ACHE TUBE

ACHE TUBE ሁለም አዝናኝ,አስተማሪና ትኩስ መረጃዎች !!

 #ነፍስ ይማርለመጀመሪያ ጊዜ የሰራበት ፊልምን ሊያስመርቅ ነው። እናም አባቱን 'ፊልሜን ካላየህ' ይልና ይጨቀጭቃቸዋል። አባት ስራቸው የማያወላዳ ቢሆንም ልጃቸው የፎከረበትን ስራ ሊመለከቱ ሰ...
25/08/2024

#ነፍስ ይማር

ለመጀመሪያ ጊዜ የሰራበት ፊልምን ሊያስመርቅ ነው። እናም አባቱን 'ፊልሜን ካላየህ' ይልና ይጨቀጭቃቸዋል። አባት ስራቸው የማያወላዳ ቢሆንም ልጃቸው የፎከረበትን ስራ ሊመለከቱ ሰው ተክተው ፊልሙ ወደሚመረቅበት ስፍራ አመሩ።

ፊልሙ ጀመረ። ጀምሮም አለቀ። አባት ግራ ተጋቡ። ባቡጂ የለበትም።
ወደልጃቸው ዞረው "እሰራበታለሁ አላልክም! የታለህ!?" አሉት።
ባቡጂም "እንዴ አባዬ የሆነ ቦታ ላይ ሁለቴ ያሳልኩት እኔ ነኝ!" ሲል ይመልስላቸዋል። አባት ትክን ይላሉ። እሱን ለማየት ነውና ሰው ተክተው ምርቃት ቦታ የተገኙት። ከመበሳጨታቸው የተነሳ ከምርቃቱ ስፍራ እስከሰፈራቸው ሳያናግሩት ቤት ደረሱ።

ባቡጂ ከ60 በላይ ፊልም ሰርቷል። በብዕር ስም ቢሆንም የጻፋቸው መጽሐፍ አሉት። ድንቅ የኮሜዲ ትወና ብቃት እንዳለውም ይመሰክሩለታል።

ፀሐፊ ተውኔት፣ ደራሲና ጋዜጠኛ ውድነህ ክፍሌ ስለጌታቸው እጅጉ(ባቡጂ)

Tube ለባቡጂ ቤተሰቦች፣ ወዳጆችና አድናቂዎች፣ መጽናናትን ይመኛል።

ማንቸስተር ዩናይትድ በፕሪሚየር ሊግ የመክፈቻ ጨዋታ ፉልሃምን 1 ለ 0 አሸነፈ*******************ዛሬ በተጀመረው የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ የመጀመሪያ ሳምንት መርሃ ግብር ማንቸስተር...
16/08/2024

ማንቸስተር ዩናይትድ በፕሪሚየር ሊግ የመክፈቻ ጨዋታ ፉልሃምን 1 ለ 0 አሸነፈ
*******************

ዛሬ በተጀመረው የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ የመጀመሪያ ሳምንት መርሃ ግብር ማንቸስተር ዩናይትድ ፉልሃምን 1 ለ 0 አሸንፏል፡፡

የ2024/2025 የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ መርሐ ግብር በዛሬው ዕለት የተጀመረ ሲሆን ምሽት 4 ሰዓት ላይ ማንቸስተር ዩናይትድ ከፉልሃም ጋር የውደድር ዘመኑን የመጀመሪያ ጨዋታ አድርገዋል፡፡

በዚህም በጨዋታው ማንቸስተር ዩናይትድ ተቀይሮ የገባው ጆሽዋ ዚርኪዝ በ87ኛው ደቂቃ ባስቆጠረው ግብ ማሸነፍ ችሏል፡፡

ፕሪሚየር ሊጉ ነገ ሲቀጥል ኢፕስዊች ከሊቨርፑል፣ አርሰናል ከወልቭስ፣ ኢቨርተን ከብራይተን፣ ኒውካስል ከሳውዝሃምፕተን፣ ዌስትሃም ከአስቶንቪላ እና ኖቲንግሃምፎረስት ከቦርንማውዝ ይጫወታሉ፡፡

ጆሽዋ ዚርኪዝ

በ33ኛው የፓሪስ ኦሎምፒክ በተመዘገበው ዝቅተኛ ውጤት ዙሪያ የሻለቃ ኃይሌ ገብረስላሴ እና የዶ/ር አሸብር ወ/ጊዮርጊስ አስተያየቶች ምን አሉ ??"የምንፈልገው ክርክር ሳይሆን በእኛ ምክንያት ...
16/08/2024

በ33ኛው የፓሪስ ኦሎምፒክ በተመዘገበው ዝቅተኛ ውጤት ዙሪያ የሻለቃ ኃይሌ ገብረስላሴ እና የዶ/ር አሸብር ወ/ጊዮርጊስ አስተያየቶች ምን አሉ ??

