Current Media Corporate-CMC.

Current Media Corporate-CMC. We as an ethiopian which ever tribe,ethnicity or religion we belong,
We all are Ethiopians together we stand. Together we are beautiful!!

31/03/2020

በጊዜያዊነት መስጂዶች እንደሚዘጉ ከጋዜጣዊ መግለጫው ይጠበቃል።

✔©ሙጂብ አሚኖ ዘ ኢስላም
═════ ═════ ═════ ═════ ═════ ═════
መጋቢት 22/2012ማክሰኞ

የፌደራል፣የአዲስ አበባ፣ የኦሮሚያ መጅሊስን ጨምሮ ተጋባዥ ዑለሞች በተገኙበት በወቅታዊ የኮሮና ቫይረስ ዙሪያ መግለጫ እንደሚሰጥ ተገለፀ።

የኢትዮጲያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት መጅሊስ መጋቢት 10/2012 ሐሙስ ኮሮና ቫይረስን ለመከላከል ሙስሊሙ ማሕበረሰብ ከኃይማኖታዊ አስተምርሆ አኳያ ሊያደርግ ስለሚገባው ጥንቃቄ ጋዜጣዊ መግለጫ መስጠቱ ይታወሳል።

በዐለምም ይሁን ሀገራችን በወረርሺኝ መልኩ እየተዘመተ ስጋት እየሆነ የመጣው የኮሮና ቫይረስን (covid-19) ለመቆጣጠር አገራችን ኢትዮጲያ በተለያዩ አከባቢዎች በቂ ባይሆንም ሕዝባዊ የትራንስፖርት አገልግሎት የማቋረጥ እርምጃዎች እየተወሰዱ ይገኛሉ።

ከቤተ እምነት አኳያም የኢትዮጲያ ኦርቶዳክስ ቤ/ክ የኃይማኖት ማስተማሪያ ማዕከላትን የዘጋች ሲሆን በሙስሊሙ ማሕበረሰብ በኩል የቤተል ተቅዋ ና የባዩሽ መስጂድ ቀዳሚ የመዝጋት ትግበራ አከናውነዋል።

በኢትዮጲያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት መጅሊስ መሪነት በዛሬው እለት ጋዜጣዊ መግለጫ ለመስጠት የተዘጋጀ ሲሆን በመግለጫውም ላይ የአዲስ አበባና የኦሮሚያ መጅሊስን ጨምሮ ተጋባዥ ዑለሞች በተገኙበት በወቅታዊ የኮሮና ቫይረስ ዙሪያ መስጂዶች ላይ ስለሚተላለፈው ሁኔታ ይገልፃሉ። በመግለጫውም ላይ በሽታን ለመግታትና የመተላለፊያ መንገዶችን ለመገደብ ሲባል በጊዜያዊነት መስጂዶች ይዘጋሉ ተብሎ ይጠበቃል።

አሏህ በሽታውን አንስቶልን፣ መሳጂዶች በጊዜ ይከፈቱ ዘንድ ዱዓችን ነው።

🔰🔰🔰🔰🔰🔰🔰🔰🔰🔰🔰🔰🔰🔰🔰🔰🔰🔰🔰 🔰🔰🔰🔰🔰🔰🔰🔰🔰🔰🔰🔰🔰
ስለፍትህ እንጮሀለን፣ ሠላምን እንሰብካለን፣ አንድነትንና መከባበርን እንሻለን!
አዲሱ ገፄ ይህ ነው...https://m.facebook.com/MujibAminoThe.Islam/
https://m.facebook.com/mujib.amino.the.islam1/

ስለፍትህ እንጮሀለን፣ ሠላምን እንሰብካለን፣ አንድነትንና መከባበርን እንሻለን!

ከደቡብ አፍሪካ ነው ትምህርት እንውሰድ።Let us help each in this very unique difficult time!
19/03/2020

ከደቡብ አፍሪካ ነው
ትምህርት እንውሰድ።
Let us help each in this very unique difficult time!

ትርጉሙን እንዲህ ቀርበዋል!ግብፃውያኑን በገዛ የቴሌቭዥን ጣቢያው ሸከሸካቸው!!ኢትዮጵያውያን በየሄዱበት አያሳፍሩንምኮ!! አል አሸርቅ የሚባል የግብፅ መንግስት ተቃዋሚ የሆነ መሰረቱ ቱርክ ውስ...
17/03/2020

ትርጉሙን እንዲህ ቀርበዋል!

ግብፃውያኑን በገዛ የቴሌቭዥን ጣቢያው ሸከሸካቸው!!
ኢትዮጵያውያን በየሄዱበት አያሳፍሩንምኮ!!
አል አሸርቅ የሚባል የግብፅ መንግስት ተቃዋሚ የሆነ መሰረቱ ቱርክ ውስጥ የሖነ የግብፆች የቴሌቭሽን ጣቢያ በአረብኛ በህዳሴው ግድብ ዙሪያ ጋዜጠኛና ፀሃፊ የሆነ ወንድማችን መሐመድ አልዐሩሲ የሚባልን ኢትዮጵያዊ እንግዳ አድርጎት ነበር፡፡
በአርብኛ የተላለፈውን እንዲህ ተተርጉሞ ቀርበዋል።

አል አሸርቅ ፡- መሐመድ አልዐሩሲ እንኳን ደህና መጣህ፡፡
መሐመድ አልዐሩሲ:- እንኳን ደህና ቆያችሁኝ፡፡

አል አሸርቅ፡- የኢትዮጵያ የጦር ሃይል አዛዡና ከፍተኛ መኮንኖች ግድቡን ጎብኝተዋል፡፡ ይህንን ጉብኝት እንዴት ነው የሚተረጎመው? አንድምታው ምንድነው?

