ጠቃሚ ንግግሮች/Useful expressions

ጠቃሚ  ንግግሮች/Useful expressions Contact information, map and directions, contact form, opening hours, services, ratings, photos, videos and announcements from ጠቃሚ ንግግሮች/Useful expressions, Digital creator, Addis Ababa.
(1)

Daily inspiration through quotes, success tips, and personal growth ቴሌግራም 👇
https://t.me/Usefulexpression

06/07/2025

ጉረኛው..😀

ብራንድ ሽቶ ትቀባለህ
ግን ኪራይ ቤት ውስጥ ነህ
ምግብ በየሆቴሉ ትበላለህ
ግን የወር ደሞዝተኛ ነህ
ከሰው አንሶ ላለመታየት ታወጣለህ
ግን ብዙ ጊዜ ተበዳሪ ነህ
ሀብታም ሀብታም ያጫውትሃል
ግን ድሃ ነህ

ጉራ ሀብት አይሆንም፤
ለጉራ የምታወጣው ግን ቢዝነስ ይፈጥራልና
ቢዝነስ ስራበት!!!

በአንዳንዶች ዘንድ "ስለማፈቅርሽ ነው የምመታሽ" የምትል phrase አለች💔። ፍፁም ውሸት! ስለሚያፈቅር ሳይሆን ስሜቱን መቆጣጠር ስለማይችል ነው የሰነዘረብሽ...❗️.... ፍቅር ንፁህ ነው፣...
06/07/2025

በአንዳንዶች ዘንድ "ስለማፈቅርሽ ነው የምመታሽ" የምትል phrase አለች💔። ፍፁም ውሸት! ስለሚያፈቅር ሳይሆን ስሜቱን መቆጣጠር ስለማይችል ነው የሰነዘረብሽ...❗️.... ፍቅር ንፁህ ነው፣ ስለሌላው ግድ የሚሰጠው ነው፣ሩህሩህ ነው።

እርግጥ ነው ፍቅር በአንድ ጀምበር ልክ እንደ fast food ቶሎ የሚበስል አይደለም። በሀላፊነት እና በመተሳሰብ ከተሰራበት በጊዜ ሂደት የሚያድግ እንጂ። ግልፍተኛም ሰው አያፈቅርም አይደለም ይሁን እንጂ ንዴትን ከፍቅር ጋር መቀየጥ የተሳሳተ መደምደሚያ ላይ ያደርሳል። ፍቅር ሌላ ቡጢ ሌላ።

ለጠብ እና ለቡጢ ቶሎ የሚጋበዝ ሰው የደከመ የስሜት ብስለት(low emotional intelligence ) ያለው ሰው ነው። ስለዚህ ስለምወድሽ ብሎ ከማስተባበል ንዴት መቆጣጠር ..🤔

''በገንዘብ ከሚበልጡህ ሰዎች ጋር ስትውል አሳ ይመግቡሀል በእውቀት ከሚበልጡህ ሰዎች ጋር ስትውል ደግሞ አሳ ማጥመድንም አሳ መመገብንም ያስተምሩሀል።ምርጫው ያንተ ነው።
06/07/2025

''በገንዘብ ከሚበልጡህ ሰዎች ጋር ስትውል አሳ ይመግቡሀል በእውቀት ከሚበልጡህ ሰዎች ጋር ስትውል ደግሞ አሳ ማጥመድንም አሳ መመገብንም ያስተምሩሀል።
ምርጫው ያንተ ነው።

ብርሃኔ  ክፍል ..ዘጠኝ✍️የአለቃዬ ቢሮ ስደርስ በሩን በጥንቃቄ አንኳኩቼ ወደውስጥ ዘለቅኩ የአለቃዬ ቢሮ ሰፊና ልዩ ነው ሁሉም ነገር ፅድት ያለ ከእንጨት የተቀረፁ የሚያምሩ ጌጦች  ኮርነሮቹ...
06/07/2025

