FANA FM98.1 Radio News

FANA FM98.1 Radio News Welcome to Fana 98.1 Radio News! https://www.youtube.com/channel/UC4E6LQ_lqIlbA_GwoVw8tAA
(2)

 ➡ “ አንድ ዓመት መዘግየት በጣም ከባድ ነው። ግዴታ መማር እንዳለብን አስጠንቅቀውናል ” - የወላይታ ሶዶ ዩኒበርሲቲ ተማሪዎች➡ “ የተማሩበት ታይም ምን ያህል ነው? ተብሎ መወሰን አለበት...
05/02/2024



➡ “ አንድ ዓመት መዘግየት በጣም ከባድ ነው። ግዴታ መማር እንዳለብን አስጠንቅቀውናል ” - የወላይታ ሶዶ ዩኒበርሲቲ ተማሪዎች

➡ “ የተማሩበት ታይም ምን ያህል ነው? ተብሎ መወሰን አለበት” - የወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች ህብረት

የወላይታ ሶዶ ዩኒቨርስቲ የ4ኛ ዓመት ተማሪዎች በዚህ ዓመት መመረቅ ሲገባቸው “ አላወቅነውም ” ባሉት ምክንያት ለምረቃ አንድ ‘ዓመት ትጨምራላችሁ’ ተብለው እየተገደዱ መሆኑን አማረው ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ቅሬታቸውን አሰምተዋል።

ለምን የእናንተ ብቻ ዘገዬ ወይም አንድ ዓመት ጭማሪ ተደረገ ? ሲል ቲክቫህ ኢትዮጵያ ጥያቄ አቅርቧል።

* ስኬጁሉ ላይ ነው ችግራቸው። በኮሮና ምክንያት 2013 ዓ/ም ሁሉም ግቢዎች ተማሪዎቻቸውን የጠሩት ሰኔ ወር ላይ ነበር። እኛም ከሁሉም ግቢ እኩል ነበር የገባነው (ሰኔ 26)። ወዲያውኑ (45 ቀናት አቆይቶ) አስወጣን (ከግቢ) ምንም ባላወቅንበት መንገድ። አንድ ሲሚስተር ጨርሰን መወሰጣት ሲገባን ሚድን ፈትኖ አስወጣን።

* በቀጣዩ ዓመት ደግሞ ሚዲ የወሰድነውን ሁለት ሲሚስተር አድርጎ በአጠቃላይ አስተማረ። ሙሉ 3 ሲሚስተር ነበር ማስተማር የነበረበት ግን አንዱን ዓመት በሁለት ሲሚስተር ብቻ አደረገ። ስህተቱን የሰሩት እዚሁ ላይ ነው።

* ሬጅስተራር ላይ የሰፈረው “4ኛ ዓመት ናችሁ” ነው የሚለው። እኛ የምንማረው ግን ገና ሦስተኛ ዓመት ሁለተኛ ሲሚስተርን እየጀመርን ነው። ሌሎች ግቢዎች ግን አሁን 4ኛ ዓመት ሁለተኛ ሲሚስተርን እያስተማሩ ነው። የእኛ ሙሉ 3 ሲሚስተሮች ወደ ኋላ ቀርቷል ማለት ነው።

* ‘ወደ ኋላ ቀረን’ ብለን ስናመለክት ‘ #አስተካክላለሁ’ ብሎ ‘3 ሲሚስተር አስተምራለሁ’ ካለ በኋላ ሁለት ሲሚስተር አስተማረና ካፌ ዘጋ። እንደዛ እየተደረገ አንድ ዓመት ባከነ። የእኛን የአንድ ዓመት በጀት ለምን እንደፈለጉት አናውቅም። ከሌሎች ግቢዎች በሚለይ ሁኔታ በሚያስጠላ ሁኔታ ላይ ነው ያለነው።