መሐመድ አልዐሩሲ፡- በመጀመሪያ ይህ ጥያቄ መጠየቅ የነበረበት ለጎብኚዎቹ ነበር፡፡ ቢሆንም ግን እኛ ኢትዮጵያዊያን በሀገራችን ላይ ለሚመጣ ማንኛውም አደጋ ምላሽ ለመስጠት ዝግጁ መሆናችንን ማሳያ ይመስለኛል፡፡ በአላህ ፍቃድ ማንኛውንም በሀገራችን የሚቃጣ ጥቃት ለመመከት ዝግጁ መሆናችንን ማሳያ ይመስለኛል፡፡

አል አሸርቅ፡- ታዲያ ግብፆች የደምስራቸው በሆነው የአባይ ውሃ ጉዳይ የሚመጣን ነገር ለመመከት ዝግጁ የማይሆኑ ይመስላችኋል ወይ?

መሐመድ አልዐሩሲ ፡- ግብፆች የሕዳሴው ግድብ በሀገራቸው ላይ ምንም አይነት ተፅዕኖ እንደማያመጣ እስከ አሁን በተደረጉ ድርድሮች ያውቃሉ፡፡ አሁን ግን በዚህ ሰበብ ሌላ የፖለቲካ ጨዋታ እየተጫወቱ ይመስለኛል፡፡

አል አሸርቅ፡- እኛ በመጀመሪያ አሁን ካለው መንግስት ጋር ተስማምተን የምንኖር አይደለንም፡፡ ቢሆንም ግን በአሁኑ ሰዓት ባለው ሁኔታ ኢትዮጵያ የውሃውን አሞላል በተመለከተ ሁሉም የተስማሙበትን አካሄድ ካልተከተለች ግብፆች ችግር ውስጥ እንደሚገቡ ግልፅ ነው፡፡ ይህንን እንዴት ታየዋለህ?

መሐመድ አልዐሩሲ፡- በነገራችን ላይ አሁን የምታነሱት የጉዳት ጉዳይ ትክክል አይደለም፡፡ ጉዳዮቹ ከዚህ ቀደም በውይይት በስለዋል፡፡ የውሃውን አሞላል በተመለከተ በኢትዮጵየ ደረጃ ከዚህ በፊት በ3 አመት ውስጥ እንዲሞላ የሚል አቋም ነበር፡፡ ነገር ግን በተደረገው ውይይት ወደ 7 አመት ከፍ እንዲል ተደርጓል፡፡

አል አሸርቅ፡- 7 አመት የሚባለው ስምምነት እንዴት እንደተፈፀመ በደንብ ማየት አለብን፡፡ ምክንያቱም በዚህ ስምምነት ላይ ከመንግስት ጋር ስምምነት ስላልነበረን አንስማማም፡፡ ሌሎች ያልተካተቱ ጉዳዮችም አሉ፡፡ ለምሳሌ የውሃ ድርቅ ቢያጋጥም እንዴት መፍታት እንደሚቻል አልተጠቀሰም፡፡ ይህ ባልሆነበት ኢትዮጵያ በመካከል የአሜሪካውን ስምምነት ሳትፈርም ወጥታለች፡፡ ይህን እንዴት ታየዋለህ?
እንደሚመስለኝ በእናንተ በኩል የሚሰጡ መግልጫዎች ጉዳዩን በማጓተት ግድቡን ከጨረሳችሁ በኋላ ግብፅ ምንም አማራጭ እንዳይኖራት ለማድረግ ያሰባችሁ ነው የሚመስለው፡፡

መሐመድ አልዐሩሲ፡- በመጀመሪያ በጣም ብዙ ነጥቦችን እያነሳህ ነው፡፡ ሆኖም ግን ኢትዮጵያ ከአሜሪካው ድርድር ላይ በፍጥነት ወጣች ላልከው ነገር ልዑኩ በዚህ ፍጥነት ላለመፈረም የፈለው በጉዳዩ ዙሪያ በሀገር ውስጥ ካሉ ሰዎች ጋር ለመመካከር ነው፡፡ ብቻውን መወሰን ስለማይችልና ዝም ብሎ ቢፈርም ኖሮ ድርድሩን አምኖ የሰጣቸው ማህበረሰብ ሊጠይቀው ስለሚችል ለሀገራቸው ያላቸውን ታማኝነት ያሳዩበት ነው፡፡ በሁለተኛ ያነሳህው… አንዳንድ የምናወራቸውን ነገር በጣም እርግጠኛ መሆን አለብን፡፡ 7 አመት ያለከው ነገር ያልተጣራ ነው ያልከው እንዲያውም አንተ ጋር ነው ያልተጣራ መረጃ ያለህ፡፡ እና እሱን ብታጣራ ጥሩ ነው፡፡

አል አሸርቅ፡- እኔ እስማውቀው እስከ ዛሬ ባለው የውሃ አሞላል ስምምነት በተመለከተ ጉዳዩን አለባብሳችሁ እያለፋችሁ ነው፡፡ እንዲያውም ዉሃውም የእኛ ነው ግድቡን የምንሰራውም በራሳችን ገንዘብ ነው እያላችሁ እንዴት ነው እየተወያየን ነው የምትሉት?

መሐመድ አልዐሩሲ፡- የተከበርክ ወንድሜ በወሬ ደረጃ ካየን እናንተም እኮ ይህ ውሃ የራሳሁ ብቻ እንደሆነ እያወራችሁ ነው፡፡ ከአባይ ውሃ ላይ አንድ ኩባያ እንኳ ማንም መጠቀም አይችልም እያላችሁ ነው፡፡ ነገር ግን ማየት ያለብህ ከዚህም ከዚያም የሚወራውን ሳይሆን በጉዳዩ ላይ መሬት እየሠሩ ያሉትን ነው፡፡ እኔ እስከማውቀው ሁለቱም ሀገራት ሳይጎዱ በፍትሃዊነት መጠቀም የሚቻልበትን ሁኔታ ላይ በባለሙያዎች ተጠንቶ ነው እየተሰራ ያለው፡፡ አሁን የማረጋግጥልህ ጉዳይ ግን ውሃው የራሳችን ነው፡፡ እኛ ሀገር ነው የበቀለው፡፡ ግድቡም የራሳችን ነው፡፡ ግንዘቡም ህዝብ ያዋጣው ነው፡፡ ዋናው ነገር ግን እናንተም ሳትጎዱ የምንጠቀምበትን ነገር ነው እያሠብን ያለንው፡፡

አል አሸርቅ፡- እና ታዲያ የትኛው ነው ፍትሃዊ እጠቃቀም ብለህ የምታስበውና በእናንተ በኩል?