ብርሃኔ ክፍል ..ዘጠኝ

✍️የአለቃዬ ቢሮ ስደርስ በሩን በጥንቃቄ አንኳኩቼ ወደውስጥ ዘለቅኩ የአለቃዬ ቢሮ ሰፊና ልዩ ነው ሁሉም ነገር ፅድት ያለ ከእንጨት የተቀረፁ የሚያምሩ ጌጦች ኮርነሮቹላይ አበቦች ያሉበት የኔ በሆነ ብለው የሚመኙት አይነት ነው ። የአለቃዬ ግርማ ሞገስ ደሞ ይበልጥ ቢሮውን ልዩ አድርጎታል ሲያየኝ በኩራት እና ከዚ በፊት አይቼ በማላውቅበት ባህሪ ተቀበለኝ ፣ እጁን ከሱ ትይዩ ካለው አነስ ያለ ሶፋ እያመለከተኝ ፣ተቀመጥ አለኝ። ልቤ ፈራ የሆነ የተበላሸ ነገር አለ ፣ አንድ ልክ ያለሆነ ነገር ሸተተኝ ........
"እሺ ጎረምሳው ! ለውጥ እንዴት ይዞሃል"አለኝ ፊቱ ላይ የማየው ንቀት መሰል እይታ ምቾት ነሳኝ በዛላይ ጎረምሳው አባባሉ ደስ አይልም ፣ ከተሽከርካሪ ወንበሩ ላይ ሲነሳ ይበልጥ ግርማው መልከመልካም እነቱ ጎልቶ ታየኝ በቀይ ፊቱ ላይ ሰልከክ ያለው አፍንጫው ሰርሳሪ የሚመስሉ ትላልቅ አይኖቹ ወፋፍራም ከንፈሮቹ በከንፈሩ ዙሪያ በጥንቃቄ የተላጨው ገብስማ ጢሙ ... በቃ ልዩ እና የሚያምር አለቃ እንዲሆን አርገውታል .....
"ጥሩ ነው ምነው አቶ ሲሳይ በሰላም ነው የጠራኽኝ ?.."አልኩት ስሜቴ በንቀቱ እየተነካ ነው ። ከዚ በፊት እንዲ አይነት ሁኔታ አይቼበት አላውቅም አልፎ አልፎ ነው በእርግጥ የምንገናኘው
"ምን ይኖራል ብለኽ ነው ፣ ያው አንድ ማወቅ ያለብህ ነገር ስላለ ፣ብዙ እርቀት ከመሄድህ በፊት ላስጠነቅቅህ ነው የጠራውህ....."ብሎ በሰርሳሪ አይኖቹ አፈጠጠብኝ
"እሺ ምን ተገኝቶብኝ ነው አቶሲሳይ?" አልኩት ግራ ገብቶኝ
