Liyu Sport - ልዩ ስፖርት

Liyu Sport - ልዩ ስፖርት www.liyu-sport.com is a dedicated professional sports website that entertains opinions, Features &News

✍️ Breaking News
24/05/2025

✍️ Breaking News

16/05/2025

RABAT, May 15, 2025 - Some AIPS members have expressed concern that content creators pose a threat to traditional...

✍️ "ልወቅሽ ኢትዮጵያ" ታላቁ ሩጫ በበቆጂ ቱሪዝም ሚኒስቴር ከታላቁ ሩጫ በኢትዮጵያ ጋር በጋራ የሚያዘጋጀው "ልወቅሽ ኢትዮጵያ" የሩጫ መርሐ-ግብር ግንቦት 17 በበቆጂ ከተማ ይካሄዳል። ሁለ...
15/05/2025

✍️ "ልወቅሽ ኢትዮጵያ" ታላቁ ሩጫ በበቆጂ

ቱሪዝም ሚኒስቴር ከታላቁ ሩጫ በኢትዮጵያ ጋር በጋራ የሚያዘጋጀው "ልወቅሽ ኢትዮጵያ" የሩጫ መርሐ-ግብር ግንቦት 17 በበቆጂ ከተማ ይካሄዳል።

ሁለቱ ተቋማት በየዓመቱ ከሚካሂዷቸው 4 መርሐ-ግብሮች መካከል የአትሌቶች መፍለቂያ በሆነችው በቆጂ የሚያዘጋጁት ውድድር አንዱ ነው።

ግንቦት 17 በሚካሄደው መርሐ-ግብር ኤሊት አትሌቶች፣ የበቆጂ እና አካባቢው ነዋሪዎች እንደሚሳተፉበት ሁለቱ ተቋማት ዛሬ በጋራ በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ አስታወቀዋል።

የስፖርት ቱሪዝምን ለማስፋፋት የተያዘውን ሀገራዊ ዕቅድ ውጤታማ ለማድረግ እንደዚህ ዓይነት መርሐ-ግብሮች ተጠናክረው መቀጠል እንዳለባቸው የቱሪዝም ሚኒስቴር ሚኒስትር ዴኤታ እንደገና አበበ (ዶ/ር) ተናግረዋል።

ስፖርት ባህል እንዲሆን ሊሰራ ይገባል ያሉት በባህልና ስፖርት ሚኒስቴር የስፖርት ዘርፍ ሚኒስቴር ዴኤታ መኪዩ መሐመድ፤ ኢትዮጵያ ከስፖርት ቱሪዝም ብዙ ተጠቃሚ መሆን እንዳለባት ተናግረዋል።

በቆጂ ስመጥር አትሌቶችን እንደማፍራቷ መጠን የሚገባትን እንዳላገኘች ያነሱት የበቆጂ ከተማ ምክትል ከንቲባ በዙ አበበ፥ እንዲዚህ ዓይነት መድረኮች ኢንቨስትመንትን ለማነቃቃት ያግዛሉ ብለዋል።

ቱሪዝም ሚኒስቴር እና ታላቁ ሩጫ በኢትዮጵያ ስፖርት ቱሪዝምን ለማስፋፋት እየሰሩት ያለው ሥራ በሌሎች አካባቢዎችም መስፋት እንዳለበት ተነግሯል።

መረጃው የኢትዮጵያ ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬሽን ነው

06/05/2025

የሴቶች ማራቶን የክበረወሰን ባለቤት ከሆነችው አትሌት ትዕግስት አሰፋ ጋር ቃለ ምልልስ በሁለት ክፍል አድርገናል!!
ክፍል አንድን ይከታተሉ!!

በቅድሚያ እንኳን ደስ አለሽ?

እንኳን አብሮ ደሰ አለን!

የቶኪዩ የአለም አትሌትክስ ሻፒዮና እቅድሽ ምንድን ነው??...... ከዚያስ በኋላ ? በኋላስ?........