"የምንፈልገው ክርክር ሳይሆን በእኛ ምክንያት ህዝቡ ውጤት አጥቷል ብለው ስልጣን እንዲለቁ ነው" - ሻለቃ ኃይሌ ገብረሥላሴ

ሻለቃ ኃይሌ ገብረሥላሴ "ለበርካታ ዓመታት ችግሩ ሳይታረም በመቆየቱ በሶስት ኦሎምፒክ ሶስት የወርቅ ሜዳሊያ ብቻ ለማግኘት ተገደናል" በማለት በኢትዮጵያ የውጤት ቀውስ የተሰማውን ቁጭት ገልጿል።

የፓሪስ ኦሎምፒክ ውጤት ላይ የታዩ ችግሮች እና ዘላቂ የመፍትሄ ሀሳቦች በሚል ርዕስ ኢቢሲ ኤፍ ኤም አዲስ 97.1 የቀጥታ ውይይት አዘጋጅቷል።

የሁለት ኦሎምፒክ ወርቅ ሜዳሊያ ባለቤቱ ሻለቃ ኃይሌ ገብረሥላሴ በውይይቱ ላይ "የእኛ ተፎካካሪዎች በሶስት ኦሎምፒክ 14 ወርቅ ወስደዋል፤ እኛ ደግሞ አሁን ኦሎምፒክ ለተሳትፎ ነው እየተባልን ነው" ሲል ተናግሯል።

"አንድን ስፖርተኛ ሂድና አሸንፍ ብለን ከመላካችን በፊት የሚመራህ አካል ፍትሃዊ ነው ብለን ማሳመን አለብን ያለው ኃይሌ ኢ-ፍትሃዊ የሆነ አስተዳደር የስፖርተኞችን በራስ መተማመን እና የማሸነፍ ፍላጎት ይቀንሳል" ብሏል።

"የኢትዮጵያ ኦሎምፒክ ኮሚቴ ከአንድም ሁለት ሶስት ጊዜ በቻሉት ልክ ሞክረዋል ነገር ግን አልተሳካም" ብሏል ሻለቃ ኃይሌ።

"አሁን ከአሸብር ወልደጊዮርጊስ (ዶ/ር) ጀምሮ ካሉት የተቋሙ አመራሮች የምንፈልገው ክርክር ሳይሆን ህዝቡን አስቀይመናል፣ በእኛ ምክንያት ህዝቡ ውጤት አጥቷል ብለው ስልጣን እንዲለቁ ነው" በማለት ሻለቃ ኃይሌ ገብረሥላሴ የመፍትሔ ሀሳቡን ጠቁሟል።

================================

"ከስልጣን የምለቅበት ምንም አይነት ምክንያት የለም" - ዶ/ር አሸብር ወልደጊዮርጊስ

በ33ኛው የፓሪስ ኦሊምፒክ ኢትዮጵያ በአንድ ወርቅ እና በሶስት የብር ሜዳልያዎች ከዓለም 47ኛ እንዲሁም ከአፍሪካ አራተኛ ደረጃን በመያዝ አጠናቃለች።

ውጤቱም ሆነ ከውጤቱ በኋለ የነበሩ ሁነቶች በሙሉ በኢትዮጵያ ህዝብ ዘንድም ቅሬታን እና ቁጭትን የፈጠሩ ሆነዋል።

ታዲያ ብዙ በተጠበቅንበት የፓሪስ ኦሊምፒክ ተሳትፎ ዙሪያ የኢትዮጵያ ኦሊምፒክ ኮሚቴም በዛሬው ዕለት ጋዜጣዊ መግለጫ ሰጥቷል።

የኢትዮጵያ ኦሊምፒክ ኮሚቴ በመግለጫው ላይ አጠቃላይ የፓሪስ ቆይታን በተመለከተ በቴክኒክ ኮሚቴው ሰብሳቢ አቶ ቢልልኝ መቆያ አጠር ያለ ሪፖርት ያቀረበ ሲሆን በሪፖርቱም ካለፉት ሁለት ኦሊምፒኮች የተሻለ ውጤት መገኘቱ ተገልጿል።

የተገኘው ውጤት የሀገራችንን የኦሊምፒክ ታሪክ የሚገልፅ አይደለም እና ተቋሙ ኃላፊነት ይወስዳል ወይ በተጨማሪም የኦሊምፒክ ኮሚቴው አመራሮች እራሳችሁን ከስልጣን ታነሳላችሁ ወይ በሚል ለቀረበው ጥያቄ የኢትዮጵያ ኦሊምፒክ ኮሚቴ ፕሬዝዳንት ዶ/ር አሸብር ወልደጊዮርጊስ፤ ለውጤት መጥፋቱ ሁሉም ኃላፊነት አለበት፤ ኦሊምፒክ ኮሚቴው ያለአግባባ በማይመለከተው ጉዳይም እየተተቸ ይገኛል ብለዋል።