"እንግዲ ባጭሩ ማሳሰብ የፈለኩት ምን መሰለህ ፣ እእ ...ማሪዛ ፍቅረኛዬ ናት ..እ እና በሷ የመጣ ነገር በአይኔ እንደመጣ ነው የምቆጥረው ስለዚህ ማሬን ማስቸገርህን ተው ፣ አለዛ እንግዲ ከስራ መባረር ብቻ አይደለም ሌላም ነገር ይኖራል !!..መቼም ይገባሃል...."ብሎ ዙሪያዬን ተሽከረከረ። በጭራሽ ያላሰብኩት ነገር ስለነበረ ክው ብዬ ቀረው ፣የሰማውትን ማመን ከበደኝ ፣ እንዴ እሱ ባለትዳርና የሁለት ልጆች አባት አይደል እንዴ ፣ እንዴት ነው የማሪዛ ፍቅረኛ የሚሆነው ። ማሪዛን ውሽማ አድርጓት ባልሆነ ። ምን እንደምል ግራ ገባኝ ምላሴ ከተናጋዬ ተጣብቆ አልላወስ አለኝ
"በትክክል ሰምተኽኛል ብዬ አስባለው ፣ ይህን የምልህ ያለምክንያት አደለም በተለያየ ቀን ከማሪዛጋር እየተዝናናን ሳለ ስትደውል አስተውያለው ጭራሽ ዛሬ ደሞ ገና ሳይነጋ እየደወልክ ነበር ።በለሊት ምን እንደሚያስደውልህ ግልፅ ባይሆንልኝም ግን ፣ ደብሮኛል ፣ እሷ ተኝታ ስለነበር እኔነኝ ስልክህን ያየውት ፣ እና ስልክህን ከማሬ ቀፎላይ ዲሌት አድርጌዋለው በዚ ልረዳህ አስቤ ፣ ምክንያቱም ያሰብከው አሳብ አይጠቅምህም ፣ ላንተ የሚያስፈልግህ በደረጃህ መጓዝ ነው ። አለበለዚያ አወዳደቅህ ቀላል አይሆንም ፣ እና ባጭሩ ወደማሪ መደወልህን በማቆም ለራስህ ትብብር አድርግ "ብሎኝ ፊለፊቴ መጥቶ በመቆም አይኖቼን ፈልጎ አፈጠጠባቸው ....አልፈራውትም ! ከሱ ይልቅ በማሪዛ ተናደድኩ ! እንዴት ከባለትዳር ሰው ጋር አደረች ? መቼም ብታድር ነው እንጂ በጠዋት ከሱጋር ምን ትሰራለች ።
"እሺ የነገርከኝን በትክክል ሰምቻለው አሁን መሄድ እችላለው ?"አልኩት እየተነሳው
"በትክክል ከተግባባን ትችላለህ "አለኝ
"ገብቶኛል !"ብዬው ወደበሩ አመራው
"ጥሩ ስራህ ላይ አተኩር ያንን ካደረክ የተሻለውን እድል እሰጥሃለው ፣"አለኝ ። አመሰግናለው ብዬው ወጥቼ ሄድኩ ፣መንገድ ላይ በተደጋጋሚ ቆምኩ ልቤ እየተነሳ የሚፈርጥ መሰለኝ ፣እንደሮጠ ሰው ትንፋሼ ከበደኝ ። ወይኔ ፍቅር ያለቦታው እንዴት ያማል.........