የሚል ማብራሪያ በአንድ ተወካያቸው በኩል ሰጥተዋል።

“ ሌሎች ግቢዎች የእኛን ባቾች በዚህ ዓመት ያስመርቃሉ። የእኛ ግን በዚህ ዓመት አይደለም” ያሉት ተማሪዎቹ፣ “ በዚህ ሳምንት ክላስ አልገባንም። ነገር ግን ግዴታ በቀጣይ ሰኞ መግባት እንዳለብን ተነግሮናል። ግዴታ መማር እንዳለብን አስጠንቅቀውናል። ” ሲሉ አስረድተዋል።

አክለውም፣ “ አንድ ዓመት መዘግየት በጣም ከባድ ነው። ሙሉ 3 ሲሚስተር አስተምሮ ሰኔ ላይ ይፈትነን (እንመረቅ) አንልም። ቢያንስ ስለ Exit exam የሚሆኑ ኮርሶችን ወደዚህ አሸጋሽገውልን Exist ተፈትነን ቀጣዩን አንድ ሲሚስተር እንድንወስድ ያድርጉን። አንድ ዓመት ከመዘግየት ግማሽ ዓመት መዘግየት ይሻላል ብለዋል ” ሲሉ አሳስበዋል።

ቅሬታውን በተመለከተ ምን ምላሽ እንዳለው ለመጠየቅ ወደ ዩኒቨርስቲው ከፍተኛ አመራሮሽ የተደረገው ሙከራ ባይሳካም፣ የወላይታ ሶዶ ዩኒቨርስቲው የተማሪዎች ኀብረት ፕሬዝዳንት ተማሪ ፍሬው ተክሌ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ በሰጡት ቃል፣ “ ስኬጁል ላይ የተቀየረ ነገር የለም። ያልተጣራ መረጃ እንጂ በእኛ ፔጅ ላይ የተለጠፈ አይደለም ” ሲሉ አስተባብለዋል።

ተማሪ ፍሬው፣ “ የሚመረቁት መቼ ነው? ለሚለው የተማሩበት ታይም ምን ያህል ነው? የሚለው መወሰን አለበት” ያሉ ሲሆን፣ የዘንድሮ ተማሪዎቹ በቀጣይ ዓመት ነው የምትመረቁት ተብለዋል ወይስ አልተባሉም? ተብሎ ከቲክቫህ ኢትዮጵያ ለቀረበላቸው ጥያቄም ቀጥኛ መልስ በመስጠት ፋንታ፤ “በእስኬጁል መሠረት ነው እኮ ይሄ ውሳኔ” ብለዋል።

መረጃውን አዘጋጅቶ የላከው የአ/አ ቲክቫህ ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባል ነው።
ምንጭ:-

ጥንቃቄ 1. አጭበርባሪዎች በኢትዮጵያ አየር መንገድ የእቃ ጭነት አገልግሎት (ካርጎ) በኩል ለተለያዩ ግለሰቦች ዕቃ እንደተላከላቸው አስመስሎ በመደወል እና ሐሰተኛ የእቃ ጭነት መለያ ቁጥር A...
17/01/2024

ጥንቃቄ

1. አጭበርባሪዎች በኢትዮጵያ አየር መንገድ የእቃ ጭነት አገልግሎት (ካርጎ) በኩል ለተለያዩ ግለሰቦች ዕቃ እንደተላከላቸው አስመስሎ በመደወል እና ሐሰተኛ የእቃ ጭነት መለያ ቁጥር Air Waybill (AWB) በመጠቀም የተላከውን ዕቃ ለመቀበል የሚከፈል በሚል ክፍያ በመጠየቅ የማጭበርበርና የማታለል ስራ እየሰሩ ስለሆነ ጥንቃቄ ይደረግ።

2. አጭበርባሪዎች በኢትዮጵያ አየር መንገድ ለመቀጠር ለምዝገባ እና ለተለያዩ ወጪዎች በሚል ገንዘብ በማስከፈል የማታለል ተግባር ላይ በመሰማራታቸው አስፈላጊውን ጥንቃቄ ማድረግ ይገባል።

