Hadiya zone Government Communication

Hadiya zone Government Communication Contact information, map and directions, contact form, opening hours, services, ratings, photos, videos and announcements from Hadiya zone Government Communication, Hossana.

This is the offical facebook home page of Hadiya Zone Communication

‹ቀልጣፋ፣ ውጤታማና ተደራሽ የሆነ የመንግሥት የኢንፎርሜሽን ኮሙዩኒኬሽን ሥርዓት በመገንባት መንግሥትንና ሕዝብን ተጠቃሚ በማድረግ አንድ ፖለቲካዊና ኢኮኖሚያዊ ማኀበረሰብን ለመገንባት በሚደረገው ጥረት ጉልህ አስተዋጽኦ ማድረግ ነው።

ለህዝብ ያለንን ክብር ተገቢ አገልግሎት በመስጠት ማረጋገጥ ይገባል፦አቶ ለንደቦ አወኖየሀዲያ ዞን ትራንስፖርትና መንገድ ልማት መምሪያ ለህዝብ በሚሰጠዉ አገልግሎት ዙሪያ ያተኮረ መድረክ አካሂዷ...
04/09/2025

ለህዝብ ያለንን ክብር ተገቢ አገልግሎት በመስጠት ማረጋገጥ ይገባል፦አቶ ለንደቦ አወኖ

የሀዲያ ዞን ትራንስፖርትና መንገድ ልማት መምሪያ ለህዝብ በሚሰጠዉ አገልግሎት ዙሪያ ያተኮረ መድረክ አካሂዷል።

(ነሐሴ 28/2017 ሆሳዕና

በመድረኩ የተገኙት የዞኑ ትራንስፖርትና መንገድ ልማት መምሪያ ኃላፊ አቶ ለንደቦ አዎኖ በዚህ ወቅት እንዳሉት፦እንደ ዞኑ ትራንስፖርትና መንገድ ልማት መምሪያ የሕዝብ እንቅስቃሴና አጠቃላይ ፍላጎት ከጊዜ ወደ ጊዜ እያደገ መምጣቱን አንስተዋል።

ለዚህ የሚመጥን አገልግሎት ለመስጠት ከሚመለከታየዉ አካላት ጋር በርካታ ስራዎች እየተሰሩ እንዳለ አንስተዉ፥በተለይ ወረዳዎችን ከሆሳዕና ከተማ ጋር የሚያገናኙ መንገዶች ተሰርተዉ ለህዝቡ ተገቢ አገልግሎት መስጠት እንዲችሉ የክልሉ ገጠር መንገዶች በበጋ ወቅት እንዲሰሩልን ሀሳብ እያቀረብንና በቅንጅት እየተሰረን እንገኛለን ብለዋል።

እንደዞናችን አሁን ባለዉ ተጨባጭ ሁኔታ ለህዝቡ የሚንሰጠዉን የትራንስፖርት አገልግሎት ለማሳለጥ ተቋሙ፣መነሃሪያ ዉስጥ ያሉ ማህበራት፣ባለንብረቶችና የተቋሙ አመራሮችና ባለሙያዎች ከሌሎች ባለድርሻ አካላት ጋር በቅንጅት መስራት እንደሚገባ የገለፁት የመምሪያዉ ኃላፊ አቶ ለንደቦ አዎኖ፥

ለህዝብ ያለንን ክብር ተገቢ አገልግሎት በመስጠት ማረጋገጥ ይገባል ብለዉ፥ የሚንሰጠዉን አገልግሎት በማጓደል ሕዝብን በመበደል የሚመጣዉ መዘዝ መንግስት ከሚጠይቀን በላይ መሆኑን መገንዘብ እንደሚያስፈልግ ተናግረዋል።

በመድረኩ የተገኙት የሀዲያ ዞን ሠላምና ፀጥታ መምሪያ ኃላፊ አቶ ደመቀ በዶሬ እንደሚሉት፦በዞኑ በትራንስፖርት አገልግሎት አሰጣጥ ዙሪያ የሚስታወሉ ጉድለቶችን ለመፍታትና ለህዝቡ ጤናማ አገልግሎት ለመስጠት፥ሁለት ችግሮች መፈታት አለባቸዉ ብለዋል።

የመጀመሪያዉና ዋናዉ መስተካከል ያለበት መነሃሪያዎች ዉስጥ ያሉ የመንግስት መዋቅሮችና ማህበራት ጤናማ አገልግሎት እንዲሰጡ በተቀናጀ መንገድ መስራት ሲሆን ሌለኛዉ ደግሞ ከመነሃሪያ ዉጪ የሚደረጉ እንቅስቃሴዎችን በትራፊክ ፖሊሶችና በመንገድ ዳህንነት ተቆጣጣሪዎች ዓማካይነት ጠንካራ ቁጥጥር በማድረግ ህግን የማስከበር ስራ መስራት ከተቻለ ለህዝቡ ተመጣጣኝና ችግር ፈቺ አገልግሎት መስጠት ይቻላል ብለዋል።

የሆሳዕና ከተማ የክልሉ ርዕሰ-መዲና መሆንዋን ተከትሎ በርካታ ኩነቶች የሚከወኑበት ከተማ በመሆኑ እናም ከፊታችን ብዙ የሚናከብራቸዉ ህዝባዊ በዓላት በመኖራቸዉ የትራንስፖርት አገልግሎት አሰጣጡ የከተማዉን ፀጥታ መረበሽ ስለማይገባ የሚመለከታቸዉ ተቋማት ከወዲሁ ያሉትን ማነቆዎች ለይተዉ በመፍታትና እንዲያስተካክሉ አሳስበዋል።