መሐመድ አልዐሩሲ፡- የመንግስትን አስተሳሰብ እንተወውና ስታስቡት ግብፆች በራሳችን ውሃ፣ በራሳችን ቦታ ላይ ባለ ውሃ ‹‹ይሄ ነው የሚደርሰን›› እያሉ ብቻቸውን የሚወስኑት ፍትሃዊ ነው ብለህ ታስባለህ ወይ? የእናንተ ባለስልጣናት ‹‹እንደዚህ አድርጉ አታድርጉ እያሉ›› ብቻቸውን ነው ውሳኔ የሚያስቀምጡት፡፡ በጣም የሚገርመውኮ ውሃው ከእኛ ጋር ነው የሚነሳው፡፡ የመነሻው ሀገር ኢትዮጵያ እያለች የመድረሻዋ ሀገር ግብፅ ‹‹ይሄ ነው ይሄ የሚደርሰኝ ውሃ›› እያለች ኢትዮጵያ ‹‹ይሄ ይሄ ነው መደረግ ያለበት›› ስትል መቃወማችሁ የሚገርም ነው፡፡ አሁን ኢትዮጵያ የምትቃወመው ግብፅ እኔ በማስበው መንገድ ብቻ ነገሮች ካልሄዱ እያለች የምትለውን አካሄድ ነው፡፡

አል አሸርቅ፡- ወደ ሌላ ጉዳይ ልውሰድህና በዚህ ጉዳይ የእስራኤል እጅ እንዳለችበት ይሰማናል፡፡ እስራኤል በሀገራችሁ የተለያዩ የልማት ስራዎች እንዳላቸው ይታወቃል፡፡ እስራኤሎች ኢትዮጵያን ተጠቅመው ግብፅ ላይ ተፅዕኖ ለማሳደር እንደሆነ ይሰማናል፡፡ በዚህ ጉዳይ ላይ እስራኤል የለችበትም ብለህ ታስባለህ ወይ?
መሐመድ አልዐሩሲ፡- ይህ ክስ በጣም የሚገርም ክስ ነው፡፡ ግብፅ ከእስራኤል ጋር ምንም አይነት ግንኙነት እንደሌላቸው ከሚያስቡ ሰዎች ነው የመጣው፡፡ ይህ የወረደ ክስ ነው፡፡ እንዲያውም ይሕ ጥያቄ ለእናንተ ነበር መነሳት ያለበት፡፡ ኢትዮጵያ ስርዓቷ ከሃይማኖች ውጪ የሆነች ሀገር ናት፡፡ በሀይማኖት የተገነባች አይደለችም፡፡ ለእሷ ከሚጠቅማት ሀገር ጋር ግንኙነት የማድረግ መብት አላት፡፡ እንዲያውም ጥያቄው ለእናንተ መነሳት ነበረበት፡፡ ‹‹እኛ ሙስሊሞች ነን›› ትላላችሁ፡፡ ነገር ግን ከእስራኤል ጋር የጠበቀ ግንኙነት አላችሁ፡፡ እንያውም የእስራኤል እጅ እናንተ ጋር ነው ሊኖር የሚችለው፡፡

አል አሸርቅ፡- እኛ በዚህ አንስማማም፡፡ አሁን ያለው መንግስት ሙስሊሞችን አይወድም፡፡ ሙስሊሞችን እየገደለ፣ እያሰረና እያሳደደ ያለ መንግስት ነው፡፡ እኛን ከዚህ መንግስት መለየት አለብህ፡፡
… ይህንን ጉዳይ የበለጠ በማስረጃ ለማስደገፍ ጠቅላይ ሚኒስትራችሁ ከኔታንያሁ ጋር በተገናኙ ጊዜ እስራኤል በውሃ በመስኖ፣ በአየር መንግድና በሌሎች ጉዳይ አግዙን ብለው ጠይቀዋል፡፡ በዚህ ምክንያት ነው ከእስራኤል ጋር አብራችሁ እየሰራችሁ ግብፆችን ልትጎዱ እንደሆን እየተሰማን ያለው፡፡ እንዲያውም ሌላ መረጃ ብንጨምር ከእስራኤል በኩል የተለያዩ መሳሪያዎች እንደሚሰጣችሁ እናውቃለን፡፡ የመሳሪዎቹ አይነት ሁላ መረጃ አለን፡፡

መሐመድ አልዐሩሲ፡- አሁን የምታነሷቸው በሙሉ ዋጋ የሌላቸውና ጊዜ ያለፈባቸው ተራ ወሬዎች ናቸው፡፡ እንደ ሀገር የራሳችን የሆነ መሪና አመራር ያለን ነን፡፡ ከማን ጋር ግንኙነት መፈፀም እንዳለብን የምንወስነው ራሳችን ነን፡፡ ማንንም አማክረን ነገሮችን አናደርግም፡፡ ራሷን የሚጠቅማትን እና ሌሎችን የማይዳ ስምምነት ማድረግ ያለባት በራሷ ውሳኔ እንጂ እናንተን አማክረን አይደለም፡፡ የምታነሷቸው ጉዳዮች የእስራኤልና የህዳሴው ጉዳይ አሳስቧችሁ አይመስለኝም፡፡ ይህንን የምታደርጉት ህዝብ ለህዝብ ለማጋጨጥና ህዝብን ለማስጨረስ ጦርነትን እየቀሰቀሳችሁ ነው፡፡ ከመንግስት ጋር ተቃዋሚ ነን እያላችሁ ህዝብን ከህዝብ የሚጋጭ ተራ ወሬ ነው የምታወሩት፡፡

