
23/08/2025
አርሰናል ኤዜን ማስፈረሙን ይፋ አደረገ
አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 17፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) አርሰናል እንግሊዛዊውን የአጥቂ አማካይ ኤቤሬቺ ኤዜ ከክሪስታል ፓላስ ማዘዋወሩን ይፋ አድርጓል።
መድፈኞቹ የ27 ዓመቱን ተጫዋች በ67 ነጥብ 5 ሚሊየን ፓውንድ የዝውውር ዋጋ ነው የግላቸው ያደረጉት፡፡
ተጫዋቹን ለማስፈረም ጫፍ ደርሰው የነበሩት ቶተንሃም ሆትስፐሮች በመጨረሻ ሰዓታት በከተማ ተቀናቃኛቸው አርሰናል ዝውውሩን መነጠቃቸው ይታወቃል።
ኤዜ ለአራት ዓመታት በኢምሬትስ የሚያቆየውን ውል የፈረመ ሲሆን፥ አርሰናል የተጫዋቹን ውል ለተጨማሪ አንድ ዓመት የማራዘም አማራጭ እንዳለው ስካይ ስፖርት ዘግቧል፡፡
በዮናስ ጌትነት
ፈጣን እና ወቅታዊ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
YouTube www.youtube.com/
Facebook www.facebook.com/fanabroadcasting
Telegram t.me/fanatelevision
Website www.fanamc.com
TikTok www.tiktok.com/
WhatsApp www.whatsapp.com/channel/0029VbB0dRxG8l59MUkoWR29
Amharic Entertainment YouTube www.youtube.com/
Facebook www.facebook.com/wmccwaltamediaandcommunicationcorporate
TikTok www.tiktok.com/
Amharic Podcast YouTube www.youtube.com/ በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስለሆኑ እናመሰግናለን!