የሆሳዕና ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አቶ ዳዊት ጡምደዶ በሰጡት አስተያዬት፦በከተማችን የሚንሰጠዉ የትራንስፖርት አገልግሎት አሰጣጥ ጉዳይ ለሚንሰራቸዉ የልማት ስራዎችና ለከተማዉ ኢኮኖሚ መነቃቃት አጋዥ እንጂ፡የመልካም አስተዳደር ጥያቄ መሆን እንደሌለበት አንስተዋል።

በከተማዉ ያሉት ሁለቱ መነሃሪያዎች ተጥረዉና የንብረት ዳህንነት ተጠብቆ ለተገልጋዪ ማህበረሰብ የሚሰጡ አገልግሎቶች በተቀመጠላቸዉ የአሰራር ስርዓት መሰረት መሆን ይገባል ያሉት ከንቲባዉ አቶ ዳዊት ጡምደዶ፥

ከተማችን የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር መቀመጫ እንደመሆኑ መጠን በርካታ እንግዶችን የሚያስተናግድ በመሆኑ እንዲሁም ተጨማሪ እንደ እምግሬሺን፣ወሳኝ ኩነት፣የሰላምና ፀጥታና ፋይናንስ ቢሮዎች በከተማችን በመሆናቸዉ አገልግሎት በመፈለግ ከሌላ አካባቢዎች የሚመላለሱ ዜጎች ፍትሃዊ አገልግሎት ማግኘት እንዲችሉ ተጨማሪ ስራ እንደሚጠይቅ አንስተዉ፥

በዘርፉ ያሉትን ጠንካራ ጎኖች በማጠናከር፥የሚስታወሉ ጉድለቶች እንደ ከተማ መዋቅር አይተን በማረም የሚሰዉ የትራንስፖርት አገልግሎት አሰጣጥ ህደት እንዲዘምን፣ፍትሃዊ እንሆንና በወቅቱ ያለዉን የተገልጋይ ማህበረሰብ ፍላጎት ታሳቢ ያደረገ እንዲሆን እንሰራለን ብለዋል።

የሆሳዕና ከተማ አስተዳደር ትራንስፖርት ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ተሾመ ኤርቆጮ በበኩላቸዉ፥በሆሳዕና ከተማ የትራንስፖርት አገልግሎት አሰጣጥ የተገልጋዩን ፍላጎት በሚመጥን ደረጀ እንዲደርስ በርካታ ስራዎች እየተሰሩ እንደሆነ ተናግረዋል።

ህዝባችን በሰላም ከቦታ ወደ ቦታ ዳህንነቱ ተጠብቆ እንድንቀሳቀስ በበኩላችን ብዙ ጥረት እየተደረገ ነዉ ብለዉ፥ነገር ግን አሁንም ያልተፈቱና ተጨማሪ ስራ የሚጠይቁ ነገሮች መኖራቸዉን አንስተዉ፥ እነዚህን ጉዳዮች ለመፍታትና ለህዝባችን የሚመጥን አገልግሎት ለመስጠት ከአቅማችን በላይ በመሆናቸዉ የሚንቸገርባቸዉ ነገሮች አሉ ብለዋል።

ለአብነት ከወረዳዎች ጋር የሚያስተሳስሩን መንገዶች በተለይም ከግቤ፣ከምሻ፣ከዱናና ዋስገበታ ጋር የሚደረጉ ምልልሶች ወደ መቋረጥ ደረጀ ደርሰዋል ያሉት አቶ ተሾመ ኤርቆጮ፥ ተሽከርካሪዎች ወደእነዚህ አካባቢዎች ሄደዉ በሰላም እየተመላለሱአገልግሎት እንዲሰጡ የሚያስችል ሁኔታ እንደሌላየ ተናግረዉ፥የሚመለከተዉ አካል እነዚህን ጉዳዮች በትኩረት አይቶ ብፈታልን ለተገልጋዮቻችን ተገቢ አገልግሎት እንሰጣለን ብለዋል።

በሌላ በኩል በእነዚህ መንገዶች መበላሸት ምክንያት በሰዉም በንበረትም የከፋ ጉዳት እንዳይደርስ እኛ የበኩላችንን ድርሻ ለመወጣት ከሚመለከታየዉ ባለድርሻ አካላት ጋር ተቀናጅተን ለመስራት ቁርጠኛ ነንም ብለዋል አቶ ተሾመ።

ለህዝብ የሚንሰጠዉ አገልግሎት በህገወጥ መንገድ በመንቀሳቀስ በተንቀሳቀሱ ተሽከርካሪዎች ማለትም የተሰጣቸዉን መርሃ ግብር የጣሱትን፣ከታሪፍ በላይ ያስከፈሉትንና ትርፍ የጫኑትን ብዙ ተሽከርካሪዎች ተመጣጣኝ የእርምት እርምጃዎችን መዉሰድ እንደተቻለ የተናገሩት አቶ ተሾመ፥

የህዝብን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ ሲባል ይህ ቁጥጥርና የእርምት እርምጃ ተጠናክሮ ይቀጥላል ብለዋል።

በሆሳዕና ከተማ መነሃሪያ በጉዳዩ ዙሪያ አግኝተን ያነጋገርናቸዉ የትራንስፖርት ተጠቃሚዎች በበኩላቸዉ፤ከወረዳዎቾ የሚመጡ ተገልጋዮች በመንገድ ብልሽት ምክንያት እንደሚጉላሉ አንስተዉ የሚመለከተዉ አካል ትኩረት ሰጥቶ መስራት ይገባል ብለዋል።

ማንኛዉም ለህዝብ የትራንስፖርት አገልግሎት የሚሰጥ መኪና ከመነሃሪያ ዉጭ በማደር በመንግስትና በህዝብ ጥረት እየተገነቡ ባለዉ የመንገድ መሰረተ ልማት ላይ ጉዳት እያደረሰ በመሆኑ፥መነኻሪያ ዉስጥ አድሮ ስምሪት በመዉሰድ ስራዉን መስራት እንደሚገባም በመድረኩ ተነስቷል።

