ እንደሻንጋይ መሆን ትችል ይሆን? የሚለው ጥያቄ ከፍራቻ ወደ ተስፋ እና እርግጠኝነት ተቀይሮ ነው የተመለስኩት፤ ምክንያቱም ይቻላል የሚለውን ፍንጭ በሀገሬ አይቼው ነበርና ሲሉ ተናግረዋል።
ብዙ ሰዎች ሌላ ሀገር ሄደው በሚያዩት የተለያየ ነገር "ሀገራችንም ቢመጣ?" በማለት እንደሚመኙ ጠቅሰው፤ ነገር ግን ያ ያዩት፣ የተመኙት ነገር በሀገራቸው ሲሰራ ደግሞ "የለም፣ አንፈልግም" ብለው እንደሚቃወሙ አንስተዋል። ይህ የእኛ ልምምድና ባህል እየሆነ ነው፤ ጠንከር ያለ ሥራ ሲሰራ ብዙ ስላልለመድን ሊሆን ይችላል ሲሉ ገልፀውታዋል።
መቼም በሀገራችን ታሪክ እንደዚህ በከሞቻችን ጠንከር ያለ ልማታዊ እና ሀገራዊ ለወጥ ተደርጎ አይታወቅም ይህንን ለመቀበል አና የልማቱ አካል ለመሆን መቸገራችን ከመጣንበት የኋላ ታሪካችን ጠንከር ያሉ ለውጦችን ካለመለማመዳችን የተነሳ መሆኑ ግልጽነው፡፡
ሆኖም ዛሬ ላይ ኢትዮጵዊያን የአለምን ፈጣን እድገት እና ተለዋዋጭነት ከግምት ውስጥ በማስገባት ለልጆቻችን ምቹ ና ተመራጭ ከተማን ለመገንባት ትላልቅ ምዕራፎችን መሻገራችን እያለፍንበት ያለነው እና አማራጭ የሌለው መፍትሄ በመሆኑ ለተግባራዊነቱ ዝግጁ መሆን እና መደገፍ እንጂ ምኞት ብቻ ሆነን መቅረት የለብንም ፡

የነገዋ ኢትዮጵያችን በአስተማማኝ  መሠረት ላይ እንድትቆም ወሳኝ በሆኑ ሀገራዊ ጉዳዮቿ ላይ እየመከረች ነው አዲስ አበባ፣ ግንቦት 24፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) የነገዋ ኢትዮጵያችን በአስተማማ...
01/06/2025

የነገዋ ኢትዮጵያችን በአስተማማኝ መሠረት ላይ እንድትቆም ወሳኝ በሆኑ ሀገራዊ ጉዳዮቿ ላይ እየመከረች ነው

አዲስ አበባ፣ ግንቦት 24፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) የነገዋ ኢትዮጵያችን በአስተማማኝ መሠረት ላይ እንድትቆም ወሳኝ በሆኑ ሀገራዊ ጉዳዮቿ ላይ እየመከረች ነው አለ የመንግሥት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት፡፡

አገልገሎቱ ባወጣው መግለጫ፤ ኢትዮጵያ እና ኢትዮጵያውያን የጋራ ዘርፈ ብዙ እና ውስብስብ የሆኑ ችግሮቻቸውን በምክክር ለመፍታት ቆራጥ ርምጃ ወስደው የተነሡበት ወቅት ነው ብሏል።

መንግሥት የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን የሚያከናውነዉን ምክክር በገለልተኝነት እንዲያከናውን የጀመረውን ድጋፍ አጠናክሮ እንደሚቀጥል መግለጫው አረጋግጧል፡፡

የመንግሥት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት ያወጣው መግለጫ ሙሉ ቃል ቀጥሎ ቀርቧል፡-

“የነገዋ ኢትዮጵያችን በአስተማማኝ መሠረት ላይ እንድትቆም ወሳኝ በሆኑ ሀገራዊ ጉዳዮቿ ላይ እየመከረች ነው።”

ኢትዮጵያ እና ኢትዮጵያውያን የጋራ ዘርፈ ብዙ እና ውስብስብ የሆኑ ችግሮቻቸዉን በምክክር ለመፍታት ቆራጥ ርምጃ ወስደው የተነሡበት ወቅት ነው።

ሀገራችን በበርካታ ጉዳዮች በተቃርኖዎች ውስጥ ለረዥም ዘመናት ስትናጥ እና በአስከፊ ግጭቶች ውስጥ ስታልፍ ቆይታለች። በተለይም ለረዥም ዓመታት እጅግ መሠረታዊ በሆኑ ሀገራዊ ጉዳዮች ላይ በፖለቲካ እና በሐሳብ መሪዎች እንዲሁም በኅብረተሰቡ ክፍሎች መካከል ልዩነት እና አለመግባባቶች ኖረዋል። እነዚህን አለመግባባቶች በየዘመኑ እየፈታን የመጣንበት መንገድ ዘላቂ ትምምን በሚፈጥር መልኩ ስላልነበረ ከጦርነት እና ግጭት አዙሪት በዘላቂነት መንጭቀን እንዳንወጣ እንዳረገን እሙን ነው።

እነዚህ የግጭት መንገዶች እጅግ በርካታ ውድመት አስከትለዋል። ለረጅም ጊዜ ይዘን የመጣነው ልምምድ እና ዝንባሌ ታላላቅ ሕልሞቻችንን በጋራ እንዳናሳካ እንቅፋት ሆኖብን ቆይቷል። እነዚህ መንገዶች አንዱ የጀመረው ላይ እየገነባን የምንሄድ ሳይሆን ሁሌም ከዜሮ ጀማሪዎች እንድንሆን፣ በተቋማት እና በመሠረታዊ የሀገር ምሰሶዎች ላይ እምነት፣ የጋራ የሆነ ሀገራዊ የተስፋ ዕይታ እንዳይኖረን አድርገውን ቆይተዋል። እኛ ኢትዮጵያውያን በጋራ ባለመምከራችን ያያያዙን፣ ያጋመዱን የተለያዩ ጥብቅ እሴቶቻችንን ለሚሸረሽሩ አካላት ምቹ ሁኔታ ስንፈጥር ኖረናል።

ይህን አዙሪት በዘላቂነት ለመፍታት ልዩነቶቻችንን እና አለመግባባቶችን ላይ ሰፋፊ ሀገራዊ የሕዝብ ምክክሮችን አካታች በሆነ መንገድ በማካሄድ ሀገራዊ መግባባት መፍጠር አስፈላጊ በመሆኑ፤ የሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ተቋቁሞ በርካታ ሥራዎችን አከናውኗል። ኮሚሽኑ እጅግ መሠረታዊ በሆኑ ሀገራዊ ጉዳዮች ላይ አካታች ሀገራዊ ምክክሮችን በማካሄድ የተሻለ ሀገራዊ መግባባትን ለመገንባት፤ በሂደትም መተማመን ለማጎልበት ያለውን የማይተካ ፋይዳ በመገንዘብ ነጻ፣ ገለልተኛ እና አካታች እንዲሆን መንግሥት አስፈላጊውን ሕጋዊና መዋቅራዊ ድጋፍ አድርጓል።

በዚህም ላለፉት ሦስት ዓመታት ከሕጋዊ እና መዋቅራዊ ዝግጅቶች ጀምሮ በርካታ ሥራዎችን አከናውኗል። በዐሥራ አንዱ የሀገራችን ክልሎች እና በኹለቱ ከተማ አስተዳድሮች በርካታ ባለድርሻዎችን እና ተሳታፊዎችን ያሳተፉ ውይይቶችን አከናውኗል፤ በቀረዉ የትግራይ ክልልም ምክክሩን ለማካሄድ የቅድመ ዝግጅት ሥራዎችን እያከናወነ ይገኛል። ባለፉት ዐሥር ወራት ብቻ ከ200 ሺህ በላይ ሰዎች በጋራ ጉዳዮቻችን ላይ ተወያይተዋል፤ ተመካክረዋል።

አሁንም 14ኛዉ የፌዴራል ተቋማት እና ማኅበራት የምክክር እና አጀንዳ የማሰባሰብ መድረክም በአዲስ አበባ ተካሂዶ በስኬት ተጠናቋል። በመድረኩ ላይ እየተሳተፉ ያሉት ማኅበራት እና ተቋማት፣ ፖለቲካ ፓርቲዎች፣ ተጽዕኖ ፈጣሪና የማኅበረሰብ አንቂዎቸ፣ የዲሞክራሲ እና የሃይማኖት ተቋማት፣ የፀጥታና ደኅንነት አካላት፣ የሚዲያ ተቋማት እንዲሁም የመንግሥት ተቋማት ተወካዮች ናቸው። አጀንዳዎቹ በተለያዩ ዘርፎች ተደራጅተው የቀረቡ ሲሆን በቀጣይ በክልልም ሆነ በፌዴራል ደረጃ የተነሡ አጀንዳዎች ላይ ምክክር ይቀጥላል።

