Yifat Media

Yifat Media Yifat media is public media serves population indeed

26/02/2025

የዘመነ መሳፍንት አካሄድ ህዝባችንን ያዳክማል እንጂ ጠንካራ ሆነን መታየትን አይፈቅድልንም

አንድ፡ፋኖ አደረጃጀት ላይ ማተኮሩ አሸናፊ ያደርጋል!

“ግብፅ እና ዮርዳኖስ በቢሊዮኖች  እየለገስናቸው፣ የጋዛ እቅዴን አለመቀበላቸው አስገርሞኛል” ~ ትራምፕየአሜሪካው ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ ከፎክስ ሬዲዮ ጋር ባደረጉት ቃለ ምልልስ፡-"ግብፅ...
22/02/2025

“ግብፅ እና ዮርዳኖስ በቢሊዮኖች እየለገስናቸው፣ የጋዛ እቅዴን አለመቀበላቸው አስገርሞኛል” ~ ትራምፕ

የአሜሪካው ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ ከፎክስ ሬዲዮ ጋር ባደረጉት ቃለ ምልልስ፡-

"ግብፅ እና ዮርዳኖስ በያመቱ በቢሊዮን የሚቆጠር ዶላር እየከፈልናቸው፣ ነገር ግን ስለ ጋዛ ያቀረብኩትን እቅድ አለመቀበላቸው አስገርሞኛል።"

"ስለ ጋዛ ያዘጋጀሁት በእውነቱ ይሰራል፣ ይጠቅማል። እኔ ሀሳቡን ማቅረብ እንጂ በግዳጅ አልመርጥም። በእቅዴ መሰረት ጋዛ በአሜሪካ ስር ትሆናለች። በቦታውም ሀማስ አይኖርም፣ የወደመችውን ጋዛ መልሰን እናለማታለን።"

🔺 ለግብፅ በቢሊዮኖች ዶላር እየለገስን፣ የጋዛውን እቅዴን አለመቀበሏ አስገርሞኛ👏

የአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ለአምስት ሙሁራን የሙሉ ፕሮፌሰርነት ማዕረግ ሰጠ   | የአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ የሥራ አመራር ቦርድ ለአምስት ሙሁራን የሙሉ ፕሮፌሰርነት ማዕረግ ሰጥቷል።በዚህም መሰ...
24/12/2024

የአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ለአምስት ሙሁራን የሙሉ ፕሮፌሰርነት ማዕረግ ሰጠ

| የአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ የሥራ አመራር ቦርድ ለአምስት ሙሁራን የሙሉ ፕሮፌሰርነት ማዕረግ ሰጥቷል።

በዚህም መሰረት፡-

1. ዶ/ር አለማየሁ ተ/ማሪያም……. በስፔሻል ኒድስ ኤጁኬሽን

2. ዶ/ር አስራት ወርቁ ……………. በጂኦቴክኒክስ ኢንጂነሪንግ

3. ዶ/ር መኮንን እሸቴ ……………. በፕላስቲክ ሰርጀሪ

4. ዶ/ር ሚርጊሳ ካባ ……………… በፐብሊክ ሄልዝ

5. ዶ/ር ተባረክ ልካ ………………. በዴቨሎፕመንት ጂኦግራፊ ከአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ የሙሉ ፕሮፌሰርነት ማዕረግ አግኝተዋል።

24/12/2024

ይህ ይፋት ሚዲያ ነው!
ሀቀኛ እና ወቅታዊ መረጃዎችን ለመዘገብ የተደራጀ ሚዲያ ነው። ከረጅም ጊዜ መታገድ በኋላ ተመልሰናል።

አሳዛኝ ዜና!አቶ ዮሐንስ ቧያለው፣ አቶ ክርስቲያን ታደለ፣ ዶ/ር ካሳ ተሻገረ እና የአማራ ህሊና እስረኞች ከቃሊቲ ማረሚያ ቤት ወደ ቂሊንጦ ማረሚያ ቤት መወሰዳቸው ይታወቃል።አቶ ዮሐንስ ቧያለ...
24/12/2024

አሳዛኝ ዜና!