በዉይይቱ መርሃ ግብር የዞንና የሆሳዕና ከተማ የሰላምና ፀጥታ፣የትራንስፖርት፣ የፖሊስና የትራፊክ ፖሊስ አመራሮችና የሚመለከታቸዉ ባለሙያዎች እንዲሁም የሆሳዕና መነሃሪያ የማህበራት ተወካዮች ተገኝተዋል።

በኤልያስ ተሰማ

በማረቆ ልዩ ወረዳ እየተገነባ ላለዉ የገራድ ቢመዶ አጠቃላይ ሆስፒታል ግንባታ የሚዉል ገቢ ማሰባሰቢያ መረሃ ግብር እየተካሄደ ነዉ።===ሆሳዕና 27/12/2017 (ሀድያ ቴለቪዥን )==== የማ...
03/09/2025

በማረቆ ልዩ ወረዳ እየተገነባ ላለዉ የገራድ ቢመዶ አጠቃላይ ሆስፒታል ግንባታ የሚዉል ገቢ ማሰባሰቢያ መረሃ ግብር እየተካሄደ ነዉ።

===ሆሳዕና 27/12/2017 (ሀድያ ቴለቪዥን )====

የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር) ባለፈው ሰኔ 7/2017 ዓ/ም የግንባታ ሥራዉውን ያስጀመሩት የጋራድ ቢመዶ አጠቃላይ ሆስፒታል ግንባታ የሚዉል ገቢ ማሰበሰቢያ መርሃ ግብር የአከባቢው ማህበረሰብ የአይነት ድጋፍ ማድረግ ተጀምሯል።

የዚሁ የገቢ አሰባሰብ አጠቃላይ መረሃ ግብር በነገዉ ዕለት ነሐሴ 29/2017 ዓ/ም የልዩ ወረዳው መቀመጫ በሆነችዉ ቆሼ ከተማ ይካሄዳል።ሀዲያ ቲቪ #

በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ከ1 ነጥብ 5 ቢሊዮን በላይ ብር ካፒታል ያስመዘገቡ አምራች ኢንደስትሪዎች መኖራቸው ተገለፀ።ሆሳዕና፣ ነሃሴ/28/2017 በሆሳዕና ከተማ ለሚገኙ የማኑፋክቸሪንግ ኢን...
03/09/2025

በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ከ1 ነጥብ 5 ቢሊዮን በላይ ብር ካፒታል ያስመዘገቡ አምራች ኢንደስትሪዎች መኖራቸው ተገለፀ።

ሆሳዕና፣ ነሃሴ/28/2017 በሆሳዕና ከተማ ለሚገኙ የማኑፋክቸሪንግ ኢንደስትሪ ዘርፍ አነስተኛና መካከለኛ ኢንተርፕራይዞች በ"ሶፍት" ክህሎት እና የቢዝነስ ልማት አገልግሎት ላይ ስልጠና በሆሳዕና ከተማ እየተሰጠ ነው።

የክልሉ የኢንዱስትሪ ፓርኮች ልማት ኮርፖሬሽን ስራ አስፈጻሚ አቶ ናትናኤል ሚሊዮን እንደገለጹት በክልሉ ከ124 በላይ አምራች ኢንደስትሪዎች ከ1 ነጥብ 5 ቢሊዮን ብር በላይ ካፒታል ማስመዝገባቸውን ተናግረዋል።

አቶ ናትናኤል በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በ10 ከተሞች በ15 ሳይቶች 154 ሼዶችን ኮርፖሬሽኑ እንደሚያስተዳድር ተናግረው በስሩ በሚገኙ አምራች ኢንደስትሪዎች ለበርካቶች የስራ ዕድል መፈጠሩን ተናግረዋል።

ኮርፖሬሽኑ በዋናነት በክልሉ የማኑፋክቸሪንግ ዕድገት እንዲስፋፋ፣ ሼዶችን የማልማትና የማስተዳደር እንዲሁም የአቅም ግንባታ ስራዎችን እንደሚሰራ ተናግረው ይኸው ስልጠና የዚሁ አንድ አካል መሆኑን ገልጸዋል።

አሰልጣኞች የንግድ ሥራዎቻቸውን ለማሳደግ እና ተወዳዳሪነታቸውን ለማጎልበት የሶፍት ክህሎት እና የቢዝነስ ልማት አገልግሎት ላይ የሚወስዱት ስልጠና በስራዎቻቸው ላይ ውጤታማ ያደርጋቸዋል ተብሎ ታምኗል።

ስልጠናው እየተሰጠ የሚገኘው የክልሉ ኢንዱስትሪ ፓርኮች ልማት ኮርፖሬሽን ከGIZ "Invest for jobs project" ጋር በመተባበር እንደሆነ ለማወቅ ተችሏል።

ስልጠናው ስማርት ኬርየር ሶልሽን ኮንሰልታንሲ ኃላፊነቱ የተወሰነ ማህበር አማካይነት እየተሰጠ ሲሆን በቀጣይ ቀናት የተግባር ስልጠና እንደሚቀጥል ተነግሯል ሲል የክልሉ ኮሙንኬሽን ቢሮ ዘግቧል።

ወሰን ተሻጋሪ የበጎ ፈቃድ አገልግሎት በህዝቦች መካከል የነበረውን አብሮነት ለማጠናከር ያለው ፋይዳ ከፍተኛ እንደሆነ ተገለፀ።የሀዲያ ዞን ብልጽግና ፓርቲ ሴቶች ክንፍ አባላት"በጎነት ለኢትዮጵ...
03/09/2025

