Kuto ye konso Liji

Kuto ye konso Liji በመከራ መካከል ብሄድም፣አንተ ሕይወቴ፣
ትጠብቃታለህ፤ በጠላቶቼ ቍጣ ላይ እጅህን ትዘረጋለህ፤በቀኝ እጅህም ታድነኛለህ።
መዝሙር 138:7

ታህሳስ 17/2017   👉በስመ   አሐዱ አምላክ አሜን አምላካችን መድኃኒታችን   በሰማእቱ ስም ለምናመሰግንበት   ወርሐዊ መታሠቢያ ክብረ በአል እንኳን አደረሰን 🙏🙏🙏👉የትውልድ ሀገሩ  #ኢ...
26/12/2024

ታህሳስ 17/2017

👉በስመ አሐዱ አምላክ አሜን አምላካችን መድኃኒታችን በሰማእቱ ስም ለምናመሰግንበት ወርሐዊ መታሠቢያ ክብረ በአል እንኳን አደረሰን 🙏🙏🙏

👉የትውልድ ሀገሩ #ኢየሩሳሌም ሲሆን አባቱ ስምዖን እናቱ ደግሞ ማርያም ትባላለች ዘመኑም የመጀመሪያው ምእተ ዓመት ነው

👉እንግዲህ በዘመነ ሐዋሪያት የማዕዱን እና የውስጡን አገልግሎት እንዲያስተናብሩ መንፈስ እና ጥበብ የሞላባቸው ሰባት ሰዎች ተመርጠው በሐዋሪያት አንብሮተ እድ ሆነው ከተሾሙት ከሰባቱ ዲያቆናት መካከል በቅድስና ሕይወቱ ለክርስቲያኖች አብነት የሆነው ሰማዕቱ ይገኝበታል እስጢፋኖስ የሚለው ቃል የግሪክ ቃል ሲሆን ትርጉሙም #አክሊል ማለት ነው

👉መፅሐፍ ቅዱስን ወደ ግእዝ በኋላም ወደ አማርኛ የመለሱት አባቶች በቀጥታ የግሪኩን እስጢፋኖስ የሚለውን ቃል ተጠቅመዋል ምንም እንኳን ስሙ የግሪክ ስም ይሁን እንጂ በትውልዱ አይሁዳዊ ነው

👉ወላጆቹ ይህንን ስም የሰጡት ተብሎ የሚታመነዉ ወላጆቹ በፍልስጤም ጠረፋማ ከተሞች ይኖሩ ስለ ነበር የግሪክ ባሕልና ቋንቋ ተጽእኖ አድሮባቸው ይሆናል ተብሎ ይገመታል

👉 በሐዋርያት ጥበቃ የነበረችውን ቤተ ክርስቲያን ከአምላክ ዘንድ ባገኘው የማስተማርና የፈውስ ሀብት ያገለግል ነበር በእርሱም ታላላቅ ተአምራት ይፈፀሙ ነበር

👉ስለዚህም ሕዝቡ ከፊት ይልቅ እጅግ እየበዛና በትምህርት እየጠነከረ መጣ አይሁድም ይህን ተመልክተው በቅዱስ #እስጢፋኖስ ላይ በቅናትና በጠላትነት ተነሡበት ነገር ግን ከመንፈስ ቅዱስ ባገኘው ጥበብና ኃይል እነርሱን በቃልም በድርጊትም ይቃወማቸው ነበርና ሊረቱት አልተቻላቸውም

👉ስለዚህም #እግዚአብሔርን ሙሴን ሲሳደብ ሰምተነዋል ሙሴ የሠራልንን ሥርዐት ይለውጣል በዚህ ቤተ መቅደስና በሕጉ ላይ የስድብን ቃል ይናገራል ይህንንም ቤተ መቅደስ የናዝሬቱ ኢየሱስ አፍርሱ ብሎአል እያለ ያስተምራል እያሉ ሕዝቡን ሽማግሌዎችንና ፀሐፍትን በማናደድ ይዘው ከሸንጎ ፊት አቆሙት

