ብራና ሚዲያ/Brana Media

ብራና ሚዲያ/Brana Media ብራና ሚዲያ በመላው ኢትዮጵያ እንዲሁም ዓለማችን ላይ ስላሉ ?

መረጃ
09/08/2025

መረጃ

126 likes, 4 comments. “Breaking News/ሰበር ዜና”

በኢትዮጵያ የእስራኤል አምባሳደር ዶ/ር አቭረሃም ንጉሴ ተወዳጁን እና ዝነኛውን አርቲስት ቴዎድሮስ ካሳሁን (ቴዲ አፍሮ) በዛሬው ዕለት አነጋግረዋል።በውይይታቸው ላይ እስራኤል እና ኢትዮጵያ ጥ...
26/03/2025

በኢትዮጵያ የእስራኤል አምባሳደር ዶ/ር አቭረሃም ንጉሴ ተወዳጁን እና ዝነኛውን አርቲስት ቴዎድሮስ ካሳሁን (ቴዲ አፍሮ) በዛሬው ዕለት አነጋግረዋል።

በውይይታቸው ላይ እስራኤል እና ኢትዮጵያ ጥልቅ ታሪካዊ እና ባህላዊ ትስስር ያላቸው ጥንታዊ ሀገራት መሆናቸውን ጠቅሰው በኪነጥበብ እና በሙዚቃው ዘርፍ በጋራ በመስራት የባህል ትስስር ለማጠናከር በሚያስችሉ ጉዳዮች ላይ ምክክር አድርገዋል፡፡

ተመልሷልበኢትዮ ሳት ላይ ተቋርጦ የነበረው ኢቢኤስ ቴሌቪዥን ዳግም ወደ አየር ተመልሶ ስርጭት ጀምሯል።
26/03/2025

ተመልሷል

በኢትዮ ሳት ላይ ተቋርጦ የነበረው ኢቢኤስ ቴሌቪዥን ዳግም ወደ አየር ተመልሶ ስርጭት ጀምሯል።

EBS የሚያስተላልፈውን ስርጭት እንዲያቆም ታግዶ ስቱዲዮ መታሸጉን መረጃዎች ያመላክታሉ።
26/03/2025

EBS የሚያስተላልፈውን ስርጭት እንዲያቆም ታግዶ ስቱዲዮ መታሸጉን መረጃዎች ያመላክታሉ።

(ብራና ሚዲያ)ለ2ኛ ጊዜ ፍርድ ቤት ቀርቧልዛሬ ለ2ኛ ጊዜ ፍርድ ቤት የቀረበው ድምፃዊ አንዱዓለም ፖሊስ አንዳንድ ምርመራ ውጤቶች ስላልደረሱልኝ ተጨማሪ ቀናት ይሰጠኝ ባለው መሰረት ተጨማሪ 1...
26/03/2025

(ብራና ሚዲያ)ለ2ኛ ጊዜ ፍርድ ቤት ቀርቧል

ዛሬ ለ2ኛ ጊዜ ፍርድ ቤት የቀረበው ድምፃዊ አንዱዓለም ፖሊስ አንዳንድ ምርመራ ውጤቶች ስላልደረሱልኝ ተጨማሪ ቀናት ይሰጠኝ ባለው መሰረት ተጨማሪ 12 ቀን ተፈቅዶለታል።

የድምፃዊ አንዱዓለም ጠበቃ በበኩሉ የዋስ መብት ይፈቀድለት ብሎ ቢጠይቅም

ፖሊስ ማስረጃዎችን ያጠፋብኛል መፈቀድ የለበትም በማለቱ ሳይፈቀድ ቀርቷል።

መጋቢት 29/2017 ዓም ቀጠሮ ተሰጥቷል።

(ብራና ሚዲያ) ዩትዩብ ወይም ቲክቶክ የመሳሰሉ መተግበሪያዎችን በመጠቀም ገንዘብ የሚያገኙ ግለሰቦች እና ተቋማት ታክስ እንዲከፍሉ ሊደረግ ነው።በክፍያ የሚቀርቡ ወይም በሚያቀርቡት አገልግሎት ...
26/03/2025