ወሰን ተሻጋሪ የበጎ ፈቃድ አገልግሎት በህዝቦች መካከል የነበረውን አብሮነት ለማጠናከር ያለው ፋይዳ ከፍተኛ እንደሆነ ተገለፀ።

የሀዲያ ዞን ብልጽግና ፓርቲ ሴቶች ክንፍ አባላት"በጎነት ለኢትዮጵያ ከፍታ"በሚል መሪ ሀሳብ የክረምት ወራት ወሰን ተሻጋሪ አገልግሎት በከምባታ ዞን ሀደሮ ከተማ አስተዳደር ተገኝተው አከናወኑ።

።።።።28/12/2017 ዓ/ም ።።።: ‎

የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የሴቶች ክንፍ ኃላፊ ወ/ሮ ኤልሳቤጥ ሽመልስ በ14 መስኮች በሚከናወነው የክረምት ወራት በጎ ተግባር ላይ የሴቶችን ተሳትፎና ተጠቃሚነት ወደ ላቀ ደረጃ ከፍ በማድረግ በቅንጅት ለቀጣይ ትውልድ ለማሸጋገር የሚያግዝ ሥራ እየተከናወነ መሆኑን ተናግረዋል።

ከብልጽግና ፓርቲ እሴቶች አንዱ የሆነውን በህዝቦች መካከል መቀራረብን እና መተጋገዝን የማጠናከር መልካም ተግባርን በማስቀጠል እሴቶችና ብዝሃ ሃብቶች አልምተን በመጠቀም ለተጀመረው የብልጽግና ጉዞ መትጋት ይኖርብናል ብለዋል።

በሴቶች ክንፍ መሪነት በክረምት ወራት የተለያዩ በጎ ተግባራት ለማከናወን ታቅዶ ወደ ተግባር መገባቱ ይታወቃል በዚህም በርካታ ሴቶችን ተጠቃሚ ለማድረግ እየተሰራ ነው ሲሉ ገልጸዋል።

በጎነት አንዱ ለአንዱ ያለውን ፍቅር የሚገልጽበት አንዱ መንገድ ነው። ስለዚህ በየአካባቢው ድጋፍ ለሚሹ ወገኖች የሚደረገው ድጋፍ ተጠናክሮ መቀጠል አለበት በማለት መልእክታቸውን አስተላፈዋል።

የከምባታ ዞን ብልጽግና ፓርቲ ዲሞክራሲና አቅም ግንባታ ዘርፍ ኃላፊ አቶ ደስታ ሰለሞን እንኳን የፍራፍሬ እና ቅመማቅመም ምርት ባለቤት ወደ ሆነችው ሀደሮ ከተማ በደህና መጣችሁ በማለት ይህ ወሰን ተሻጋሪ የበጎ ፈቃድ ጉዞ ወንድማማችነትንና እህትማማችነት በማጠናከር አብሮነት እንዲፀና የሚያግዝ ነው ብለዋል።

አክለውም ሀዲያ እና ከምባታ ዞኖች ከጥንት ጀምሮ እጅግ የተጋመደ ባህልና ታሪክ ያላቸው ህዝቦች ሲሆኑ ይህ ጉዞ ደግሞ ይበልጥ እንዲጠናከሩ ያደርጋቸዋል በማለት ተናግረዋል።

የሀዲያ ዞን ብልጽግና ፓርቲ ሴቶች ክንፍ ጽ/ቤት ኃላፊ ወጋሜ ጴጥሮስ ይህ ወሰን ተሻጋሪ የበጎ ፈቃድ አገልግሎት በሁለቱም ህዝቦች መካከል ያለውን አብሮነት ለማጠናከር ያለመ ሲሆን ጎን ለጎን ደግሞ አቅመ ደካሞችን ስንደግፍ ብልጽግና ፓርቲ ሰው ተኮር ፓርቲ መሆኑን የሚያሳይ ነው በማለት ገልጸዋል።

በጉዟቸው መረሐ ግብር አንዱ በሀደሮ ከተማ አስተዳደር የምትገኝ የአንዲት የአቅመ ደካማ እናት ቤት እድሳት ማስጀመር እና ከከተማው ለተወጣጡ አቅመ ደካማ ወገኖች የዱቄትና የዘይት ድጋፍ ማድረግ እንዲሁም የነገ ሀገር ተረካቢ ለሆኑት ተተኪ ትውልዶች የትምህርት ቁሳቁስ መለገስ ሲሆን ጎን ለጎንም የከተማ መንገድ ዳር የጽዳት ተግባር ማከናወናቸውንም ተናግረዋል።

በመጨረሻም ድጋፍ የተደረገላቸው ወገኖች በተደረገላቸው ድጋፍ የተሰማቸውን ደስታ በመግለጽ ልባዊ ምስጋናቸውን አቅርበዋል።

በመርሐ ግብሩ የሀዲያ ዞን ምክር ቤት ዋና አፈ-ጉባኤ ክብርት ወ/ሮ እቴነሽ ሙሉጌታ፣ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ብልጽግና ፓርቲ ሴቶች ክንፍ ኃላፊ ወ/ሮ ኤልሳቤት ሽመልስ፣ የሀዲያ ዞን ብልጽግና ፓርቲ ሴቶች ክንፍ ኃላፊ ወጋሜ ጴጥሮስ፣የሀዲያ እና የከንባታ ዞን ከፍተኛ ሴት አመራሮችን ጨምሮ የሀደሮ ከተማ አስተዳደር አመራር ተገኝተዋል።

በታከለ አጋፋሪ

በሀዲያ ዞን የዞን ማዕከል የብልጽግና ህብረት አባላት "ኢትዮጵያን ወደ ተምሳሌት ሀገር" እና "የአገልግሎት ልህቀት ለኢትዮጵያ ማንሰራራት" - በሚሉ መሪ ሀሳቦች የተደረጉ ውይይቶች በኮንፈረን...
02/09/2025

