CDU TUBE

CDU TUBE Contact information, map and directions, contact form, opening hours, services, ratings, photos, videos and announcements from CDU TUBE, Broadcasting & media production company, Addis Ababa.

06/07/2025
ሰበር ዜና ➖➖➖➖➖➖➖➖➖➖➖➖➖➖➖➖➖የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ አ.ማ ውድድር አመራርና ስነ-ስርዓት ኮሚቴ ወሳኔ!የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ውድድር አመራርና ስነ-ስርዓት ኮሚቴ ማክሰኞ ሰኔ 25...
04/07/2025

ሰበር ዜና
➖➖➖➖➖➖➖➖➖➖➖➖➖➖➖➖➖
የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ አ.ማ ውድድር አመራርና ስነ-ስርዓት ኮሚቴ ወሳኔ!

የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ውድድር አመራርና ስነ-ስርዓት ኮሚቴ ማክሰኞ ሰኔ 25 2017 ዓ.ም ባደረገው ስብሰባ የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ሰኔ 24 2017 በተራ ቁጥር 3 ላይ ባስተላለፈው ውሳኔ መሰረት ውሳኔዎችን በሲዳማ ፣ በመቻል እና በሀዋሳ ከተማ ስፖርት ቡድኖች ላይ አስተላልፏል።

ሶስቱ ክለቦች በኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የክለቦች የክፍያ ስርዓት አስተዳደር መመሪያን በመተላለፍ እግድ ከተጣለባቸው ተጫዋቾች መካከል ቢያንስ አንዱን አሰልፈው ስለማጫወታቸው በእለቱ ጨዋታውን ከመሩት ዳኞች ከቀረበው ሪፖርት ተረጋግጦ ውሳኔዎች ተላልፈዋል።

ክለቦቹ ተጫዋቾቹን በመጠቀም ያደረጓቸውን ጨዋታዎች በፎርፌ እንዲሸነፉ ለተጋጣሚዎቹ በሙሉ 3 ነጥብና 3 ንጹህ ግቦች ፤ ለሶስቱ ክለቦች ደግሞ በእያንዳንዱ ጨዋታ 0 ነጥብ እና 3 የግብ እዳ እንዲመዘገብ የውድድርና ስነስርዓት ኮሚቴ ወስኗል።

በተሰጡት የፎርፌ ውሳኔዎች መሰረት የ2017 የፕሪሚየር ሊግ ደረጃና ግብ አግቢዎች እንደሚከተለው ተስተካክሏል።

የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ አ.ማ ውድድር አመራርና ስነ-ስርዓት ኮሚቴ

 #እግዚአብሔር ያስገርማችሁ እንደዚህ ሰርግ _።ይሄ ሰርግ የባለስልጣን ወይም የባለሃብት እንዳይመስልህ  ነገሩ እንዲህ ነው የ2 የሚያገኙት ከገቢ አንጻር ለእንደዚ አይነት ሰርግ ለማዘጋጀት ይ...
24/06/2025

#እግዚአብሔር ያስገርማችሁ እንደዚህ ሰርግ _።

ይሄ ሰርግ የባለስልጣን ወይም የባለሃብት እንዳይመስልህ ነገሩ እንዲህ ነው የ2 የሚያገኙት ከገቢ አንጻር ለእንደዚ አይነት ሰርግ ለማዘጋጀት ይቅርና ለማሰብም በፍጹም የሚከብድ ነገር ግን የሞተላቸውን እየሱስ ሁሌም ስሙን ጠርተው የማይጠግቡ የጌታ ወዳጆች ሰርግ ነው እግዚአብሔር በመገኘቱ ብቻ ነው እንዲ እልል ድምቅ ያለው

የብዙ አገልጋዮች የፀሎት ውጤት


የተባለው ሰርግ እግዚአብሔር በመገኘቱ በእንደዚህ መልኩ እግዚአብሔር ራሱ የሉም የተባለውን #ኮሚቴዎችንና #ሚዜዎችን እንዲሁም #ሕዝቡን ተጠቅሞ የተከተሉትን ጌታ በዚህ መልኩ ተድረዋል ።
ሙሽራውም ሲናገር ለእጮኛዬ 3 ወር ገደማ ቀርቶ እያለ ለሰርጋችን ማንንም ማስቸገር የለብንም አይኖረንም ስለዚህ
በ መኪና መጥቼ እወስድሻለሁ ከቤት ከዛን ወደ ቤተክርስትያን ቀለበት አድርገን ጋብቻ ፈጽመን ቀለል እናደርገዋለን ነበር ያላት።

ጌታ ሁለቱን ጥንዶች አስደንቆ አስገረማቸውም አሳቃቸውም!!