(ብራና ሚዲያ)

ዩትዩብ ወይም ቲክቶክ የመሳሰሉ መተግበሪያዎችን በመጠቀም ገንዘብ የሚያገኙ ግለሰቦች እና ተቋማት ታክስ እንዲከፍሉ ሊደረግ ነው።

በክፍያ የሚቀርቡ ወይም በሚያቀርቡት አገልግሎት ገንዘብ ከሚያገኙ የድረገጽ እና የመተግበሪያ ውጤቶች ላይ መንግሥት ታክስ ሊሰበስብ መዘጋጀቱን አሰራሩን ለመተግበር ከወጣው የመንግሥት ሰነድ መመልከቱን ዋዜማ ሬድዮ ዘግቧል።

በድረገጽ የሚቀርቡ የሚዲያ አገልግሎቶች ፖድካስት፣ ፊልም ፣ ሙዚቃን ጨምሮ በሚቀርቡ አገልግሎቶች ላይ የተጨማሪ እሴት ታክስ ወይም ቫት ይጣልባቸዋል።

በደምበኝነት ምዝገባ ላይ የተመሰረተ የሚዲያ አገልግሎት የሚሰጡ ግለሰቦችና ድርጅቶችም ተጨማሪ እሴት ታክስ እንዲከፍሉ የሚያስገድደው አሰራር በኤሌክትሮኒክስ ዘንዴ በሚቀርብ የትራንስፖርት አገልግሎት ላይ በተመሳሳይ ሁኔታ እሴት ታክስ እንዲካተት አድርጓል።

ባለፈው ዓመት ሰኔ ወር የፀደቀው የተጨማሪ እሴት ታክስ ለማስፈጸም የወጣው የሚኒስትሮች ምክር ቤት የተጨማሪ እሴት ታክስ የተሰኘው ደምብ በ13 ክፍሎች እና በ66 አንቀፆች ተከፋፍሏል።

የተጨማሪ እሴት ታክስ አዋጅ እንዲታወጅ ካስፈለገበት ምክንያት ውስጥ የኤሌክትሮኒክስ ግብይትን እና በዓለም አቀፍ ደረጃ ተቀባይነት ያገኙ አዳዲስ እሳቤዎችን በሀገሪቱ የህግ ማዕቀፍ ውስጥ በማካከት ታክሱ ለኢኮኖሚው እድገት እገዛ እንዲያደርግ ማስቻል የሚለው ይገኝበታል።

በዚህ መሰረት ከዚህ ቀደም ተጨማሪ እሴት ታክስ ውስጥ ያልተካተቱ በኤሌክትሮኒክስ ዘዴ የሚቀርቡና የደምበኝነት ምዝገባ በመጠቀም የሚተላለፉ ሚዲያዎች ፣ መፅሄቶች፣ ጋዜጦች ፣ የቴሌቪዥን ፕሮግራሞችና ሙዚቃዎች ተጨማሪ እሴት ታክስ ተጥሎባቸዋል።

አሁን አዋጁን ለማስፈፀም የወጣው የተጨማሪ እሴት ታክስ ደምብ በየነመረብ በመጠቀም የሚተላለፉ ፖድካስቶች፣ ብሎጎች፣ ጆርናሎች ለመንግሥት ታክስ መክፈል እንዳለባቸው ያስገድዳል።

የማህበራዊ ትስስር አገልግሎት / ዌብሳይት እና መተግበሪያዎችን ማቅረብ ተጨማሪ እሴት ታክስ የሚታሰብባቸው አገልግሎቶች መሆናቸው ተመላክቷል።