በሀዲያ ዞን የዞን ማዕከል የብልጽግና ህብረት አባላት "ኢትዮጵያን ወደ ተምሳሌት ሀገር" እና "የአገልግሎት ልህቀት ለኢትዮጵያ ማንሰራራት" - በሚሉ መሪ ሀሳቦች የተደረጉ ውይይቶች በኮንፈረንስ ተጠናቋል።

ሆሳዕና፡ ነሐሴ 27/2017 ዓ.ም በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ሀዲያ ዞን የዞን ማዕከል የብልጽግና ህብረት አባላት ኢትዮጵያን ወደ ተምሳሌት ሀገር በሚል መሪ ሀሳብ የህብረቱ አባላትና አመራሮች በተገኙበት ለሁለት ተከታታይ ቀናት ኮንፍረንስ አካሄደዋል።

በየመድረኩ ለህብረቱ አባላትና አመራሩ በሀገራዊ፣ ቀጠናዊ እና አከባቢያዊ ነባራዊ ሁኔታ ላይ ግንዛቤ የተፈጠረ ሲሆን፤ የሀገሪቱን ሁለንተናዊ ብልጽግና ጉዞ ዕውን ለማድረግ በአገልግሎት አሰጣጥም የነበሩ ጉድለቶችን በማረም የህዝቡን የመልካም አስተዳደር ችግር ለመፍታት በቁርጠኝነትና በአገልጋይነት መንፈስ ለመስራት የጋራ መግባባት ላይ ተደርሷል።

በኮንፍረንሱ በፓርቲው የአሰራርና አደረጃጀት መመሪያ መሰረት የዞን ማዕከሉ ህብረት ሶስት ህብረቶችን መልሶ በማደራጀት ስራ የህብረት አመራሮች ዴሞክራሲያዊ በሆነ አግባብ ምርጫ ተካሂዷል።

በዚህም የፓርቲውን ዓላማ በሚገባ የተረዳ እና የህብረተሰቡን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ በሚደረገው ርብርብ የድርሻውን የሚወጣ ጥራት ያለውን አባል በማፍራት ረገድ በቀጣይ በትኩረት እንደሚሰራ አቋም ተይዟል።

በኮንፍረንሱ ላይ በየተደረገው ውይይት በአመለካከትና በተግባር ግንባር ቀደም አባል ሆኖ ለመገኘት እና በተቀመጡ አቅጣጫዎች ዙሪያ የጋራ መግባባት ላይ ተደርሶ ኮንፍራንሱ በስኬት ተጠናቋል።

የ 2017 ዓ.ም ማጠቃለያ የሆነችው የኢትዮጵያ 13ኛዋ ወር የጳጉሜ ቀናት እንደሚከተለው ተሰይመው በሀገር አቀፍ ደረጃ በተለያዩ ትልልቅ ሀገራዊ ሁነቶች ይከበራሉ ።!
02/09/2025

የ 2017 ዓ.ም ማጠቃለያ የሆነችው የኢትዮጵያ 13ኛዋ ወር የጳጉሜ ቀናት እንደሚከተለው ተሰይመው በሀገር አቀፍ ደረጃ በተለያዩ ትልልቅ ሀገራዊ ሁነቶች ይከበራሉ ።!

የጊምቢቹ ቴክኒክና ሙያ ኮሌጅ በተለያዩ የሙያ ዘርፎች ያሰለጠናቸውን ተማሪዎች አስመረቀበምረቃ ፕሮግራሙ መክፈቻ የእንኳን ደህን መጣችሁ መልዕክት ያስተላለፉት የኮሌጁ ዲን አቶ ታፈሰ ላምቦሬ እ...
02/09/2025

የጊምቢቹ ቴክኒክና ሙያ ኮሌጅ በተለያዩ የሙያ ዘርፎች ያሰለጠናቸውን ተማሪዎች አስመረቀ

በምረቃ ፕሮግራሙ መክፈቻ የእንኳን ደህን መጣችሁ መልዕክት ያስተላለፉት የኮሌጁ ዲን አቶ ታፈሰ ላምቦሬ እንደገለፁት፤ ኮሌጁ እንደዕድሜው ሳይሆን በመንግስት የተጣለበትን ሀላፊነት በአግባቡ እየተወጣ ይገኛል።

ሰልጣኝ ተማሪዎች በኮሌጅ ቆይታቸው በንድፈ ሀሳብና በተግባር ትምህርት ብቻ ሳይሆን በዘመን ተሻጋሪ አብሮነትና አንድነት እንዲሁም የሥራ ለውጥ አስተሳሰብ በመታነፅ ብቁና ተወዳዳሪ ዜጎች ለመሆን በቁርጠኝነት መነሳት አለባቸው ብለዋል።

ኮሌጁ የትኩረት መስክ ልየታ በማድረግ በመማር ማስተማር በቴክኖሎጂ ሽግግርና ለኢንዱስትሪ ኤክስቴንሽን የተሟላ ድጋፍ በመስጠት የተጣለበትን ሀገራዊ ሀላፊነት በስኬት እየተወጣ እንደሚገኝ አቶ ታፈሰ ገልፀዋል።

የጊምቢቹ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አቶ ታገሠ ተመስገን በዚሁ ወቅት እንዳሉት፤ የተማረ የሰው ኃይል ለሀገር ዕድገት የተሻለ ዕውቀት በማፍለቅና ሀሳብ በማመንጨት አዎንታዊ አስተዋዕፆ እንደማበርከቱ መንግስት የቴክኒክና ሙያ ተቋማት ተልዕኮ እንዲሳካ ከፍተኛ እገዛ እያደረገ ነው።

ስራን ፈጥሮ የራስን ህይወት በአግባቡ ከመምራት ባለፈ በየአካባቢው የሚታዩ ችግሮችን ሊፈቱ የሚችሉ ተግባራትን በማከናወን የህብረተሰቡን አለኝታነት ማሳየት ያስፈልጋልም ብለዋል።