06/07/2025

ዛሬ ሰኔ 29 ዓለም አቀፍ የመሳሳም ቀን ነው..😀

ብርሃኔ ክፍል ...ስምንትወደ ለገሀር አካባቢ ቤት ተከራይቼ ገባው  እራሴን የቻልኩበት መንገድ ደስታን ፈጠረልኝ ። ማሪዛን ያገናኘኝ አምላክ ክብሩ ይስፋ ፣  ሕይወቴ ላይ ብርሃን ፈንጥቃበታለ...
05/07/2025

ብርሃኔ ክፍል ...ስምንት

ወደ ለገሀር አካባቢ ቤት ተከራይቼ ገባው እራሴን የቻልኩበት መንገድ ደስታን ፈጠረልኝ ። ማሪዛን ያገናኘኝ አምላክ ክብሩ ይስፋ ፣ ሕይወቴ ላይ ብርሃን ፈንጥቃበታለች ..
ግን ማሪዛ የኑሮዬን አቅጣጫ እንድቀይር ምክንያት ብትሆነኝም ፣ ለሷ ያለኝን ስሜት ግን ለመረዳት የምትፈልግ አልመሰለኝም ፣ ላገኛት ብፈልግም ጊዜ እንደሌላት ነግራ አሳቤን ሳትቀበል ትቀራለች ተሳክቶላት ያገኘችኝ ጊዜ ደሞ ፣ የወሬዋ አቅጣጫ በጭራሽ እኔ ባሰብኩት ዙሪያ አይሆንም ... እና እንዲሁ የስራ ጉዳይ እያወራን ጊዜው ይሄድና እንለያያለን ፣ በቃ ስለፍቅር የማወራበት መንገድ አጣው ፣ .....
አብዲ ሁሉም ነገር እንደፈራው ሳይሆን ቀርቷል የሰሚራ ቤተሰቦች ፣ አክብረው ተቀብለው ለልጃቸው በልነት ፈቅደውታል ፣ እሱም የሚያሳፍር ባል አልሆነም በጥረቱ ሕይወቱን በፍጥነት ቀይሯል ፣ ለጓደኛዬ መልካም እድል ተመኘው ።
አንድ እሁድ ቀን እኔና አብዲ ተገናኝተን ስለተፈጠሩልን የተሻለ እድል እያወራን ሳለ ድንገት አብዲ ስለ ማሪዛ ጠየቀኝ ...
"እንዴት ነው ታዲያ ፍራ ማሪዛን ጠየካት "አለኝ ምን እንደምለው ግራ ገባኝ
"አይ እእ ማለቴ ሁኔታዎች ለዛ አይጋብዙም ....."ብዬ በረጅሙ ተነፈስኩ
"ማለት አይጋብዙም ስትል?"አለኝ ፊቱን ቅጭም አድርጎ
"አይ በቃ ማሪዛ እኔን በፍቅር እያስተዋለችኝ አይደለም ፣ ከዛ ይልቅ እኔላይ የበጎ አድራጎት ስራ እየሰራች የነበር ነው የሚመስለው ። እንጃ ብቻ በተለይ አሁን ላይ በኔ ውትወታ እንጂ እሷ አስባ አግኝታኝ አታውቅም ፣ ስንገናኝም ፣ ስለስራ ስለለውጥ ብቻ ነው የምታወራኝ ፣ ከዛ ካለፈ ስለኔ የወደፊት ሕይወት መቀየር በትጋት ሰርቼ የራሴ አለቃ እንድሆን ፣ ያለውበትን ቦታ በቂነው ብዬ በደሞዝ የምኖር እንዳልሆን እራሴን እንድጠብቅ ከመምከር የተለየ ነገር የለም ፣ "ብዬ ተከዝኩ
"ውይ ወንድሜ እየተጎዳህ ነዋ ! ምን ይሻላል ታዲያ ? እሺ አንተ እንደምትወዳት ብትነግራትስ ፣ ምን አልባት እሷ በዚ መንገድ ለማውራት ሴትነቱም ይዟት ቢሆንስ "አለኝ አብዲ ግራ ቢገባው