👉ቅዱስ #እስጢፋኖስን በሸንጎ ፊት ባቆሙት ጊዜም ፊቱ ልክ እንደ #መልአክ ፊት ሆኖ በርቶ ነበር እርሱም ለተከሰሰበት ነጥብ መልስ ሰጠ ከአብርሃም እስከ ክርስቶስ ለእነርሱ የተሰጣቸውን በረከት በመቃወማቸው ከተስፋ ቃል እርቀው እንደተወገዱ ገለጠላቸው

👉 #ክርስቶስንም ባለመቀበላቸው ወቀሳቸው በዚህም ምክንያት በቁጣ ተነሣስተው ከከተማ ውጭ በመውሰድ በድንጋይ ወግረው ገደሉት አይሁድ በድንጋይ እየወገሩት ሳለ ሰማያት ተከፍተው #ክርስቶስን በአብ ቀኝ ቆሞ ተመለከተ ይህንን ራእይ የክርስቶስን ትንሣኤን ለማይቀበሉት አይሁድ አሰምቶ ተናገረ

👉እነርሱ ከፊት ይልቅ በእርሱ ጨከኑ በድንጋይም ወገሩት ነገር ግን ጌታውን ክርስቶስን መስሎ ነበርና ልክ እንደ መምህሩ ” ብሎ በታላቅ ድምፅ ጮኾ ነፍሱን ሰጠ በቤተክርስቲያንም ታሪክ ስለ ክርስቶስ መስክሮ ሰማዕትነትን የተቀበለ የመጀመሪያው ዲያቆን ሆኖአል

👉በደማስቆ መንገድ ላይ ክርስቲያኖችን ያሳድድ የነበረ ሳውል በኋላም ቅዱስ ጳውሎስ ተብሎ ስያሜ የተሰጠው ሐዋርያ ቅዱስ እስጢፋኖስ በድንጋይ በሚወግሩበት ወቅት በእርሱ ሞት ተስማምቶና ድንጋይን በእስጢፋኖስ ላይ ያነሡትን የአይሁድ ልብስ ይጠብቅ የነበረ ብላቴና ነበር

👉ነገር ግን ሐዋርያ ከሆነ በኋላ የሰማእቱ #የእስጢፋኖስን ቤተሰቦች አጥምቆአቸዋል ። ሰማያዊ ቅዱስ እስጢፋኖስ በረከት ና ምላጁ አይለየን 🙏🙏

ታህሳስ 16/2017    "ከመረጥኋቸዉ ጋር   አደረግኹ"መዝ.88፥3👉በስመ   አሐዱ አምላክ አሜን አምላካችን መድኃኒታችን   በምስጋና ከፍ ለምናደርግበት እናታችን   በቃል ኪዳኗ እንድታስበ...
25/12/2024

ታህሳስ 16/2017

"ከመረጥኋቸዉ ጋር አደረግኹ"መዝ.88፥3

👉በስመ አሐዱ አምላክ አሜን አምላካችን መድኃኒታችን በምስጋና ከፍ ለምናደርግበት እናታችን በቃል ኪዳኗ እንድታስበን ለምንማፀንበት ወርሐዊ መታሠቢያ ክብረ በአሏ እንኳን አደረሰን

👉 #ኪዳነምህረት ስንል የምህረት ቃል ኪዳን ማለት ነው በዚህ ውስጥም ምህረት አድራጊው ጌታችን መድኃኒታችን #ኢየሱስ ክርስቶስ ሲሆን ምህረት ተቀባይም መላው የአዳም ዘር ነው

👉 በምድራዊ ቆይታዋ ዘውትር ወደ እየሔደች ትፀልይ ነበር ልጇ እና ወዳጇ ጌታችን መድሐኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ያደረገችውን ልመናና ፀሎት ተመልክቶና ሰምቶ ሰጣት