3. የካናዳ መንግስት የስራ እና የትምህርት እድል እንዳወጣ እና የኢትዮጵያ አየር መንገድ ከዚህ ጉዳይ ጋር በተያያዘ ሰው እንደወከለ እንዲሁም መመዝገብ ለሚፈልጉም ሁሉ ክፍያ የሚፈፅሙበት የባንክ አካውንትም አንዳሳወቀ በማስመሰል ደብዳቤ በማዘጋጀት ሰዎችን የማታለል ተግባር ላይ አጭበርባሪዎች በመሰማራታቸው ተገቢው ጥንቃቄ ይደረግ።

እንድታውቁት ፦

➡ የኢትዮጵያ አየር መንገድ ዕቃ ለተላከላቸው ደንበኞቹ ዕቃቸው መድረሱን እና ወደ ድርጅቱ በመምጣት አስፈላጊ ሂደቶችን እንዲያስጀምሩ ከማሳወቅ ውጪ ምንም አይነት ቅድመ ክፍያ እንዲከፍሉ በስልክ አይጠይቅም።

➡ ለስራ ቅጥር በሚል የኢትዮጵያ አየር መንገድ ምንም አይነት ቅድመ ክፍያ አይጠይቅም ፤ ከማንኛውም አይነት ኤጀንት ጋር አብሮ አይሰራም ፤ ለስራም ሆነ ለትምህርት ወደ የትኛውም ሀገር ሰዎችን የመላክ ስራ ላይ አልተሰማራም።

#የኢትዮጵያአየርመንገድ

16/01/2024
ኢትዮጵያ ለአንድ ቻይና ፖሊሲ አሁንም አቋሟ ያልተቀየረና የፀና መሆኑን አሳውቃለች። የኢትዮጵያ ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ አምባሳደር መለስ ዓለም (ዶ/ር) ለኢዜአ በሰጡት ቃል ፤ ኢትዮ...
16/01/2024

ኢትዮጵያ ለአንድ ቻይና ፖሊሲ አሁንም አቋሟ ያልተቀየረና የፀና መሆኑን አሳውቃለች።

የኢትዮጵያ ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ አምባሳደር መለስ ዓለም (ዶ/ር) ለኢዜአ በሰጡት ቃል ፤ ኢትዮጵያ የአንድ ቻይና ፖሊሲ ላይ ያላት አቋም ዛሬም የጸና ነው ብለዋል።

ኢትዮጵያ የአንዲት ቻይና ፖሊሲን ለረጅም ዓመታት ስታራምድ መቆየቷን አስታውሰው ይህ አቋሟ በዘመናት መካከል መንግስታት አፅንተው የያዙት መሆኑን ገልጸዋል።

በመሆኑም ኢትዮጵያ የአንድ ቻይና ፖሊሲ ላይ ያላት አቋም ዛሬም የጸና መሆኑን አረጋግጠዋል።

በሌላ በኩል ፤ ከሰሞኑን ራሷን ከቻይና ነጥላ እንደ ነፃ ሀገር በምትቆጥረው ታይዋን ፕሬዜዳንታዊ ምርጫ ተደርጎ ነበር።

በዚህ ምርጫ ቻይና አትወዳቸውም የሚባሉት፣ አስቸጋሪና አደገኛ ሰው ብላቸው የምትጠራቸው በሙያቸው ሐኪም የሆኑት ዊሊያም ላይ ማሸነፋቸው ተዘግቧል።

ዶክተሩ " ለቻይና አንንበረከክም !! " በሚል አቋማቸው ነው የሚታወቁት።

ቻይና ከምርጫው በፊት አምርራ ለምትጠላው ለገዢው ዲሞክራቲክ ፕሮግረሲቭ ፓርቲ (ዲፒፒ) ህዝቡ ድምጽ እንዳይሰጡ አሳስባ የነበረ ቢሆንም የዚሁ ፓርቲ አባል የሆኑት የሕክምና ዶክተሩ ዊሊያም ላይ ቺንግ አሸንፈዋል።

ሰውየው በምርጫ ቅስቀሳ ወቅት " ታይዋን ነጻ አገር መሆኗን ማወጅ አያስፈልጋትም፣ ምክንያቱም ታይዋን ሉአላዊና ነጻ አገር ስለሆነች " ብለዋል።

