21/11/2025
በተወሠኑ ቦታዎች ላይ ተጨማሪ የምርጫ ክልል አስፈጻሚዎችን ለመመልመል የወጣ የቅጥር ማስታወቂያ
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ “ምርጫ የሚያስፈጽሙ” ገለልተኛ የምርጫ ክልል ሠራተኞችን በጊዜያዊነት ለመቅጠር ማስታወቂያ ማውጣቱ ይታወቃል። ሆኖም ግን ቦርዱ ተጨማሪ የሰው ኃይል በሚፈልግባቸው ከዚህ በታች በተዘረዘሩት የምርጫ ክልሎች ላይ ድጋሚ ማስታወቂያ ማውጣት አስፈልጓል።
በዚኽም መሠረት ከዚህ በታች የተዘረዘሩትን መሥፈርቶች የምታሟሉ “በምርጫ ክልል በአስፈጻሚነት” መሥራት የምትፈልጉ አመልካቾች በሙሉ፤ ተከታዩን ማስፈንጠሪያ https://nebe-election.org/registration_co በመጠቀም ከኅዳር 12 እስከ ኅዳር 15 ቀን 2018 ዓ.ም. ባሉት አራት ተከታታይ የሥራ ቀናት እንድታመለክቱ ቦርዱ ያሳውቃል።
የምልመላ መሥፈርት፡-
• ዕድሜው/ዋ ከ21 ዓመት በላይ የሆነ/ች፣
• የማንኛውም የፖለቲካ ፓርቲ አባል ያልሆነ/ች፣
• የትምህርት ዝግጅት፦ የመጀመሪያ ዲግሪ እና ከዚያ በላይ የሆነ/ች፣
• የሥራ ቦታ፦ በሁሉም ክልሎች፣
• የሥራ ቆይታ ፦ ለሰባት ወር፣
• ሴት አመልካቾች ይበረታታሉ።
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ
ኅዳር 12 ቀን 2018 ዓ.ም.
ለማመልከት የሚትቸገሩ ካላችህ
https://t.me.sokboye
DM