👉እንኳን የእናቱን ፀሎት እና ልመና ቀርቶ ዘውትር በሀጥያት የምንዘፈቀውን እኛን ክፉዎቹን የሚሰማ አምላክ ስለ አንቺ ስለ እናቴ ክብርና ፀጋ ስል ይኸው ቃሌ ብሎ አደረገ

👉ስሟን ለሚጠሩ በእርሷ አማላጅነት ለሚታመኑ በምድር በረከትን በሰማይ የዘለዓለም መንግስትን እንደሚወርሱ የምህረት እና የቸርነት ሰጥቷታል

👉በታላቁም መፅሐፍ ቀስቲቱም በደመና ትሆናለች በእኔና በምድር ላይ በሚኖር ሥጋ ባለው በሕያው ነፍስ ሁሉ መካከል ያለውን የዘላለም ለማሰብ አያታለሁ ኦሪት ዘፍ.9፥16

👉አምላካችን መድኃኒታችን ለእናቱ በሠጣት ያስበን ሀገራችንን ህዝባችንን ከክፉ መከራ ይጠብቅልን የአበዉ ነብያት ረድኤት በረከት አይለየን "አሜን" ✝️ 💒 ✝️

🥀🌴🌴🌻🌻 ታህሳሲ 12 - ኃያሉ ቅዱስ ሚካኤል ፣ አሳዳጊዬ ) 🇪🇹🇪🇹🌷🌷❤እንኳን ለሊቀ መላእክት ቅዱስ ሚካኤል ወራዊ ክብረ በዓል አደረሰን፤ አደረሳችሁ!!!👏ሚካኤል “መኑ ከመ አምላክ ፤ ማን...
21/12/2024

🥀🌴🌴🌻🌻 ታህሳሲ 12 - ኃያሉ ቅዱስ ሚካኤል ፣ አሳዳጊዬ ) 🇪🇹🇪🇹🌷🌷

❤እንኳን ለሊቀ መላእክት ቅዱስ ሚካኤል ወራዊ ክብረ በዓል አደረሰን፤ አደረሳችሁ!!!👏

ሚካኤል “መኑ ከመ አምላክ ፤ ማን እንደ እግዚአብሔር” ማለት ነው፡፡ ቅዱስ ሚካኤል ወንጌላዊው ቅደስ ዮሐንስ በራእዩ “በእግዚአብሔር ፊት የቆሙ ሰባት መላእክትን አየሁ” ብሎ ከተናገረላቸው መላእክት ውስጥ አንዱ ሲሆን፤ የሰባቱም ሊቃነ መላእክት አለቃ እንዲሆን እግዚአብሔር መርጦ ሹሞታል፡፡

የቅዱስ ሚካኤል ሹመት በነገደ መላእክት ላይ ብቻ አይደለም፤ ነገር ግን የእግዚአብሔር ሕዝብ በሆኑት ላይ ጭምር ነው፡፡ ሊቀ መላእክት ቅዱስ ሚካኤል፣ ለእኛ ለሰዎች አማላጅ ሲሆን ለቅዱሳን፣ ፃድቃን ሰማዕታት ደግሞ አጋዣቸው ነው፤ በሕይወታቸውናተ በተጋድሏቸውም እስከ መጨረሻው ይረዳቸዋል፡፡

የቅዱስ ሚካልን ሲመት ምክንያት በማድረግም ዕለቱን የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ኅዳር ፲፪ ቀን በየዓመቱ በድምቀት ታከብረዋለች፡፡
12/472017 ዓ,ም

07/12/2024

Shout out to my newest followers! Excited to have you onboard! Mathewos Kanu, Demeke Dana Times, Asrat Kepo, Sahile Sama, Demeke Dana, Ermias Bekele, Kasi Man, Esha Geletu, Abriham Kusse, Nebiy Amsalu Alena, ገዙ ማኛዉ, Geremu Karto, ስማቸው ስጦታ, Mita Ababa, Temu Gehano, ሌኒዝ አለማየሁ