መንግሥት ኮሚሽኑ የሚያከናውነዉን ምክክር በገለልተኝነት እንዲያከናውን የጀመረውን ድጋፍ አጠናክሮ ይቀጥላል።

የመንግስት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት
ግንቦት 24 ቀን 2017 ዓ/ም

28/05/2025

የገንዘብ ሚኒስቴር መግለጫ
እ.ኤ.አ ሜይ 25/2025 ሪፖርተር ጋዜጣ “እያንዳንዱ ኢትዮጵያዊ ያለበት የውጭ ዕዳ መጠን ከ575 ዶላር መድረሱ ተነገረ" በሚል ርዕስ የኢትዮጵያ ኢኮኖሚክስ ማህበር ያወጣው ሪፖርት ገለጸ በማለት ዘገባ መታተሙ ይታወሳል።
ዘገባው ላይ ግድፈቶች ያሉት በመሆኑ እንዲሁም ትክክለኛውን አውድን ማሳወቅ አስፈላጊ በመሆኑ ይህንን መግለጫ ማውጣት አስፈላጊ ሆኗል።
ዘገባው ግንቦት 14 ቀን 2017 ዓ.ም ማኅበሩ ያወጣውን ሪፖርት በማጣቀስ ኢትዮጵያ እ.ኤ.አ እስከ 2023 ድረስ ያለባት የብድር መጠን 62.5 ቢሊዮን ዶላር መድረሱንና “እያንዳንዱ ኢትጵያዊ የተጠቀሰው መጠን የውጭ ብድር ዕዳ” እንዳለበት ይገልጻል። በዘገባው ኢትዮጵያ ያለባት የውጭና የሀገር ውስጥ የብድር መጠን ተለይቶ መቅረብ ሲገባው በተጠቀሰው ጊዜ የነበረው የውጭ ዕዳ መጠን 28.5 ቢሊዮን ዶላርን 62.5 ቢሊዮን ዶላር ብሎ ማቅረብ የተሳሳተ ነው።
እ.ኤ.አ እስከ 2024 መጨረሻ ድረስ ኢትዮጵያ ያለባት የውጭ የብድር መጠን የመንግሥት ልማት ድርጅቶችን ጨምሮ 31.6 ቢሊዮን የአሜሪካን ዶላር ነው፡፡
በተጨማሪም የሀገሪቱን የውጭ ብድር በተመለከተ አውዳዊ ማብራሪያ (contextual background) ለመስጠት ያህል፣ የኢትዮጵያ የውጭ ብድር ሙሉ ለሙሉ በሚባል ደረጃ የተጠራቀመ ውርስ ዕዳ (legacy debt) ሲሆን የዕዳ ጫና በዚህ ምክንያት የተባባሰ መሆኑ ይታወቃል። ላለፉት ሰባት ዓመታት ይህንን ውዝፍ ዕዳ ያስከተለውን የክፍያ ጫና ለመቀነስ በመንግስት በኩል የተደረጉ ወሳኝ ጥረቶችን መጥቀስ አስፈላጊ ነው።
1. መንግሥት ባለፉት በርካታ ዓመታት ምንም የውጭ የንግድ ብድር ያልወሰደ ሲሆን ለልማት ፕሮጀክቶች ማስፈጸሚያ የውጭ ብድር ሲወስድ የነበረው በአብዛኛው ከዓለም አቀፍ የልማት አጋሮችና ከመንግሥታት ከሚገኙ ብድሮች በመሆኑ የብድር ጫናን የማያስከትሉና ወለድ የማይታሰብባቸው በሌላ አገላለጽ በጣም ዝቅተኛ ወለድ እና ረዥም የእፎይታና የክፍያ ጊዜ ያላቸው ብድሮች (concessional loans) ናቸው፡፡ ለዚህም ማሳያ ከዓለም ባንክ ማለትም ከዓለም አቀፍ የልማት ማህበር (International Development Association) የሚወሰደው ብድር 0.75 በመቶ የአገልግሎት ክፍያ ውጭ ምንም ወለድ ክፍያ የሌለውና በረዥም የክፍያ ጊዜ ማለትም በ38 ዓመት የሚከፈል ነው። እነዚህን መሰል ብድሮች ከአጠቃላ የውጭ ብድር 42 በመቶ ድርሻ ያላቸውና የብድር ጫና የማያስከትሉ ናቸው።
2. መንግሥት የሀገሪቱን የዕዳ ክፍያ ጫና ለመቀነስ የተለያዩ የብድር ሽግሽግና ማቅለያ ስምምነቶችን ኃላፊነት በተሞላ መልኩ እያደረገ እንደሚገኝ ይታወቃል። ባለፉት ዓመታትም የተለያዩ የብድር ሽግሽጎች የተደረጉ ሲሆን ከ2023 ጀምሮ ደግሞ በG-20 Common Framework የዕዳ ሽግሽግ ተጠቃሚ በመሆን ከአበዳሪዎችና ጋር ስኬታም ድርድር በማድረግ የዕዳ ክፍያ ጫና እንዲቀንስ እየተሰራበት ይገኛል።
በተጨማሪም ጋዜጣው ያወጣው ትንተና አውዱን ያልጠበቀ እና የተሳሳተ አረዳድ የሚሰጥ እንደሆነ ለመረዳት ተችሏል። በዓለም አቀፍ ደረጃ የአንድ አገር የብድር ጫና መለኪያዎች የውጭ ብድር መጠን ከጠቅላላ የሀገር ውስጥ ምርት ጥመርታ፣ የውጭ ብድር መጠን ከወጭ ንግድ ገቢ ጥመርታ፣ ዓመታዊ የውጭ ብድር ክፍያ ከወጭ ንግድ ገቢ ጥመርታ እና ዓመታዊ የውጭ ብድር ክፍያ ከዓመታዊ የመንግሥት ገቢ ጥመርታ ናቸው፡፡ የአገሪቱን በእነዚህ መለኪያዎች መሠረት ያለችበትን የዕዳ ሁኔታ ለማሻሻል ከላይ እንደተገለጸው ከአበዳሪዎች ጋር የተሳካ ድርድር እየተደረገ በመሆኑ በቅርብ ዓመታት ውስጥ የአገሪቱ የብድር ሁኔታ ወደ ተሻለ ሁኔታ የሚሸጋገር ይሆናል፡፡
የነፍስ ወከፍ ዕዳ እንደ መመዘኛ ሪፖርቱ እንደሚጠቅሰው የፐብሊክ ፋይናንስ አቅምን ለመመዘን የማያስችል፣ የዕዳ ጫናን የማያመላክትና ዘገባውን ስሜት ቀስቃሽ ከማድረግ ውጪ አግባብነት የሌለው ነው።
የሀገር ውስጥ ብድር ክምችትን በተመለከት እ.ኤ.አ በ2024 መጨረሻ የሀገር ውስጥ ብድር 2.3 ትሪሊየን ብር ነው።
የሀገሪቱን ብድር በሚመለከት የሚሰራጩ መረጃዎች ለህብረትሰቡ ትክክለኛ ግንዛቤ የሚያስጨብጡ፣ የገበያውን እንቅስቃሴና ምላሽ እንዲዛባ በማያደርጉ መልኩ መቅረብ እንዳለባቸው እሙን ነው።
ስለሆነም የተለያዩ መረጃዎችና መሰል ትንተናዎች ሲዘጋጁ እንደአግባብነቱ የገንዘብ ሚኒስቴር ባለሙያዎችን ማማከር፣ ኦፊሻል መረጃዎችን መጠየቅና ሃሳብን መቀብል እንደአማራጭ እንዲወሰዱ እንመክራለን።

Send a message to learn more

ከኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ የተሰጠ ወቅታዊ መረጃ ሰሞኑን የጤና ባለሙያዎች ያነሱትን የመብት ጥያቄ ሽፋን በማድረግ በሀገራችን ትርምስ እንዲፈጠር ከሚሠሩ ኃይሎች ጋር በማበር ሕገ ወጥ የሥራ ማቆ...
23/05/2025

ከኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ የተሰጠ ወቅታዊ መረጃ

ሰሞኑን የጤና ባለሙያዎች ያነሱትን የመብት ጥያቄ ሽፋን በማድረግ በሀገራችን ትርምስ እንዲፈጠር ከሚሠሩ ኃይሎች ጋር በማበር ሕገ ወጥ የሥራ ማቆም አድማ በማድረግ፣ በጤና ዘርፉ ላይ ሁከት በመፍጠር እና የታካሚዎችን ህይወት አደጋ ላይ በመጣል የተጠረጠሩ 47 የጤና ባለሙያዎችን የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ በቁጥጥር ሥር አውሎ ምርመራ ማጣራት ጀምሯል፡፡

እነዚህ ተጠርጣሪዎች የጤና ባለሙያዎች ያነሱትን የደመወዝ እና የጥቅማ ጥቅም ጥያቄ እንደሽፋን በመጠቀም ሕገ-ወጥ የሥራ ማቆም አድማ በማድረግ፤ ሌሎችም ሥራ እንዲያቆሙ ለአድማ በማነሳሰት፣ የታካሚዎች ሕይወት ለሞትና ለአደጋ እንዲጋለጥ በማድረግ ሁከትና ብጥብጥ በመፍጠር የተጠረጠሩ ናቸዉ፡፡

ተጠርጣሪዎቹ በተለያዩ የጤና ተቋማት የአድማ መረቦችን በመዘርጋት፤ የጤና ባለሙያ ያልሆኑ አካለትን ነጭ ጋዋን በማስለበስ የሆስፒታል ቅጥር ግቢ ውስጥ ገብተዉ ሁከት እንዲፈጥሩ በማድረግ፣ ያልተገባ ወሬ በመንዛት እና በተለያየ መንገድ ሰላማዊ የሕክምና ሂደትን በማደናቀፍ የሕሙማንና የጤና እርዳታ የሚያስፈልጋቸውን ሰዎች ሕይወት አደጋ ላይ እንዲወድቅ በማድረግ፣ በመንግሥት የሕክምና አገልግሎት እና ትምህርት በሚሰጥባቸው ተቋማት ውስጥ ሰላማዊ የመማር ማስተማር ሂደት እንዲስተጓጎል አድርገዋል፡፡እንዲሁም ሙያቸውን አክብረው በሥራ ላይ በተገኙ ባልደረቦቻቸው ላይ ዛቻ እና ማስፈራራት ከማድረስ ባለፈ ሁከት እንዲፈጠር ሙከራዎችን አድርገዋል ያላቸውን 47 ተጠርጣሪዎች በመረጃና በማስረጃ በመለየት በቁጥጥር ሥር አውሎ ምርመራ እያካሄደ እንደሚገኝ የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ አስታውቋል።

የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ የጤና ባለሙያዎቹ የሙያው ሥነ-ምግባርና ሕግ በማይፈቅደው ሁኔታ የዜጎችን ሕይወት ለሞትና ለአደጋ በማጋለጥ ሥራ ማቆም፣ ሌሎችም ሥራ እንዲያቆሙ ማነሳሳት እና ማስፈራራት፣ የወንጀል ተግባር መሆኑን እየገለፀ ሌሎችም ከዚህ ተግባር እንዲቆጠቡ ያሳስባል። በዚህ አጋጠሚ ሕዝባቸውን እና ሕግ አክብረው አገልግሎት እየሰጡ ላሉ የጤና ባለሙያዎች ፖሊስ አስፈላጊውን ጥበቃ እንደሚያደርግ እያረጋገጠ፤ ከዚህ ውጭ ሁከትና ብጥብጥን ለማስፋፋት በሚንቀሳቀሱ አካላት ላይ ፖሊስ እየወሰደ ያለውን ሕጋዊ እርምጃ አጠናክሮ እንደሚቀጥል ያሳውቃል።

የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ
ግንቦት 15 ቀን 2017 ዓ.ም
አዲስ አበባ፣

መንግሥት ሀገራዊ ተቋማትን ለማጠናከር ያለው ቁርጠኝነት የጸና ነው።********************************************ከዚህ በፊት አንዳንድ ወገኖች በፈጠሩት ችግር የተነሣ ...
03/05/2025

መንግሥት ሀገራዊ ተቋማትን ለማጠናከር ያለው ቁርጠኝነት የጸና ነው።
********************************************
ከዚህ በፊት አንዳንድ ወገኖች በፈጠሩት ችግር የተነሣ በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ሲኖዶስ ጉባኤ ለመሳተፍ ላልቻሉ ሦስት አባቶች ሁኔታዎች መመቻቸታቸውን መንግሥት ያሳውቃል።
ሀገራዊ ተቋማት ለሀገረ መንግሥት ግንባታ ያላቸውን የላቀ ሚና መንግሥት ስለሚረዳ በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን አባቶች መካከል የተፈጠረው መለያየት እንዲፈታ መንግሥት የመሪነቱን ሚና መጫወቱ ይታወሳል።
የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን በሀገር ግንባታ የነበራትንና የሚኖራትን ሚና በመገንዘብ መንግሥት አስፈላጊውን ድጋፍ ሲሰጥ ቆይቷል። በዚህ አቋሙም ይቀጥላል።
ይሄንን ያልተረዱ አንዳንድ አካላት ችግሮችን ፈጥረው የነበረ ቢሆንም እንኳን፣ መንግሥት ለቤተ ክርስቲያንዋ እና ለምእመንዋ ሲል በሆደ ሰፊነት ለማለፍ ወስኗል። ይሄም ከግለሰቦች ችግር ይልቅ የቤተ ክርስቲያንዋን አስተዋጽዖ ስለሚመለከት ነው።
መንግሥት ችግሩ እንዲፈታ ሲኖዶሱ ያቀረበውን ጥያቄ ተቀብሏል። በሂደቱም ተቀራርቦ መነጋገር ከሁሉም የተሻለ የመፍትሔ መንገድ መሆኑ ታይቷል።
ስለዚህም ሲኖዶሱ መንግሥት ነገሩን በሆደ ሰፊነት እንዲመለከተው በጠየቀው መሠረት፣ ብፁዕ አቡነ ጴጥሮስ (ዶ/ር)፣ ብፁዕ አቡነ ቴዎፍሎስ (ዶ/ር) እና ብፁዕ አቡነ ያዕቆብ በሲኖዶሱ ስብሰባ ለመገኘት እንዲችሉ ከመንግሥት የሚጠበቀውን ሁሉ እንደሚያደርግ ይገልጣል።
የመንግስት ኮሚኒኬሽን አገልግሎት
ሚያዝያ 24 ቀን 2017 ዓ/ም

02/05/2025
“ፈጠራና ፍጥነት የታከለበት የክህሎት ግንባታ ቀጣይነት ላለው የሥራ እድል ፈጠራና ዋስትና ወሳኝ ነው።”እንኳን ለዓለም የሠራተኞች ቀን በሰላም አደረሳችሁ!ሀገራችን “በአምራች ኢንዱስትሪዎችና ...
01/05/2025

“ፈጠራና ፍጥነት የታከለበት የክህሎት ግንባታ ቀጣይነት ላለው የሥራ እድል ፈጠራና ዋስትና ወሳኝ ነው።”

እንኳን ለዓለም የሠራተኞች ቀን በሰላም አደረሳችሁ!

ሀገራችን “በአምራች ኢንዱስትሪዎችና አገልግሎት ሰጪ ተቋማት ምቹ የሥራ ሁኔታ ለማህበራዊ ፍትህ” በሚል መሪ ቃል በዓለም አቀፍ ደረጃ ለ136ኛ በሀገራችን ደግሞ ለ50ኛ ጊዜ የሚከበረውን የዓለም አቀፍ ሠራተኞች በዓል እያከበረች ትገኛለች።

ኢትዮጵያ የዓለም የሠራተኞች ቀንን የምታከብረው የኢንዱስትሪ ሰላምን፣ የሥራ ላይ ደኅንነትንና የሠራተኞችን ክሕሎት ማሳደግን ልዩ ትኩረት በመስጠት ነው፡፡ ወደ ብልጽግና የሚደረገዉ ጉዞ ያለ ኢንዱስትሪ ሰላም፣ ያለ ሠራተኞች የሥራ ላይ ደኅንነት እና ዘመኑ የሚጠይቀዉን ክሕሎት ለሠራተኛዉ ሳያስታጥቁ የሚታሰብ አይደለም፡፡ በመኾኑም በዓሉን ስናከብር ሠራተኞች፣ የሠራተኛ ማኅበራት እና የክህሎት ሥልጠና ተቋማት ለኢንዱስትሪ እና አገራዊ ሰላም እያበረከቱ ያለውን አስተዋጽኦ ዕውቅና በመስጠት፣ አሠሪዎች ደግሞ ለሠራተኞች የሚፈጥሩትን ምቹ የሥራ አካባቢ እና የሥራ ላይ ደኅንነት በማበረታታት ነው፡፡

ኢትዮጵያ ለሁለንተናዊ ብልጽግና ለምታደርገዉ ጉዞ በምሰሶነት የተለዩት የምጣኔ ሀብት ዘርፎች ማለትም ግብርና፣ ማኑፋክቸሪንግ፣ ማዕድን፣ ቱሪዝምና ዲጂታል ኢኮኖሚ የሠራተኞችን ሁለንተናዊ ክህሎትንና ጥረት የሚጠይቁ ናቸው፡፡ ይህንን ታሳቢ በማድረግም መንግሥት ኢንዱስትሪዎች በብዛት የሚፈልጓቸዉን በመካከለኛ ደረጃ የሠለጠኑ ሠራተኞች ለማቅረብ ሰፋፊ የክሕሎት ሥልጠናዎችን በቴክኒክና ሙያ ተቋማት እና በተለያዩ አማራጮች እያቀረበ ይገኛል፡፡ የአምስት ሚሊዮን ኮደርስ ኢኒሼቲቭ ለዚህ አንዱ አብነት ተደርጎ የሚወሰድ ነው፡፡ መርሐ ግብሩ ሠራተኞች ለአሁኑና ለቀጣዩ ዲጂታላይዝድ ዓለም ብቁ የሚያደርጋቸውን አቅም የሚገነባ ሲሆን ከዓለም እውቅ የኦንላይን ሥልጠና ማዕከል በነጻ የሚሰጡ አራት የሥልጠና መስኮችን የሚያካትት ነው።

የሥራ ፈጠራንና ለሥራ ፈጠራ ምቹ የሆነ ምህዳር መፍጠር የመንግስት ዋነኛ ትኩረቶች መካከል ሲሆን ከዚህ አንጻር በዚህ ዓመት በሁሉም የኢኮኖሚ መስኮች ከሦስት ሚሊዮን በላይ ስራዎች ተፈጥረዋል። ዜጎች መብታቸው ተጠብቆ በውጭ ሃገራት ሥራዎች እንዲሰማሩ ለማድረግ መንግስት ከመዳረሻ ሃገራት መንግስታት ጋር በደረሰው ስምምነት መሰረት ከ340ሺህ በላይ የውጭ ሃገር የሥራ እድሎች ተፈጥረዋል። ከዚህም በተጨማሪ ቴክኖሎጂ የፈጠረውን አስቻይነት ሚና በማስፋት ከ45ሺህ በላይ የርቀት ስራዎች (remote jobs) ተፈጥረዋል። እንዲህ አይነት አዳዲስ የሥራ ፈጠራ መስኮች እንዲስፋፉ ዜጎች በመንግስት የሚመቻቹ እንደ የአምስት ሚሊዮን ኮደርስ አይነት የሥልጠና እድሎችን እና ሌሎች በግል ጥረት የሚገኙ የአቅም መገንቢያ መንገዶችን በመጠቀም ራሳቸውን ብቁ ማድረግ ይጠበቃል።

ይህን ለማሳካት በተለያየ ደረጃ ያሉ በርካታ የመንግስት ተቋማት ከፍተኛ ጥረትን የጠየቀ ቢሆንም ካለው ፍላጎት አንጻር ተጨማሪ ስራዎች እንደሚጠበቁ መንግስት ይገነዘባል። ለዚህም ፈጠራና ፍጥነት የታከለባቸው የፖሊሲና የተግባር ምላሾች ከሁሉም ባለድርሻ አካላት ይጠበቃል። በዚህ አጋጣሚ የሲቪል ማህበረሰብ ተቋማት፣ የትምህርትና ስልጠና ተቋማት፣ የግሉ ዘርፍ፣ የሠራተኛ ማህበራት እና ሌሎችም ባለድርሻዎች የድርሻቸውን እንዲወጡ ጥሪውን ያስተላልፋል።

በድጋሜ እንኳን ለሠራተኞች ቀን በሰላም አደረሳችሁ!