ጥያቄ 1. የለንደን ማራቶን ዝግጅትሽ ምን ይመስል ነበር?

መልስ 👉 ከምንግዜም በላይ የታቀደ ፤በጣም ጥልቅና ሰፊ ዝግጅት የተደረገበት ነበረ ፤

ጥያቄ 2. በሳምንት ስንት ቀን ምን ያክል ኪሎ ሜትር ልምምድ ላይ ታሳልፊ ነበረ?

መልስ 👉እረፍት የሚባል አልነበረኝም በሳምንት ሁሉንም ቀን እስራ ነበረ በየሳምንቱ ከ190 እስከ 210 ኪሎ ሜትር የሚሸን ልምምድ አደርግ ነበረ፤

ጥያቄ 3. ለውድድሩ በትክክል ያቀድሽው ምንድን ነበር?

መልስ 👉 ክብረወሰኑን ማሻሻል ነበር ተሳክቶልኛል ።
4. የውድድሩ ሁኔታ እንዴት እንዴት ነበር? ምን ፈታኝ ነገር ነበር?

መልስ👉 ውድድሩ ቆንጆ ነበረ ፤ የአየር ሁኔታውም ከአምናው በተሻለ ጥሩ ነበረ፤ ፈታኝ የነበረው ለውድድሩ የሰጠነው ቦታና ያስቀመጥነው ግምት በጣም ከባድ ነበረ ሁለቱ ልጆች ወተው ነው እንጂ ውድድሩ ከዚህ በላይ ፈታኝ የሚሆን ነበር ፤ዝግጅቱ ከባድ ነበረ፤ በውድድሩ ላይ ግን የፈተነኝ ነገር የለም። ምክንያቱም ቀድሜ ተፈተኝው አልፌው ነበረ።
ጥያቄ 5. ስለ ሽልማቱ ንገሪን እስኪ (350,000 ዶላር የሚባለው እውነት ነው?

መልስ 👉 ውሸት ነው።

ጥያቄ 6. ትእግስት በተከታታይ በማራቶን ውጤታማ የሆነችበት ምስጢር ምንድን ነው?

መልስ👉 ከሰው የተለየ ሚስጥር የለኝም ሁል ጊዜ ከራሴ ጋር እወዳደራለሁ ትልቁ ነገር ለስራዬ የሰጠሁት ቦታና ቁርጠኝነት ነው ።

ጥያቄ 7. ከሁሉም የአለም ሪከርዶች የቱን ታስበልጫለሽ? የትኛው ከባድ ነው?

መልስ👉የበርሊኑን 2:11 የገባሁበትን ነገር ግን ይኼኛውም ቀላል የሚባል አይደለም።

8. ወደ ውድድር ከመግባሽ በፊት የተለዬ የምታደርጊው ነገር ምንድን ነው?

መልስ 👉የረጅም ሰዓት ፀሎት።

ጥያቄ 9. የምትወጅው የምግብ አይነት ምንድን ነው?

መልስ 👉 ቁርጥ ነው።

ጥያቄ 10. እንደ ፖሊስነትሽ ወንጀልኛ ይዘሽ ታውቂያለሽ ወይ?

መልስ👉 በሰፈር ውስጥ ስንቀሳቀስ ፤ ልምምድ ሳደርግ በተለይ ወንድ ትንንሽ ልጆች ከእድሜአቸው በላይ የሆነ ነገር ለምሰሌ ሲጋራ ሲያጨሱ ወይም ሌላ አላስፈላጊ ነገር ሲያደርጉ ካየሁ የምሄድበት ጉዳይ ይቀራል አንጂ ልጆቹን ይዤ አስገድጄ በመኪና በማስገባት ከቤተሰቻቸው አገናኛለሁ አላልፍም።

ጥያቄ 11. ስለ ቤተሠብ ሁኔታሽ ትንሽ ንግሪን ስለ ትዳር?

