22/07/2025
የፍርድ ቤት ውሳኔ
* 16 ዓመት አደይ ጌታቸው ፅኑ እስራት
* 15 ዓመት ሉንጎ ሉቃስ ፅኑ እስራት
የአለልኝ አዘነ ግድያ እና የተላለፈው ፍርድ!
የቀድሞው እግር ኳስ ተጫዋች አለልኝ አዘነን በመግደል ወንጀል ተከሰው የነበሩት ባለቤቱ ወ/ሮ አደይ ጌታቸው እና የእህቷ ባል ሉንጎ ሉቃስ በጋሞ ዞን ከፍተኛ ፍርድ ቤት የጽኑ እስራት ተፈረደባቸው።
ፍርድ ቤቱ በዛሬው ዕለት ባስተላለፈው ውሳኔ፣
1. ወ/ሮ አደይ ጌታቸው የ16 ዓመት ጽኑ እስራት ሲፈረድባቸው፣
2. የባለቤቱ የእህቷ ባል (ሉንጎ ሉቃስ) ላይ ደግሞ የ15 ዓመት ጽኑ እስራት ተበይኖበታል።
ይህ አስደንጋጭ ክስተት የተከሰተው አለልኝ አዘነ እና ባለቤቱ ከተጋቡ ከ15 ቀናት በኋላ መጋቢት 17 ቀን 2016 ዓ.ም. ነበር።
ፍርድ ቤቱ በሰውና በሰነድ ማስረጃዎች መሠረት ወንጀሉ መፈጸሙን ካረጋገጠ በኋላ ይህን ውሳኔ ማሳለፉ ታውቋል።
የአለልኝ አዘነ ግድያ በብዙዎች ዘንድ አስደንጋጭ እና አሳዛኝ ክስተት ሆኖ ሲነገር ቆይቷል።