በኤሌክትሪክስ ዘዴ ከሚቀርቡና ታክስ ከሚከፈልባቸው አቅርቦቶች ተከታከቱት ሌሎች አገልግሎቶች ውስጥ በበየነ መረብ የተመሰረተ የጨረታ አገልግሎት መስጫ አቅርቦት፣ የማንኛውም ዲጅታል ይዘት ያለው መፅሀፍ ወይም ህትመትን ጨምሮ የኤሌክትሮኒክ መፅሀፍ አቅርቦት የሚሉት ይገኙበታል።

በተንቀሳቃሽ ስልክ የሚጫኑ ዲጅታል ይዘት ያላቸው መተግበሪያዎች እና ፊልሞች በታክሱ ተካተዋል።

- የሙዚቃ አቅርቦት
- የቀጥታ ስርጭት አገልግሎት
- የስልክ ጥሪ ድምጽ
- ለቀጥታ ዝግጅቶች፣ ትያትሮች እና ምግብ ቤቶች የሚውሉ ትኬቶችን በኢንተርኔት በኩል መሸጥ በአዋጁ መሰረት የተጨማሪ እሴት ታክስ አገልግሎት የሚከደልባቸው ናቸው።

ደምቡ በኢትዮጵያ ግዛት በዲጅታል መንገድ የሚሰጥ የትራንስፖርት አገልግሎት አቅርቦት በተጨማሪ እሴት ታክስ ውስጥ ተካቷል።

የመንገደኞችን የትራንስፖርት አገልግሎት በመመቻቸት በኤሌክትሮኒክስ ዘዴ መንገደኞችን ከትራንስፖርት አቅራቢዎች ጋር የሚያገናኙ ማንኛውም ሰው ተጨማሪ እሴት ታክስ ከፋይ መሆኑንም በደምቡ ላይ ተብራርቷል።

የፕላትፎርም / በዲጅታል የሚሰጥ የትራንስፖርት አገልግሎት አቅራቢ ማናቸውም ክፍያዎችን እና ኮሚሽኖችን ጨምሮ ሌሎች ተሳፋሪዎች ከሚከፍሏቸው ጠቅላላ ክፍያዎች ላይ የተጨማሪ እሴት ታክስ መሰብሰብ አለበት ሲል ደምቡ ያዛል።

የፕላትፎርም አቅራቢው በየዕለቱ መጨረሻ ለመንገደኞች ትራንስፖርት አገልግሎት ሰጪው የተጨማሪ እሴት ታክስ ደረሰኝ መስጠት እንዳለበት ደምቡ ያብራራል።

ይህ መረጃ ባለቤትነቱ የዋዜማ ራድዮ ነው።

(ብራና ሚዲያ)የትግራይ  ጊዜያዊ አስተዳደር ፕሬዝዳንት ዕጩዎችን እንዲጠቁም ለትግራይ ህዝብ ጥሪ ቀረበ ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ፤ የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደርን በፕሬዝዳንትነት ለ...
26/03/2025

(ብራና ሚዲያ)የትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር ፕሬዝዳንት ዕጩዎችን እንዲጠቁም ለትግራይ ህዝብ ጥሪ ቀረበ

ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ፤ የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደርን በፕሬዝዳንትነት ለመምራት ብቁ የሚሆኑ ዕጩዎችን እንዲጠቆሙ ለክልሉ ህዝብ ጥሪ አቀረቡ። ዕጩዎቹ “የጊዜያዊ አስተዳደሩን ስራዎች በብቃት የሚያከናውኑ” እንዲሁም “የክልሉን ሰላም እና ደህንነት ማረጋገጥ የሚችሉ መሆን” ይገባቸዋል ተብሏል።

ጠቅላይ ሚኒስትሩ ይህን ጥሪ ያቀረቡት፤ ለመላው የትግራይ ህዝብ በይፋዊ የማህበራዊ ትስስር ገጾቻቸው በዛሬው ዕለት ባስተላለፉት መልዕክት ነው። በትግርኛ ቋንቋ የተጻፈው የጠቅላይ ሚኒስትሩ መልዕክት፤ “የትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር ፕሬዝዳንት ጥቆማ ጥሪ” በሚል ርዕስ የቀረበ ነው።