30/04/2025

Bole bulbula park

“በስኬት ማማ ላይ የደረስን መስሎ በመሀል ዘመን ወጥመድ እንዳንያዝ መትጋት ያስፈልጋል”***********************ከብልፅግና ፓርቲ ሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ የተሰጠ መግለጫየብልፅግና ፓር...
27/04/2025

“በስኬት ማማ ላይ የደረስን መስሎ በመሀል ዘመን ወጥመድ እንዳንያዝ መትጋት ያስፈልጋል”
***********************
ከብልፅግና ፓርቲ ሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ የተሰጠ መግለጫ
የብልፅግና ፓርቲ ሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ከሚያዝያ 17 እስከ 18/ 2017 ዓም መደበኛ ስብሰባውን በአዲስ አበባ አካሂዷል፡፡ በዚህ ስብሰባም የኢትዮጵያን ፖለቲካዊ፣ ኢኮኖሚያዊ፣ ማኅበራዊና ዲፕሎማሲያዊ ጉዳዮች በዝርዝር ተመልክቷል፡፡
ኢትዮጵያ በ2018 ከተስፋ ወደሚጨበጥ ብርሃን ለመሻገር፤ በ2023 የአፍሪካ የብልጽግና ተምሳሌት ለመሆን፤ በ2040 ደግሞ ዓለም አቀፍ የብልጽግና አርአያ ለመሆን ያስቀመጠችው ርእይ እንደሚሳካ የሚያረጋግጡ የስኬት ፍንጮች መታየታቸውን የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴው አረጋግጧል፡፡ እነዚህ የስኬት ፍንጮች የያዝነው ፍኖተ ብልጽግና ትክክል መሆኑን አመላክተውናል፡፡
ከብልፅግና ፓርቲ ሁለተኛ መደበኛ ጉባኤ በኋላ አያሌ ፖለቲካዊና ዲፕሎማሲያዊ ስኬቶች ተመዝግበዋል፡፡ ከተለያዩ ተፎካካሪ የፖለቲካ ፓርቲዎች ጋር በየደረጃው የሚደረገው ምክክርና ትብብር በኢትዮጵያ የፖለቲካ ታሪክ ወደ አዲስ ምእራፍ ገብቷል፡፡ ከአንድ ክልል በስተቀር፣ ለሀገራዊ ምክክር አጀንዳ የማሰባሰብ ምእራፍ በሁሉም ክልሎች ተጠናቅቋል፡፡
በሀገሪቱ የጸጥታ ችግር በነበረባቸው አንዳንድ አካባቢዎችም ሰላም እየሰፈነ ነው፡፡ መንግስት በተደጋጋሚ ያቀረበውን የሰላም ጥሪ ተከትሎ እጅ የሚሰጡና ወደ ሰላም ድርድር የሚመጡ ታጣቂዎች ከዕለት ወደ ዕለት ቁጥራቸው እየጨመረ ይገኛል፡፡ የመንግሥት ሕግ የማስከበርና የማድረግ ዐቅም እየጎለበተ መጥቷል፡፡
ከሶማሊያ ጋር ተፈጥሮ የነበረው ውዝግብ በዲፕሎማሲያዊ መንገድ ተፈትቷል፡፡ ኢትዮጵያ የባሕር በር እንዲኖራት የተያዘው አቋም ዓለም አቀፋዊ ተቀባይነቱ እየጨመረ ነው፡፡ ኢትዮጵያ ከዓለም አቀፍ የፋይናንስ ተቋማት ጋር ያላት ግንኙነት ከመሻሻሉም በላይ የሚደረግላት ድጋፍ እያደገ ነው፡፡ በዓለም አቀፍ መድረክ የኢትዮጵያ ተፈላጊነት ጨምሯል፡፡ የዲፕሎማሲ ግንኙነቷም በሁሉም አቅጣጫ ከፍ ብሏል፡፡
እስከአሁን ያለው አፈፃፀም የሚያሳየው በያዝነው አመት አጠቃላይ ኢኮኖሚው በታቀደው መሠረት በ8.4 በመቶ የሚያድግ መሆኑን የሥራ አስፈጻሚው ገምግሟል፡፡ በዘርፍ ደረጃ ደግሞ ግብርና በ6.1 በመቶ፣ ኢንዱስትሪ በ12.8 በመቶ፣ ማኑፋክቸሪንግ በ12.0 በመቶ፣ ኮንስትራክሽን በ12.3 በመቶ፣ አገልግሎት ደግሞ በ7.1 በመቶ የሚያድጉ መሆናቸው ተገምግሟል፡፡ ያለፉት 9 ወራት ጠቅላላ የመንግሥት ገቢ ከአምናው ተመሳሳይ ወቅት አንጻር የ134 በመቶ ብልጫ አሳይቷል፡፡ የውጭ ብድር ከጠቅላላ የሀገር ውስጥ ምርት ያለው ድርሻ ወደ 13.7 በመቶ ወርዷል፡፡
ወደ ውጭ ገበያ የሚቀርቡት ስድስት ዋና ዋና ምርቶች፣ ካለፈው ዓመት ጋር ሲነጻጸሩ ከ82 በመቶ እስከ 386 በመቶ ጭማሪ አሳይተዋል፡፡ በስንዴ፣ በሩዝ፣ በቡና፣ በሻሂ ቅጠል እና በፍራፍሬ ምርቶች በአፍሪካ ቀዳሚ ሆኖ ለመውጣት እየተደረገ ያለው ትግል ፍሬ እያፈራ መሆኑን አይተናል፡፡
ውድ የብልፅግና አመራሮች፣ የብልፅግና አባላትና መላው ሕዝባችን፣
የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያው ዝቅተኛ ኑሮ በሚኖሩ ወገኖች ላይ ጫና እንዳያሳድር አስፈላጊ የሆኑና የታቀዱ የድጋፍ መርሐ ግብሮች መከናወናቸውንም የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴው መርምሯል፡፡
ለማዳበሪያ 62 ቢልዮን ብር፣ ለሴፍቲኔት 41.2 ቢልዮን ብር፣ ለነዳጅ 60 ቢልዮን ብር፣ ለመድኃኒት 3.5 ቢልዮን ብር፣ ለምግብ ዘይት 6.1 ቢልዮን ብር፣ እንዲሁም ለደመወዝ 38.4 ቢልዮን ብር ድጎማ ተደርጓል፡፡ ባለፉት 9 ወራት ብቻ 344,790 የውጭ ሀገር ሕጋዊ የሥራ ዕድሎች እና ከ3 ሚልዮን በላይ የሀገር ውስጥ የሥራ ዕድሎች ተፈጥረዋል፡፡ የርቀት የሥራ ዕድሎች ቁጥርም እየጨመረ መምጣቱ ታይቷል፡፡
የመንግሥት የልማት ተቋማትን በአዲስ አስተሳሰብና በአዲስ መንገድ መልሶ ለማደራጀትና ለመምራት መቻሉ፣ እያስገኘው ያለው ውጤት ለሌሎች አርአያ የሚሆን እንደሆነ የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴው ገምግሟል፡፡ የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ሆልዲንግስ አሁን ያለው ጠቅላላ ገቢ 1.5 ትሪልዮን መድረሱ ታይቷል፡፡
ከባለፈው ዓመት የ9 ወራት አፈጻጸም አንጻር የዘንድሮ ገቢው የ86 በመቶ ጭማሬ ማሳየቱም ተረጋግጧል፡፡ ይሄም መንግሥት የሀገርን ሀብት ለማወቅ፣ ዐውቆም በሚገባ ለማስተዳደር፣ አስተዳድሮም ወረት ለማከማቸት የተከተለው መርሕ ትክክል መሆኑን አረጋግጧል፡፡
የውጭ ምንዛሬ ክምችት ዕድገት ከባለፈው ዓመት ተመሳሳይ 9 ወራት ጋር ሲነጻጸር የ203.99 በመቶ ዕድገት አሳይቷል፡፡ የባንኮች ተቀማጭ ገንዘብ ከ3 ትሪልየን በላይ ተሻግሯል፡፡ የ9 ወራት የወጪ ንግድ አፈጻጸም ከ5 ቢልዮን ዶላር በላይ ሲሆን፣ ይሄም ካለፈው ዓመት ጋር ሲነጻጸር የ150.39 በመቶ ዕድገት አምጥቷል፡፡ ባለፉት ስምንት ወራት 473.9 ቢልዮን ብር ብድር ከንግድ ባንኮች ተለቅቋል፡፡ ይሄም ካለፈው ዓመት ተመሳሳይ ጊዜ አንጻር በ61.9 በመቶ ከፍ ይላል፡፡ ከዚህ ብድር ውስጥም 76.6 በመቶ ለግሉ ዘርፍ የተሰጠ ነው፡፡ ለግሉ ዘርፍ የበለጠ ብድር መሰጠቱ፣ የግሉ ዘርፍ በኢኮኖሚው ተገቢውን ሚና እንዲጫወት ያስቀመጥነው ፖሊሲ በተግባር እየተገለጠ መሆኑን አመላካች ነው፡፡
ዲጂታል ኢትዮጵያ 2030ን ለማሳካት የጀመርናቸው ሁሉን አቀፍ ጥረቶች ፍሬያቸው እየጎመራ ነው፡፡ የኢንተርኔት ተጠቃሚዎች 50.2 ሚልዮን፣ የሞባይል ተጠቃሚዎችም 86.6 ሚልዮን ደርሰዋል፡፡ የቴሌ ብር ደንበኞችም ከ52.56 ሚሊዮን በላይ ናቸው፡፡ ዲጂታል ፋይናንስ፣ የኅብረተሰቡን ፍትሐዊ ተጠቃሚነት ከማረጋገጥ ባለፈ ለኢኮኖሚው መሣለጥ ጉልህ ድርሻ እያበረከተ ነው፡፡ ባለፉት 9 ወራት በዲጂታል መንገዶች 7.73 ቢልዮን ብር ተቆጥቧል፡፡ 26.77 ቢልዮን ብር በዲጂታል በኩል ብድር ተሰጠ ሲሆን፣ የ12.51 ትሪሊዮን ብር ግብይት ደግሞ በዚሁ መንገድ ተከናውኗል፡፡
ዋና ዋና ፕሮጀክቶችን በጊዜና በተገቢ ደረጃ ለማጠናቀቅ የተሰጠው አቅጣጫ ብዙዎችን ለፍጻሜ እያበቃቸው ነው፡፡ የሕዳሴ ግድብ ግንባታ አፈጻጸም 98.66 በመቶ ደርሷል፡፡ የኮይሻ፣ አይሻና አሰላ የኃይል ማመንጫዎች በተያዘላቸው ዕቅድ መሠረት እየተጓዙ መሆናቸው ተገምግሟል፡፡ የቢሾፍቱ ዓለም አቀፍ የአውሮፕላን ማረፊያ ግንባታም የኢትዮጵያን ነገ ታሳቢ ባደረገ መልኩ የቅድመ ዝግጅት ምእራፉ እየተከናወነ ይገኛል፡፡ የኮሪደር ልማት በአዲስ አበባ በ8 ኮሪደሮች እና በመላው ኢትዮጵያ በ65 ከተሞች እየተከናወነ መሆኑ ተስፋ ሰጪ ነው፡፡ ብዙዎቹ የመስኖ ግድቦች ወደ ፍጻሜያቸው እየደረሱ ናቸው፡፡ ከዘጠኙ የመስኖ ግድቦች ውስጥ ስድስቱ አፈጻጸማቸው ከ75 በመቶ በላይ ደርሷል፡፡
“ትምህርት ለትውልድ” በሚል መሪ ቃል ከ82 ቢልዮን ብር በላይ ድጋፍ የተሰበሰበ ሲሆን፣ በአጠቃላይ 6815 ትምህርት ቤቶች በመላ ሀገሪቱ ተገንብተዋል፡፡ የነባር ትምህርት ቤቶችን ዐቅም ለማሻሻል እና በግጭት የተጎዱትን ለመጠገን የተደረገው ጥረት በትውልድ ላይ ለሚሠራው ሥራ መሠረት የሚጥል መሆኑ ታይቷል፡፡ የወላድ እናቶችን እና የጨቅላ ሕጻናትን ሞት በመቀነስ ረገድ የተሻለ ውጤት መመዝገቡም ታይቷል፡፡