አል አሸርቅ፡- እንደዚያ አታስብ፡፡ ህዝብ ለህዝብ እንዲጣላ አንፈልግም፡፡ ከአንድ አካባቢ የተፈጠርን፣ አንድ አህጉር ላይ የምንኖር ብዙ የሚያገናኙን ጉዳዮች ያሉን ነን፡፡ እንጂ ህዝብ ለህዝብ እንዲጋጭ ፍላጎት የለንም፡፡ ይህንን ማወቅ አለብህ፡፡
ደግሞ እናስታውስህ… ኢትዮጵያኮ በተዘረፈ የፍልስጤም ምድር ላይ ለእስራኤል ወግና ፈላሺዎችን እየላከች እያሰፈረች ነው፡፡ እስራኤሎች ከፈላሺያዎቹ ባይስማሙም እንኳ ኢትዮጵያ እንደ ሀገር ፈላሺያችን እየላከች ከእስራኤል ጋር እየሰራች መሆኑን እንዴት ትክዳለህ?

መሐመድ አልዐሩሲ፡- በነገራችን ላይ የተከበርክ ወንድሜ ከያዝነው ጉዳይ ጋር የማይገናኙ ጉዳዮችን እየሳብክ ታመጣብኛለህ፡፡ ይህንን ነገር ቀድሜ አስረግጬ ነግሬሃለሁ፡፡ ኢትዮጵያ እንደ ሀገር የራሷ አመራር ያላት፣ ስርዓትና ስትራቴጂ ያላት ናት፡፡ ከማንም ጋር ግንኙነት ለመፍጠር ማንንም የማትጠይቅና የማታማክር፣ የምታደርገውን የምታውቅ፣ ለራሷ የሚጎዳትንና የሚጠቅማትን የምታውቅ፣ ማንም ገብቶ ውሳኔ የማይወስንባት ሀገር ናት፡፡ እንዲያውም ጉዳዩን የበለጠ እናውራበት ካልን እናንተ የአልሲሲን መንግስት እየተቃወማችሁና እያወገዛችሁ እያላችሁ፤ አሁን ስናያችሁ ከአሁን በፊት በእስራኤልና በግብፅ መካከል የተደረጉ ትልልቅ ጉዳዮችንና ውሳኔዎችን ሲወሰኑ የት ነበራችሁ? ለማሳሌ የዲቪድ ካምፕ ጉዳይ፡፡ አሁን ነወይ የኢትዮጵያና የእስራኤል ጉዳይ ያሳሰባችሁ? እኔ በጣም እያዘንኩ ነው፡፡ አሁን የምታነሷቸው ጉዳዮች ከውሃው ጋር ግንኙነት የሌላቸው አልባሌ ወሬዎች ናቸው፡፡ ካነሳንው ሃሳብ ጋር የሚገናኙ አይደሉም፡፡

አል አሸርቅ፡- እኛኮ ከካምፕ ዴቪድ ግንኙነት ሲደረግ ፈላሺዎችን አንስተን ወደ እስራኤል አልወሰድንም፡፡ ከዚያ ጋር ስናነፃፅረው ፋላሺያዎችን ወደ እስራኤል መውሰድ ወንጀል ሆኖ አግኝተንዋል፡፡ አሁን ጊዜ ስለሌለን አንድ ሰበሰብ ያለ ጥየቄ ልጠይቅህ፡፡ ግብፅ በአሁኑ ጉዳይ በጣም ተቆጥጣ የከፋ ነገር ወይም ጦርነት ብታነሳ ግብፅን በብርጭቆ እንደተሰራች ወይንም እንደ ደካማ ሀገር የሚያየው መንግስታችሁ ምን ሊያደርግ ይችላል?

መሐመድ አልዐሩሲ፡- በፍፁም እኔ ከግብፅ በኩል ኢትዮጵያን ሊጎዳ የሚችል ጦርነት ይመጣል ብየ አላስብም፡፡ ጉዳዩ የፖለቲካና የገንዘብ ጥቅም ለማግኘት እንዲሁም የሚዲያ ፍጆታ ከማግኘት ውጭ ይህ ነው የሚባል ነገር ይመጣል ብየ አላስብም፡፡

አል አሸርቅ፡- እንዴት ነው ከግብፅ ጦርነት መጥቶ ሊያጠቃን ይችላል ብለህ የማታስበው? ከዚህ በፊትኮ አፄ ሃይለስላሴን ገማል አብዱል ናስር በአንድ ደብዳቤ ነውኮ ግድቡን እንዳይሰራ ያስቆመው፡፡ ከዚያ በኋላምኮ በሳዳት ጊዜ እንደዚያው የእናንተ መንግስት ስርዓት እንዲይዝ ተነግሮት ነው አርፎ የተቀመጠው፡፡ ከዚያም በኋላ ግድቡ ቢሰራ ሊከሰት የሚችለውን ጥፋት ስለተነገራቸው ነው የቆመው፡፡ ሁስኒ ሙባረክ በነበረ ጊዜ እንኳ በጥቂት ደቂቃ ውስጥ የሰራችሁትን ግድብ አፈር ማብላት እንችላለን ብሎ ሳላለ ነውኮ እስከ አሁን የተቀመጣችሁት፡፡ አሁን 2020 ላይ መጥተህ እንዴት ነው ምንም ሊመጣ አይችልም የምትለው? እኛኮ ከእናንተ የተሻለ መከላከያ ያለን ነን፡፡ ጦርነት እንዲመጣ የምንመኝ አይደለንም፡፡ ጉዳዩ ከባሰ ግን እስከዚያ እንደሚኬድ የማትፈራው ለምንድነው?