የሀዲያ ዞን ቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ስልጠና መምሪያ ኃላፊ አቶ ተስፋዬ ርስቱ በበኩላቸው፤ የዕለቱ ተመራቂዎች ከስራ ጠባቂነት አስተሳሰብ ተላቀው ስራ ፈጥረው የራሳቸውን፣ የቤተሰቦቻቸውን እና የማህበረሰቡን ኑሮ የሚለውጥ ቴክኖሎጂዎችን በመፍጠር የበኩላቸውን መወጣት እንዳለባቸው አሳስበዋል።

የቴክኒክና ሙያ ትምህርት በስራ ገበያ ላይ ተፈላጊ ሆኖ ክህሎቶችን በማስተማር ብቁና የሰለጠነ የሰው ኃይል በማፍራት ረገድ አበረታች ውጤት እየተመዘገበ ይገኛል ያሉት ደግሞ የሀዲያ ዞን ረዳት የመንግስት ተጠሪና የፖለቲካና የአቅም ግንባታ ዘርፍ ኃላፊ እንዲሁም የዕለቱ የክብር እንግዳ አቶ መሳይ ተስፋዬ ሰልጣኞች በስራ ዓለም ውስጥ አዳዲስ ነገሮችን ለመማር ዝግጁ መሆን እንዳለባቸው አንስተዋል።

ለውጥን መቀበልና የሚያጋጥሙ ተግዳሮቶችን ወደ መልካም ዕድል መቀየር ወሳኝ ጉዳይ መሆኑን የጠቆሙት አቶ መሳይ ሀቀኝነት፣ ታታሪነትና በተቀናጀ መልኩ ተግባራትን ማከናወን የስኬት ጅምር ነው ሲሉ ተናግረዋል።

አንዳንድ ሰልጣኝ ተመራቂዎች በሰጡት አስተያየት ከኮሌጁ ባገኙት ዕውቀትና ክህሎት የበቁ ዜጎች በመሆን የፈጠራ ስራዎች ላይ እንደሚሰማሩ ተናግረዋል።

"በጎነት ለኢትዮጵያ ከፍታ" በሚል መሪ ሀሳብ የሀዲያ ዞን ወሰን ተሻጋሪ ልዑካን ቡድን ወደ ከምባታ ዞን ተጓዘ።ወሰን ተሻጋሪ ልዑካን ቡድኑ በከንባታ ዞን ሀደሮ ከተማ ላይ የእንኳን ደህና መጣ...
02/09/2025

"በጎነት ለኢትዮጵያ ከፍታ" በሚል መሪ ሀሳብ የሀዲያ ዞን ወሰን ተሻጋሪ ልዑካን ቡድን ወደ ከምባታ ዞን ተጓዘ።

ወሰን ተሻጋሪ ልዑካን ቡድኑ በከንባታ ዞን ሀደሮ ከተማ ላይ የእንኳን ደህና መጣችሁ አቀባበል ተደርጎለታል።

።።።።።።።27/12/2017 ዓ/ም ።።።።።።።።።

በሀዲያ ዞን ብልጽግና ፓርቲ ሴቶች ክንፍ የተዘጋጀው የወሰን ተሻጋሪ ልዑካን ቡድን የተለያዩ ለምግብነት የሚውሉ ፍጆታዎችን፣ለተማሪዎች ትምህርት የሚያስፈልጉ ቁሳቁስ እና ለቤት ሥራ የሚሆን የተለያዩ የድጋፍ ቁሳቁሶችን በመያዝ የተጓዘ ሲሆን ቡድኑ ወደ ከንባታ ዞን ሲገባ ሀደሮ ከተማ ላይ የመንገድ ዳር ጽዳት ሥራ አከናውነዋል።

በጉዞው የሀዲያ ዞን ምክር ቤት ዋና አፈ-ጉባኤ ክብርት ወ/ሮ እቴነሽ ሙሉጌታ፣ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ብልጽግና ፓርቲ ሴቶች ክንፍ ኃላፊ ወ/ሮ ኤልሳቤጥ ሽመልስ፣ የሀዲያ ዞን ብልጽግና ፓርቲ ሴቶች ክንፍ ኃላፊ ወጋሜ ጴጥሮስ፣የዞኑ ከፍተኛ ሴት አመራርን ጨምሮ ከወረዳ እና ከከተማ አስተዳደሮች የመጡ የሴቶች ክንፍ ኃላፊዎች ተገኝተዋል።
በታከለ አጋፋሪ

ያሆዴ...ያሆዴ...ያሆዴ....                              ሆያ..ሆ  ሆየሀዲያ ብሔር የዘመን መለወጫ "ያሆዴ" በዓል ደረሰ!  የ"ያሆዴ" በዓል በሀዲያ አዲስ የተስፋ ብርሃ...
02/09/2025

ያሆዴ...ያሆዴ...ያሆዴ....
ሆያ..ሆ ሆ

የሀዲያ ብሔር የዘመን መለወጫ "ያሆዴ" በዓል ደረሰ!

የ"ያሆዴ" በዓል በሀዲያ አዲስ የተስፋ ብርሃን የሚሞላበት፣ ያለፈውን ዓመት ወደ ማይመለስበት አሰናብቶ ለአዲሱ ዓመት ዝግጅት የሚደረግበት፣ በጉጉትና ናፍቆት የሚጠበቅ ነው፡፡

ያሆዴ ከምንም በላይ ለሀዲያ ህዝብ የሁሉም ነገር መጀመሪያው ነው ተብሎ ይታመናል።

እናም በሀድያ ትልቅ ቦታ ተሠጥቷቸው በታላቅ ስነ ስርዓት ከሚከበሩ በዓሎች አንዱ ያሆዴ ነው፡፡

ይህ ታላቅ በዓል የብሔሩ ተወላጆችና ሌሎች የበዓሉ ተሳታፊዎች በየዓመቱ ከያሉበት በመሰባሰብ ሰፊ በሆነ ዝግጅት በተለያዩ ባህላዊ እሴቶች ክዋኔ በድምቀት ይከበራል ፡፡