ይህንን ምርጫ ተከትሎ ሀገራት አቋማቸውን እና አስተያየታቸውን ሲሰጡ ነበር።

አሜሪካ በምርጫው ላሸነፉት ፕሬዜዳንት በይፋ የ" እንኳን ደስ አልዎት " መልዕክት አስተላልፋ ፤ ከታይዋን እና ከገዢው ፓርቲ ጋር ያላትን ግንኙነት እንደምታጠናክር አሳውቃለች።

ከምርጫው በኃላ ፕሬዜዳንት ጆ ባይደን ፤ " እኛ ነፃነትን አንደግፍም ... " የሚል አስተያየት ሰጥተው ነበር።

አሜሪካ ከታይዋን ጋር ይፋዊ ያልሆኑ ግንኙነቶች ያሏት ሲሆን ታዋይም የአሜሪካ ድጋፍ እንዳላት በተለያየ ጊዜ ተናግራለች ፤ የአሁኑን ምርጫም ተከትሎ የቀድሞ ብሄራዊ ደህንነት አማካሪ ስቴፋን ሃድሌይ ጭምር ያሉበት ይፋዊ ያልሆነ ልዑክ ወደ ታይዋን ልካ ከአሁኑ ተመራጭ ፕሬዜዳንት እና ከቀድሞ ጋር ውይይት አድርጋለች።

ከአሜሪካ በተጨማሪ፣ ዩናይትድ ኪንግደም፣ የአውሮፓ ህብረት፣ እንዲሁም ካናዳ ፣ ጃፓን ለገዢው ፓርቲ ደስታ መልዕክት አስተለልፈዋል።

በሌላ በኩል፤ ሩስያ ምርጫውን ተከትሎ ታይዋን የቻይና አንድ አካል መሆኗን ገልጻለች። ኢራን ፣ ኢንዶኔዥያ፣ ቬትናም ፣ታጃኪስታን " የአንድ ቻይና " ፖሊሲን እንደምትደግፍ አረጋግጣለች።

ከአፍሪካ ደግሞ የኢትዮጵያ ጎረቤት ሶማሊያ ለአንድ ቻይና ፖሊሲ ድጋፍ በማሳየት ፤ ታይዋን የቻይና ግዛት ናት ስትል መግለጫ አውጥታለች። ከቀናት በፊት ቻይና " ሶማሌላንድ የሶማሊያ ግዛት ናት " ማለቷ ይታወሳል።

ኢትዮጵያ ስለምርጫው ምንም ባትልም አሁንም " የአንድ ቻይና " ፖሊሲዋ እንዳልተቀየረ አሳውቃለች።

ቻይና ታይዋንን " የራሷ ግዛት አድርጋ ነው የምታስባት፤ መመለስ አለባትም ብላ ታምናለች ለዚህም ታይዋንን የሚደግፉ ሁሉ በሀገር አንድነት ላይ አደጋ ያመጡ አድርጋ ነው የምትወስዳቸው።

ሶማሊያ እና ኤርትራ ምን መከሩ ? የሶማሊያው ፕሬዜዳንት ሀሰን ሼክ ሞሀሙድ ወደ ኤርትራ አቅንተው የሁለት ቀን የስራ ጉብኝት አድርገው ወደ ሞቃዲሾ ተመልሰዋል። ፕሬዜዳንቱ ጉብኝታቸውን በተመለ...
10/01/2024

ሶማሊያ እና ኤርትራ ምን መከሩ ?