መሐመድ አልዐሩሲ፡- ይህንን አይነት በራስ መተማመን ውስጥ ሆኜ የምናገረው አሁን ባነሳህው ጉዳይ ምክንያት ነው፡፡ እስከ ዛሬ ድረስ እነ ገማል አብዱልናስርም በላቸው ሌሎች አወሩ እንጂ ምንም የፈጠሩት ነገር የለም፡፡ አሁንም ወሬ እንጂ ሌላ የሚመጣ ነገር አይኖርም፡፡ እነዚህ የጠቀስካቸው መንግስታት በሙሉ በኢትዮጵያ ላይ ጦርነት እንሰብቃለን የሚሉት በኢትዮጵያ ብቻ ሳይሆን በአፍሪካውያን በሙሉ ስምምነት ውስጥ ባልገባ በቅኝ ግዛት ሀገርን ይዘው በነበሩ ( በእንግሊዝ በፈረንሳይ…) ጉዳይ ነው፡፡ ግብፅ ክእነዚህ ሀገራት ጋር ብቻዋን ተስማምታ ነበር፡፡ የአፍሪካ ሀገራት ባልተስማሙበት ጦርነት ቢነሳ ጦርነቱ ከኢትዮጵያ ጋር ብቻ ሳይሆን ከአፍሪካ ከአህጉሩ ጋር ነው፡፡ ትልቅ ፈተና በራሷ ላይ ማምጣት ካልፈለገች በስተቀር ግብፅ ይህንን አትፈፅምም፡፡
አል አሸርቅ፡- በጣም የሚገርም ነው!! አንተ ፀሃፊ ነህ፡፡ ብዙ ጉዳዮችን ታውቃለህ ብለን እናስባለን፡፡ ነገር ግን መቶ በመቶ ለሀገርህ ብቻ ነው የምታደላው፡፡ ይሄ ልክ ነወይ?

መሐመድ አልዐሩሲ፡- ታዲያ ለሀገሬ ነው እንጂ ለማን ነው የማደላው፡፡ ላበቀለኝና ለምኖርበት ሀገር ነው ራሴን የምሰጠው፡፡ ሙሉ ለሙሉ እየደረገፍኩ ያለሁትም ለዚያ ነው፡፡

አል አሸርቅ፡- ያለው እንዳለ ሆኖ አንተ ሀገርክን እንደደገፍከው ሁሉ እዚህ ያሉት ሰዎችስ አያሳዝኑህም ወይ? የግብፅ ህዝብ የሚጎዳ መሆኑን እያወክ ዝም ብለህ ትደግፋለህ ወይ?

መሐመድ አልዐሩሲ፡- እንዲያውም ግራ ጎኖቻችን ለሆኑት ወንድሞቻችን ፈፅሞ ከእነሱ የበለጠ የምናስብላቸው ነው የሚመስለኝ፡፡ ግድቡም እነሱን እንማይጎዳ ነው የምናስበው፡፡ ለወንድሞቻችን መጥፎ ነገር አናስብም፡፡ እንዲያውም ከግብፆች በኩል የሚሰማውን አስቀያሚ ነገር ጆሮ ዳባ ልበስ ብለን መልካም በሆነ ነገር እንዴት ያልቅላቸዋል ብለን ነው የምነስበው፡፡

አል አሸርቅ፡- ይህ ንግግራችሁማ በጣም ይጣፍጣል፡፡ መልካምነትን መስበካችሁ የተለመደ ነው፡፡ እስከ አሁንም እንዲህ እያላችሁ እያጓተታችሁ መጥታችሁ አሁን የፊርማው ጊዜ ስትደርሱ እጃችሁን ሰበሰባችሁ፡፡ አሁን መንግስታችን የፈረመውን እኛ የተስማማንበት እንኳ ባይሆን አንፈርምም ብላችሁ ግብፆችን በውሃ ድርቅ ልትገድሏቸው ነው፡፡

መሐመድ አልዐሩሲ፡- ይሄ ተራ አሉባልታ ነው፡፡ ወፍ ዘራሽ ወሬ ነው፡፡

አል አሸርቅ፡-እንዴት እንደዚህ ትላለህ? እኛ በፍፁም ያልተጨበጠ ወሬ አላወራንም፡፡ በመረጃ ነው የምናወራው፡፡

መሐመድ አልዐሩሲ፡- በነገራችን ላይ እናንተኮ መሬታችሁ ላይ ብዙ ውሃ ያላችሁ ሰዎች ናችሁ፡፡ ለምንድነው ውሃችሁን ከመሬታቸሁ ውስጥ አውጥታችሁ የማትጠቀሙት? ይህንን ውሃችሁን ብትጠቀሙት ኖሮ አሁን የምታስወሩት የውሃ እጥረት በሌለ ነበር ፡፡ እንዲያውም ኢትዮጵያ እስከ አሁን እያደረገች ያለችው ስምምነት ግብፅ ላይ ምንም አይነት ጉዳት እንደማያሳድር ከእኛ በበለጠ ታውቃላችሁ፡፡ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ እቶ ገዱ አንዳርጋቸው እየተናገሩ ያሉት ነገር የሚያረጋግጠውም ይህንን ነው፡፡ ሌላው ቀርቶ በውሃ አሞላሉ ላይ ችግር ቢፈጠር እንኳ እንዴት መፍታች እንደሚቻል ነው፡፡ አያምጣውና ከባድ ነገር ቢፈጠር እንኳ እኛ ካጠራቀምንው ውሃ ላይ እንዴት ለእናንተ መድረስ እንደሚቻል እያሰብንበት ነው፡፡ እንደ ሀገር ምንም አይነት ጉዳት እንዲደርስባችሁ አንፈልግም፡፡ የእኛ ወዳጆች ናችሁ፡፡ ወዳጅ ሆናችሁ ትቀጥላላችሁ፡፡ እኛ የምንፈልገው ሀገራችንን አሳድገን ተጠቃሚ ሆነን እናንተም የድርችሁን የምታገኙበትና የምትጠቀሙበትን ነገር ነው፡፡