የ ያሆዴ በዓል ሲከበር በርካታ የብሔሩ ማንነት፣ ታሪክ፣ ቋንቋ ፣ የአኗኗር ስርዓትና ባህላዊ እሴቶች ተዛንቀው የሚፀባረቁበት ነው፡፡

በዓሉ የርስበርስ ግንኙነት የመቻቻል፣ የአብሮነትና የአንድነት እሴቶች ትስስርን በማጠናከር አንድነትን በይበልጥ የሚያጎለብትና ሌሎች በርካታ ፋይዳዎች ያሉት ነው፡፡

በሀድያ የ ያሆዴ በዓልን ለማክበር የሚደረጉ ዝግጅቶች በርካታ ሲሆኑ፤

በተለይ ደግሞ ከነሐሴ ወር መግቢያ ጀምሮ እስከ በዓሉ መዳረሻ የሚደረጉ ዝግጅቶት ደማቅና ማራኪ ናቸው።

በዓሉ ሲከበርም....

1. የብሔሩ ባህላዊ እሴቶች የሚተዋወቁበት የባህልና ልማት ኤግዝቢዥን ይከፈታል።

2. ያሆዴ ካፕ የእግር ኳስ ውድድር በዞኑ በሚገኙ የወረዳና የከተማ አስተዳደር መዋቅሮች የተሳተፉበት ይካሄዳል።

3. በርካታ የህብረተሰብ ክፍሎች የሚሳተፉበት ባህሌን ጠብቃለሁ ለያሆዴ እሮጣለሁ በሚል መሪ ሃሳብ "ያሆዴ" የጎዳና ላይ ሩጫ በሆሳዕና ከተማ ይካሄዳል።

4.በሀድያ ባህል የልጅ አገረዶች የአለባበስና አጋጌጥ ውድድር ይካሄዳል።
5. "አተካን ሂሞ" የአተካና ምሽት በያሆዴ ፉሊታ ጭፈራ፣ ልጆች ምርቃት የአባቶች ስጦታ እና በሌሎችም ተያያዥ ዝግጅቶቾ ዕለተ ዋዜማው ምሽቱ ይደምቃል።

ነሐሴ 27/2017 ዓ.ም

በካሳሁን አባይነህ

ጥራት ያለው የህክምና አገልግሎት ከመስጠት በተጓዳኝ በማህበራዊ አገልግሎትች ላይ በመሳተፍ ህብረተሰቡን ማገልገል እንደሚገባ ተመላከተ።የንግስት እሌኒ መሐመድ መታሰቢያ ኮምፕርሄንሲቭ ስፔሻላይዝ...
02/09/2025

ጥራት ያለው የህክምና አገልግሎት ከመስጠት በተጓዳኝ በማህበራዊ አገልግሎትች ላይ በመሳተፍ ህብረተሰቡን ማገልገል እንደሚገባ ተመላከተ።

የንግስት እሌኒ መሐመድ መታሰቢያ ኮምፕርሄንሲቭ ስፔሻላይዝድ ሆስፒቲል ”በጎ ፍቃደኝነት ለጤናማ ማህበረሰብ” በሚል መሪ ሀሳብ የክረምት በጎ ፍቃድ አገልግሎት መርሃ-ግብር አካሄዷል።

።።።።።።።።።።። ነሐሴ፤27/2017 ።።።።።።።።።።።።

ሆስፒታሉ በክረምት ወራት ለአከባቢው ማህበረሰብ የተለያዩ ዘርፈ ብዙ በጎ ተግባራት እያከናወነ እንደሚገኝ ተገልጿል።

የንግስት እሌኒ መሐመድ መታሰቢያ ኮምፕርሄንሲቭ ስፔሻላይዝድ ሆስፒቲል ቺፍ ኤክስኪዩቲቭ ዳይሬክተር ዶ/ር ይድነቃቸው ደዳቸው፤ሆስፒታሉ ለአከባቢው ህብረተሰብ ጥራት ያለው የጤና አገልግሎት ከመስጠት በተጓዳኝ ባለፉት 3 ወራት በማህበራዊ አገልግሎቶች ላይ ተሳታፊ በመሆን ኃላፊነቱን መወጣቱን ገልፀዋል።

በዛሬ መርሃ-ግብር “በጎ ፍቃደኝነት ለጤናማ ማህበረሰብ” በሚል ሀሳብ ደም ልገሳ እየተካሄደ እንደሚገኝ የተናገሩት ዶ/ር ይድነቃቸው ከተለምዶ በተለየ ሁኔታ ከ200 በላይ የደም ዩኒት ለማሰባሰብ ታቅዶ እየተሰራ ይገኛል ነው ያሉት።

በክረምት ወራት በሚከናወኑ ተግባራት ለአከባቢው ማህበረሰብ በርካታ የበጎ ፍቃድ አገልግሎቶች እየተሰጠ ይገኛል ያሉት ቺፍ ኤክስኪዩቲቭ ዳይሬክተሩ ባለፈው 1 ሳምንት ለ30 ሺ የህብረተሰብ ክፍሎች የተለያዩ አይነት ምርመራ በማድረግ የራሳቸውን ጤንነት እንዲያውቁ መደረጉን አስታውሰዋል።

ከጤና አገልግሎት ባለፈ ተማሪዎች አዲሱን የትምህርት ዘመን በአዲስ መንፈስ እንዲጀምሩ ለ150 ተማሪዎች የመማሪያ ቁሳቁስ እና ለምግብነት የሚውሉ መሰረታዊ ፍጆታዎች ድጋፍ መደረጉን ዶ/ር ይድነቃቸው አክለዋል ።