 #ህዳር  2️⃣1️⃣ እንኳን ለእናታችን ለቅድስት ጽዮን ማርያም አመታዊ መታሰቢያ ክብረ በዓል በሰላም አደረሳችሁ/             አደረሰን!! አሜን✝️🕯👏                 👉  ...
30/11/2024

#ህዳር 2️⃣1️⃣ እንኳን ለእናታችን ለቅድስት ጽዮን ማርያም አመታዊ መታሰቢያ ክብረ በዓል በሰላም አደረሳችሁ/
አደረሰን!! አሜን✝️🕯👏

👉 ❤️

➢ በዚች ዕለት ህዳር 21 ቀን እመቤታችን ድንግል ማርያም ታቦተ ፅዮን በፍልስጥኤም ሀገር በምርኮ በሔደችበት ጊዜ ዳጎን የተባለውን ጣኦት አድቅቃ ፡ አውልቃ የመጣችበት ዕለት ነው ፡፡ 1ኛ ሳሙ 1:6

➢ በዚች ዕለትም ታቦተ ፅዮን ንጉስ ሰለሞን በክብር ወደ ሰራላት ቤተመቅደስ የገባችበት ዕለት ነው 1ኛ ነገ 8:1

➢ በዚች ዕለት ታቦተ ፅዮን በንግስት ሳባ ልጅ በአፄ ሚኒሊክ አማካኝነት ወደ ኢትዮጵያ ምድር የገባችበት ዕለት ነው

➢ እነ ዩዲት ጉዲት በነገሱበት ዘመን የተሰደደችው እመቤታችን የስደት ጊዜዋን ጨርሳ ወደ ክብረ መንበሯ የተመለሰችበት ዕለትን በማሰብ ህዳር ፅዮንንን በድምቀት እናከብራለን

👉 #ጽዮን ማርያም የተባለችበት ምክንያትም

➨ አክሱም ጽዮን እንደዛሬው ድርቅ ያለ መሬት አልነበረም ባህር ነበር እንጂ፤ አብርሃና አጽብሃ ለታቦተ ጽዮን ምን ዓይነት ቤተክርስቲያን ነው የምንሰራላት ? ቦታውስ የት
ጋር ነው የሚሆነው ? እያሉ ዘወትር ሲጨነቁ ጌታችን ተገልፆ ድንጋይ ላይ ቆሞ አዩት

➨ #እርሱም ቤተክርስቲያኗን እዚህ ባህር ላይ ስሯት ስሟንም በእናቴ ስም ሰይሟት አላቸው

➨ እነርሱም ጌታ ሆይ ይህ እኮ ባህር ነው ይሉታል በዚህ ጊዜ ቅዱስ ሚካኤል ከገነት አፈር ይዞ መጣና ባህሩ ላይ ነሰነሰው ባህሩም ደረቀ የዛሬውንም ቅርጽ ያዘ ይላል ጌታችን የቆመበት የእግሩ ምልክት ዛሬም ድረስ ይታያል እንደሚለው በድርሳነ ጽዮን ላይ

🌿 #ከእመቤታችን ረድኤትና በረከት ያሳትፈን ሀገራችንና ህዝባችን በፅኑ ሰላም ትጠብቅልን አሜን(፫) 💚💛❤️🙏
21/3/2017 ዓ,ም

28/11/2024

!