አል አሸርቅ፡- መሀመድ በጣም እናመሰግናለን፡፡ አንተ ለሀገርህ እንደቆምከው ሁሉ እኛም ሀገራችንን የምንወድና ለሀገራችን ቆመን ነው ይህንን ያነሳነው፡፡ ውይይቶቹ ይቀጥላሉ፡፡ የፖለቲካ ተንታኝና ፀሃፊ መሀመድ አልዐሩሲ እናመሰግናለን፡፡
ይደረግ

15/03/2020

"በኮሮና ቫይረስ የተያዙት ሰዎች ቁጥር አራት ደርሷል። በተጨማሪ የተያዙት ሶስት ሰዎች በሙሉ ከመጀመሪያው ታማሚ ጋር ቀጥተኛ ግንኙነት የነበራቸው ናቸው። ከእነርሱ መሀከል አንዱ የ42 አመት ኢትዮጵያዊ ነው። ሶስቱ ጃፓናውያን ናቸው።"

ስለዚህ
መረጃውን ለህዝብ በሙሉ በማደረስና ጥንቃቄ በመጨመር ላይ ሁላችንም ሀላፊነታችንን እንወጣ ዘንድ አደራ እላለሁ።

★ እኔ አልጨብጥም። ከንክኪ ራሴን እቆጥባለሁ።
★ እኔ እጄን በአግባቡ ደጋግሜ በመታጠብ ንፅህናዬን እጠብቃለሁ።
★ ሳስነጥስም ሆነ ሳስል አፍና አፍንጫዬን እሸፍናለሁ።
★ ሳልና ትኩሳት ከተሰማኝ ከቤት ባለመውጣት ሀላፊነቴን እወጣለሁ።
★ የትንፋሽ መቆራረጥ ካጋጠመኝ ራሴን ጠብቄ ወደ ህክምና ጣቢያ እሄዳለሁ። በነፃ የስልክ መስመር 8335 ለሚመለከተው አካል አስታውቃለሁ።

#ኮሮና
#ኮሮናመረጃ
#ኢትዮጵያኮሮና
#ኮቪድ19
#ኃላፊነቴንእወጣለሁ

BREAKING NEWS!CORONA VIRUS VACCINE!
14/03/2020

BREAKING NEWS!
CORONA VIRUS VACCINE!

ከአዲስ አበባ ምክትል ከንቲባ ታከለ ዑማ የተላለፈ መልዕክት★★★★★★★★★★★★★★★★★★★ለአዲስ አበባ ነዋሪዎች፤ በተደረገው ምርመራ አንድ ጃፓናዊ  የኮሮና ቫይረስ ተገኝቶበታል። ሁላችንም ከ...
13/03/2020

ከአዲስ አበባ ምክትል ከንቲባ ታከለ ዑማ የተላለፈ መልዕክት
★★★★★★★★★★★★★★★★★★★
ለአዲስ አበባ ነዋሪዎች፤

በተደረገው ምርመራ አንድ ጃፓናዊ የኮሮና ቫይረስ ተገኝቶበታል።

ሁላችንም ከእጅ ንክኪዎች እና አላስፈላጊ ስብሰባዎች እንቆጠብ ለማለት እፈልጋለሁ።

አላህ በጥበቡ ሀገራችንን ይጠብቅልን። የመጀመሪያው የኮሮና ቫይረስ በአዲስ አበባ በአንድ ጃፓናዊ ዜጋ ላይ ተገኝቷል። ስለዚህ ተገቢውን ጥንቃቄ እናድርግ። 1) ማንኛውንም የእጅ ንክኪ እንቆጠብ...
13/03/2020

አላህ በጥበቡ ሀገራችንን ይጠብቅልን።

የመጀመሪያው የኮሮና ቫይረስ በአዲስ አበባ በአንድ ጃፓናዊ ዜጋ ላይ ተገኝቷል።

ስለዚህ ተገቢውን ጥንቃቄ እናድርግ።
1) ማንኛውንም የእጅ ንክኪ እንቆጠብ!
2) በተደጋጋሚ የእጅ ንፅህናችንን እንጠብቅ።
3) በብዛት ሰው በሚሰበሰብባቸው ቦታዎች ላይ አንገኝ።
4) በምናስነጥስበት ወቅት አፍና አፍንጫችንን እንሸፍን።
5) ለመሸፈኛ የተጠቀምንባቸውን ማንኛውንም ነገሮች በተገቢው መልኩ በቆሻሻ መጣያ ላይ እናስወግድ።
6) ማስነጠስ፣ ትኩሳትና የጉሮሮ ህመም የታየበት ሰው በፍጥነት ወደ ህክምና ጣቢያዎች በመሄድ ምርመራውን ያድርግ። በነፃ የስልክ መስመርም 8335 ላይ ደውሎ ለህክምና ባለሙያዎች ያሳውቅ።

★በዋንኝነት በንስሃና በፀፀት ወደ አላህ እንመለስ። ዱዓም አብዝተን እናድርግ።

What the hell is gone on ?
10/03/2020

What the hell is gone on ?