(ብራና ሚዲያ)የትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር የስልጣን ዘመን ለአንድ ዓመት መራዘሙን ጠቅላይ ሚኒስትሩ በትግረኛ ባስተላለፉት መልዕክት ይፋ አድርገዋል። ለህዝቡ ፕሬዝዳንት የሚሆናችሁን እጩዎች በ...
26/03/2025

(ብራና ሚዲያ)የትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር የስልጣን ዘመን ለአንድ ዓመት መራዘሙን ጠቅላይ ሚኒስትሩ በትግረኛ ባስተላለፉት መልዕክት ይፋ አድርገዋል። ለህዝቡ ፕሬዝዳንት የሚሆናችሁን እጩዎች በኢሜል ጠቁሙ ብለዋል።

በኢቢኤስ ቲቪ ተላልፎ በአስገዳጅነት እንዲነሳ የተደረገውን ቪዲዮ ማየት የሚፈልጉ ከሆነ ይህን ሊንክ ይጠቀሙ እጅግ አሳዛኝ ታሪክ በኢትዮጵያ ተፈጽሟል።
24/03/2025

በኢቢኤስ ቲቪ ተላልፎ በአስገዳጅነት እንዲነሳ የተደረገውን ቪዲዮ ማየት የሚፈልጉ ከሆነ ይህን ሊንክ ይጠቀሙ እጅግ አሳዛኝ ታሪክ በኢትዮጵያ ተፈጽሟል።

#ክሪፕቶከረንሲ ...

(ብራና ሚዲያ) ደምቢዶሎ ዩኒቨርሲቲ በኢቢኤስ ቴሌቭዥን ላይ የቀረበችው ብርቱካን ተመስገንን "አላውቃትም" አለ።  ዩኒቨርሲቲው "የቴሌቭዥን ጣቢያው ያቀረበብኝን ውንጀላ ካላስተባበለ እከሰዋለሁ...
24/03/2025

(ብራና ሚዲያ) ደምቢዶሎ ዩኒቨርሲቲ በኢቢኤስ ቴሌቭዥን ላይ የቀረበችው ብርቱካን ተመስገንን "አላውቃትም" አለ። ዩኒቨርሲቲው "የቴሌቭዥን ጣቢያው ያቀረበብኝን ውንጀላ ካላስተባበለ እከሰዋለሁ" ሲል ማስጠንቀቂያ አውጥቷል።
ዩኒቨርሲቲው ዛሬ "ማስታወቂያ" በሚል ባሰራጨው የማስጠንቀቂያ መልዕክት "በ14/7/ 2017 ዓ.ም በEBS ፕሮግራም ላይ በተደረገ ቃለ ምልልስ ብርቱኳን ተመስገን ከበደ የተባለች በ2013 የትምህርት ዘመን በደምቢ ዶሎ ዩኒቨርሲቲ የሁለተኛ ዓመት የፋርማሲ ተማሪ ነበርኩ በማለት የሰጠችዉ ሃሳብ ስህተት መሆኑና ዩኒቨርሲቲው የፋርማሲ ትምህርት ሲሰጥ በ2013 የሁለተኛ ዓመት ተማሪ እንዳልነበረው ይገልጻል።" በማለት አስተባብሏል።
ዩኒቨርሲቲው ማስጠንቀቂያውን በመቀጠል "ስለሆነም ይህ ድርጊት በጣም ሃላፊነት የጎደለው እና ምንም አይነት ማስረጃ የሌለው ስለሆነ ግልጽ የሆነ ስም ማጥፋት እና የዩኒቨርሲቲያችንን ስም የሚያጎድል ስለሆነ ኢቢኤስ ይህን ውንጀላ እስካልቀለበሰ ድረስ ዩኒቨርሲቲው ጉዳዩን ወደ ፍርድ ቤት ለመውሰድ እገደዳለሁ" ሲል አሳስቧል።