ውስጥህን አዘጋጅ፣ ለምታምነው አምላክ የልብህን በር ክፈት፣ እራስህን አረጋጋ፣ ምንም እንዳልተፈፀመ እያሰብክ የእምነት ደረጃህን መዝነው። በእርግጥ አማኝ ነኝ ብለህ ታስባለህ? አማኝ በእምነቱ አሸናፊ ነው። እናም አንድ ጥያቄ እራስህን ጠይቅ፦ የምርም ማሸነፍ የምፈልገው ነገር አለን? ተሻግረሀው ማለፍ የምትፈልገው፣ ጥለሀው መሔድ የምትፈልገው፣ ሸክሙን ማራገፍ፣ ከጭንቀቱም መገላገል የምትፈልገው ነገር አለህን? ከማንም ሰው የተለየህ አይደለህምና እንደ ማንኛውም ሰው የግል ጦርነት ይኖርብሃል፤ እለት እለት የሚያታግልህ፣ በነጋ ቁጥር ከፊቱ የምትቆመው፣ እንደ አዲስ የምትገዳደረው የህይወት ፈተና አለበህ። እንደምታሸንፈውም እርግጠኛ አይደለህም፤ ነገር ግን መጋፈጥ ስላለብህ ብቻ ትጋፈጠዋለህ፣ መታገል ስላለብህ ብቻ ትታገለዋለህ።
እመን ታሸንፈለህ! በእግዚአብሔር አምላክህ ተማመን ጥለሀው ትሔዳለህ፤ ፈጣሪህን አስቀድመህ ተዋጋው ትማርከዋለህ። ሰውነትህ ደካማ ነው አብሮት ያለው ፈጣሪህ ግን ሃያል ነው፤ ሰውነትህ ተስፋ ይቆርጣል አብሮህ የሚሰራው አምላክህ ግን በእራሱ ተስፋ ነው፤ ፀጋ ነው፤ በረከት ነው፤ አሸናፊ ነው፣ ድል አድራጊ ነው። ለአማኝ ማሸነፍ ብርቁ አይደለም፤ እውነታን ለሚይዝ፣ ከእውነት ለሚጠጋ መሰናክልም ብርቁ አይደለም። ምክንያቱም የሚያምነው ሞትን ባሸነፈ አምላኩ ነውና ነው፤ ምክንያቱም እውነት በእራሱ ፈጣሪው ስለሆነ ነው። በህይወት እስካለን ድረስ የምድር ፈተና ማብቂያ የላትም። በተለይ በተንሹም በትልቁም የምንጨነቅና የምንሰበር ከሆንን ፈተናችን በእጥፍ ይጨምራል። እውቀታችን ውሱን ብትሆን እንኳን አምላክ በሚያድለን በረከትና ፀጋ ግን ለአሸናፊነት የሚያበቃንን፣ ከመዳረሻችን የሚያደርሰንን፣ ህልማችንን እውን የሚያደርግልንን ጥበብና ማስተዋልን እንወርሳለን፣ መንፈሳዊ ብለሃትንም እንላበሳለን።

አዎ! እምነት የጦር ጋሻችን ነው። ቃሉም እንደሚለው "ለሚያምን ሁሉ ይቻለዋል።" ማንን ማመን እንዳለብን ካወቅን ከልባችን የማመኑ ጉዳይ የእራሳችን ነው። እመን ታሸንፋለህ። የምታምነው በነፍስህ ነው፤ የምታምነው በጥልቁ ማንነትህ ነው። እምነትህን ሆነህ ማሳየት ይጠበቅብሃል፤ እምነትህን በየቀኑ እየኖርከው ልትገልፀው ይገባል። እምነታችን ስለጎደለ ብቻ የምንፈልገውን ብዙ ነገር አጥተናል፤ መድረስ ከሚገባን ደረጃ ቀርተናል። ያለችው ትንሿዋ እምነትህ በምንም በማንም እንድትሸረሸር አትፍቀድ፤ ማንም ተስፋህን እንዲቀማህ፣ በደስታህ እንዲቀልድና ሰውነትህን እንዲያሳንስ እድል አትስጠው። ከቃል በላይ በተግባር ስታምን ሁሉም የሚበጅህ ነገር እንደሚከናወንልህ አትጠራጠር።
/ከምርጥ ፅሁፎች የተወሰደ/

💐💒ፆመ ነብያት (የገና ፆም)💐💒💐💒 በመላው አለም የምትኖሩ ውድ የተዋሕዶ ልጆች እንኳን ለፆመ ነብያት (የገና ፆም) አምላክ ፈቅዶ በሰላም አደረሰን አደረሳችሁ!💐💒ይህ ፆም፣ፆመ፣ድህነት፣ፆመ፣...
20/11/2024

💐💒ፆመ ነብያት (የገና ፆም)💐💒

💐💒 በመላው አለም የምትኖሩ ውድ የተዋሕዶ ልጆች እንኳን ለፆመ ነብያት (የገና ፆም) አምላክ ፈቅዶ በሰላም አደረሰን አደረሳችሁ!