ይድረስ ለአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደርለአዲስ አበባ ፖሊስለአዲስ አበባ የሰላምና የፀጥታ ጽ/ቤት★★★★★★★★★★★★★★★★★★★★★የአብዱልጀሊል አሊ ካሳን "ተምኔታዊ ደሴት" የተሰኘውን መጽሐፉ...
07/03/2020

ይድረስ ለአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር
ለአዲስ አበባ ፖሊስ
ለአዲስ አበባ የሰላምና የፀጥታ ጽ/ቤት
★★★★★★★★★★★★★★★★★★★★★
የአብዱልጀሊል አሊ ካሳን "ተምኔታዊ ደሴት" የተሰኘውን መጽሐፉን በተያዘለት ቀጠሮ ነገ በአምባሳደር ሲኒማ አዳራሽ እንዳይመረቅ ልደታ ክፍለ ከተማ በኩል ሴራ መጀመሩን እየሰማን ነው። ከጀርባ ያለው አካል ማነው? አማረ የሚባለው የክ/ከተማው የሰላምና የፀጥታ ዘርፍ ኃላፊ ወደ አምባሳደር ሲኒማ ደዉሎ "መጽሐፉን ሳናነበውና ሳናምንበት ነው የፈቀድነው። ምርቃቱ እንዳይደረግ" ብሎ በስልክ ማዘዙን ሰማን።ያለፈው ሳምንት ሊመረቅ የነበረው መጽሐፍ ወደ ነገ የተዛወረው የመፅሐፍ ምርቃቱን በማይፈልጉ አካላት ጫና መሆኑን ሰማን። የነገውም አስፈላጊውን ቅድመ ሁኔታ ካሟላ በኋላ መከልከሉ በቸልታ የሚታለፍ አይደለም።ቀልዱ ይበቃል።
Ahmedin Jebel Official - አህመዲን ጀበል

መነበብ ያለበት ወሳኝ መረጃየሰው ሕይወት ሳይቀር የጠፋበት ቦታ የአቶ ሪያድ ደማጅ የተባሉ ሰው ቦታ መሆኑን ዋዜማ ራዲዬ አረጋግጣለችየዋዜማ መረጃን እንደሚከተለው ይቀርባል ዋዜማ ራዲዮ- ጥር ...
06/03/2020

መነበብ ያለበት ወሳኝ መረጃ

የሰው ሕይወት ሳይቀር የጠፋበት ቦታ የአቶ ሪያድ ደማጅ የተባሉ ሰው ቦታ መሆኑን ዋዜማ ራዲዬ አረጋግጣለች

የዋዜማ መረጃን እንደሚከተለው ይቀርባል

ዋዜማ ራዲዮ- ጥር 24 ቀን 2012 በአዲስ አበባ ከተማ ቦሌ ክፍለ ከተማ ወረዳ 4 እና 5፣ ሀያ ሁለት አካባቢ ከቅዱስ ገብርኤል ሆስፒታል ፊትለፊት ልዩ ስሙ 24 ተብሎ በሚታወቀው ስፍራ ሌሊቱን ህግን እናስከብራለን ያሉ የጸጥታ ሀይሎች በከፈቱት ተኩስ ሁለት ወጣቶች (ምዕመናን) ሲገደሉ በርካቶችም ቆስለዋል። ጽላትን ጨምሮ በርካታ ንዋየ ቅድሳት እንደተወሰዱባትም ቤተክርስቲያን ገልጻለች።ነገሩም ትልቅ ውዝግብን ያስነሳ ሆኖ ሰንብቷል። ዋዜማ ራዲዮ ይህ እጅግ አሳዛኝ ድርጊት የተፈጸመበት ቦታን አስመልክቶ ሰፊ መረጃ የማሰባሰብ ስራን ሰርታለች።

መረጃውን ለማግኘት የቦሌ ክፍለ ከተማ ወረዳዎችን፣ የከተማ አስተዳደሩን የመሬት አስተዳደርና ፕላን ኮሚሽን ምንጮቻችንን ያናገርን ሲሆን ፣ ችግር የተፈጠረበት መሬት ሲጀመር ባለቤትነቱ የማነው? እንዴት የዕምነት ተቋም የውዝግቡ አካል ሆነ ? የሚሉትን ጉዳዮች ለመረዳት ሞክረናል።

የመሬቱ ባለቤትነት

አሁን ችግር የተፈጠረበት በቦሌ ክፍለ ከተማ ወረዳ 4 እና 5 ላይ ያለው መሬት 17 ሺህ 115 ካሬ ስፋት ያለው ሲሆን መለያ ቁጥሩ A – 7357 ፣ የቦታው አገልግሎትም የድርጅት መሆኑን ይጠቁማል። የዚህ ቦታ ህጋዊ ሰነድ ያላቸው ግለሰብም አቶ ሪያድ ደማጅ እንደሚባሉ ለመረዳት ችለናል። ከቦሌ ክፍለ ከተማ ፣ ሁለቱ ወረዳዎች እና ከከተማ አስተዳደሩ የመሬት አስተዳደርና ፕላን ኮሚሽን ምንጮቻችን መረዳት እንደቻልነው አሁንም በህይወት ያሉት አቶ ሪያድ ደማጅ ባለቤት ከመሆናቸው በፊት መሬቱ አስቀድሞ በሌሎች ግለሰቦች ባለቤትነት ስር የነበረ ሲሆን ሁለት ጊዜ ተሽጦ ነው አቶ ሪያድ በ1985 አ.ም የገዙት። በደርግ ጊዜ የተሰራው ካርታም እጃቸው ላይ አለ ። ከወረዳ እስከ ከተማ አስተዳደሩ ያሉ ቢሮዎች ይህ መረጃ አላቸው።

እንደ አስተዳደሩ ባለሙያዎች ማብራሪያ ከሆነ የደርግ ካርታ አሁንም ህጋዊነቱን ያላጣ ሲሆን የካርታው ባለቤት ስፍራው ላይ ግንባታ ማከናወን ፈልጎ ማመልከቻ ካስገባ ነው እንዲቀይር የሚጠይቀው። አቶ ሪያድም መሬቱን መግዛታቸውንና ባለቤት መሆናቸው በፍርድ ቤት ተረጋግጦላቸዋል ፣ የሽማግሌዎች ውልም አላቸው ። ሰነድ አልባ በሚለው ቢወሰድም የይዞታው ባለቤት መሆናቸውን አያጡም።

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ቤተክርስቲያን የማምለኪያ ቦታ በስፍራው ተሰርቶ ከጥቂት ሳምንታት በፊት ችግር ከመነሳቱም በፊት አቶ ሪያድ በስፍራው ላይ መጋዘን እና ሁለት የቅርብ ሰዎቻቸውን የሚያኖሩበት ቤት አላቸው። ታድያ ይህ ሰፊ መሬት እስካሁን ሙሉ ለሙሉ ጥቅም ላይ ሳይውል ለዚህ አሳዛኝ ነገር መፈጠሪያነት እንዴት በቃ?