(ብራና ሚዲያ) የኤርትራ መንግስት በኢትዮጵያ የባህር በር ጥያቄ ላይ ለመጀመሪያ ጊዜ ማብራሪያ ሰጠ፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ ዛሬ በፓርላማ ላይ ይህንን ጉዳይ በተመለከተ ገለፃ ያደረ...
22/03/2025

(ብራና ሚዲያ) የኤርትራ መንግስት በኢትዮጵያ የባህር በር ጥያቄ ላይ ለመጀመሪያ ጊዜ ማብራሪያ ሰጠ፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ ዛሬ በፓርላማ ላይ ይህንን ጉዳይ በተመለከተ ገለፃ ያደረጉ ሲሆን በንግግራቸውም ‹‹የባህር በር ጥያቄን ሌሎች አገራትም የደገፉት በጋራ ተጠቃሚነት ሊሳካ የሚችል ፍትሀዊ ጥያቄ መሆኑም የመሰከሩለት ነው›› ብለዋል፡፡

ጨምረውም የኢትዮጵያ የወደብ ጥያቄ መንግስት ለአጀንዳነት የመዘዘው ሳይሆን ታፍኖ የቆየ የትውልድ ጥያቄ መሆኑን ገልፀው በቀይ ባህር ያለው ዳርቻ ለሁሉም እንደሚበቃ አስረድተዋል፡፡ ይህንን ተከትሎ የኤርትራ ማስታወቂያ ሚኒስቴር በጉዳዩ ላይ ዘለግ ያለ ማብራሪያ ሰጥቷል፡፡ ሚኒስቴሩ ‹‹ብዙ ኢትዮጵያዊያን ምሁራንና ፖለቲከኞች አለም ሲቀየር ከፊውዳል አስተሳሰብ የተላቀቁ አይመስሉም›› በማለት ማብራሪያውን የጀመረ ሲሆን አገርንና ህዝቡን እያፈረሰ ያለው ይህ አመለካከት እንደሆነ አስታውቋል፡፡

የሌላውን የመሻት በሽታ ከዚህ የፊውዳል አስተሳሰብ የመነጨ መሆኑንም ገልጿል፡፡ ሲቀጥልም በኢትዮጵያ ውስጥ የእኔ ብሄር እና የእኔ መሬት በሚል የተለያዩ ግጭቶችና አለመግባባቶች እንዳሉ ጠቅሶ ከቅርብ አመታት ወዲህ በዚህ የተነሳ የብሄሮች መፈናቀል፣ መሰቃየትና መገደል እየተለመደ መምጣቱን አስረድቷል፡፡ ‹‹የኢትዮጵያ ህዝቦች እንደአንድ ዘመናዊ አገር ዜጋ በመላ አገሪቱ ተንቀሳቅሰው በነፃነት መኖር ያልቻሉበት አደገኛ ሁኔታ ተፈጥሯል›› ያለው ሚኒስትሩ ዋና ከተማዋ አዲስ አበባ እንኳ የእኔ በሚል ክርክር ውስጥ እንደምትገኝ ጠቅሷል፡፡

የኢትዮጵያ ምሁራንና ፖለቲከኞች ይህ የመስፋፋት አባዜ በአገር ውስጥ ብቻ የተወሰነ አለመሆኑን ገልፆ ያለፉት ‹‹መንግስታት ትልቁ የውድቀት ምክንያት የሌላውን ለመቀማት የሚደረግ ፊውዳላዊ አስተሳሰብ ነበር›› ብሏል፡፡ በተለይም የባህር በርን ለመቆጣጠር ያለው ፍላጎት ያለፉትን ስርአቶች ለውድቀት መዳረጉን አውስቷል፡፡ የኤርትራ ማስታወቂያ ሚኒስቴር ማብራሪያውን ሲቀጥል የኢትዮጵያ ምሁራንና ፖለቲከኞች አሁንም የመስፋፋት ህልም እንዳላቸው ገልፆ በማህበራዊ ሚዲያና በመንግስት ሚዲያዎች ጭምር ይህንን የሚያስተጋቡ የጂኦ ፖለቲካ ተንታኞችን ማየቱን ጠቅሷል፡፡ በተለይ የትግራይ ክልል ግጭት በፕሪቶሪያ ስምምነት ካበቃ በኋላ ይህ ጉዳይ ዋነኛ አጀንዳ ሆኖ መቅረቡን መታዘቡንም አስታውቋል፡፡