የሶማሊያው ፕሬዜዳንት ሀሰን ሼክ ሞሀሙድ ወደ ኤርትራ አቅንተው የሁለት ቀን የስራ ጉብኝት አድርገው ወደ ሞቃዲሾ ተመልሰዋል።

ፕሬዜዳንቱ ጉብኝታቸውን በተመለከተ ማብራሪያ ሰጥተው ነበር።

በማብራሪያቸውም ፤ " ኤርትራን በተደጋጋሚ ጎብኝቻለሁ። ኤርትራ ለኛ እንደ ቤታችን ናት " ብለዋል።

ወደ ኤርትራ የሄዱት ፦
- ኤርትራ ከፍተኛ ድጋፍ እያደረገች ባለችበት በሶማሊያ ሽብርተኝነትን መዋጋት ዙሪያ ለፕሬዝዳንት ኢሳያስ አፈወርቂ ገለጻ ለማድረግ፤
- ከሰሞኑ በቀጠናው እየተስተዋለ ስላለው ተለዋለዋጭ ሁኔታ ላይ ለፕሬዝዳንት ኢሳያስ ገለጻ ለማድረግ፤
- በአካባቢው ስለላለው ሁኔታ የሶማሊያን አቋም ለፕሬዜዳንት ኢሳያስ ለማስረዳት ነው ብለዋል።

ፕሬዜዳንቱ ፤ " ኤርትራ ሁልጊዜም ከሶማሊያ ጎን ናት፤ ለዚህም እናመሰግናለን " ሲሉ ተደምጠዋል።

" ኤርትራ የሶማሊያን አንድነት፣ ሉዓላዊነትና የግዛት አንድነት ለማስጠበቅ ስትደግፍ ቆይታለች ይህም የኤርትራ ዓለም አቀፍ አቋም ፤ አሁንም ይህንን አቋም ክቡር ፕሬዝዳንቱ ዛሬ ደግመውኛል፤ ለዚህም እናመሰግናለን " ሲሉ ተናግረዋል።

የኤርትራ መንግሥት ምን አለ?

የኤርትራ መንግሥት ፕሬዝዳንት ኢሳያስ አፈወርቂ እና ፕሬዜዳንት ሀሰን ሼክ መሀሙድ ባለፉት ሁለት ቀናት በሁለትዮሽ፣ አህጉራዊ እና ዓለምአቀፋዊ ጉዳዮች ላይ ሰፊ እና ጥልቅ ውይይት አድርገዋል ብሏል።

ሁለቱ መሪዎች በሁለትዮሽ ጉዳዮች ዙሪያ በጋራ እንደሚሰሩ መስማማታቸውን እና በቅርቡ የሁለትዮሽ እና ቀጣናዊ ጉዳዮች ላይ ሰፊ መግለጫ እንደሚያወጣ አስታውቋል።

NB. የሶማሊያው ፕሬዜዳንት ሀሰን ሼክ ሞሀሙድ ኤርትራ በነበሩበት ወቅት የግብፁ መሪ አብዱል ፈታህ አል ሲሲ ግብፅን እንዲጎበኙ ግብዣ አድርገውላቸዋል። የኢትዮጵያ እና የራስ ገዟ ሶማሌላንድ የመግባቢያ ስምምነት ከተፈረመ በኃላ የሶማሊያው ፕሬዝዳንት በቅድሚያ ስልክ ደውለው የተነጋገሩ ከአል ሲሲ ጋር እንደነበር አይዘነጋም።

የኢትዮጵያ የባህር በር ጥያቄ ከዓለም አቀፍ ሕግ አንጻር⁉️ በሀዋሳ ዩኒቨርስቲ የህግ መምህር አቶ በፍቃዱ ድሪባ ለኢፕድ በሰጡት ማብራሪያ‼️  👉 የተባበሩት መንግስታት የባህር በር ህግ አንቀ...
09/01/2024

የኢትዮጵያ የባህር በር ጥያቄ ከዓለም አቀፍ ሕግ አንጻር⁉️

በሀዋሳ ዩኒቨርስቲ የህግ መምህር አቶ በፍቃዱ ድሪባ ለኢፕድ በሰጡት ማብራሪያ‼️

👉 የተባበሩት መንግስታት የባህር በር ህግ አንቀጽ 69 የባህር በር የሌላቸው ሀገራት በአካባቢው ያለውን የባህር በር የመጠቀምና የመሸጋገር አለም አቀፍ መብት እንዳላቸው ይደነግጋል፣