"አይ አሳቧን ለመግለፅ ችግር ያለባት አይነት ሴት አደለችም ፣ ማሪዛ መናገር የምትፈልገውን ፊት ለፊት የምትናገር ናት ፣ እኔ እንደሚመስለኝ ፣ እሷ ለኔ ያንን ሁሉ ስታደርግ አዘን ተሰምቷት ብቻ ነው በቃ ፣ እና እኔ ደሞ ያላሰበችውን ጥያቄ ጠይቄ ምስጋና ቢስ መሆን አልፈልግም ፣"አልኩት በተዳከመ ድምፅ ። አብዲ የሱ የፍቅር ሕይወት ተሳክቶ ፣ የኒ እንዲ ግራ መጋባት በጣም አሳዘነው ፣ሊያፅናናኝ ሊያበረታኝ የሚያውቃቸውን ጠንካራ ቃላት ሁሉ እየተጠቀመ ፣ መከረኝ ። ለመፅናናት ሞከርኩ ፣ ጨርሶ ብቸኛ እንዳልሆን አብዲን የመሰለ ጓደኛ ስለሰጠኝ አመሰገንኩ ....
✍️በጠዋት ነበር ወደሰራ የገባውት ማታ በጊዜ ስለተኛው ነው መሰል ከአስራ አንድ ሰአት ተኩል በዋላ እንቅልፍ አልመጣ ብሎኝ ተቸግሬ ነበር የቆየውት ከዛ ለመተኛት ከመታገል ይልቅ ተነስቼ ስራ ብገባ ይሻላል ብዬ ወደስራ ተጣጥቤ አቀናው ። ማንም የለም በርግጥ በዛ ሰአት ማንስ ይኖራል ። ዘበኛው እንኳን እንቅልፍ እያንጎላጀጀው ነበር ። ሲያየኝ አዲስ ነገር ነው የሆነበት ፣ ሰላም ብዬው ወደውስጥ ገብቼ ቢሮዬ ውስጥ ተቀመጥኩ ፣ ምን እንደምሰራ ግራ ገባኝ ልቤ ደሞ ርብሽብሽ ብሏል ፣ አይምሮዬ ወደማሪዛ እየሸፈተ አስቸግሮኛል ተው ብለው እንኳ ሊተወኝ አልቻለም ። ፍቅር ጨምድዶ ይዞኛል በቃ ከእውነታው መሸሽ አልቻልኩም ፣ ስልኬን አንስቼ ፣የማሪዛን ስልክ ቁጥር አወጣው ፣ እና ደወልኩ ፣ ይጠራል አይነሳም ........ጠርቶ ጠርቶ ተዘጋ ይባስ ጨነቀኝ ፣ መልሼ በዚ በጠዋት ምን ነክቶኝ ነው ብዬ እራሴን ታዘብኩት .... ይሄኔ አይታው ተናዳብኝ ነው ያላነሳችው ብዬ አሰብኩ ። እንደው ብታነሳው ምን ልላት ነበር ? የራሴ አሳብ መልሶ አስደነገጠኝ ። የማወራውን እንኳ ሳላዘጋጅ በስሜት ሲጨንቀኝ መደወሌ አግባብ እንዳልሆነ ስረዳ እንኳንም አላነሳችው አልኩ ......
የዛን ለት እንዲቺው እንደከበደኝ ዋልኩ ፣ማሪዛም ስልኬን አይታ እንኳ ትደውላለች ብዬ ነበር ሳትደውል ቀረች ። ድብርቴ ጨመረ ...
ወደ ከሰአት አካባቢ አለቃዬ ቢሮዬ በፍጥነት ና እፈልግሃለው ሲለኝ ያልተለመደ ስለሆነብኝ አሳሰበኝ ፣ እሱ የሚገኝበት ቢሮ ወደ አራት ኪሎ አካባቢ ነበር እኔ ከሳርቤት አካባቢ ነው የምሰራው ፣ እና እንዴት እዛ ድረስ እንድመጣ ፈለገ ፣ሌላ ጊዜ እራሱ መጥቶ ነበር የሚያናግረኝ ፣ የሱ ቢሮ በሦስት ወር አንዴ ስለስራው ለማውራት ስብሰባ ሲጠራን ብቻ ነው የምንሄደው ። ልቤ ፈራ ምን ተፈጥሮ ይሆን ........