ስለሙሽራው የሆነ ነገር እንበላችሁ ሙሽራው ወንጌልን በተለያዩ ጎዳናዎች ላይ እየሱስን በመመስከር ይታወቃል በሰርጉም ዕለት ያከበረውንና ያስገረመውን እየሱስ በጎዳናዎች ላይ ብዙ ሰዎች በተገኙበት መስክሯል፡፡

ብቻ እመኑ እንጂ እግዚአብሔር አያሳፍራችሁም

የኢራን ፓርላማ ወሳኙን የሆርሙዝ የባህር ሰርጥን ለመዝጋት የቀረበውን ሀሳብ አፀደቀ **************************የኢራን ፓርላማ የአለማችን 20 በመቶ የሚሆነው ድፍድፍ ነዳጅ የሚ...
22/06/2025

የኢራን ፓርላማ ወሳኙን የሆርሙዝ የባህር ሰርጥን ለመዝጋት የቀረበውን ሀሳብ አፀደቀ
**************************

የኢራን ፓርላማ የአለማችን 20 በመቶ የሚሆነው ድፍድፍ ነዳጅ የሚተላለፍበት የባህር ሰርጥን ለመዝጋት የቀረበውን የውሳኔ ሀሳብ አፅድቋል፡፡

ፓርላማው ውሳኔውን ያስተላለፈው አሜሪካ እስራኤልን በማገዝ በኢራን ሶስት የኒውክሌር ማብለያ ተቋማት ወታደራዊ እርምጃ መውሰዷን ተከትሎ ነው።

የፓርላማው ውሳኔ ተፈጻሚ የሚሆነው የኢራኑ መሪ አያቶላህ አሊ ኻሚኒ በሚያሳልፉት የመጨረሻ ትእዛዝ መሆኑ ተነግሯል።

40 ኪሎ ሜትር ብቻ ስፋት ያለው የሆርሙዝ የባህር ሰርጥ የመዘጋት አደጋ ካጋጠመው በአለም የነዳጅ ዋጋ ላይ ትልቅ ተፅእኖ ሊፈጥር እንደሚችልም ተገልጿል፡፡

የኢራን ፓርላማ ያቀረበው ይህ ውሳኔ የኢራኑን መሪ የአያቶላህ አሊ ኻሚኒን የመጨረሻ ውሳኔ እየጠበቀ ነው ሲል ኒውስ ዊክ የኢራን ቴሌቪዥንን ጠቅሶ ዘግቧል።

የሆርሙዝ የባህር ሰርጥ ፈሳሽ ነዳጅና የተፈጥሮ ጋዝ የጫኑ መርከቦች ዋነኛ መተላለፊ ሲሆን፤ እኤአ 2024 በየቀኑ ብቻ 20.3 ሚሊዮን በርሜል ነዳጅና ፔትሮሊየም ተላልፎበታል ተብሏል።

አሜሪካ ፎርዶውን ጨምሮ ኢራን ውስጥ በሚገኙ 3 የኒውክሌር ተቋማት ላይ ጥቃት ማድረሷን ተከትሎ ኢራን በቀጣይ ምን አይነት እርምጃ ትወስዳለች የሚለው የሚጠበቅ ሆኗል።

በላሉ ኢታላ

ስለአሜሪካ ጥቃት ዓለም ምን አለ?*************አሜሪካ በኢራን ላይ የፈፀመችውን ጥቃት ተከትሎ ዓለም ምን ምላሽ እየሰጠ ነው?አፍሪካ በግለሰቦች ከሚሰነዘሩ ሃሳቦች በስተቀር በዛሬው የአ...
22/06/2025

ስለአሜሪካ ጥቃት ዓለም ምን አለ?
*************

አሜሪካ በኢራን ላይ የፈፀመችውን ጥቃት ተከትሎ ዓለም ምን ምላሽ እየሰጠ ነው?

አፍሪካ በግለሰቦች ከሚሰነዘሩ ሃሳቦች በስተቀር በዛሬው የአሜሪካን ጥቃት ላይ እስከአሁን ዝምታን መርጣለች። አንድም የአፍሪካ መንግስት እስከአሁን በጉዳዩ ላይ ያለው ነገር የለም።

ሆኖም በርካታ የዓለም ሀገራትና ቡድኖች እንዲሁም የተለያዩ መገናኛ ብዙሃን በጉዳዩ ላይ ሃሳብ እየሰነዘሩ ይገኛሉ።

ሳውዲ አረቢያ
የሳውዲ አረቢያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር በኤክስ (X) ገጹ ባወጣው መግለጫ፥ አሜሪካ የፈጸመችውን ጥቃት ተከትሎ ከፍተኛ ስጋት እንዳደረበት ገልጿል።