በኢትዮጵያ የቱሪዝም መዳረሻዎችና የስፖርት ሥፍራዎች በቁጥርም፣ በዓይነትም እያደጉ መጥተዋል፡፡ በተለያዩ ከተሞች በመገንባት ላይ የሚገኙ ዓለም አቀፍ ስታዲየሞች በመጠናቀቂያ ምእራፍ ላይ ናቸው፡፡ ይሄም ኢትዮጵያ ታላላቅ አፍሪካዊ ጨዋታዎችን ለማስተናገድ ለያዘችው ዕቅድ መሳካት ወሳኝ ነው፡፡ ከዚህ በተጨማሪ፣ ኢትዮጵያ ዓለም አቀፍ ኩነቶችን ለማስተናገድ ያላት መሠረተ ልማት እና የመስተንግዶ ዐቅም እያደገ ይገኛል፡፡
ባለፉት ዘጠኝ ወራት ከ66 በላይ ዓለም አቀፍ ኩነቶች በሀገራችን ተደርገዋል፡፡ በቱሪስት ፍሰት ጭማሪ ከአፍሪካ ቀዳሚ ሀገር በመሆን ላይ ነን፡፡ የኢትዮጵያን ተፈጥሯዊ፣ ባህላዊ፣ ታሪካዊ እና ሃይማኖታዊ ጸጋዎች አውጥተን ማሳየት ከቻልን፣ በቱሪዝም መስክ የቀዳሚነት ሚና መጫወት እንደምንችል ጅምሮቹ ያሳያሉ፡፡
ባለፉት ዘጠኝ ወራት በተከናወኑ ተግባራት አምራችነትን በማበረታታት፣ ሥራ ያቆሙ ኢንዱስትሪዎችን ወደ ሥራ በማስገባት፣ ገቢ ምርቶችን በሀገር ውስጥ ምርት በመተካት፣ የሀገር ውስጥ ገቢን በማሰባሰብ፣ ወጪ ምርቶችን በብዛት በማምረት፣ ከአንድ ጊዜ በላይ መሬትን ደጋግሞ በማረስ፣ ሪፎርሞችን በየዘርፋቸው አግባብ በመተግበር፣ የተመዘገቡ ውጤቶች ተስፋ ሰጪ ናቸው፡፡
በዚህ እንቅስቃሴ የተነሣ ራስን የመቻል ተነሣሽነት ጨምሯል፡፡ ዘጠኝ ክልሎች ሰብአዊ ድጋፍን በራሳቸው ዐቅም ከመሸፈናቸውም በላይ የሰብአዊ ድጋፍ ፈላጊዎች ቁጥርም ባለፉት አምስት ዓመታት በሀገር አቀፍ ደረጃ በ86 በመቶ ቀንሷል፡፡ ሂደቱ ተረጂነትን መጸየፍና አምራችነትን ባህል ማድረግ በሀገራችን ሥር እየያዘ መሆኑን አመላካች ነው፡፡
ውድ የብልፅግና አመራሮች፣ የብልፅግና አባላትና መላው ሕዝባችን፣
እነዚህ ስኬቶች የጉዟችን መጀመሪያ እንጂ መጨረሻ አይደሉም፡፡ ማበረታቻዎች እንጂ ፍጻሜዎች አይደሉም፡፡ ስኬቶቹ መንገዳችን ትክክል መሆኑን የሚያሳዩ የተራራ ላይ መብራቶች ናቸው፡፡ ለበለጠ ሥራ የሚያነሣሡ፣ ለበለጠ ወኔ የሚቀሰቅሱ፣ የጠለቀ ቁጭት የሚቆሰቁሱ ናቸው፡፡
በሠራናቸው የፖለቲካ፣ የኢኮኖሚና የጸጥታ ተቋማት ሪፎርሞች ሀገራችን ከነበረባት የህልውና አደጋ ወጥታ ወደ አስተማማኝ ህልውና እየተሻገረች ነው። ሪፎርሙ የነበረውን የህልውና ሥጋት መቀልበስ ብቻ ሳይሆን፣ የሀገርን ህልውና ለመጠበቅ የሚያስችል አስተማማኝ ዐቅም ፈጥሯል፡፡ ይሄም በተቃራኒው መንግሥትን በኃይል ለመጣል የነበረውን ፍላጎት አምክኗል፡፡
በተደረጉ ሀገር በቀል ማሻሻያዎች፣ በተፈጠረው ዐቅም እና ዝግጁነት ኢኮኖሚያችን ወደ ተሟላ የኢኮኖሚ ማሻሻያ ትግበራ ገብቷል፡፡ ይሄ ደግሞ የኢኮኖሚ ሂደታችንን እና የብልጽግና ጉዟችንን የሚቀይር አዲስ ምእራፍ ፈጥሯል።
የሕዳሴ ግድብ መጠናቀቅ እና የባሕር በር ጉዳይ በቀጣናችን የአጀንዳ የበላይነት እንድንፈጥር አስችሎናል፡፡ በዚህም የተነሣ ሀገራችንን ከተከላካይነት ወደ ተጽዕኖ ፈጣሪነት አሸጋግሯታል።
በመሆኑም ለውጡ ከመተከል ወደ ማንሠራራት ተራምዷል ማለት ይቻላል።
መንግሥት የፈጠረው ዐቅም፣ የፀረ ለውጥ ኃይሉ መዳከም እና ዓለም አቀፍ ለውጡ የኢትዮጵያን ሪፎርም ለማሳካት የተሻለ ዕድል የሚሰጥ ነው፡፡ መንግሥትን በኃይል ለመጣልና ፍላጎትን በጉልበት ለማሳካት የሚደረገው መፍጨርጨር ውጤት እንደማያስገኝ ሀገራዊ እውነት እየሆነ ነው፡፡ በየጊዜው ወደ ሰላም የሚመጡት ታጣቂዎች ቁጥር መጨመርም ይሄንን ያመለክታል፡፡
በአንድ በኩል እነዚህን ስኬቶች ይበልጥ ማስፋትና ማጽናት አለብን፡፡ በሌላ በኩል ደግሞ ራሳችንን ከመሐል ዘመን ወጥመድ መጠበቅ ይገባናል፡፡ የመሐል ዘመን ወጥመድ፣ አንድ ሀገር ከፖለቲካ ሥርዓት ሽግግር በመውጣት፣ ወደ ቀጣዩ የማጽናት ምእራፍ ከመድረሷ በፊት፣ በሚገኘው የመሐል ዘመን፣ በስኬቶች ረክቶና ተዘናግቶ የመቀመጥ አባዜ ነው፡፡ ከፖለቲካ ሽግግር በመውጣትና የጸና ሥርዓትን በመትከል መካከል የሚገኝ ፈታኝ ዘመን ነው፡፡
የሀገራችን ኢኮኖሚ በማደግ ላይ ያለ እንጂ በሚፈለገው መጠን ያደገ አይደለም፡፡ በግብርና፣ በኢንዱስትሪ፣ በከተማ ልማት፣ በወጪ ምርቶች፣ በማዕድን፣ በአገልግሎት ዘርፍ፣ በዲጂታል ኢትዮጵያ፣ ወዘተ. ያየናቸው ለውጦች ብንሠራ የት እንደምንደርስ አመላካቾች ናቸው፡፡ ከግባችን መድረሳችንን ግን አያበሥሩም፡፡ የፖለቲካ ባህላችን እየተለወጠ ነው፤ ነገር ግን የሠለጠነ የፖለቲካ ባህል ገና አልገነባንም፡፡ የጸጥታ ተቋሞቻችን እየዘመኑና እየደረጁ ናቸው፤ ይሁን እንጂ በኢትዮጵያ ልክ ገና አልደረሱም፡፡ የፖለቲካ ፍላጎትን በኃይል የማስፈጸም አካሄድ ፋሽኑ እያለፈበት መጥቷል፡፡ ነገር ግን ገና ከፖለቲካና ከማኅበራዊ ባህላችን ተፍቆ አልጠፋም፡፡ የሲቪል ሰርቪስ ሪፎርም ገና በጅምር ላይ ነው፡፡ ዕዳችን ቢቃለልም ገና ከጫንቃችን ፈጽሞ አልወረደም፡፡ የዋጋ ግሽበትን ብንቋቋመውም፣ የኑሮ ውድነትን ግን በተገቢው መንገድ ገና አላቃለልነውም፡፡
በመሆኑም ከስኬት ማማ ላይ የደረስን መስሎን፣ በመሐል ዘመን ወጥመድ እንዳንያዝ አመራሮችና አባላት ነቅተው እንዲታገሉ፣ የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴው በአጽንዖት ያሳስባል፡፡
የመሐል ዘመን ወጥመድ በዋናነት የሚከሠተው በውጤት በመዘናጋት፣ ችግርን በመላመድ፣ ሀገራዊ ዕይታን ትቶ በጎጥ ውስጥ በማደር እና የሕዝብን ችግሮች በጊዜያቸውና በልካቸው ባለመፍታት ነው፡፡ በመሆኑም እነዚህ ችግሮች የመሐል ዘመን ወጥመድን እንዳያመጡብን በአመራሩና በአባላቱ ዘንድ ትግል ሊደረግባቸው ይገባል ፡፡
ውድ የብልፅግና አመራሮች፣ የብልፅግና አባላትና መላው ሕዝባችን፣
የተዛባ ትርክት እንዳይፈጠር የብሔራዊ ዐርበኝነት ትርክትን በሚገባ ማሥረጽ ይጠበቅብናል፡፡ የሕዝብን ጥያቄዎች በየደረጃው መፍታት አለብን፡፡ ምርትና ምርታማነትን ከፍ በማድረግ የኑሮ ውድነትን የሚያቃልሉ ሥራዎችን መሥራት ይጠበቅብናል፡፡ የተጀመሩ ኢኒሼቲቮችን የሕዝብ ርካታ በሚፈጥሩ መልኩ ወደ ውጤት ማድረስ አለብን፡፡ ከጠላቶቻችንን ላይ የመሣሪያም የትርክትም ትጥቅ ማስፈታት ይገባል፡፡ ለጠላት ተጋላጭነትን ሊፈጥሩ የሚችሉ አሠራሮችን ማረም ጊዜ የማይሰጠው ተግባር ነው፡፡ የአመራር ሥምሪትን መፈተሽና ማጥራት መንገዳችንን የበለጠ ምቹ ያደርገዋል፡፡ ትጋትና ቁርጠኝነትን መጨመር፣ መናበብንና ቅንጅትን ማሣለጥ አለብን፡፡
ኅብረ ብሔራዊ አንድነትን የሚፈጥሩ፣ ገዥ ትርክትን የሚያሠርጹ፣ ብሔራዊ ጥቅሞቻችንን የሚያስከብሩ እና የኢትዮጵያን ብልጽግና የሚያረጋግጡ ተግባራትን ባለማሰለስ በየአካባቢያችን ተግተን ማከናወን ያስፈልገናል፡፡
የክረምት የበጎ ፈቃድ ሥራዎችን በተገቢ ዕቅድ እና ቅንጅት መርተን ለውጤት ማብቃት ይገባናል፡፡ በአረንጓዴ ዐሻራ መርሐ ግብር በዚህ ዓመት የተያዘውን ዕቅድ ለማሳካት ሕዝቡን የማትጋትና የማሳተፍ ሥራ ከአሁኑ መጀመር አለበት፡፡ ለመኸር የእርሻ ሥራዎች የሚያስፈልጉ ግብዓቶችና ማሽነሪዎች በተገቢ ቦታና ጊዜ እንዲደርሱ የአመራር ሚናችንን እንወጣ፡፡ አንድም መሬት ጦም በማያድርበት ሁኔታ የግብርና ሥራዎች እንዲከናወኑ እናድርግ፡፡
በአጠቃላይ፣ በሰላማዊ እና በሠለጠነ መንገድ ልዩነቶቻችን በመፍታት፣ የጀመርናቸው ሪፎርሞች በማሳካት፣ የገጠሙንን ፈተናዎች በጽናት በማለፍ፣ ተግዳሮቶቻችንን በመጋፈጥና በማሸነፍ፣ የኢትዮጵያን ብልጽግና እውን እንድናደርግ፣ የብልፅግና ሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ለብልፅግና ፓርቲ አመራርና አባላት፣ ለተፎካካሪ ፓርቲዎች እና ለመላው የኢትዮጵያ ሕዝብ ጥሪ ያቀርባል፡፡
የብልፅግና ፓርቲ የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ
ሚያዝያ 18/ 2017፤ አዲስ አበባ

