Zema news

Zema news ታማኝ የዜና ምንጭ

19/04/2025

የጉለሌ ክፍለ ከተማ አስተዳደር ዋና ስራ አስፈጻሚ አቶ ወልዴ ወገሴ የ2017 የትንሳኤ በዓልን ምክንያት በማድረግ ያስተላለፉት የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት ፤

ውድ የክፍለ ከተማችን ነዋሪዎች እንኳን ለኢየሱስ ክርስቶስ የትንሣኤ በዓል አደረሰን፣ አደረሳችሁ !!

በክርስቲያኖች ዘንድ ከፍተኛ ሥፍራ ተሰጥቷቸው ከሚከበሩ በዓላት መካከል በዓለ ትንሣኤው በቀዳሚነት ይጠቀሳል። የጌታ ኢየሱስ ክርስቶስ ትንሣኤ የፍቅር ጥግ የታየበት ፣ የዕርቅና የይቅርታ ትርጉም የተገለጠበት ፣ ምሕረትና ድኅነት የተረጋገጠበት ፣ የአዳም ተስፋ የተፈፀመበት ታላቅ በዓል ነው።

በቀዳሚዎቹ ዘመናት አባታችን አዳም አትብላ የተባለውን ዕጸ በለስ በልቶ የፈጣሪን ትእዛዝ ከተላለፈ በኋላ የሰው ልጅ የአምላክ ፍቅር ርቆት የፍዳ ዘመናትን አሳልፏል።

በዲያቢሎስ ሤራ የተቆረጠው የፈጣሪና የፍጡር ፍቅር ዳግም እንዲታደስ አምላክ ከዙፋኑ ወደ ምድር ወረደ፤ በሰው ቁመትና ወርድ ተወሰነ፤ በደሙ አጥቦ የሰው ልጅን ከዘላለም ርግማን ሊያነፃ ክርስቶስ ታመመ፤ ስድብና ማንጓጠጡን ፣ ውንጀላና ግርፋቱን ፣ የዓለምን መከራ ሁሉ ያለ በደሉ ተቀበለ። ፍቅር በመስቀል ላይ ተሰቅሎ ታየ። ፍፁም ፍቅር ከክብር ዙፋን ላይ መውረድን እንደሚጠይቅ፤ እውነተኛ መውደድ በቅድመ ሁኔታዎች እንደማይታጠር ክርስቶስ በተግባር አስተምሮናል።

እንደ ክርስቶስ ትንሣኤ ሁሉ የሀገራችን ብልጽግና እውን እንደሚሆን፣ የኢትዮጵያችን ትንሣኤ እንደሚሳካ ምንም ጥርጥር የለውም።

የብልፅግና ጉዞ ሁሉም አሸናፊ የሚሆንበት የህብረት ጉዞ እንጂ ጥቂቶች የሚያሸንፉበት የጥሎ ማለፍ ሩጫ አይደለም። ስለሆነም በትብብር ፋንታ መጓተትን፣ በመደጋገፍ ፋንታ መገፋፋትን ከመረጥን ጉዟችን አንድ ርምጃ ወደፊት መቶ ርምጃ ወደኋላ ስለሚሆን ካሰብንበት ግብ በፍጥነት እንደርሳለን ማለት ዘበት ነው። ትንሣኤው አይቀሬ ነው። ፈተናው ተሸናፊ ነው። የጸናም አሸናፊ ይሆናል።

በድጋሜ መልካም የትንሣኤ በዓል!

አቶ ወልዴ ወገሴ ናኦ
የጉለሌ ክፍለ ከተማ አስተዳደር ዋና ስራ አስፈጻሚ

ሚያዚያ 11 ቀን 2017 ዓ.ም

19/04/2025

የጉለሌ ክ/ከተማ ብልጽግና ፓርቲ ቅ/ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ይከበር ስማቸው ለክርስትና እምነት ተከታዮች ለትንሳኤ በዓል ያስተላለፉት የእንኳን አደረሳችሁ መልእክት!!

የትንሳኤ በዓል በህዝበ ክርስትያኑ ዘንድ በፆም ፣በስግደት እና በምስጋና የሚከበር በንጹሕ ህሊና እና እርስ በርስ ይቅር በመባባል ክርስቲያኖች ወደ ፈጣሪያቸው የሚቀርቡበት ታላቅ በዓል መሆኑ እጅግ ልዩ እና ደማቅ ያደርገዋል ።

የትንሣኤ በዓል እስራኤላውያን ከግብፅ ምድር ከከባድ መከራና ስቃይ ወደ ተስፋይቱ ምድር ከነዓን የተሻገሩበትን እውነት የሚያስታውስ የመሻገር፣ የአሸናፊነትና የድል አድራጊነት መታሰቢያ ተምሳሌት ታላቅ በዓል ነው ።