ስልጣንን በመልቀቅ እና በመሸሽ መፍትሔ ስለማይመጣ ከስልጣን የምለቅበት ምንም አይነት ምክንያት የለም ያሉት ፕሬዝዳንቱ፤ ከዚህ ቀደም ከኢትዮጵያ እግርኳስ ፌዴሬሽን በመልቀቄ የመጣ ለውጥ የለም ሲሉ ተናግረዋል።

ፕሬዚዳንቱ አያይዘውም ኦሊምፒክ ተሳትፎ ነው ብዬ ለሰጠሁት ሀሳብ የቃሉ አውድ ለህዝባችን አዲስ ስለሆነ ይቅርታ እጠይቃለሁ፤ ነገር ግን የአለም አቀፉ ኦሊምፒክ ኮሚቴ ዋና ፅነሰ ሀሳብ የአትሌቶች ተሳትፎ ነው በሚል ስለሚገልፅ ነው ሲሉ ምላሽ ሰጥተዋል።

😰😰
06/07/2024

😰😰

ለፈተና ሄደው ዩኒቨርሲቲ ውስጥ ለወለዱ ተፈታኞች በቀጣይ እንደመደበኛ ተማሪ እንዲፈተኑ ዕድል ተሰጠአዲስ አበባ፣ መስከረም 29፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) ለፈተና ሄደው ዩኒቨርሲቲ ውስጥ ለወለዱ ...
10/10/2022

ለፈተና ሄደው ዩኒቨርሲቲ ውስጥ ለወለዱ ተፈታኞች በቀጣይ እንደመደበኛ ተማሪ እንዲፈተኑ ዕድል ተሰጠ

አዲስ አበባ፣ መስከረም 29፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) ለፈተና ሄደው ዩኒቨርሲቲ ውስጥ ለወለዱ ተፈታኞች በቀጣይ እንደመደበኛ ተማሪ እንዲፈተኑ ዕድል የተሰጣቸው መሆኑን የትህምርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት አስታወቀ።

አገልግሎቱ ማምሻውን እንዳስታወቀው፥ በእርግዝና ላይ ላሉ እና ወልደው ጡት እያጠቡ ላሉ ለተመዘገቡ ሴት የ12ኛ ክፍል ተፈታኞች የእነርሱን ነባራዊ ሁኔታ ታሳቢ ያደረገ የመፈተኛ ስርዓት በቀጣይ ተዘጋጅቷል፡፡

በመሆኑም ከመስከረም 30 ቀን 2015 ዓ.ም ጀምሮ በሚሰጠው ፈተና መፈተን አያስፈልጋቸውም ብሏል፡፡

ይህም ከወራት በፊት ከወረዳ ደረጃ አንስቶ ገለጻ ተሰጥቷል፤ መመሪያ ሆኖ ወርዷልም ነው ያለው።

ሆኖም ለመፈተን ወደ ዩኒቨርሲቲ ከመጡ ተፈታኞች መካከል ወደ ተቋማቱ እንደደረሱ የወለዱ እንዳሉ ሪፖርት እንደደረሰው አመልክቷል፡፡

ስለሆነም እነዚህ ወላድ ተፈታኞች የቤተሰብ ክብካቤና ፈተናውን ለመፈተንም አካላዊ ማገገሚያ ጊዜ እንደሚያስፈልጋቸው ገልጿል።

በመሆኑም በቀጣይ እንደመደበኛ ተማሪ እንዲፈተኑ አገልግሎቱ ዕድል የሰጣቸው መሆኑን አስታውቋል።

ይህ ታውቆ ቀድሞ በተላለፈው መመሪያ መሠረት በመጀመሪያው ዙር መፈተን የማይችሉ መሆኑን ገልጿል።

አደይ ድራማ ምዕራፍ 2 በዝህ ቻናል ማግኘት ትችላላችሁ !https://youtu.be/LY55duC47WA
01/10/2022

አደይ ድራማ ምዕራፍ 2 በዝህ ቻናል ማግኘት ትችላላችሁ !
https://youtu.be/LY55duC47WA

👉: I use different stock footage: "paid"All of which fall with under fair use. Scenes of a video that I find relat...