የበጎ ፍቃድ አገልግሎት በሀገራችን የተለመደና ባህል የሆነ ተግባር በመሆኑ ሁሉም ህብረተሰብ ድጋፍ ለሚሹ አካላት አስፈላጊውን በማድረግ ማስቀጠል እንደሚገባ ዶ/ር ይድነቃቸው መልዕክት አስተላልፈዋል።

ሆስፒታሉ በዞኑ በሚገኙ ጤና ጣቢያዎችና ሆስፒታሎች የመድኃኒት እና የተለያዩ አይነት ቁሳቁስ ድጋፍ በማድረግ እንዲሁም ጥራት ያለው አገልግሎት ለህብረተሰቡ በመስጠት በሀገር አቀፍ ደረጃ ተወዳዳሪ መሆኑን የገለጹት የሀዲያ ዞን ጤና መምሪያ ኃላፊ ዶ/ር ደሳለኝ ሽጉጤ ናቸው።

በሀገር አቀፍ እየተከናወነ የሚገኘውን የክረምት በጎ ፍቃድ አገልግሎት በመቀበል ለህብረተሰቡ የተለያዩ አይነት ነፃ የህክምና ምርመራ በማካሄድ እና ተማሪዎች ከትምህርት ገበታ እንዳይቀሩ የመማሪያ ቁሳቁስ ድጋፍ በማድረግ አመርቂ ስራ በመስራቱ የሆስፒታሉ ማናጅመንትና ሰራተኞች ሊመሰገኑ እንደሚገባ አክለዋል።

የሆስፒታሉ ቺፍ አስተዳደርና ልማት ዳይሬክተር አቶ ተክሌ እጃጆ በበኩላቸው የሆስፒታሉ አጠቃላይ ሰራተኞች ሀብት ከራሳቸው በማሰባሰብ በክረምት በጎ ፍቃድ አገልግሎትመሳተፋቸው አመላክተዋል።

በወሊድ ወቅት በደም እጥረት የእናቶች ሞት ለመቅረፍ እና በተለያየ አደጋ ወቅት ደም ለሚያስፈልጋቸው አካላት በመድረስ ውድ የሆነውን የሰው ልጅ ህይወት መታደግ ያስፈልጋል ያሉት ደም የለገሱ የሆስፒታሉ ሰራተኞች ናቸው።

በፍላጎት ለማ

መጪዎቹ የጳጉሜን ቀናት…ሆሣዕና ነሐሴ 27፣ 2017  በተገባደደው ዓመት የተከናወኑ ስኬታማ ተግባራትና የቀጣይ ሀገራዊ እቅዶች የሚተዋወቁባቸው መጪዎቹ የጳጉሜን ቀናት የተለያዩ ስያሜ ተሰጥቷቸ...
02/09/2025

መጪዎቹ የጳጉሜን ቀናት…

ሆሣዕና ነሐሴ 27፣ 2017 በተገባደደው ዓመት የተከናወኑ ስኬታማ ተግባራትና የቀጣይ ሀገራዊ እቅዶች የሚተዋወቁባቸው መጪዎቹ የጳጉሜን ቀናት የተለያዩ ስያሜ ተሰጥቷቸዋል፡፡

ጳጉሜን-1 የጽናት ቀን

የጽናት ቀን “ጽኑ መሰረት ብርቱ ሃገር” በሚል መሪ ሀሳብ ለኢትዮጵያ ብልጽግና የሚተጉና ዋጋ የከፈሉ ኢትዮጵያውያንን በመዘከርና በማመስገን ይከበራል፡፡

ጳጉሜን-2 የህብር ቀን

የህብር ቀን “ብዝሃነት የኢትዮጵያ ጌጥ” በሚል ሀሳብ የኢትዮጵያን የብዝሃነትና የአንድነት ውበት እንዲሁም የአብሮነት እሴት በሚያጎሉ ዝግጅቶች ተከብሮ ይውላል፡፡

በዕለቱ ድጋፍ ለሚሹ ወገኖች የቁሳቁስ፣ የማዕድ ማጋራት፣ የመማሪያ ቁሳቁስና መሰል ድጋፎችን በማድረግ አብሮነትን የሚያሳዩ የበጎ አድራጎት ተግባራት ይከናወናሉ፡፡

ጳጉሜን-3 የእመርታ ቀን

የእመርታ ቀን “እመርታ ለዘላቂ ከፍታ” በሚል መሪ ሀሳብ ባለፉት አመታት የተመዘገቡ ስኬቶችንና ለቀጣዩ አመት የተሻለ ስራዎች እንዲሰሩ በማሰብ ይከበራል፡፡

በግብርናው ዘርፍ የምግብ ሉአላዊነትን ለማረጋገጥ፣ በአረንጓዴ አሻራ መርሐ ግብር፣ በኢንዱስትሪ፣ በማዕድንና ሌሎች ዘርፎች የተመዘገቡ ስኬቶች ይወሱበታል፡፡

ጳጉሜን-4 የማንሰራራት ቀን

የማንሰራራት ቀን “ዘላቂ ልማት ለሀገራዊ ማንሰራራት” በሚል መሪ ሀሳብ ኢትዮጵያ በለውጥ የማንሰራራት ጅማሮ ላይ መሆኗን በሚያሳዩ ሁነቶች ይከበራል፡፡

ጳጉሜን-5 የነገው ቀን

የነገው ቀን “ዲጂታል ኢትዮጵያን እውን ማድረግ” በሚል መሪ ሀሳብ የነገዋን ኢትዮጵያ በዲጂታል ለመገንባት እየተከናወኑ ያሉ ስራዎችን በማውሳት የሚከበር ይሆናል፡፡
ኤፍ ኤም ሲ

02/09/2025

Address

Hossana

Telephone

+251465551908

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Hadiya zone Government Communication posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to Hadiya zone Government Communication:

Share