መልስ 👉 ምነ ነው? ልታጋባኝ ነው? 😁 ባለትዳር ነኘ። ከቤተሰቤ ሌላ ሯጭ ቤተሠብ ካለ? የለኝም።

ጥያቄ 12. ለውጤትሽ በተለዬ ሁኔታ የምታመሰግኝው ሰው ማንን ነው?

መልስ 👉 ሁሉንም ሆድ ይመርቅ።

ጥያቄ 13 እስኪ በ2024 በአሜሪካ ስለተዘጋጀው የእውቅና ፕሮግራም ላስታውስሽና በአሜሪካ እያለሽ ማታ ልትሸለሚ ጧት ላይ ክብረወሰኑ በኬኒያዊቷ አትሌት በችካጎ ተሻሻለ ምን ተሰማሽ?

መልስ 👉 በመጀመሪያ ሸላሚዎቹን አመሰግናለሁ!!

እውቅናው ሊሰጠኝ የነበረው እ ኤ አ በ2023 ነበረ ግን እኔ በግሌ ሌላ ፕሮግራም ስለነበረኝ አልተገኘሁም። በዚህ ምክንያት ፕሮግራሙ ለ2024 ሆነና እውቅናውን ተቀበልኩ ፤እየሳቀች ደግሞም በ2024 በአካል ተገኝቼ ዕውቅናውን ልውሰድ እንጂ በሀሳቤ በ2023 እውቅናውን ወስጄዋለሁ ክብረወሰኑ እስኪፀድቅ ድረስም ለጊዜው የኢትዮጵያ ነው።

ጥያቄ 14.እንደ አጠቃላይ ክብረወሰኑ በመሻሻሉ ምን ተሰማሽ?

መልስ👉ተገረምኩ ግን እንኳንም አሁን ላይ ክብረወሰኑን አሻሻለችው አልኩ!!

በመሻሻሉ እጅግ በጣም ደስ ብሎኛል ።

ጥያቄ 15. እንዴት በመሻሻሉ ደስ ሊልሽ ቻለ?

መልስ፦👉 ከአምስትና ከስድስት አመት በኋላ ብታሻሽለው ኖሮ እቆጭ ነበረ ምክንያቱም ሴት ልጅ ነኝ ነገ ልጅ መውለድና ፤ሩጫን በተለያየ ምክንያት ማቆም አለና ፤ እንደገናም አቅሙም አይኖርህም እና እቆጭ ነበረ፤ አሁን ግን እኔ ገና ባሻሻልኩት በዓመቱ ነውና የተሻሻለው እንደገናም አምላክ ጤና ይስጠኝ እንጂ እኔም ሙሉ አቅሙ ባለኝ ሰዓት ነውና የሰበረችው።

ጥያቄ 16. ቲጂ አንወሻሽ እውነቱን ተናገሪ

ሰው የሆነ ሁሉ የራሱ ያደረገውን ነገር ሲወሰድበት ማንም ደስ አይለውም እና እንዴት ነው ቅር ያላለሽ?

መልስ👉ነገርኩህ ክብረወሰኑ ሁል ጊዜ የእኔ ሆኖ እንደማይኖር አውቃለሁ ክብረወሰኑን ማሻሻሏ ቅር አላሰኘኝም ግን ትንሽ ቅር ያለኝ ወይም ቢሆን ደስ የሚለኝ የነበረው ፤ ሴት ልጅ ማራቶንን ከ2:10 በታች መሮጥ ትችላለች ብዬ ደጋግሜ ተናግሬ ነበረ

ዓላማዬም ጠንክሬ ሰርቼ ከ2:10 በታች በመሮጥ የዓለም የመጀመሪያዋ ሴት የማራቶን አትሌት መባል እፈልግ ነበረ

ነገር ግን ቀድማኝ 2፡10 በታች በመግባቷ ብቻ ቅር ብሎኛል።



ጥያቄ 17. በወቅቱ የልጅቷ ብቃት ብቻ አይደለም

ዶፒንግ ነው እየተባለ ኬኒያዊቷ ላይ ይወራል እና ምን አስተያየት በወቅቱ ነበረሽ?