ከብልፅግና ፓርቲ ሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ የተሰጠ መግለጫ***************የብልፅግና ፓርቲ ሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ከሚያዝያ 17 እስከ18/ 2017 ዓም መደበኛ ስብሰባውን በአዲስ አበባ አካሂ...
26/04/2025

ከብልፅግና ፓርቲ ሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ የተሰጠ መግለጫ
***************

የብልፅግና ፓርቲ ሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ከሚያዝያ 17 እስከ18/ 2017 ዓም መደበኛ ስብሰባውን በአዲስ አበባ አካሂዷል። በዚህ ስብሰባም የኢትዮጵያን ፖለቲካዊ፣ ኢኮኖሚያዊ፣ ማኅበራዊና ዲፕሎማሲያዊ ጉዳዮች በዝርዝር ተመልክቷል።

ኢትዮጵያ በ2018 ከተስፋ ወደሚጨበጥ ብርሃን ለመሻገር፤ በ2023 የአፍሪካ የብልጽግና ተምሳሌት ለመሆን፤ በ2040 ደግሞ ዓለም አቀፍ የብልጽግና አርአያ ለመሆን ያስቀመጠችው ርእይ እንደሚሳካ የሚያረጋግጡ የስኬት ፍንጮች መታየታቸውን የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴው አረጋግጧል። እነዚህ የስኬት ፍንጮች የያዝነው ፍኖተ ብልጽግና ትክክል መሆኑን አመላክተውናል።

ከብልፅግና ፓርቲ ሁለተኛ መደበኛ ጉባኤ በኋላ አያሌ ፖለቲካዊና ዲፕሎማሲያዊ ስኬቶች ተመዝግበዋል። ከተለያዩ ተፎካካሪ የፖለቲካ ፓርቲዎች ጋር በየደረጃው የሚደረገው ምክክርና ትብብር በኢትዮጵያ የፖለቲካ ታሪክ ወደ አዲስ ምእራፍ ገብቷል። ከአንድ ክልል በስተቀር፣ ለሀገራዊ ምክክር አጀንዳ የማሰባሰብ ምእራፍ በሁሉምክልሎች ተጠናቅቋል።

በሀገሪቱ የጸጥታ ችግር በነበረባቸው አንዳንድ አካባቢዎችም ሰላም እየሰፈነ ነው። መንግስት በተደጋጋሚ ያቀረበውን የሰላም ጥሪ ተከትሎ እጅ የሚሰጡና ወደ ሰላም ድርድር የሚመጡ ታጣቂዎች ከዕለት ወደ ዕለት ቁጥራቸው እየጨመረ ይገኛል። የመንግሥት ሕግ የማስከበርና የማድረግ ዐቅም እየጎለበተ መጥቷል።

ከሶማሊያ ጋር ተፈጥሮ የነበረውውዝግብ በዲፕሎማሲያዊ መንገድ ተፈትቷል። ኢትዮጵያ የባሕር በር እንዲኖራት የተያዘው አቋም ዓለም አቀፋዊ ተቀባይነቱ እየጨመረ ነው። ኢትዮጵያ ከዓለም አቀፍ የፋይናንስ ተቋማት ጋር ያላት ግንኙነት ከመሻሻሉም በላይ የሚደረግላት ድጋፍ እያደገ ነው። በዓለም አቀፍ መድረክ የኢትዮጵያ ተፈላጊነት ጨምሯል። የዲፕሎማሲ ግንኙነቷም በሁሉም አቅጣጫ ከፍ ብሏል።

እስከአሁን ያለው አፈፃፀም የሚያሳየው በያዝነው አመት አጠቃላይ ኢኮኖሚው በታቀደው መሠረት በ8.4 በመቶ የሚያድግ መሆኑን የሥራ አስፈጻሚው ገምግሟል። በዘርፍ ደረጃ ደግሞ ግብርና በ6.1 በመቶ፣ ኢንዱስትሪ በ12.8 በመቶ፣ ማኑፋክቸሪንግ በ12.0 በመቶ፣ ኮንስትራክሽን በ12.3 በመቶ፣ አገልግሎት ደግሞ በ7.1 በመቶ የሚያድጉ መሆናቸው ተገምግሟል። ያለፉት 9 ወራት ጠቅላላ የመንግሥት ገቢ ከአምናው ተመሳሳይ ወቅት አንጻር የ134 በመቶ ብልጫ አሳይቷል። የውጭ ብድር ከጠቅላላ የሀገር ውስጥ ምርት ያለው ድርሻ ወደ 13.7 በመቶ ወርዷል። ወደ ውጭ ገበያ የሚቀርቡት ስድስት ዋና ዋና ምርቶች፣ ካለፈው ዓመት ጋርሲነጻጸሩ ከ82 በመቶ እስከ 386 በመቶ ጭማሪ አሳይተዋል። በስንዴ፣ በሩዝ፣ በቡና፣ በሻሂ ቅጠል እና በፍራፍሬ ምርቶችበአፍሪካ ቀዳሚ ሆኖ ለመውጣት እየተደረገ ያለው ትግል ፍሬእያፈራ መሆኑን አይተናል።