በዓሉ ጌታችንና መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በምድር ላይ ለሰው ልጆች ደህንነት ሲል ያጋጠመውን መከራ፣ስቃይና ግርፋት በፅናት ተቋቁሞና ሞትን አሸንፎ የዲያብሎስን ቀንበር ሰብሮ የሰውን ልጅ ወደ ብርሃን ያሻገረበት የፅናት፣ የአሸናፊነትና የነፃነት በዓል ተምሳሌት በመሆኑ አርአያነቱ የጎላ ነው ።

ይቅር ባይነት ፣መቻቻልና መተሳሰብ ፣አሻጋሪ እሴቶች በመሆናቸው በታላቁ የዐቢይ ፆም ወቅት የእምነቱ ተከታዮች ያሳየነውን የይቅር ባይነትና የመተሳሰብ እሴቶቻችንን በዕለት-ተዕለት ተግባሮቻችን ኃላፊነቶቻችንን በአራአያነት ማሳየት ይጠበቅብናል ።

የተወደዳችሁ የፓርቲያችን አባላት፣ የክ/ከተማችን ነዋሪዎች :-

በተለይ በዚህ ዓመት እህትማማችነትንና ወንድማማችነትን በማንገስ በኢየሱስ ክርስቶስ አስተምሮ መሠረት ጥላቻን ነቅለን ፍቅርን እየተከልን ፣አንዳችን ለሌላችን አቅም እና ጉልበት እየሆንን ፣ተደምረን በሁሉም መስክ የተቀመጡ የብልጽግና ግቦችን በማሳካት ሁለንተናዊ ብልጽግናን ለማረጋገጥ በቁርጠኝነት እጅ ለእጅ ተያይዘን መስራት ይጠበቅብናል ።

በመጨረሻም የትንሣኤ በዓልን ስናከብር ከመብላትና ከመጠጣትም በላይ ለአፍታም መዘንጋት የሌለብን የማህበረሰባችን መለያ ሆኖ ከኖረው ቱባ ባህል ፣እምነት አስተምህሮትና ልምድ የሚቀዱ እሴቶችን በመላበስና ይበልጥ ህብረተሰባዊ አንድነት ላይ በመመስረት ቤተሰባቸውን ያጡ እና ጧሪ ደጋፊ የሌላቸውን አቅመ ደካማ የማህበረሰብ ክፍሎችን አስቦ በመደጋገፍ መሆን ይገባል።

በድጋሜ ለመላው የክርስትና እምነት ተከታዮች በሙሉ እንኳን ለትንሣኤ በዓል በሠላም አደረሳችሁ ! አደረሰን ! በማለት በዓሉ የሰላም ፣የፍቅርና የአብሮነት እንዲሆን እመኛለሁ ።

አቶ ይከበር ስማቸው
የጉለሌ ክ/ከተማ ብልጽግና ፓርቲ ቅ/ጽ/ቤት ኃላፊ

19/04/2025

"እንኳን ለትንሳኤ በዓል በሰላም አደረሳችሁ"!!

የጉለሌ ክፍለ ከተማ ወረዳ 10 ዋና ስራ አስፈጻሚ አቶ ሲሳይ ምንዳዬ የእንኳን አደረሳችሁ መልእክት!

ጉለሌ ወረዳ 10 ኮሙኒኬሽን
ሚያዚያ 11/2017 ዓ.ም

ለመላው የክርስትና እምነት ተከታዮች በሙሉ እንኳን ለለጌታችን ለምድሀኒታችን ለእየሱስ ክርስቶስ የትንሣኤ በዓል በሰላም አደረሳችሁ በማለት በዓሉን ስናከብር የሌላቸውን በመርዳት ፣ የወደቁትን በማንሣት እርስ በእርስ በመረዳዳት ማክበር እንዳለበት መልእክት አስተላልፈው።

በመጨረሻም በዓሉ በሰላም ፤ በፍቅር ፤ በአንድነት ሆነን በያለንበት እርስ በእርስ በመተሳሰብ በደስታ እናሳልፍ ሲሉም በአጠቃላይ ለእምነቱ ተከታዮች ሁሉ መልካምን ተመኝተዋል።

በድጋሚ መልካም የትንሳኤ በዓል ይሁንላችሁ !!

19/04/2025

ለክርስትና እምነት ተከታዮች በሙሉ እንኳን ለጌታችን ለእየሱስ ክርስቶስ ትንሳኤ በዓል በሰላም አደረሳችሁ፤ አደረሰን!!