መልስ👉 የ Doping ጉዳይ ለ AIU እንተዉላቸዉ ነገር ግን በዚች አለም ላይ ሁልጊዜ ያልተለመደ አዲስ ነገር ይዘክ ስትመጣ ለተወሰነ ጊዜ ግር ሊል ይችላል እየቆየ ሲመጣ ግን ሁሉም ይለምደዋል እናም አለም የኬኒያዊቷን Ruth ብቃትን አምኖ መቀበል አለበት። እኔም 2011 ቤት ስሮጥ ሰዎች ብዙ ተጠራጥረውኝ ነበረ ልጅቷንም ሆነ እኔን መጠራጠር ማለት የሴቶችን ብቃትና ችሎታ ለማሳነስ የሚደረግ ሙከራ ነው። ይቻላል!!

በዚህ አጋጣሚ ለጀግኖቹ ለሀገሬ ሴት አትሌቶች የማስተላልፈዉ መልዕክት ቢኖር ሴት ልጅ እንዲህ መሮጥ አትችልም የሚለዉን አባባል ከጭንቅላታቸዉ ሰርዘዉ አበበ ቢቂላ በባዶ እግሩ ሮጦ ያስከበራትን ማራቶንን እኛ ሴቶች በጫማ አናስደፍረዉም።እናሻሽለዋለን እኔ ድንገት ባይሳካልኝ እንኳ ጀግኖች የሀገሬ ልጆች ያሳኩታል ክብረወሰኑን ወደ ኢትዮጵያ ይመልሱታል የሚል ሙሉ እምነት አለኝ።

ጥያቄ 18. ከ2:10 በታች መግባት ማለት ወንዶችን ከሁለት ቤት ውጡልን ሁለት ቤት የኛ የሴቶች ነው እንደማለት አይደለም ወይ?

መልስ 👉 ኮስተር ባለ ሙድ ስለሴቶች እያወራን ለምን ስለወንዶች ታስገባለህ?

ኮስተር ብላ ስትመልስልኝ

በሆዴ 2:10 በታች ቀድሜአት የገባሁት እኔ መሰልኳት?😂

ጥያቄ 19.

አይ ወንዶቹ ምን ይሰማቸዋል ይሆን ብዬ ነው?

መልስ 👉 ምን ያገናኘዋል?

እኔ ማራቶን ሮጦ ውጤት ለሚያመጣ ብቻ ሳይሆን ለጨረሰም ትልቅ ክብር አለኝ ምክንያቱም ማራቶንን ሊረዳ የሚችለው የሮጠው ብቻ ነው።

ሴቶች 42 ኪ ሜ ስንሮጥ ሙሉ ለሙሉ በወንዶች ፔስ ሜከር ንፋስ እየተጋረደልን ነው የምንሮጠው፤ እኛ ፔስ ሜከር በሌለበት ወይም እስከ ግማሽ ማራቶን ብቻ ወንዶች አሯሩጠውን ቀሪውን ለብቻችን ስንጨርስ ሪከርዱ እስካሁን ድረስ ያለው 2:15 ቤት ነው። በተመሳሳይ ወንዶችም ልክ እንደ እኛ ፔሶቹ ከ25ኪ ሜ በኋላ ሲወጡ ቀሪውን ለብቻቸው ሄደው ክብረወሰኑ 2:00 ነው። ስለዚህ በመካከላችን የ15 ደቂቃ ልዮነት አለ ብዬ ነው የማምነው።ወንዶች እሰከ 42 ኪ ሜ ንፋስ እየተከላከለ የሚያስርጣቸው አሯሮጭ ቢያገኙ ከ2:00 በታች በተደጋጋሚ ይሮጣሉ።ስለዚህ በዚህ ጉዳይ ሊሸማቀቁ አይገባም። ልዩነታችን የ15 ደቂቃ ነው እኛ አድቫንቴጅ ወስደናል እስከ 42 ፔስ አለን።