አቶ ዮሐንስ ቧያለው፣ አቶ ክርስቲያን ታደለ፣ ዶ/ር ካሳ ተሻገረ እና የአማራ ህሊና እስረኞች ከቃሊቲ ማረሚያ ቤት ወደ ቂሊንጦ ማረሚያ ቤት መወሰዳቸው ይታወቃል።

አቶ ዮሐንስ ቧያለው ግን በሚያሳስዝን ሁኔታ በጠና መታመማቸው እየታወቀ ወንድሞቻቸው እንኳን አንዳይረዷቸው እና ሆን ተብሎ በታቀደ እቅድ የስነ-ልቦና ጉዳት እንዲደርስባቸው ከአሸባሪው ሸኔ እስረኞች ጋር በዞን 5 በተለምዶ የቅጣት ቤት በሚበለው ማሰቃያ ክፍል መታሰራቸውን የማረሚያ ቤት ምንጮች ገልፀዋል።

16/12/2022

ይፋት የነብር ጣት🙏🙏🙏

13/12/2022

የአማራን ህዝብ ሰቆቃ ድምፅ የሚሆኑ ታጋዮችን በማሰር የእውነት ትግልን መደበቅ አይቻልም

02/11/2022

ከእነ ቀለጠ የበሰበሰ መንጋጋ አብንን መንግጎ ማውጣት የኔ፣ ያንተ፣ ያንቺ ግዴታ ነው። የአምሳ ሚሊዮን ሕዝብ ድርጅት አምስት በማይሞሉ ኅሊና ቢሶች ሊዳከም የቻለው በእነሱ ብርታት ሳይሆን በእኛ ድከመት ነው።

"አሳዬ ደርቤ"

"በአማራ ትግል ውስጥ ሰርጎ ገቦች ተቋማቶቻችንን እያዳከሙ እና እያፈረሱብን ነው" - ዶ/ር ደሳለኝ ጫኔየአማራ ህዝብ ትግል ቀላል ፈተና የለውም። ለአማራ ህዝብ ቴግል አንድ ጠጠር ለመወርወር ...
29/09/2022

"በአማራ ትግል ውስጥ ሰርጎ ገቦች ተቋማቶቻችንን እያዳከሙ እና እያፈረሱብን ነው" - ዶ/ር ደሳለኝ ጫኔ

የአማራ ህዝብ ትግል ቀላል ፈተና የለውም። ለአማራ ህዝብ ቴግል አንድ ጠጠር ለመወርወር የተነሳ ሁሉ ጠላት ይበዛበታል። ይሳደዳል፣ ይታሰራልም። የአማራ ተቋማቶቻችን ተጠናከሩ ሲባል ይዳከማሉ፣ ተደራጁ ሲባል ይፈርሳሉ። ይሄ የሆነው ደግሞ በአማራ ትግል ውስጥ በርካታ ሰርጎ ገቦች ስላሉ ነው። ነገር ግን የአባቶቻችን ልጆች ስለሆንን ፈተናዎችን እየፈታን ወደ ነፃነታችን እንጓዛለን።

(ዶክተር ደሳለኝ ጫኔ - በባህርዳር የተሰው ፋኖዎችን ለማሰብ በተዘጋጀ ኘርግራም ላይ የተናገረውና ከአሻራ ሚዲያ የተወሰደ)

29/09/2022

አንድ የብአዴን ግለሰብ ተነካብኝ ብለህ በየጉድጓዱ ስትጮህ የነበረው ሁሉ እስኪ የማያቋርጠውን የወለጋ አማራ ጭፍጨፋ አውግዙ

29/09/2022

ለ13 አመታት ባለቤት ያጣው የከርሰ ምድር ውሃ

ቆቦ ወይም የ06 ቀበሌ በሸዋ ሮቢት ከተማ አስተዳደር ስር ከሚገኙ ቀበሌዎች አንዱ ሲሆን በደርግ ዘመነ መንግስት ተበታትነው የነበሩ ገበሬዎችን በመንደር ምስረታ በአንድ አካባቢ አንዲሰፍሩ በማድረግ የተመሠረተች ውብ ቀበሌ ነች::

የአካባቢው ማህበረሰብ በዋናነት በግብርና የሚተዳደር ሲሆን ሌት ከቀን ደከመኝ ሰለቸኝ ሳይል የሚሰራ እንደሆነ ይታወቃል:: ደግ ና ቀና ማህበረሠብ ነው::

የቆቦ ወንዝ በመጥለፍ የተለያዩ ፍራፍሬዎችን ለገበያ በማቅረብ ይታወቃል::