💐💒ይህ ፆም፣ፆመ፣ድህነት፣ፆመ፣ማርያም፣ ፆመ፣ አዳም፣ ፆመ ፊልጶስ፣ፆመ፣ ስብከት፣ በመባል፣ይጠራል።
💐💒ህዳር( 15 )ይጀመራል ታህሣሥ (፳፱) ይፈታል።
ይህ ፆም ከቤተ ክርስቲያናችን የአዋጅ ፆሞች ውስጥ አንዱ
ሲሆን አበው ነብያት የጌታችን የኢየሱስ ክርስቶስን መውረድ
መወለድ በትንቢት መነፅር እየተመለከቱ የፆሙት፣ታላቅ ፆም ነው። ዛሬም እኛ ክርስቲያኖች የአባቶቻችንን ፈለግ ተከትለን በፆምና በጸሎት ወቅቱን በማሳለፍ ኢየሱስ ክርስቶስ ራሱን ዝቅ አድርጎ ወደ አለም መምጣቱና የዓለም ቤዛ መሆኑን የምናስብበት ነው።

💐💒 ፦ የተባለበት ምክንያት መርገመ ስጋ መርገመ ነብስ የአዳም እዳ በደል ጠፍቶ ድህነት ስለተገኘበት ነው።

💐💒 ፦ የተባለበት ምክንያት ንፅይተ ንፁሃን ቅድስተ ቅዱሳን እመቤታችን ቅድስ ድንግል ማርያም ጌታን በማህፀኔ ተሸክሞ ልፆም ልፀልይ ይገባል ብላ ለ40 ቀን እስከ ጌታችን መድሃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ልደት ድረስ የፆመችው ፆም ስለሆነ ይህ ስያሜ ተሰጥቶታል።

💐💒 ፦ የተባለበት ምክንያት ለአዳም የተነገረው ትንቢት፣ የሚጠበቀው ሱባኤ እንደደረሰ የሚያበስር በመሆኑ ጾመ አዳም ይባላል፡፡ አዳም ቢበድልም ንስሐ ገብቶ በማልቀሱ ከልጅ ልጅህ ተወልጄ አድንሀለሁ ብሎ የተነገረው ተስፋ መድረሱን፣ ምሥጢረ ሥጋዌ እውን ሊሆን መቃረቡን የሚያስረዳ ጾም ነው፡፡

💐💒 ፦ የተባለበትም ምክንያት ሐዋርያው ፊልጶስ በአረማውያን ዘንድ ገብቶ ሲያስተምር በሰማዕትነት ሲሞት አስከሬኑ ከደቀመዛሙርቱ ስለተሰወረ እግዚአብሔር የተሰወረውን የመምህራቸውን አስከሬን እንዲገልጽላቸው ከኅዳር አስራ ስድስት ጀምረው ሲጾሙ በሦስተኛው ቀን የመምህራቸው አስከሬን ቢመልስላቸውም ጾሙን ግን እስከ ልደት ቀጥለዋል ለዚህም ይህ ስያሜ ተሰጥቶታል፡፡


💐💒 ፦ የተባለበትም ምክንያት የወልደ እግዚአብሔርን ሰው መሆን ያስተማሩበት የሰውልጆች ተስፋ የተመሰከረበት የምሥራቹ የተነገረበት ስለሆነም «ጾመ ስብከት» ይባላል፡፡