ወንዶች ግን ግፋ ቢል 25 ኪ ሜ ድረስ አሯሮጭ ሊኖራቸው ይችላል ከዚያ በኋላ ያለውን ብቻቸውን ነው የሚታገሉት ይህንን ጉዳይ ሚዲያውም፤ አሰልጣኙም፤ ማናጀሩም ፤ ካንፓኒዎቹም ሊገነዘቡት ይገባል እንጂ ወንዶችን በዚህ ልክ ዝቅ ማድረጉ ልክ አይደለም። ሴቶችን 2:09 ገቡ ብሎ ወንዶችን ማሳነስ ወይም ዝቅ ማድረግ ወይም ሳይኮሎጂዓቸውን እንዲነካና ሴቶችን እንዲጠሉ ማድረግ ደስ አይልም ልክም አይደለም።

👉 ያው በቃላት አሽሞነምንሺው እንጂ ሁለት ቤት የኛ ነው ወንዶች ውጡልን ነው ቅኔው አልኩና ምን አስጨነቀኝ የማራቶን ሯጭ አይደለሁ ብዬ ተፅናናሁ !!

ርዕሴን ቀየርኩ።

ጥያቄ 20. ስለ ፓሪስ ኦሊምፒክ

የ2024 የለንደንን ማራቶን ከሮጥሽ በኋላ ወደ ፓሪስ ሄደሽ ነበር ለምንድን ነው?

መልስ👉 ውድድሩ ኦሊምፒክ ስለሆነ የማራቶን ኮርሱን ለማየት
ጥያቄ 21. አዲዳስና ማናጀሮችሽ ናቸው ያመቻቹልሽ?

መልስ👉ማንም አላመቻቸልኝም በራሴ ወጪ
ኮርሱን እያዞረ ለሚያሳየኝ ባለሙያም በግሌ ዓበል ከፍዬ ኮርሱን ተመለከትኩ ኮርሱ ከበድ የሚል
ወጣ ገባ የሚበዛው ዳገታማ እንደሆነ ጉልበት እንደሚጠይቅ አውቄ ተመለስኩ ከኮርሱ የተማርኩትም በልምምድ ጊዜ ጉልበት መጨረስ እንደሌለብኝ ተረዳሁ።
👉በጣም ትገርሚያለሽ (ትለያለሽ) ይህ እኮ የሚያሳየው ምን ያህል ለውድድሩ ትኩረት እንደሰጠሽ ነው የሚያሳየው ። ሰው ቢኖር ሊያሸልምሽ ይገባ ነበረ።
ጥያቄ 22. አለም ሻምፒዮናውን በሚመለከት እቅድሽ ምንድን ነ

ክፍል 2 ይቀጥላል...




marathonworldrecord

06/05/2025

✍️ ብቻ ለታሪክ ይቀመጥ...

04/05/2025
04/05/2025
04/05/2025

8:22.72 and on the rise. 👏

Hirut Meshesha clocks a personal best to win the 3K and lock in second place overall — and a $50K check. 💰

28/04/2025

✍️ በአለም አቀፍ ደረጃ በተለያዩ የአትሌቲክስ ውድድሮች የአለም ክብረ ወሰኖች በተከታታይ እየተሰበሩ ይገኛሉ:: ይህንን ተከትሎ ቴክኖሎጂ የአትሌቶችን ብቃት በማሳደግ ረገድ ስላለው ሚና የሚነሱ ክርክሮች እየበዙ መጥተዋል።