ይህ ወንዝ ታዲያ በጣም ትንሽ ና በበጋ የሚደርቅ በመሆኑ የእግዜር ውሀ ካልተጨመረ በስተቀር ከፍተኛ ጉልበት ና አቅም ቢኖርም በአመት ከአንድ ጊዜ በላይ ለማምረት አልተቻለም:: አብዛኛው ወጣት በየፑል ቤት ጫት ቤት ና ጆተኒ ሲጫወት ወዘተ ይውላል:: የወጣትነት ጉልበቱም በመባከን ላይ ይገኛል::

ነገር ግን ከሸዋሮቢት ከተማ በአራት ና አምስት ኪሎ ሜትር ላይ ከሦሥት ቦታ ከገበሬው ማሣ ላይ ተቆፍሮ ከአስራ ሶስት አመት በፊት ማለትም በ2003 ዓ.ም የተመረቀ ሦሥት የከርሰ ምድር ውሃ ወደ ስራ አለመግባቱ እጅግ ያሳዝናል::

ባጠቃላይ 3ቱም የከርሰምድር ውሃዎች ከ2000 ስኩየር ኪሎሜትር በላይ መሬትን የማልማት አቅም ያላቸው ሲሆን ላለፋት 13 አመታት በስራ ላይ ባለመዋሉ ምክንያት 2,496,000,000,000.00 ብር በላይ ገቢ አሳጥቶናል::

ይህ ውሃ ወደስራ ቢገባ ማህበረሰቡ በአመት አራት ጊዜ ማምረት ይችላል በሰፋት በማምረት ለገበያ ተደራሽ ማድረግ ይቻላል ሰፊ የስራ ዕድል ይፈጥራል:: ማህበረሰቡ በራሱ አምርቶ በመሸጡ በከፍተኛ ተጠቃሚ ይሆናል:: ነገር ግን የከተማ አስተዳደሩ ያለውን ሀብት አሟጦ መጠቀም እየቻለ ባላቸው የጥገኝነት አስተሳሰብ ምክንያት አስራሶስት አመት ሙሉ በማፈን እስካሁን ያለምንም ግልጋሎት አስቀምጠውታል::

መራዊ አካባቢ ያለው የቆጋ መስኖ ጋር በተመሳሳይ ጊዜ ነው የተጀመረው መራዊ አካባቢ ያለው ገበሬ በማህበር ተደራጅቶ የተለያዩ ፍራፍሬዎችን በማምረት ለማህበረሰቡ ያቀርባል ሰፊ የስራ ዕድል ተፈጥሯል አልፎ ተርፎም ወደውጭ በመላክ ከፍተኛ ምንዛሬ አስገኝቷል:: ይህ ግን ባለቤት እንደሌለው የህዝቡን ድምፅ በማፈን ትርፍ አንጀቱ የብአዴን/ብልፅግና

በማህበረሰቡም በሀገረም ላይ ከፍተኛ ኪሳረ አድረሷል እያደረሰም ይገኛል::

የአካባቢዉ አመራሩ ምን አስቧል

የመስኖ ውሃው ከመለቀቁ በፊት ለኢንቨስትመንት ለገበሬው ዝቅተኛ የካሳ ክፍያ በመስጠት ና የኢንቨስተር ቅጥረኛ ማድረግ ና ትንሽ ፍርፋሪ በማግኘት መጠቀሚያ ዘዴ ለማድረግ እንደሆነ የውስጥ አዋቂዎች ያስረዳሉ::

የአካባቢውን ገበሬ በማህበር በማደራጀት የስራ እድል እንዲፈጥር እነዲያመርት ለገበያ እንዲያቀርብ ና ቀጥተኛ ተጠቃሚ እንዲሆን ለማድረግ መስራት ለበአዴን/ብልፅግና መራሹ የቅጥረኝነት ና ጥገኛነት መፍለቂያ ማዕከል የሆነ አመራር ፈፅሞ በአምሮው የማይታሰብ ሆኖ መታየቱ ህዝቡን የሚጠቅም ሳይሆን አመራሩ በህዝቡ ተጠቃሚ የሆነ ላም የሌለበት ኩበት የሚለቅም አመራር መፈጠሩ እጅግ ያስገርማል!!! ያሳዝናል!!!

በመጨረሻም መንግስት የማህበረሰቡን ማነቆ የሆነበትን ችግር ፈቶ መስኖውን ወደስራ በማስገባት የአካባቢው ማህበረሰብ ቀጥተኛ ተጠቃሚ የሚሆንበትን መንገድ እንዲመቻች ስል ለማስገንዘብ እንፈልጋለን

ከይፋት ሸዋሮቢት

Address

Addis Ababa

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Yifat Media posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to Yifat Media:

Share