ክረምት እንደገባ ለምን አትነግሯትም ..😀
05/07/2025

ክረምት እንደገባ ለምን አትነግሯትም ..😀

አፄ ቴዎድሮስን አንዲት ሴት እየተከታተለች በሄዱበት ቦታ ሁሉ ትሰድባቸዋለች። የአፄው አጃቢዎችና መኳንንቶች ሴትየዋን አደብ ለማስያዝ ፍቃድ ከአፄው ይጠይቃሉ። አፄው "አይሆንም አትንኳት" አሉ...
05/07/2025

አፄ ቴዎድሮስን አንዲት ሴት እየተከታተለች በሄዱበት ቦታ ሁሉ ትሰድባቸዋለች። የአፄው አጃቢዎችና መኳንንቶች ሴትየዋን አደብ ለማስያዝ ፍቃድ ከአፄው ይጠይቃሉ። አፄው "አይሆንም አትንኳት" አሉ።

ምክንያታቸውን ሲገልፁ ምን አሉ:–

"ይህች ሴት ወንድሟን በውጊያ ገድዬባታለሁ። ወንድሟን ገድዬ ሀዘንና ብስጭቷን አትተንፍሺ እንዴት እላለሁ። ፀቤ ከወንድሟ ጋር ነበረ። እሷ በዚህ ውስጥ የለችበትም። ተዋት"

ወዳጄ አዕምሮህ ነፃ ካልሆነ እውነትን አዙረህ አታይም ነፃ ሁን።

ፍቅር እውነትም ያምራል ትኩረትህ በአንድ ሰው ላይ ከተገደበ ❤
05/07/2025

ፍቅር እውነትም ያምራል ትኩረትህ በአንድ ሰው ላይ ከተገደበ ❤

05/07/2025

!!

አቋምህን አስተካክል።
ጸጉርህን ተቆረጥ።
ቆዳህን ተንከባከብ።
ኢነርጅ የሚሰጥህን ተመገብ።
መልፈስፈስ አቁም!!!

ልብ በል. . .

ጥሩ ሆነህ ስትታይ፣ ጥሩ ይሰማሃል።
ጥሩ ሲሰማህ ጥሩ ትሰራለህ።
ራስህ ላይ ስትሰራ ለኢነርጅህ ጥሩ ነው!!

🙏🙏🙏🙏

ዲያጎ ጆታ እና ወንድሙ ህይወታቸውን ስላጡባት መኪና አንዳንድ መረጃ መኪናው ላምቦርጊኒ ሁራካን ይባላል። እነዚህ መኪኖች በብዛት የሚመረጡት ለፍጥነት፣ ለረጅም አመታት አገልግሎት እና ለምቾታቸ...
05/07/2025

ዲያጎ ጆታ እና ወንድሙ ህይወታቸውን ስላጡባት መኪና አንዳንድ መረጃ

መኪናው ላምቦርጊኒ ሁራካን ይባላል። እነዚህ መኪኖች በብዛት የሚመረጡት ለፍጥነት፣ ለረጅም አመታት አገልግሎት እና ለምቾታቸው ነው።

ሞተራቸው ተነስቶ ከፍተኛ ፍጥነት ላይ ለመድረስ የሚፈልጉት ጥቂት ሰከንዶችን ነው። ከፍተኛ ፍጥነት ስንል ደግሞ ከ 310 ኪሜ እስከ 325 ኪሜ በሰዓት ማለት ነው። ከቆሙበት በአንዴ 100 ኪሜ በሰዓት ፍጥነት ላይ ለመድረስ የሚፈልጉት ከ3 ሰከንድ ያነሰ ጊዜ ነው።

በጣሊያኑ መኪና አምራች ላምቦርጊኒ የሚመረተው ይሄ መኪና ባለ አስር ሲሊንደር ሲሆን ሞተሩ ሲነሳ በራሱ የተለየ የራሱ የሆነ ግርማ ሞገስ ያለው ድምፅ ያወጣል። አቅሙ በፈረስ ጉልበት ከ572 እስከ 630 የሚደርሰው ይህ መኪና እስከ ሰባት ማርሽ ያለው ሲሆን አሁን ባለው የአለም ገበያ እንደየ ሞዴሉ ከ230,000 ዶላር እስከ 350,000 ዶላር የሚሸጥ ነው። በኢትዮጵያ የባንክ ምንዛሪ ከ32 ሚሊዮን እስከ 50 ሚሊዮን ድረስ ማለት ነው።

ዛሬ የዲያጎ ጆታን እና የወንድሙን ህይወት የቀጠፈው ይህ መኪና ነው። የአደጋው መነሻ የተባለው ከፊታቸው የነበረውን መኪና ለመቅደም በሚሞክሩበት ወቅት የመኪናው ጎማ በመፈንዳቱ ነው።

✅አስቡት በዚህ ሁሉ ብር የገዛችሁት መኪና ጎማው መንገድ ላይ ይፈነዳል።

✅በዚህ ሁሉ ብር ገዝታችሁ ህይወታችሁን አሳልፋችሁ የሰጣችሁት መኪና የሚንቀሳቀሰው በ500 ዶላር ጎማ ነው ....