በዚህ ጉዳይ ላይ ሁለት ዋና ዋና አስተሳሰቦች የሚንፀባረቁ ሲሆን: የመጀመሪያዎቹ ለውጥ የማይቀር የተፈጥሮ ሂደት ነው ብለው የሚያምኑ እና አነሰም በዛም እያንዳንዱ ትውልድ ከቀደመው ጋር ሲነፃጸር የተሻለ ተጠቃሚ ነው በዚህም ምክንያት የቴክኖሎጂ ተፅእኖ ደረጃን በትክክል ለመለካት አስቸጋሪ ነው ብለው ያምናሉ።

ሌላኛው አስተሳሰብ በበኩሉ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ በቴክኖሎጂው ዘርፍ የተመዘገቡት መመንደጎች (በመሮጫ ጫማ: በስልጠና: ህክምናና ህጋዊ እንክብሎች ወዘተ...) ከዚህ ቀደም ታይቶ የማይታወቅ መሆኑን በመጥቀስ የዛሬዎቹ አትሌቶች ካለፉት ዘመናት መሰሎቻቸው ጋር ሲነፃፀሩ የላቀ ጥቅም አስገኝቶላቸዋል ብለው የሚያምኑት ናቸው:: እንዲያውም በዚህ ጎራ የሚመደቡ አንዳንዶች: የዘመኑ አትሌቶችን ጥረት እስከማጥላላትም ይደርሳሉ።

የሚከተለው ቀረጻም አትሌት ታምራት ቶላ በፓሪስ ኦሊምፒክ ማራቶን ማሸነፉን ተከትሎ በሱፐር ስፖርት ስቱዲዮ ልዩ የኦሊምፒክ ሽፋን በተመሳሳይ ርእሰ ጉዳይ ላይ የተደረገውን ውይይት ያሳያል።

በፓናሉ ላይ የአራት ጊዜ የኦሎምፒክ ማራቶን ተወዳዳሪው ሄንድሪክ ራማላ፣ የ2004 እና 2008 ኦሊምፒያኗ ጄራልዲን ፒላይ ከደቡብ አፍሪካ እና ሃይለእግዚአብሔር አድሃኖም ከኢትዮጵያ ተሳታፊዎች ሆነዋል።

እርስዎ ቴክኖሎጂ በዘመናዊ አትሌቶች ውጤታማነት ላይ እያሳደረ ስለሚገኘው ተፅእኖ ምን አስተያየት አለዎት?

©️ሱፐር ስፖርት

✍️ As world records continue to fall across various athletics events around the globe, debates about the role of technology in enhancing athlete performance are becoming more frequent.

There are two main schools of thought on this issue. One believes that change is inevitable, and that each generation naturally holds an advantage over its predecessors, making it difficult to fairly measure the level of technological influence.

The other argues that recent advancements in technology are unprecedented, giving today's athletes a significantly greater advantage compared to those of previous eras. Some even go so far as to discredit the efforts of contemporary athletes.

The following footage captures a discussion from SuperSport’s special Olympic coverage, following Tamirat Tola’s victory at the Paris Olympic Marathon. The panel features four-time Olympic marathoner Hendrick Ramaala, 2004 and 2008 Olympian Geraldine Pillay from South Africa, and Haileegziabher Adhanom from Ethiopia.

What are your thoughts on how technology is influencing the performance of modern-day athletes?

©️SuperSport

✍️ የትዕግስት አሰፋ ውጤት እንዴት የዓለም ሪከርድ ሆኖ ተመዘገበ?በጋዜጠኛ ምስጋናው ታደሰጀግናዋ አትሌት ትዕግስት አሰፋ ዛሬ በተካሄደው 45ኛው የለንደን ማራቶን ከመጀመሪያው እስከ መጨረሻው...
27/04/2025

✍️ የትዕግስት አሰፋ ውጤት እንዴት የዓለም ሪከርድ ሆኖ ተመዘገበ?