ጃፓን
የጃፓን ጠቅላይ ሚኒስትር ሺገሩ ኢሺባ፥ "ግጭቱ በፍጥነት እንዲረግብ ማድረግ ወሳኝ ነው፤ ሁኔታውን በከፍተኛ ስጋት በቅርበት እየተከታተልነው ነው" ብለዋል።

ቻይና
የቻይና መንግሥታዊ መገናኛ ብዙኃን ባቀረበው ትንታኔ፥ አሜሪካ "በኢራቅ የሰራችውን ስህተት በኢራን ላይ እየደገመችው ነው?" የሚል ጥያቄን አንስቷል።

ደቡብ ኮሪያ
የደቡብ ኮሪያ የፕሬዚዳንት ጽ/ቤት የአሜሪካን ጥቃት ተከትሎ ሊከሰቱ የሚችሉ የጸጥታና የኢኮኖሚ አንደምታዎችን ለመገምገም አስቸኳይ ስብሰባ ጠርቷል።

ኒውዚላንድ
የኒውዚላንድ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዊንስተን ፒተርስ የመካከለኛው ምስራቅ ሁኔታ "እጅግ አሳሳቢ" መሆኑን ገልጸው፤ ለችግሩ መፍትሄ ለመሻት ዲፕሎማሲያዊ ጥረት እንዲደረግ አሳስበዋል።

አውስትራሊያ
የአውስትራሊያ መንግሥት ቃል አቀባይ በሰጡት መግለጫ፥ "በቀጣናው ያለው የጸጥታ ሁኔታ እጅግ ውጥረት የነገሰበት ነው፤ ውጥረቱ እንዲረግብ፣ በውይይትና በዲፕሎማሲ እንዲፈታ ጥሪያችንን እንቀጥላለን" ብለዋል።

ሜክሲኮ
የሜክሲኮ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር በኤክስ (X) ገጹ ባስተላለፈው መልዕክት፥ "በመካከለኛው ምስራቅ ግጭት ውስጥ ያሉ ወገኖች ለሰላም ሲባል አስቸኳይ ዲፕሎማሲያዊ ውይይት እንዲያደርጉ" ጠይቋል።

ኩባ
የኩባው ፕሬዚዳንት ሚጌል ዲያዝ-ካኔል በኤክስ (X) ገጻቸው ላይ፥ "አሜሪካ በኢራን የኑክሌር ተቋማት ላይ የፈጸመችውን የቦምብ ጥቃት በጽኑ እናወግዛለን፤ ድርጊቱ በመካከለኛው ምስራቅ ግጭቱን ወደ አደገኛ ምዕራፍ የሚያሸጋግር ነው" ሲሉ አስፍረዋል።

ዲያዝ-ካኔል አክለውም፥ "ይህ ጥቃት የተባበሩት መንግሥታት ቻርተርን እና ዓለም አቀፍ ሕግን በእጅጉ የሚጥስ ከመሆኑም በላይ፤ የሰው ልጅን የማይቀለበስ ቀውስ ውስጥ የሚከት ነው" ብለዋል።

ዩናይትድ ኪንግደም
የብሪታንያው ጠቅላይ ሚኒስትር ኬር ስታርመር፥ ኢራን ቀውሱን በዲፕሎማሲ ለመፍታት ወደ ድርድር ገበታ እንድትመለስ ጥሪ አቅርበዋል። አክለውም፥ ውጥረት በነገሰበት በዚህ ቀጣና መረጋጋት ቅድሚያ የሚሰጠው ጉዳይ መሆኑን ተናግረዋል።

ሀማስ
የፍልስጤሙ ታጣቂ ቡድን ሀማስ በበኩሉ፥ "ይህ ግጭትን የሚያባብስ አደገኛ የጭካኔ ጥቃት ነው" ብሏል። "ዓለም አቀፍ ሕግን በገሃድ የጣሰ፣ በዓለም ሰላምና ደህንነት ላይ የተደቀነ ቀጥተኛ ስጋት ነው" ሲል ገልጾታል ሀማስ ጥቃቱን።

ሁቲ
መሀመድ አል-ፋራህ የተባሉ የሁቲ ባለስልጣን፥ አሜሪካ በኢራን የኑክሌር ተቋማት ላይ የፈጸመችው ጥቃት የጦርነት "መጀመሪያ" ነው ማለታቸውን አልጀዚራ ዘግቧል።

የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት
የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ዋና ፀሐፊ አንቶኒዮ ጉተሬዝ፥ ድርጊቱ የዓለም ሰላምና ደህንነትን አደጋ ላይ የሚጥል ነው ሲሉ ተናግረዋል።

በጌትነት ተስፋማርያም

ኢራን የአሜሪካን ድብደባ ተከትሎ እስራኤል ላይ ጥቃት ፈፀመች************የኢራን የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አባስ አራቅቺ "አሜሪካ በኢራን ሰላማዊ የኒውክሊየር ተቋማት ላይ የፈጸመችው አስነ...
22/06/2025

ኢራን የአሜሪካን ድብደባ ተከትሎ እስራኤል ላይ ጥቃት ፈፀመች
************

የኢራን የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አባስ አራቅቺ "አሜሪካ በኢራን ሰላማዊ የኒውክሊየር ተቋማት ላይ የፈጸመችው አስነዋሪ ጥቃት የማያባራ መዘዝ ያስከትላል" ሲሉ አስጠንቅቀዋል።

ይህን ተከትሎም ኢራን እስራኤል ላይ በባለስቲክ ሚሳኤል የታገዘ ጥቃት መፈጸሟን ቢቢሲ ዘግቧል።

የኢራን ወታደራዊ ኃይልን ምንጭ ያደረገው ፋርስ ኒውስ፥ ኢራን ቤን ጉሪዮን አየር ማረፊያንና የባዮሎጂካል ጥናት ማዕከልን የጥቃቱ ዒላማ ማድረጓን ዘግቧል።

በእስራኤል በኩል ስለጥቃቱ እስከአሁን የሰጠችው ማረጋገጫ የለም።

በጥቃቱ ምክንያት በአሁኑ ወቅት በእስራኤል ሃይፋ እና ቴል አቪቭ ከተሞች ውጥረት መንገሱን የቢቢሲ ዘገባ አመላክቷል።

በጌትነት ተስፋማርያም

20/06/2025
ኢራንና እስራኤል በአፋጣኝ የተኩስ አቁም ስምምነት እንዲያደርጉ ተመድ ጠየቀ****************************ላለፉት 7 ቀናት ጦርነት  ውስጥ የገቡት ኢራንና እስራኤል በአፋጣኝ የተ...
20/06/2025

ኢራንና እስራኤል በአፋጣኝ የተኩስ አቁም ስምምነት እንዲያደርጉ ተመድ ጠየቀ
****************************

ላለፉት 7 ቀናት ጦርነት ውስጥ የገቡት ኢራንና እስራኤል በአፋጣኝ የተኩስ አቁም ስምምነት እንዲያደርጉ የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ዋና ፀሃፊ አንቶኒዮ ጉተሬዝ ጥሪ አቅርበዋል።

በሁለቱ ሀገራት መካከል እየተካሄደ የሚገኘው ጦርነት እየተባባሰ መሆኑን የተናገሩት ዋና ፀሃፊው ሀገራቱ ግጭቱን በማቆም በአስቸኳይ የተኩስ አቁም ስምምነት እንዲያደርጉም ጠይቀዋል።

በሁለቱ ሀገራት መካከል እየተካሄደ ያለውን ጦርነት ሁሉም የዓለም አቀፍ ማህበረሰብ ወደ ዓለም አቀፍ ግጭትና ጦርነት እንዳይስፋፋ መከላከል እንዳለበትም አሳስበዋል።

ዋና ፀሃፊው ይህን ያሉት የአሜሪካው ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ ሀገራቸው ከእስራኤል ጎን በመሆን በጦርነቱ ልትሳተፍም ላትሳተፍም ትችላለች፤ ማንም አያውቅም ማለታቸውን ተከትሎ ነው።

በሁለቱ ሀገራት መካከል ያለውን ጦርነት ለማቆም ፕሬዝዳንት ዶንልድ ትራምፕ ኢራን ያለምንም ቅድመ ሁኔታ እጅ እንድትሰጥ ያቀረቡትን ጥሪ የኢራኑ መሪ አያቶላ ካሚኒ ውድቅ ማድረጋቸው ይታወሳል።

በሁለቱ ሀገራት መካከል በቀጠለው ጦርነት ምክንያት
በርካታ ሀገራት ዜጎቻችውን ከኢራንና ከእስራኤል ማስወጣት ጀምረዋል።

በላሉ ኢታላ

ፕሬዚዳንት ትራምፕ የኢራንን የአየር ክልል ሙሉ በሙሉ ተቆጥረነዋል አሉ*****************የጂ7 ስብሰባን አቋርጠው ወደ ሀገራቸው የተመለሱት የአሜሪካው ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ ማምሻ...
17/06/2025