ውድ የብልፅግና አመራሮች፣ የብልፅግና አባላትና መላው ሕዝባችን፣

የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያው ዝቅተኛ ኑሮ በሚኖሩ ወገኖችላይ ጫና እንዳያሳድር አስፈላጊ የሆኑና የታቀዱ የድጋፍ መርሐግብሮች መከናወናቸውንም የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴውመርምሯል። ለማዳበሪያ 62 ቢልዮን ብር፣ ለሴፍቲኔት 41.2 ቢልዮን ብር፣ ለነዳጅ 60 ቢልዮን ብር፣ ለመድኃኒት 3.5 ቢልዮንብር፣ ለምግብ ዘይት 6.1 ቢልዮን ብር፣ እንዲሁም ለደመወዝ 38.4 ቢልዮን ብር ድጎማ ተደርጓል። ባለፉት 9 ወራት ብቻ 344,790 የውጭ ሀገር ሕጋዊ የሥራ ዕድሎች እና ከ3 ሚልዮን በላይ የሀገር ውስጥ የሥራ ዕድሎች ተፈጥረዋል።

የርቀት የሥራ ዕድሎች ቁጥርም እየጨመረ መምጣቱ ታይቷል።

የመንግሥት የልማት ተቋማትን በአዲስ አስተሳሰብና በአዲስመንገድ መልሶ ለማደራጀትና ለመምራት መቻሉ፣ እያስገኘውያለው ውጤት ለሌሎች አርአያ የሚሆን እንደሆነ የሥራአስፈጻሚ ኮሚቴው ገምግሟል። የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንትሆልዲንግስ አሁን ያለው ጠቅላላ ገቢ 1.5 ትሪልዮን መድረሱታይቷል። ከባለፈው ዓመት የ9 ወራት አፈጻጸም አንጻርየዘንድሮ ገቢው የ86 በመቶ ጭማሬ ማሳየቱም ተረጋግጧል።ይሄም መንግሥት የሀገርን ሀብት ለማወቅ፣ ዐውቆም በሚገባለማስተዳደር፣ አስተዳድሮም ወረት ለማከማቸት የተከተለውመርሕ ትክክል መሆኑን አረጋግጧል።

የውጭ ምንዛሬ ክምችት ዕድገት ከባለፈው ዓመት ተመሳሳይ9 ወራት ጋር ሲነጻጸር የ203.99 በመቶ ዕድገት አሳይቷል።የባንኮች ተቀማጭ ገንዘብ ከ3 ትሪልየን በላይ ተሻግሯል። የ9 ወራት የወጪ ንግድ አፈጻጸም ከ5 ቢልዮን ዶላር በላይሲሆን፣ ይሄም ካለፈው ዓመት ጋር ሲነጻጸር የ150.39 በመቶዕድገት አምጥቷል። ባለፉት ስምንት ወራት 473.9 ቢልዮንብር ብድር ከንግድ ባንኮች ተለቅቋል። ይሄም ካለፈው ዓመትተመሳሳይ ጊዜ አንጻር በ61.9 በመቶ ከፍ ይላል። ከዚህ ብድርውስጥም 76.6 በመቶ ለግሉ ዘርፍ የተሰጠ ነው። ለግሉ ዘርፍየበለጠ ብድር መሰጠቱ፣ የግሉ ዘርፍ በኢኮኖሚው ተገቢውንሚና እንዲጫወት ያስቀመጥነው ፖሊሲ በተግባር እየተገለጠመሆኑን አመላካች ነው።

ዲጂታል ኢትዮጵያ 2030ን ለማሳካት የጀመርናቸው ሁሉንአቀፍ ጥረቶች ፍሬያቸው እየጎመራ ነው። የኢንተርኔትተጠቃሚዎች 50.2 ሚልዮን፣ የሞባይል ተጠቃሚዎችም 86.6 ሚልዮን ደርሰዋል። የቴሌ ብር ደንበኞችም ከ52.56 ሚሊዮንበላይ ናቸው። ዲጂታል ፋይናንስ፣ የኅብረተሰቡን ፍትሐዊተጠቃሚነት ከማረጋገጥ ባለፈ ለኢኮኖሚው መሣለጥ ጉልህድርሻ እያበረከተ ነው። ባለፉት 9 ወራት በዲጂታል መንገዶች7.73 ቢልዮን ብር ተቆጥቧል። 26.77 ቢልዮን ብር በዲጂታልበኩል ብድር ተሰጠ ሲሆን፣ የ12.51 ትሪሊዮን ብር ግብይትደግሞ በዚሁ መንገድ ተከናውኗል።

ዋና ዋና ፕሮጀክቶችን በጊዜና በተገቢ ደረጃ ለማጠናቀቅየተሰጠው አቅጣጫ ብዙዎችን ለፍጻሜ እያበቃቸው ነው።የሕዳሴ ግድብ ግንባታ አፈጻጸም 98.66 በመቶ ደርሷል።የኮይሻ፣ አይሻና አሰላ የኃይል ማመንጫዎች በተያዘላቸውዕቅድ መሠረት እየተጓዙ መሆናቸው ተገምግሟል። የቢሾፍቱዓለም አቀፍ የአውሮፕላን ማረፊያ ግንባታም የኢትዮጵያንነገ ታሳቢ ባደረገ መልኩ የቅድመ ዝግጅት ምእራፉእየተከናወነ ይገኛል። የኮሪደር ልማት በአዲስ አበባ በ8 ኮሪደሮች እና በመላው ኢትዮጵያ በ65 ከተሞች እየተከናወነመሆኑ ተስፋ ሰጪ ነው። ብዙዎቹ የመስኖ ግድቦች ወደፍጻሜያቸው እየደረሱ ናቸው። ከዘጠኙ የመስኖ ግድቦችውስጥ ስድስቱ አፈጻጸማቸው ከ75 በመቶ በላይ ደርሷል።

“ትምህርት ለትውልድ” በሚል መሪ ቃል ከ82 ቢልዮን ብርበላይ ድጋፍ የተሰበሰበ ሲሆን፣ በአጠቃላይ 6815 ትምህርትቤቶች በመላ ሀገሪቱ ተገንብተዋል። የነባር ትምህርት ቤቶችንዐቅም ለማሻሻል እና በግጭት የተጎዱትን ለመጠገንየተደረገው ጥረት በትውልድ ላይ ለሚሠራው ሥራ መሠረትየሚጥል መሆኑ ታይቷል። የወላድ እናቶችን እና የጨቅላ ሕጻናትን ሞት በመቀነስ ረገድ የተሻለ ውጤት መመዝገቡም ታይቷል።

በኢትዮጵያ የቱሪዝም መዳረሻዎችና የስፖርት ሥፍራዎችበቁጥርም፣ በዓይነትም እያደጉ መጥተዋል። በተለያዩከተሞች በመገንባት ላይ የሚገኙ ዓለም አቀፍ ስታዲየሞችበመጠናቀቂያ ምእራፍ ላይ ናቸው። ይሄም ኢትዮጵያ ታላላቅ አፍሪካዊ ጨዋታዎችን ለማስተናገድ ለያዘችው ዕቅድ መሳካት ወሳኝ ነው። ከዚህ በተጨማሪ፣ ኢትዮጵያ ዓለምአቀፍ ኩነቶችን ለማስተናገድ ያላት መሠረተ ልማት እናየመስተንግዶ ዐቅም እያደገ ይገኛል። ባለፉት ዘጠኝ ወራትከ66 በላይ ዓለም አቀፍ ኩነቶች በሀገራችን ተደርገዋል።በቱሪስት ፍሰት ጭማሪ ከአፍሪካ ቀዳሚ ሀገር በመሆን ላይነን። የኢትዮጵያን ተፈጥሯዊ፣ ባህላዊ፣ ታሪካዊ እናሃይማኖታዊ ጸጋዎች አውጥተን ማሳየት ከቻልን፣ በቱሪዝምመስክ የቀዳሚነት ሚና መጫወት እንደምንችል ጅምሮቹያሳያሉ።

ባለፉት ዘጠኝ ወራት በተከናወኑ ተግባራት አምራችነትንበማበረታታት፣ ሥራ ያቆሙ ኢንዱስትሪዎችን ወደ ሥራበማስገባት፣ ገቢ ምርቶችን በሀገር ውስጥ ምርት በመተካት፣የሀገር ውስጥ ገቢን በማሰባሰብ፣ ወጪ ምርቶችን በብዛትበማምረት፣ ከአንድ ጊዜ በላይ መሬትን ደጋግሞ በማረስ፣ሪፎርሞችን በየዘርፋቸው አግባብ በመተግበር፣ የተመዘገቡውጤቶች ተስፋ ሰጪ ናቸው። በዚህ እንቅስቃሴ የተነሣራስን የመቻል ተነሣሽነት ጨምሯል። ዘጠኝ ክልሎችሰብአዊ ድጋፍን በራሳቸው ዐቅም ከመሸፈናቸውም በላይየሰብአዊ ድጋፍ ፈላጊዎች ቁጥርም ባለፉት አምስት ዓመታትበሀገር አቀፍ ደረጃ በ86 በመቶ ቀንሷል። ሂደቱ ተረጂነትንመጸየፍና አምራችነትን ባህል ማድረግ በሀገራችን ሥርእየያዘ መሆኑን አመላካች ነው።

ውድ የብልፅግና አመራሮች፣ የብልፅግና አባላትናመላው ሕዝባችን፣

እነዚህ ስኬቶች የጉዟችን መጀመሪያ እንጂ መጨረሻአይደሉም። ማበረታቻዎች እንጂ ፍጻሜዎች አይደሉም።ስኬቶቹ መንገዳችን ትክክል መሆኑን የሚያሳዩ የተራራ ላይመብራቶች ናቸው። ለበለጠ ሥራ የሚያነሣሡ፣ ለበለጠ ወኔየሚቀሰቅሱ፣ የጠለቀ ቁጭት የሚቆሰቁሱ ናቸው።