👉 ኢትዮጵያን ያለቀይባህር ፤ቀይባህርንም ያለኢትዮጵያ ማሰብ አይቻልም፣

👉 በትርክት የነበረን እውነታ መቀየር ባይቻልም ማንሻፈፍ ግን ይቻላል፤

👉 ከባህር በር ተያይዞ ኢትዮጵያ የገጠማት ችግር የትርክ መንሻፈፍ ነው፣

👉 ባለፉት 30 አመታት ሰለባህር በር ማውራትም ሆነ የኢትዮጵያን የባለቤትንት መብት መጠይቅ እንደነውር ይቆጠር ነበር፣

👉 በእነዚሁ አመታት ከባህር በር ጋር የተያያዙ ጥናቶችና ምርምሮች ሁሉ ታግደው ቆይተዋል፣

👉 ኢትዮጵያ ለወደብ ኪራይና ለመጓጓዣ ከፍተኛ ዶላር ስለምታፈስ የኑሮ ውድነቱ እንዲባባስ ምክንያት ሆኗል፣

👉 ኢትዮጵያ ከቀይ ባህር እንድትርቅ የተደረገበት አካሄድ ምንም አይነት ህጋዊ መሰረት የሌለው፣

👉 የተመድ ሲቋቋም ካወጣቸው ድጋጌዎች አንዱ ሀገራት የቅኝ ግዛት ውሎችን የመቀበል ግዴታ የለባቸውም፣

👉 ኢትዮጵያ አንደኛ የባህር በር የማግኘት መብት፤ ሁለተኛ የባህር በር ባለቤትነት መብት ያላት ሀገር ነች፣

👉 ኢትዮጵያ እነዚህ መብቶች የመጎናጸፍ መብት ያላት በመሆኑ ያነሳቻቸው ጥያቄዎች ህጋዊ መሰረት ያላቸው ናቸው፣

👉 የአለም አቀፍ ውሎችን ስንመለከት ኢትጵያን የባህር በር የሚያሣጣት አንዳችም ነገር የለም፤

👉 የአለም አቀፍ ፍርድ ቤት መመስረቻ ጽሁፍ አንቀጽ 38 ላይ አንድ ሀገር ኢፍትሃዊ ውሳኔ ተወስኖብኛል ብሎ ካሰበ ጥያቄውን ማቅረብና መሟገት ይችላል፣

👉 በቨርሳይለስ ስምምነት ጀርመን ለፖላንድ የራሷን መሬት ቆርሳ ሰጥታለች፣

👉 ፖላንድ ተቆልፎባት መኖር ስለሌለባት ጀርመን መሬቷን አሳልፋ በመስጠትና ፖላንድ የባህር በር ባለቤት ሆናለች፣

👉 ሁሉም ኢትዮጵያዊ መንግስት የጀመረውን ጥረት ሊያግዝና ኢትዮጵያም ወደ ታሪካዊ መበቶቿ እንድተመለስ የበኩሉን ጥረት ሊደርግ ይገባል፣

#የዜና ምንጭ የኢትዮጵያ ፕሬስ ኤጀንሲ

የሰራተኞች ፈተና ውጤት ይፋ ሆነ።ለአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ሰራተኞች የተሰጠው ፈተና  #ውጤት ይፋ ሆኗል።በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ እና በኮተቤ የትምህርት ዩኒቨርሲቲ የተዘጋጀው እና ለአ...
09/01/2024

የሰራተኞች ፈተና ውጤት ይፋ ሆነ።

ለአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ሰራተኞች የተሰጠው ፈተና #ውጤት ይፋ ሆኗል።

በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ እና በኮተቤ የትምህርት ዩኒቨርሲቲ የተዘጋጀው እና ለአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ሰራተኞች ሲሰጥ የነበረው ፈተናን በሚመለከት በዛሬው ዕለት መግለጫ ተሰጥቷል።

በዚህ መግለጫም ፤ ፈተናውን የወሰዱት የከተማ አስተዳደሩ የቴክኒክና ባህሪ ብቃት ፈተና ለአመራሮች፣ ለባለሙያዎችና ሰራተኞች ቁጥር 15 ሺህ 151 መሆኑ ተገልጿል።