ፕሬዚዳንት ትራምፕ የኢራንን የአየር ክልል ሙሉ በሙሉ ተቆጥረነዋል አሉ
*****************

የጂ7 ስብሰባን አቋርጠው ወደ ሀገራቸው የተመለሱት የአሜሪካው ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ ማምሻውን ትሩዝ በተሰኘ ማህበራዊ ገፃቸው ባጋሩት ጽሁፍ፥ የኢራንን የአየር ክልል ሙሉ በሙሉ ተቆጣጥረነዋል ብለዋል።

ትራምፕ አያይዘውም ኢራን ጥሩ የተባለ የአየር ክልል መቆጣጠሪያ እና ሌሎች ወታደራዊ መሳሪያዎች በብዛት አሏት፤ ነገር ግን አሜሪካ ከሰራቻቸው አይበልጡም ብለዋል።

ማንም ሀገር አሜሪካ ከምትሰራቸው የላቁ ወታደራዊ መሳሪያዎች ሊሰራ አይችልም፤ የአሜሪካ ወታደራዊ ቴክኖሎጂዎች የትኛውም ሀገር ከሚሰራቸው የተሻሉ ናቸው ሲሉ ተናግረዋል።

የኢራን አብዮታዊ ዘብ የእስራኤልን የደኅንነት መስሪያ ቤት ማጥቃቱን ገለጸ************** ዛሬ አምስተኛ ቀኑን ባስቆጠረው የእስራኤል እና ኢራን ግጭት  ሁለቱም ሀገራት በርካታ ጉዳት ያ...
17/06/2025

የኢራን አብዮታዊ ዘብ የእስራኤልን የደኅንነት መስሪያ ቤት ማጥቃቱን ገለጸ
**************

ዛሬ አምስተኛ ቀኑን ባስቆጠረው የእስራኤል እና ኢራን ግጭት ሁለቱም ሀገራት በርካታ ጉዳት ያስተናገዱ ሲሆን፣ ዛሬ ከማለዳው በጀመረው ግጭት ኢራን 30 ሚሳኤሎችን ወደ እስራኤል ማስወንጨፏ ታውቋል።

ይህን ተከትሎም የኢራን ወታደራዊ ምንጮች፣ የእስራኤልን የደኅንነት ቢሮ ማጥቃታቸውን ገልጸዋል።

ይህ ከተሰማ በኋላም እስራኤል የቴህራንን ከተሞች መደብደቧን እንደቀጠለች ስካይ ኒውስ ዘግቧል።

6ኛው መላ ኢትዮጵያ ጨዋታዎች በጅማ ከተማ መካሄድ ጀመረ*********6ኛው መላ ኢትዮጵያ ጨዋታዎችየመክፈቻ  መርሀ  ግብር በጅማ  ዩኒቨርሲቲ ስቴዲየም  እየተካሄደ  የሚገኝ  ሲሆን የኢፌዴሪ...
17/06/2025

6ኛው መላ ኢትዮጵያ ጨዋታዎች በጅማ ከተማ መካሄድ ጀመረ
*********

6ኛው መላ ኢትዮጵያ ጨዋታዎችየመክፈቻ መርሀ ግብር በጅማ ዩኒቨርሲቲ ስቴዲየም እየተካሄደ የሚገኝ ሲሆን የኢፌዴሪ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ፣ የኦሮሚያ ክልል ምክትል ርዕሰ መስተዳደር አወሉ አብዲ እና የባህልና ስፖርት ሚኒትሯ ሸዊት ሻንካን ጨምሮ ሌሎች ከፍተኛ የመንግስት የስራ ኃላፊዎች ተገኝተዋል፡፡

በኦሎምፒክ መርህ የሚካሄደውን መላ ኢትዮጵያ ጨዋታዎች ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ ተመስገን ጥሩነህ የኦሎምፒክ ችቦውን በመለኮስ ለአትሌት ጌጤ ዋሚ እና አትሌት ኢብራሂም ጄይላን አስረክበዋል፡፡

ለ9 ዓመት ተቋርጦ በነበረው ውድድር ሁሉም ክልሎችና ከተማ አስተደደሮች ተካፋይ ሆነውበታል፡፡

“ስፖርት ለህብር ኢትዮጵያ አርበኝነት” በሚል መሪ ሀሳብ በሚካሄደው መድረክ በ26 የስፖርት አይነቶች ከ4500 በላይ ስፖርተኞች የሚሳተፉበት ይሆናል፡፡

በአንተነህ ሲሳይ

#መላኢትዮጵያጨዋታዎች

Address

Addis Ababa

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when CDU TUBE posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share