ማብራሪያው ጨምሮም ‹‹በአፍሪካ ቀንድ ከፍተኛ የህዝብ ቁጥር ያላት ኢትዮጵያ ህግን የሚያውቁ፣ አለም አቀፍ ግንኙነትንና ስነምግባርን የሚረዱ አስተዋይ መሪዎች ቢኖሯት ኖሮ የወደብ ወይንም የባህር በር ለማኝ መሆን አይገባትም ነበር፡፡›› ያለ ሲሆን የኤርትራን፣ የጅቡቲን፣ የሱዳንን፣ የሱማሊያን የኬንያን ወደቦች መጠቀም ትችል እንደነበር ገልጿል፡፡ የባህር በር የሌላት አገር ከጎረቤቶቿ ጋር በመመካከር በሌሎች አገራት የባህር በር የመጠቀም መብት እንዳላትም አውስቷል፡፡ የወደብ አገልግሎት የኢኮኖሚ ጉዳይ ከመሆኑ አኳያ የወደብ ባለቤትንም ጭምር ተጠቃሚ እንደሚያደርግ የጠቀሰው ሚኒስትሩ ጨምሮም ‹‹በቀጠናችን ለኢትዮጵያ የወደብ አገልግሎት በመስጠት ተጠቃሚ መሆን የማይፈልግ አገር ሊኖር አይችልም›› ብሏል፡፡

ይህም በተግባር መታየቱን ጠቅሶ ኤርትራ ነፃ ከወጣች በኋላ በነበሩት አመታት ኢትዮጵያ በኤርትራ ወደቦች በነፃነት ስትጠቀም መቆየቷን አውስቷል፡፡ እንዲሁም እ.ኤ.አ በ2000 አ.ም የእርዳታ ድርጅቶች በአሰብ ወደብ በኩል እርዳታ እንዲያስገቡ ፈቃደኝነቱን መግለፁን ጠቅሷል፡፡ ‹‹የኢትዮጵያ ልሂቃን ወደቡን ለመጠቀም ፈልገው ቢሆን ኖሮ የሚቃወማቸው አካል አይኖርም›› ያለው ማብራሪያው ይሁንና ህልማቸው የባህር ዳርቻውን ወስዶ የስነ ህዝብ ወይንም ዲሞግራፊ ለውጥ ማድረግና በባህሩ ዳርቻ ወታደራዊ እንቅስቃሴ ማድረግ እንደሆነ አስረድቷል፡፡

ይህ ደግሞ በተባበሩት መንግስታት ድርጅትና በአፍሪካ ህብረት እንዲሁም በሌሎች አለም አቀፍ ህጎች የማይፈቀድ መሆኑን ጠቅሶ የዘመናዊ አገራትን ድንበር ለመለወጥ የሚደረግ ጥረት ተቀባይነት የለውም ብሏል፡፡ ሲቀጥልም ‹‹የኢትዮጵያ የወደብ አገልግሎት ፍላጎት በማንኛውም ጊዜ ተቀባይነት አለው›› ያለው የኤርትራ ማስታወቂያ ሚኒስትር ይሁን እንጂ ኢትዮጵያዊያን የሚያስቡት ወረራ እንጂ አገልግሎት አለመሆኑን አስታውቋል፡፡

ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ የአሜሪካ የትምህርት ሚኒስቴር እንዲዘጋ ትዕዛዝ ሊሰጡ ነው ተባለ***********************የአሜሪካው ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ የሀገሪቱ የትምህርት ሚኒስ...
20/03/2025

ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ የአሜሪካ የትምህርት ሚኒስቴር እንዲዘጋ ትዕዛዝ ሊሰጡ ነው ተባለ
***********************