💐💒ፆሙን የኃጢአት መደምሰሻ መንግስተ ሰማያተን መውረሻ ያድርግልን። የቅዱሳን ነብያት አባቶቻችንንም በረከት በሁላችንም ላይ ያሳድርብን።

ፆም ጸሎታችንን ይቀበለን የቅዱሳን የነቢያት የፃድቃን ወሰማዕታት የመላእክት አምላክ ቅዱስ አማኑኤል የድንግል ማርያም ልጅ በደላችንን ይቅር ይበለን ይማረን አሜን 🤲🤲አሜን🙏🙏

ጥቅምት 19/2017          " እኔ  #በእግዚአብሔር ፊት የምቆመው  #ገብርኤል ነኝ "                                         ሉቃስ.1፥19👉በስመ   አሐዱ አ...
28/10/2024

ጥቅምት 19/2017

" እኔ #በእግዚአብሔር ፊት የምቆመው #ገብርኤል ነኝ "
ሉቃስ.1፥19

👉በስመ አሐዱ አምላክ አሜን አምላካችን መድኃኒታችን በመልአኩ ስም ለምናመሰግንበት ለመልአኩ ወርሐዊ መታሠቢያ ክብረ በአል እንኳን አደረሰን

👉ገብርኤል ‘ገብረ’ እና ‘ኤል’ ከሚሉ ሁለት ቃላት የተመሠረተ የመልአክ ስም ነው ማለትም ነው

👉አብሳሪ መልአክ ሆይ እጅግ አፅናኝና አስደሳች የሆነውን ምስጢረ ሥጋዌን ዜና ይዘህ ከሰማይ ወደ ምድር እንደወረድክ የአምላክ እናት ለመሆን ፈቃድዋ ሆኖ በተፈጸመ ጊዜ ደስ እንዳለህ እኛም እግዚአብሔርን በማክበርና ግዴታችንን በመፈፀም ደስ የምንሰኝበትን ፀጋ አሰጠን

👉ጠባቂያችን ሆይ ሦስቱን ወጣቶች ከሚያቃጥል እሳት እንዳዳንካቸው እኛንም በዚህ ዓለም ከሚወራው ከሚታየውና ከሚሰማው ሁሉ አድነን እየነደደ የሚለበልበንን የኃጢያት እሳትም አጥፋልን

👉የኑሯችንን ቀጠሮ በክንፈ ረድኤትህ ከልለው ሰይጣን እንዳይሰለጥንብን ክፉ አድራጊዎች ሟርተኞች ሰላቢዎች ዘረኞችና ነፍሰ ገዳዮች እንዳያጠቁን ከልለን ያንተን የእሳት አጥር ዘሎ ጠላት ያጠቃን ዘንድ ጠላት አይችልምና #ጥበቃህ ከእኛ ከባርያዎችህ አይለየን

👉 ሆይ ሕፃኑ ቂርቆስና እናቱ እየሉጣን በንፍር ውኃ ከመቀቀል እንዳዳንካቸው ልጆችህን በማናውቀው ሁኔታ የተዘጋጀልንን ሁሉ አስወግድልን በላያችን ላይም በክፉ ሰዎች ምክንያት የተነሳብንን እሳት አጥፋልን

👉 የጨከንንና የቆረጥንም አድርገን የሰይጣንን ፈተና የምናልፍበት እውነተኛውን ጥበብ እንደ ነብዩ ዳንኤል አስተምረን

👉 ቅዱስ #ገብርኤል ሆይ በደል በተገኘብን ቁጥር እያለቀስን እንጠራሃለን ጎስቋላ የምንሆን በጥቃትና በሀዘን ውስጥ የምንገኝ ልጆችህ የአንተን ማፅናናትና ረዳትነት እንፈልጋለንና ፈጥነህ ናልን

👉እናታችን #ማርያምን ያበሰርክ ለዓለም ሁሉ የምታበራ ገብርኤል ሆይ በሰራዊት አምላክ ፊት ዘወትር ትቆማለህና ፀሎትና ልመናችንን ስማ