ዋዜማ ራዲዮ ያገኘችው መረጃ እንደሚያሳየው በቦሌ ክፍለ ከተማ ያለው መሬት ባለቤት እንዳለው በመንግስት ቢታወቅም ቦታው እጅግ ተፈላጊ ስፍራ ላይ ያለ በመሆኑ ብዙ ፈላጊ ነበረው። ሆኖም አቶ ሪያድ ቦታውን ለማልማት ካርታ ተለውጦ እንዲሰራላቸው ጥያቄ ቢያቀርቡም በወቅቱ የነበሩ የመንግስት ባለስልጣናት ከባለሀብቶች ጋር በመመሳጠር ቦታውን እንዲለቁ ያግባቡዋቸው ነበር ።

ቦታውን ሪል ስቴቶች በተለይ አጥብቀው ይፈልጉት ነበር። መስኪድ እንዲሰራበትም ጥያቄ ቀርቦላቸው ነበር። ሆኖም አቶ ሪያድ ደማጅ ራሳቸው በንግድ ስራ የተሰማሩ በመሆናቸው ቦታውን ለማልማት አቅም እንዳላቸው በመጥቀስ ጥያቄ ያቀርባሉ። በወቅቱም የቦሌ ክፍለ ከተማ ለአዲስ አበባ ከተማ መሬት አስተዳደር ካርታ እንዲሰራላቸው ደብዳቤም ጽፎ ነበር። ሆኖም ከ2000 አ.ም በሁዋላ ለቅይጥ አገልግሎት ጥቅም ላይ እንዲውል ተለይቶ የነበረው ቦታ የአረንጓዴ ልማት ቦታ ነው ተብሎ ፕላኑ እንዲቀየር ይደረጋል።

ምንጮቻችን እንደነገሩን መሬቱን ለአረንጓዴ ልማት ይሁን ተብሎ ፕላኑ እንዲቀየር የተፈለገው እውነት አረንጓዴ ልማት እንዲሰራበት ተፈልጎ ሳይሆን የመንግስት የስራ ሀላፊዎች በሚሊየን የሚቆጠር ብር ሙስና ጠይቀውበት እምቢ ስለተባሉ የመሬቱን ባለቤት አቶ ሪያድን መሬቱን ለማስለቀቅ በማሰብ ነው።

በዚሁ መሀልም የአዲስ አበባ አካባቢ ጥበቃ ቢሮ ካርታ እንዲያወጣበት ይደረጋል። የአካባቢ ጥበቃ ቢሮው ካርታ እንዲያወጣ የተደረገበት መንገድ ራሱ ፍጹም ህገ ወጥ እና መሬቱ ከማን ተወስዶ አዲስ ካርታ እንደወጣበት ራሱ እውቅና ባልተሰጠበት ሁኔታ ነው። ካገኘናቸው መረጃዎች እንደተረዳነውም መሬቱ ጥቅም ላይ እንዳይውል የሆነውም የቦታው ህጋዊ ባለቤት ውሳኔውን ለማስቀልበስ ባደረጉት ትግልና መሬቱን ለመቀራመት በቀድሞ የመንግስት ባለስልጣናት በተሰራ ውስብስብ ስራ ነው።

እስከ ቅርብ ጊዜም የቦታው ባለቤትነት ጉዳይ ተንጠልጥሎ የቆየ ነው። የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክክርስቲያን በዚህ ቦታ ላይ ቤተክርስቲያን ለመስራት ከ1988 አ.ም ጀምሮ ጥያቄን ስታቀርብ እንደነበር ጉዳዩን እየተከታተሉ ያሉ ተወካዮች ይናገራሉ። ቦታው ህጋዊ ባለቤት እንዳለው ግን እንደማያውቁ ፣ ቤተ ክርስቲያንም ቦታው ላይ ጥያቄ ስታቀርብ የቆየችውም እንደማንኛውም ፍላጎት እንዳለው አካል መሆኑንም ይገልጻሉ።

በይዞታው ላይ ይህ ሁሉ እንቅስቃሴ ሲደረግ የመሬቱ ህጋዊ ባለቤት አቶ ሪያድ በቦታው ላይ ያለውን እንቅቃሴ በፍርድ ቤት ሊጠይቁ እንቅስቃሴ ላይ ነበሩ።በዚህ መሀል ከጥቂት ሳምንታት በፊት በሌሊት ህግ እናስከብራለን ባሉ የጸጥታ አካላት በተተኮሰ ጥይት ሁለት ወጣቶች ህይወታቸው አልፏል፣ በርካቶችም ቆስለዋል።

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን አሁን ወጣቶች የተገደሉበት ቦታ ቤተክርስቲያን እንዲሰራበት በቅዱስ ሲኖዶስ በኩል ጥያቄን አቅርባለች። ዋዜማ ራዲዮ ግን መሬቱ ህጋዊ ባለቤት ናቸው ለተባሉት አቶ ሪያድ ደማጅ እንዲሰጥ የመጨረሻ ውሳኔ እየተጠበቀ መሆኑን ሰምታለች። [ዋዜማ ራዲዮ]

02/03/2020

Address

Addis Ababa

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Current Media Corporate-CMC. posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share