✅የ350,000 ዶላር መኪናን አመድ ያደረገው የ500 ዶላር ጎማ ነው ....

✅አስቡት በሳምንት 150,000 ፓውንድ የሚከፈለውን የእግር ኳስ ተጫዋች ህይወት የቀጠፈችው የ360 ፓውንድ ጎማ ፈንድታ ነው ....

✅አንዳንዴ ህይወታችሁን የሚወስኑት ትንሽ የሚባሉት፣ ከዋናዎቹ አንፃር ንቀን ትኩረት የማናደርግባቸው ነገሮች ናቸው።

ከስር በተቀመጡት ሁለት ፎቶዎች ላይ ልዩነት ያመጣችው አንድ የ500 ዶላር ጎማ ናት።

✅የአለምን ህዝብ ቀልብ በዚህ ልክ የገፈፈችው እና ብዙዎቹን ለረጅም ጊዜ አብሯቸው በሚቆይ እና ለአመታት በማይረሱት ድንጋጤ ውስጥ የከተተችው በ350,000 ዶላር ቅንጡ መኪና ላይ የተገጠመች የ500 ዶላር ጎማ ናት።

#ማራኪ ስፖርት

ሶቅራጥስ ህፃን እያለ ከእንቅልፉ በጠዋት መነሳት አይወድም ነበር። ወደፊት ልጇ አድጎ ሃብታም ነጋዴ እንዲሆንላት የምትመኘው እናቱ፣ በዚህ ስንፍናው በጣም አምርራ ትናደድ ነበር። ከእለታት በአ...
04/07/2025

ሶቅራጥስ ህፃን እያለ ከእንቅልፉ በጠዋት መነሳት አይወድም ነበር። ወደፊት ልጇ አድጎ ሃብታም ነጋዴ እንዲሆንላት የምትመኘው እናቱ፣ በዚህ ስንፍናው በጣም አምርራ ትናደድ ነበር። ከእለታት በአንዱ ቀን ወደ መምህሩ በመሄድ " በጠዋት የመነሳት ጥቅሞችን" ለሶቅራጥስ እንዲያስረዳው በሚስጥር ትነግረዋለች። በጊዜው በመምህሩና በሶቅራጥስ መካከል የነበረውን ቃለ ምልልስ ይህ እንዲህ የሚል ነበር;-

መምህሩ ፦ " ፍቃድህ ከሆነ አንድ ቆንጆ ታሪክ ልንገርህና ከታሪኩ ያገኘኸውን ፋይዳዎች ወይም ጥቅሞች ምን እንደሆነ ትነግረኛለህ?"

ሶቅራጥስ፦ "በሚገባ!"

መምህሩ ፦ "ሁለት ወፎች ነበሩ። አንደኛው በማለዳ ከእንቅልፉ በመነሳት ራሱንም ልጆቹንም መመገብ ቻለ። ሁለተኛው ደግሞ ከእንቅልፉ አርፍዶ በመነሳት ራሱንም ልጆቹንም ሳይመግብ ቀረ።" አሁን ከነገርኩህ ታሪክ ምን ቁም ነገር አገኘህ?

ሶቅራጥስ ፦እኔ የተረዳሁት "በማለዳ ተነስተው የሚርመሰመሱ ነፍሳት ለአዕዋፍ ምግብ እንደሚሆኑ ነው።" 😀😀

"ከመፃህፍት ማዕድ"

Address

Addis Ababa

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when ጠቃሚ ንግግሮች/Useful expressions posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to ጠቃሚ ንግግሮች/Useful expressions:

Share