Ache Tube  አዲስ ነገር !አርቲስት ሰላም ተስፋዬ,  ከባለቤቷ ጋር ተለያየች 😳😳አርቲስት ሰላም ተስፋዬ እና አማኑኤል ተስፋዬ ለ4 አመታት በዘለቀው የትዳር ቆይታ በፍቺ መቋጨቱን ኢትዮፒ...
19/09/2022

Ache Tube አዲስ ነገር !
አርቲስት ሰላም ተስፋዬ,
ከባለቤቷ ጋር ተለያየች 😳😳

አርቲስት ሰላም ተስፋዬ እና አማኑኤል ተስፋዬ ለ4 አመታት በዘለቀው የትዳር ቆይታ በፍቺ መቋጨቱን ኢትዮፒካሊንክ ዘገበዋል።
አርቲስት ሰላም ተስፋዬ ኑሮዋን ኢትዮጲያ ያደረገች ሲሆን አማኑኤል ተስፋዬ ኑሮውን በሀገረ አሜሪካ አድርጓል።
ሁለቱ በትዳር ቆይታቸው 1 ልጅ አግኝቷል።

09/09/2022

ፆታቸውን የቀየሩ(transgender) ያረጉ ታዋቂ ስዎች።

Ache Tube አዲስ ነገር !በአጣጥ የኬላ ፍተሻ ላይ 308 ሽጉጥ ተያዘ።በጎንደር ከተማ አዘዞ ጠዳ ክፍለ ከተማ ከተማ 308 የቱርክ ሰራሽ  ሽጉጥ በኬላ ፍተሻ መያዙን የአዘዞ ጠዳ ክ/ከተማ...
06/09/2022

Ache Tube አዲስ ነገር !

በአጣጥ የኬላ ፍተሻ ላይ 308 ሽጉጥ ተያዘ።

በጎንደር ከተማ አዘዞ ጠዳ ክፍለ ከተማ ከተማ 308 የቱርክ ሰራሽ ሽጉጥ በኬላ ፍተሻ መያዙን የአዘዞ ጠዳ ክ/ከተማ ሰላምና ደህንነት ጽ/ቤት አሳውቋል።

ፅህፈት ቤቱ ሽጉጡ የተያዘው በክፍለ ከተማው በድማዛ ቀበሌ አጣጥ በተባለው የኬላ ፍተሻ መሆኑን ገልጾ 2 ተጠርጣሪዎች በህግ ቁጥጥር ስር ውለው ምርመራ እየተደረገ ነው ማለቱን ከጎንደር ከተማ ኮሚኒኬሽን የተገኘው መረጃ ያሳያል።

በመዲናዋ በጎርፍ አደጋ ልጆቻቸውን ላጡ ቤተሰቦች ባለ 2 መኝታ ቤትና 150 ሺህ ብር ተበረከተላቸው በመዲናዋ አማኑኤል ሆስፒታል አካባቢ በተከሰተው የጎርፍ አደጋ ሁለት ልጆቻቸውን በሞት ላጡ ...
06/09/2022

በመዲናዋ በጎርፍ አደጋ ልጆቻቸውን ላጡ ቤተሰቦች ባለ 2 መኝታ ቤትና 150 ሺህ ብር ተበረከተላቸው

በመዲናዋ አማኑኤል ሆስፒታል አካባቢ በተከሰተው የጎርፍ አደጋ ሁለት ልጆቻቸውን በሞት ላጡ ቤተሰቦች የአዲስ ከተማ ክፍለ ከተማ አስተዳደር ባለ 2 መኝታ ቤትና የ150 ሺህ ብር ድጋፍ አደረገላቸው፡፡

የክፍለ ከተማው ዋና ስራ አስፈፃሚ ወ/ሮ ሽታዬ መሃመድ÷ "ሀዘናችሁ ሀዘናችን ነው፤ አስተዳደራችን በሚችለው ሁሉ ከጎናችሁ ነው፤ ያጣችኋቸውን ልጆቻችሁን መመለስ ባንችል እንኳን መፅናኛ ይሆናችሁ ዘንድ ይህን ድጋፍ አድርገንላችኋል" ብለዋል፡፡

የአዲስ አበባ ምክትል ከንቲባ አቶ ጃንጥራር ዓባይ÷ ስጦታው ክፍለ ከተማው ከከተማ አስተዳደሩ ጋር በመነጋገር ያበረከተው ስጦታ መሆኑን ገልፀው መጭውን አዲስ ዓመት ሀዘናችሁን ቀንሳችሁ ተደስታችሁ መዋል ይገባችኋል ሲሉ ተናግረዋል፡፡

ሁለት ልጆቻቸውን በጎርፍ አደጋ ያጡት እናት ወይዘሮ ረውዳ ጀማል በበኩላቸው÷ አስተዳደሩ ላደረገላቸው ገንዘብና የቤት ስጦታ ምስጋና ማቅረባቸውን ከአዲስ ከተማ ክፍለ ከተማ ያገኘነው መረጃ ያመላክታል፡፡
(ኤፍ ቢ ሲ)

Address

18
Addis Ababa

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when ACHE TUBE posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to ACHE TUBE:

Share