በጋዜጠኛ ምስጋናው ታደሰ

ጀግናዋ አትሌት ትዕግስት አሰፋ ዛሬ በተካሄደው 45ኛው የለንደን ማራቶን ከመጀመሪያው እስከ መጨረሻው ከመሪዎቹ ተርታ ተሰልፋ በስተመጨረሻም የዓለም አትሌቲክስ አፍቃሪያንን ባስደመመ ድንቅ ብቃት ውድድሩን ለማሸነፍ ችላለች።

ብቃቷንም ታላላቅ የዓለም ሚዲያዎች እያሞገሱላት ይገኛሉ።

የ2024 ፓሪስ ኦሎምፒክ የብር ሜዳልያ አሸናፊዋ ትዕግስት ዛሬ በለንደን ማራቶን ቀዳሚ ሆና ለመግባት የፈጀባት ጊዜ 2፡15.50 ነው።

ይህም "Women's-only World Record" በሚለው ዘርፍ አዲስ የዓለም ሪከርድ ሆኖ ተመዝግቦላታል።

ሁኔታው ብዙዎቹን ግራ አጋብቷል...

ምክንያቱም የዓለም የሴቶች ማራቶን ሪከርድ በኬንያዊቷ ሩት ቼፕቴጌይ እጅ ሲሆን ሰዓቷም 2፡09.56 ነው።

ታዲያ ትዕግስት በዛሬው ውድድሯ ከዚህ በዘገየ ሰዓት 2፡15.50 ገብታ እንዴት "Women's-only World Record" ተብሎ በዓለም ሪከርድነት ሊመዘገብላት ቻለ?

ነገሩ ወዲህ ነው...

ትዕግስት ራሷ በቼፕቴጌይ ከመነጠቋ በፊት በሴፕቴምበር 24/2023 በበርሊን ማራቶን 2፡11.53 በመግባት የዓለም ሪከርድን ሰብራ ነበር። በዚህም በምድራችን በሴቶች ማራቶን ከ2 ሰዓት ከ12 ደቂቃ በታች የገባች የመጀመሪያዋ አትሌት በመሆን በዓለም ድንቃድንቅ ታሪኮች መዝገብ (Gunnies World Book of Records) ላይ ለመስፈር ችላለች።

ነገር ግን እሷም ሆነች ቼፕቴጌይ ሪከርዱን የሰበሩት በወንድ አሯሯጮች (Pacemakers) ተጠቅመው ነው።

ይህ ራሱን የቻለ ዘርፍ ነው...

ሴቶች ወንድ አሯሯጮችን ሳይጠቀሙ በሴቶች አሯሯጮች ብቻ ታግዘው የሚያስመዘግቡት ውጤት ደግሞ "Women's-only World Record" ተብሎ ይመዘገባል ማለት ነው። የዛሬው የትዕግስት ሪከርድም በዚህ ዘርፍ ነው አዲስ የዓለም ሪከርድ ሆኖ ሊመዘገብላት የቻለው። በውድድሩ ላይ ሴት አሯሯጭ ብቻ ነው የነበሩት።

በ"Women's-only world record" ዘርፍ ቀደም ሲል ሪከርዱ ተይዞ የነበረው በኬንያዊቷ ፔሬስ ጄፕቺሪር ነው። ይህም የተመዘገበው በዚሁ የለንደን ማራቶን አምና ነው። ሰዓቷም 2፡16.16 ነበር። ይህንን ሰዓት ነው ትዕግስት ዛሬ ያሻሻለችው።

27/04/2025
✍️ የ2025 ለንደን ማራቶን የውጤት መግለጫ📸 SuperSport
27/04/2025

✍️ የ2025 ለንደን ማራቶን የውጤት መግለጫ

📸 SuperSport

Address

Haile Gebreselasse Street
Addis Ababa

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Liyu Sport - ልዩ ስፖርት posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to Liyu Sport - ልዩ ስፖርት:

Share

Category