በበጀት ዓመቱ የህዝባችንን አብሮነት የሚያጠናክሩ የፓርቲያችንን እሳቤዎች እንዲሰርፁ እና የከተማችን የልማት ስራዎች እንዲስፋፉ በተደረገው ቅንጅታዊ ስራ ስኬቶች ማስመዝገብ ተችሏል፤ የተጀመሩ የልማት ስራዎች ተጠናክረዉ እንዲቀጥሉ የህዝባችን የመልማት ፍላጎት እዉን ለማድረግ ተጠቃሚነቱ ለማረጋገጥ የከተማችንን ብሎም የሀገራችንን ብልጽግና እዉን ለማድረግ የምናደርገዉን ጉዞ በሁለንተናዊ መልኩ ተሳትፏችሁን አጠናክራችሁ እንድትቀጥሉ አደራ እላለሁ።

በዓሉ የሰላም፣ የይቅርታ፣ የምህረት፣ የመተሳሰብ፣ የመርዳዳት፣ የፍቅር፣ የደስታ እና አብሮነታችን የሚጠናከርበት እንዲሆንልን ከልቤ እመኛለሁ።

በድጋሚ እንኳን አደረሳችሁ፣ መልካም በዓል

አቶ ዮሴፍ ወንድሙ

የጉለሌ ክፍለ ከተማ ወረዳ 10 ብልፅግና ፓርቲ ፅ/ቤት ሀላፊ

19/04/2025

የጉለሌ ምክትል ዋና ስራ አስፈጻሚና ስራና ክህሎት ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ሰለሞን ታደሰ የትንሳዔ በዓልን አስመልክቶ የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት አስተላለፉ

ለመላው ለክፍለ ከተማችን ነዋሪዎች የክርስትና እምነት ተከታዮች እንኳን ለ2017 ዓ.ም የጌታችን የመድሃኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስ የትንሳዔ በዓል በሠላምና በጤና አደረሳችሁ አደረሠን!!

በዓሉ በክርስትና እምነት ተከታዮች ዘንድ ከፍተኛ ትኩረት ከሚሰጣቸው ሃይማኖታዊ በዓላቶች የትንሳኤ በዓል አንዱ ሲሆን ጌታችንና መድሐኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ለሰው ልጆች ፍቅርን ፣ ይቅርታን ፣ ምህረትን እና መስዋዕትነትን ዝቅ ብሎ ያስተማረበት ከብዙ መከራና ስቃይ በኋላ ሞትን ድል አድርጎ ትንሳኤውን ያሳየበት ለሰው ልጆች የመዳን ተስፋን ያስተማረበት ታላቅ በዓል ነው።

የህይወት መንገዳችን በጨለማና ሁከት ፣ በእሾህና አሜኬላ ፣ በስቃይና መከራ የተፈተነ ቢሆንም ከመከራ በኋላ ስኬት ፣ ከሞት በኋላ ትንሳኤ እንዳለ በማሰብ ጌታችን እና መድሐኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ባስተማረን የርህራሄና የፅናት ተምሳሌትነት በርካታ ፈተናዎችን በድል እያለፍን ለትንሳዔው እንደምንበቃ አልጠራጠርም።

የክፍለ ከተማችን ነዋሪ ተስፋ ከሚሰጡ የኮሪደር ልማትና የወንዝ ዳርቻ ፕሮጀክት ስራዎች ሰፊ ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ትስስር እየፈጠሩ የሚገኙ የስራ እድል ፈጠራ ፣ የገቢ አሰባሰብ ስራ ፣ ሰላም የማስከበር ስራ ፣ የከተማ ግብርናና የሌማት ትሩፋት ፣ የትምህርት ፣ ጤና ፣ ሌሎች በማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ዘርፎች ላይ የሚታዩ ለውጦች ተግባራትን አቀናጅቶና አስተባብሮ በውጤታማነት ማሳለጥ መቻሉ የተስፋችን ማሳያዎች ናቸው።

በመሆኑም የትንሳኤ በዓልን ስናከብር የአካባቢያችንን ሰላምና ልማት በሚያጎለብቱ እሴቶች ላይ በማተኮር ፣ ልዩነትን ሳይሆን አንድነትን ፣ ጥላቻን ሳይሆን ፍቅርን ፣ መተሳሰብን ፣ ወንድማማችነትን እና መደጋገፍን በማስተማር የተቸገሩ ወገኖችን በመርዳት ሃይማኖታዊ ትውፊቱን በጠበቀ መልኩ በዓሉን እንድናከብር አሳስባለሁ ።

መላው ህዝባችን በክፍለ ከተማው በሚያከናውናቸው የልማት እና የመልካም አስተዳደር ስራዎች ሁሉ የነቃ ተሳትፎ በማድረግ የአካባቢያችንን የልማት ተሳትፎ እና ተጠቃሚነት እንዲናረጋግጥ የድርሻችሁን እንድትወጡ በዚህ አጋጣሚ ጥሪዬን አስተላልፋለሁ።

በድጋሚ መልካም የትንሳኤ በዓል

አቶ ሰለሞን ታደሰ ወንድሙ
የጉለሌ ክፍለ ከተማ ምክትል ዋና ስራ አስፈጻሚና ስራና ክህሎት ጽ/ቤት ኃላፊ

ሚያዝያ - 11- 2017 ዓ.ም

19/04/2025

Address

Addis Ababa

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Zema news posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share