የአሜሪካው ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ የሀገሪቱ የትምህርት ሚኒስቴር እንዲዘጋ የሚያደርገውን ትዕዛዝ በፊርማቸው ሊያፀድቁ መሆኑን እየተነገረ ነው።

የትምህርት እና የሲቪክ መብት ተከራካሪዎች እንዲሁም ዴሞክራት ፓርቲን የወከሉ እንደራሴዎች ትዕዛዙ የሀገሪቱን የትምህርት ሥርዓት ለማፈራረስ ያለመ ነው ሲሉ ተቃውሞአቸውን እያሰሙ ስለመሆኑም ተነግሯል።

የጥቁሮች መብት ላይ አተኩሮ የሚሠራው ‘NAACP’ የተባለ ተቋም ፕሬዚዳንት ዴሪክ ጆንሰን፣ “የትምህርት ጥራትን ለማስጠበቅ በፌዴራል መንግሥት ድጎማ ላይ ጥገኛ ለሆኑ በሚሊዮኖች ለሚቆጠሩ የአሜሪካ ሕፃናት የዛሬ ቀን ጨለማ ቀን ነው” ብለዋል።

የዴሞክራቲክ ፓርቲ ሴናተር ፓቲ ሙሬይ በበኩላቸው፣ “ትራምፕ እና ኢሎን መስክ ትምህርት ሚኒስቴርን ለማፍረስ የማይሆን ጨዋታ እየተጫወቱ እና የሚኒስቴር መሥሪያ ቤቱን ግማሽ የሰው ኃይል እያባረሩ ነው” ሲሉ ተችተዋል።

የሀገሪቱ ብሔራዊ የወላጆች ኅብረት ደግሞ “እየተደረገ ያለው የትምህርት ሥርዓቱን ማስተካከል ሳይሆን በሚሊዮን የሚቆጠሩ ሕፃናት የሚገባቸውን ነገር እንዳያገኙ የማድረግ እንቅስቃሴ ነው፤ እኛ ግን ይህ እንዲሆን በፍፁም አንፈቅድም” ብሏል።

እንደ ሚዲያዎች ዘገባ ከሆነ ትራምፕ የሚፈርሙት ትዕዛዝ የትምህርት ሚኒስትሯ ሊንዳ ማክማሆን የትምህርት ሚኒስቴሩ እንዲዘጋ አስፈላጊውን ሒደት እዲያመቻቹ እና ሥልጣኑን ለግዛቶች አንዲያስተላልፉ ያዝዛል።

በዚያውም አሜሪካውያን የሚተማመኑባቸው ውጤታማ እና ያልተቋረጡ አገልግሎት፣ ፕሮግራሞች እና ጥቅሞችን እንዲያቀርቡ የማድረግ ሥራዎች ይሠራሉ ይላል።

የትምህርት ሚኒስቴር ፈንድ ተጠቃሚ የሆኑ ማናቸውም ፕሮግራሞች እና ኢንሼቲቮች የብዝኃነት፣ የፍትሕን እና የአካታችነት እንዲሁም የሥርዓተ-ፆታ ፕሮግራሞችን ማስፋፋት እንደማይችሉም የሚደነግግ መሆኑን የኋይት ሐውስ መገለጫ አመልክቷል።

ፕሬዚዳንት ትራምፕ የትምህርት ሚኒስቴሩን አባካኝ እና በሊበራል ርዕዮተ ዓለም የተበከለ ነው ብለው እንደሚያስቡ አልጀዚራ ዘግቧል።

ይሁንና ሚኒስቴር መሥሪያ ቤቱ ከተቋቋመበት የ1979ኙ የኮንግረስ አዋጅ ውጪ ሚኒስቴሩን የማፍረሱ ጉዳይ እውን ሊሆን እንደማይችልም ዘገባው አመላክቷል።

Address

Addis Ababa
1000

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when ብራና ሚዲያ/Brana Media posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to ብራና ሚዲያ/Brana Media:

Share