በሠራናቸው የፖለቲካ፣ የኢኮኖሚና የጸጥታ ተቋማትሪፎርሞች ሀገራችን ከነበረባት የህልውና አደጋ ወጥታ ወደአስተማማኝ ህልውና እየተሻገረች ነው። ሪፎርሙ የነበረውንየህልውና ሥጋት መቀልበስ ብቻ ሳይሆን፣ የሀገርን ህልውናለመጠበቅ የሚያስችል አስተማማኝ ዐቅም ፈጥሯል። ይሄምበተቃራኒው መንግሥትን በኃይል ለመጣል የነበረውን ፍላጎትአምክኗል።

በተደረጉ ሀገር በቀል ማሻሻያዎች፣ በተፈጠረው ዐቅም እናዝግጁነት ኢኮኖሚያችን ወደ ተሟላ የኢኮኖሚ ማሻሻያትግበራ ገብቷል። ይሄ ደግሞ የኢኮኖሚ ሂደታችንን እናየብልጽግና ጉዟችንን የሚቀይር አዲስ ምእራፍ ፈጥሯል።የሕዳሴ ግድብ መጠናቀቅ እና የባሕር በር ጉዳይ በቀጣናችንየአጀንዳ የበላይነት እንድንፈጥር አስችሎናል። በዚህምየተነሣ ሀገራችንን ከተከላካይነት ወደ ተጽዕኖ ፈጣሪነትአሸጋግሯታል። በመሆኑም ለውጡ ከመተከል ወደማንሠራራት ተራምዷል ማለት ይቻላል።

መንግሥት የፈጠረው ዐቅም፣ የፀረ ለውጥ ኃይሉ መዳከምእና ዓለም አቀፍ ለውጡ የኢትዮጵያን ሪፎርም ለማሳካትየተሻለ ዕድል የሚሰጥ ነው። መንግሥትን በኃይል ለመጣልናፍላጎትን በጉልበት ለማሳካት የሚደረገው መፍጨርጨርውጤት እንደማያስገኝ ሀገራዊ እውነት እየሆነ ነው።በየጊዜው ወደ ሰላም የሚመጡት ታጣቂዎች ቁጥርመጨመርም ይሄንን ያመለክታል።

በአንድ በኩል እነዚህን ስኬቶች ይበልጥ ማስፋትና ማጽናትአለብን። በሌላ በኩል ደግሞ ራሳችንን ከመሐል ዘመንወጥመድ መጠበቅ ይገባናል። የመሐል ዘመን ወጥመድ፣አንድ ሀገር ከፖለቲካ ሥርዓት ሽግግር በመውጣት፣ ወደቀጣዩ የማጽናት ምእራፍ ከመድረሷ በፊት፣ በሚገኘውየመሐል ዘመን፣ በስኬቶች ረክቶና ተዘናግቶ የመቀመጥአባዜ ነው። ከፖለቲካ ሽግግር በመውጣትና የጸና ሥርዓትንበመትከል መካከል የሚገኝ ፈታኝ ዘመን ነው።

የሀገራችን ኢኮኖሚ በማደግ ላይ ያለ እንጂ በሚፈለገውመጠን ያደገ አይደለም። በግብርና፣ በኢንዱስትሪ፣ በከተማልማት፣ በወጪ ምርቶች፣ በማዕድን፣ በአገልግሎት ዘርፍ፣በዲጂታል ኢትዮጵያ፣ ወዘተ. ያየናቸው ለውጦች ብንሠራየት እንደምንደርስ አመላካቾች ናቸው። ከግባችንመድረሳችንን ግን አያበሥሩም። የፖለቲካ ባህላችንእየተለወጠ ነው፤ ነገር ግን የሠለጠነ የፖለቲካ ባህል ገናአልገነባንም። የጸጥታ ተቋሞቻችን እየዘመኑና እየደረጁናቸው፤ ይሁን እንጂ በኢትዮጵያ ልክ ገና አልደረሱም።የፖለቲካ ፍላጎትን በኃይል የማስፈጸም አካሄድ ፋሽኑእያለፈበት መጥቷል። ነገር ግን ገና ከፖለቲካና ከማኅበራዊባህላችን ተፍቆ አልጠፋም። የሲቪል ሰርቪስ ሪፎርም ገናበጅምር ላይ ነው። ዕዳችን ቢቃለልም ገና ከጫንቃችንፈጽሞ አልወረደም። የዋጋ ግሽበትን ብንቋቋመውም፣ የኑሮውድነትን ግን በተገቢው መንገድ ገና አላቃለልነውም።

በመሆኑም ከስኬት ማማ ላይ የደረስን መስሎን፣ በመሐልዘመን ወጥመድ እንዳንያዝ አመራሮችና አባላት ነቅተውእንዲታገሉ፣ የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴው በአጽንዖት ያሳስባል።
የመሐል ዘመን ወጥመድ በዋናነት የሚከሠተው በውጤትበመዘናጋት፣ ችግርን በመላመድ፣ ሀገራዊ ዕይታን ትቶ በጎጥውስጥ በማደር እና የሕዝብን ችግሮች በጊዜያቸውናበልካቸው ባለመፍታት ነው። በመሆኑም እነዚህ ችግሮችየመሐል ዘመን ወጥመድን እንዳያመጡብን በአመራሩናበአባላቱ ዘንድ ትግል ሊደረግባቸው ይገባል።

ውድ የብልፅግና አመራሮች፣ የብልፅግና አባላትናመላው ሕዝባችን፣

የተዛባ ትርክት እንዳይፈጠር የብሔራዊ ዐርበኝነት ትርክትንበሚገባ ማሥረጽ ይጠበቅብናል። የሕዝብን ጥያቄዎችበየደረጃው መፍታት አለብን። ምርትና ምርታማነትን ከፍበማድረግ የኑሮ ውድነትን የሚያቃልሉ ሥራዎችን መሥራትይጠበቅብናል። የተጀመሩ ኢኒሼቲቮችን የሕዝብ ርካታበሚፈጥሩ መልኩ ወደ ውጤት ማድረስ አለብን።ከጠላቶቻችንን ላይ የመሣሪያም የትርክትም ትጥቅማስፈታት ይገባል። ለጠላት ተጋላጭነትን ሊፈጥሩ የሚችሉአሠራሮችን ማረም ጊዜ የማይሰጠው ተግባር ነው።የአመራር ሥምሪትን መፈተሽና ማጥራት መንገዳችንንየበለጠ ምቹ ያደርገዋል። ትጋትና ቁርጠኝነትን መጨመር፣መናበብንና ቅንጅትን ማሣለጥ አለብን።

ኅብረ ብሔራዊ አንድነትን የሚፈጥሩ፣ ገዥ ትርክትንየሚያሠርጹ፣ ብሔራዊ ጥቅሞቻችንን የሚያስከብሩ እናየኢትዮጵያን ብልጽግና የሚያረጋግጡ ተግባራትን ባለማሰለስ በየአካባቢያችን ተግተን ማከናወን ያስፈልገናል።

የክረምት የበጎ ፈቃድ ሥራዎችን በተገቢ ዕቅድ እና ቅንጅትመርተን ለውጤት ማብቃት ይገባናል። በአረንጓዴ ዐሻራመርሐ ግብር በዚህ ዓመት የተያዘውን ዕቅድ ለማሳካትሕዝቡን የማትጋትና የማሳተፍ ሥራ ከአሁኑ መጀመርአለበት። ለመኸር የእርሻ ሥራዎች የሚያስፈልጉ ግብዓቶችናማሽነሪዎች በተገቢ ቦታና ጊዜ እንዲደርሱ የአመራርሚናችንን እንወጣ። አንድም መሬት ጦም በማያድርበትሁኔታ የግብርና ሥራዎች እንዲከናወኑ እናድርግ።

በአጠቃላይ፣ በሰላማዊ እና በሠለጠነ መንገድ ልዩነቶቻችንበመፍታት፣ የጀመርናቸው ሪፎርሞች በማሳካት፣ የገጠሙንንፈተናዎች በጽናት በማለፍ፣ ተግዳሮቶቻችንን በመጋፈጥናበማሸነፍ፣ የኢትዮጵያን ብልጽግና እውን እንድናደርግ፣የብልፅግና ሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ለብልፅግና ፓርቲ አመራርናአባላት፣ ለተፎካካሪ ፓርቲዎች እና ለመላው የኢትዮጵያሕዝብ ጥሪ ያቀርባል።

የብልፅግና ፓርቲ የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ
ሚያዝያ 18/ 2017፤ አዲስ አበባ

23/04/2025

ለመለወጥ ከልብ የሚሠራ ከሆነ መለወጥ ይቻላል፡፡

የካዛንቺስ ኮሪደር እና የመልሶ ማልማት ስራ:-- 1000 ሄክታር መሬት የሚሸፍን - 40.9 ኪ/ሜ  የአስፋልት መንገድ - 81.9 ኪ/ሜ የእግረኛ መንገድ- 20.7 ኪ/ሜ ሳይክል ሌን- 15 የ...
23/04/2025

የካዛንቺስ ኮሪደር እና የመልሶ ማልማት ስራ:-

- 1000 ሄክታር መሬት የሚሸፍን
- 40.9 ኪ/ሜ የአስፋልት መንገድ
- 81.9 ኪ/ሜ የእግረኛ መንገድ
- 20.7 ኪ/ሜ ሳይክል ሌን
- 15 የህጻናት መጫዎቻ ቦታዎች
- 5 የስፖርት ማዘውተሪያ ስፍራዎች
- 16 የህዝብ መዝናኛ ፕላዛዎች እና አረንጓዴ ፓርኮች
- 19 የመጸዳጃ ቤቶች
- 105 የንግድ ሱቆች
- 40 የመኪና ማቆሚያዎች እና ተርሚናሎች ተካትተው ተገንብተዋል::

Address

Addis Ababa

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Hiber Ethiopia posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to Hiber Ethiopia:

Share