👉ቅዱስ #ገብርኤል ሆይ ቀድመህ የደስታ የምሥራች ቃልህን ልታበስር ወደ ገሊላ እንደወረድህ ዛሬም ለአዘንንና ለእኛ ለቃል ኪዳን ልጆችህ ከሠማይ በሠረገላ ናልን የደስታንም ቃል አሰማን

👉እናታችን #ማርያምን ያበሰርክ ተወዳጁ መልአክ ቅዱስ #ገብርኤል ሆይ በምህረትና በይቅርታ ወደ እኛ ናልን ዓለም የጥፋት የሞት የክስረት የውድመትና የተስፋ መቁረጥ ድምፅን ያሰማናልና አንተ ግን ጉስቁልናችንን የሚያነሳ ስብራታችንን የሚጠግን እንባችንን የሚያብስ #የብስራት ድምፅህን አሰማን እንድንፅናናም አድርገን

👉እውነተኛ ጠባቂያችን ቅዱስ #ገብርኤል ሆይ እኛን ለማዳን ሰው የሆነውን አምላካችን መድኃኒታችን ማደሪያው የሆነችው በጣም እንወዳታለን

👉በዚህ ዓለም የምሥጢረ ሥጋዌ ተካፋዮች በመሆናችን ተካፋዮች ለመሆን ሁላችንንም በምልጃህ አብቃን ለምንልን #የእግዚአብሔር መልአክ ጥበቃህ ተራዳኢነትህ አይለየን

👉 #ገብርኤል ሆይ ለሀገራችን ሠላምን ለህዝባችን ፍቅር አንድነትን ይሰጠን ዘንድ በአምላካችን #በክርስቶስ ፊት ቆመህ ለምንልን የሀገራችንና #የህዝቦቿ የቤተክርስቲያናችን ጠላቶችን አስታግስልን ጦርነትና ረሐብ ከምድራችን ላይ ይወገድ ዘንድ ለምንልን "አሜን" ✝️⛪️✝

22/09/2024

Ten Unknown Facts About

1. Founding and History: BMW, Bayerische Motoren Werke AG, was founded in 1916 in Munich, Germany, initially producing aircraft engines. The company transitioned to motorcycle production in the 1920s and eventually to automobiles in the 1930s.

2. Iconic Logo: The BMW logo, often referred to as the "roundel," consists of a black ring intersecting with four quadrants of blue and white. It represents the company's origins in aviation, with the blue and white symbolizing a spinning propeller against a clear blue sky.

3. Innovation in Technology: BMW is renowned for its innovations in automotive technology. It introduced the world's first electric car, the BMW i3, in 2013, and has been a leader in developing advanced driving assistance systems (ADAS) and hybrid powertrains.

4. Performance and Motorsport Heritage: BMW has a strong heritage in motorsport, particularly in touring car and Formula 1 racing. The brand's M division produces high-performance variants of their regular models, known for their precision engineering and exhilarating driving dynamics.

5. Global Presence: BMW is a global automotive Company

6. Luxury and Design: BMW is synonymous with luxury and distinctive design, crafting vehicles that blend elegance with cutting-edge technology and comfort.

7. Sustainable Practices: BMW has committed to sustainability, incorporating eco-friendly materials and manufacturing processes into its vehicles, as well as advancing electric vehicle technology with models like the BMW i4 and iX.

8. Global Manufacturing: BMW operates numerous production facilities worldwide, including in Germany, the United States, China, and other countries, ensuring a global reach and localized production.

9. Brand Portfolio: In addition to its renowned BMW brand, the company also owns MINI and Rolls-Royce, catering to a diverse range of automotive tastes and luxury segments.

10. Cultural Impact: BMW's vehicles often become cultural icons, featured in fi

Address

Addis Ababa

Telephone

+251925915264

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Kuto ye konso Liji posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to Kuto ye konso Liji:

Share