ከዚህ ውስጥ የአመራሩ ቁጥር 4 ሺህ 213 ሲሆን የፈተውን ማለፊያ ውጤት ያመጡት 1 ሺህ 422 ናቸው። ይህም 34 በመቶው አመራሮች አልፈዋል። አመራሩ ለማለፍ ከ60 በመቶ በላይ ማምጣት ይጠበቅባቸዋል።

ፈተናውን የወሰዱ የሠራተኞች ቁጥር 10 ሺህ 257 ሲሆኑ ያለፉት 5 ሺህ 95 ናቸው ተብሏል። ይህም 50 በመቶ ነው። ሰራተኞች ለማለፍ ከ50 በመቶ በላይ ማምጣት አለባቸው።

ለፈተና ከተቀመጡት አጠቃላይ ቁጥር 681 የሚሆኑት በተለያየ የስነ ምግባር ጥሰት ከፈተና ውጪ መሆናቸውን እና 441 የሚሆኑት ደግሞ በፈተና ስፍራ ያልተገኙ መሆናቸው ተገልጿል።

መረጃው ከኢፕድ እና ከአዲስ አበባ ፐብሊክ ሰርቪስና የሰው ልማት ቢሮ ነው ያገኘው።

በሊቢያ ደርና የደረሰውን የጎርፍ አደጋ መከላከል ይቻል ነበር ሲሉ ባለሙያዎች ገለጹአዲስ አበባ፣ ታኅሣስ 29፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) ባለፈው መስከረም ወር በሊቢያ ደርና ከተማ በጎርፍ አደጋ ...
08/01/2024

በሊቢያ ደርና የደረሰውን የጎርፍ አደጋ መከላከል ይቻል ነበር ሲሉ ባለሙያዎች ገለጹ

አዲስ አበባ፣ ታኅሣስ 29፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) ባለፈው መስከረም ወር በሊቢያ ደርና ከተማ በጎርፍ አደጋ የፈረሱት ግድቦች ደካማ እንደነበሩ የዳኝነት ምርመራ ውጤት አመላከተ።



የሊቢያ ጠቅላይ ዐቃቤ ሕግ አል-ሲዲቅ አል-ሱር በትናንትናው ዕለት እንደተናገሩት፤ በግድቡ ግምገማ ወቅት ቢያንስ 25 ባለሙያዎች ግዴለሽ መሆናቸው ለአደጋው መከሰት ምክንያት ሆኗል።



ከፈረንጆቹ 2003 ጀምሮ እነዚህን ግድቦች ለመጠገን እና ሶስተኛውን ግድብ ለመገንባት የቀረበው ምክረ ሀሳብ ተግባራዊ ተደርጎ ቢሆን ኖሮ አደጋውን ማስቀረት ይቻል እንደነበር በውጤቱ ተመላክቷል።



በፈረንጆቹ መስከረም 10 እና 11 የደረሰው ከፍተኛ የጎርፍ አደጋ የሊቢያ ሰሜን ምስራቅ ከተማ የሆነችውን ደርና ከተማን ማውደሙ ይታወሳል፡፡



አደጋውንም ተከትሎ ከ11 ሺህ በላይ ሰዎች ህይወታቸውን ማጣታቸው ይታወሳል።



የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ጎርፉ ጎረቤት አካባቢዎችንም መንካቱንና ወሳኝ የፍሳሽ እና የውሃ መሠረተ ልማቶችን ማውደሙን የገለፀ ሲሆን በወቅቱ አብዛኛውን ሞት ማስቀረት ይቻል እንደነበርም አመላክቷል፡፡



በደርና ከ 30 ሺህ በላይ ሰዎች እንደተፈናቀሉና ወደ አንድ ሚሊየን የሚጠጉ ሰዎችም በጎርፍ መጎዳታቸውን የተባበሩት መንግስታት ዓለም አቀፍ የስደተኞች ድርጅት (አይ ኦ ኤም) መግለጹን አፍሪካ ኒውስ በዘገባው ጠቁሟል።

Address

Addis Ababa
Addis Ababa
1000

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when FANA FM98.1 Radio News posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share