Maze Ethiopia

Maze Ethiopia Contact information, map and directions, contact form, opening hours, services, ratings, photos, videos and announcements from Maze Ethiopia, Digital creator, Addis Ababa.

01/07/2025
የትንሳኤ ቅዳሴን በአ/ምንጭ ደብረ መድኃኒት መድኃኔዓለም ሲያገለግል የነበረው የጎፋ ዞን አስተዳዳሪ የሆነው ዲያቆን ኢንጅነር ዳግማዊ አየለ***በየትኛውም የሕይወት ዘመኑ አምላኩን የማይረሳ ሠ...
21/04/2025

የትንሳኤ ቅዳሴን በአ/ምንጭ ደብረ መድኃኒት መድኃኔዓለም ሲያገለግል የነበረው የጎፋ ዞን አስተዳዳሪ የሆነው ዲያቆን ኢንጅነር ዳግማዊ አየለ
***

በየትኛውም የሕይወት ዘመኑ አምላኩን የማይረሳ ሠው ክቡር ነው። በየዘመኑ ሃይማኖቱን የማይዘነጋ እና ሰማያዊ ጥሪውን ያልነቀ አገልጋይ ለቡክርናው የታመነ ነው።

የታላቁ ጎፋ ሕዝብ እና መንግስትን በዋና አስተዳዳሪነት ይመራ ዘንድ ኃላፊነት ወስዶ እያገለገለ የሚገኘው ወንድማችን ዲያቆን ኢንጅነር ዳግማዊ አየለ በትላንትናው ዕለት የትንሳኤ ቅዳሴ ከሚመሩ ልዑክ ካህናት መሃል አንዱ ሆኖ በአርባምንጭ ደብረ መድኃኒት መድኃኔዓለም ካቴድራል አገልግሏል።

የሁለት ርምጃ ያህል ክብደት ያላትን የመንግስት ስልጣን ሲረከቡ ቤተክርስቲያንን ለመሳለም የሚደነግጡ፣ገልጠው ያሳዩት የነበረውን መስቀል ለመደበቅ ለሚጣጣሩ እና የቀደመውን አገልግሎታቸው ማስቀጠል እንደ ፓለቲካ ክህደት ለሚመለከቱት ለእኛ ቤት ሰዎች የዲያቆኑ ግብር ትልቅ ስብከት ነው።

ያለህን ስታከብር ክብርህ ይጸናል።

ስለ ፍትህ እና ስል እውነት እያገለገላችሁ ለሀገር እና ለቅድስት ቤተክርስቲያን ኩራት የሆናችሁ ወንድሞች እና እህቶች ዋጋችሁ ታላቅ ነው ።

ዲያቆን ኢንጂነር ዳግማዊ አየለ...ዘመንህ በመቅደሱ ይለቅ !!! በላቀው የክህነት ማዕረግ እና የሀገር ኃላፊነት እንድናይህ እንመኛለን !!!

ያከበርከው አምላክ ይከተልህ !!!

 1- ግቦችን አያስቀምጡም2- ሌሎችን ያወቅሳሉ3- ሰበቦች ያበዛሉ4- መቆጠብ አይችሉም5- በበጀት መኖር አይችሉም6- ሌሎችን ማስደነቅ ይፈልጋሉ7- እንዴት ኢንቨስት ማድረግ እንዳለባቸው አያው...
06/04/2025



1- ግቦችን አያስቀምጡም
2- ሌሎችን ያወቅሳሉ
3- ሰበቦች ያበዛሉ
4- መቆጠብ አይችሉም
5- በበጀት መኖር አይችሉም
6- ሌሎችን ማስደነቅ ይፈልጋሉ
7- እንዴት ኢንቨስት ማድረግ እንዳለባቸው አያውቁም
8- መጥፎ የማውጣት ልምድ አለባቸው
9- ራሳቸው ላይ ኢንቨስት አያደርጉም።

14/03/2024
ብፁዕነታቸው ወደ አሜሪካ እንደተመለሱ ተሰምቷል።ብፁዕ አቡነ ጴጥሮስ የቅዱስ ሲኖዶስ ዋና ጸሐፊ እና የኒውዮርክና አካባቢው ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ወደ ሀገር እንዳይገቡ በመከልከላቸው ወደ አ...
07/02/2024

ብፁዕነታቸው ወደ አሜሪካ እንደተመለሱ ተሰምቷል።

ብፁዕ አቡነ ጴጥሮስ የቅዱስ ሲኖዶስ ዋና ጸሐፊ እና የኒውዮርክና አካባቢው ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ወደ ሀገር እንዳይገቡ በመከልከላቸው ወደ አሜሪካ ለመመለስ መገደዳቸውን አሳውቀዋል።

ብፁዕነታቸው ከደቂቃዎች በፊት ለማሕበረ ቅዱሳን ቴሌቪዥን ጣቢያ በሰጡት ቃል ፤ " አሁን አሳፍረውኝ ተመለስኩ፤ ወደ አሜሪካ ወደመጣሁበት መለሱኝ ፤ ወደ ስራዬ እንዳልመለስ ከለከሉኝ። " ብለዋል።

ለቴሌቪዥን ጣቢያው ቃላቸውን በሰጡበት ወቅት አውሮፕላኑ ሊነሳ እንደነበር ለማወቅ የተቻለ ሲሆን ወደ አሜሪካ እንዲመለሱ የሚደረግበት ምክንያት ምንድነው ? ተብለው ተጠይቀው ፤ ብፅዕነታቸው ፤ " በቃ ግሪን ካርዱን ብቻ ነው የምንፈልገው እኛ ያንተን ፓስፖርት አንፈልግም ግሪንካርድ ብቻ ነው የምንፈልገው ብለው ወሰዱ በሩን ዘጉ !! " ሲሉ ተናግረዋል።

ይህን ያደረጉት የደህንነት ሰዎች ናቸው ብለዋል።

ብፅዕነታቸው ወደ አውሮፕላን እንዲገቡ ከመደረጋቸው በፊት ውጭ ላይ ሲጉላሉ እንደነበር ተናግረው አንድ የኢሚግሬሽን ሰው " የማውቀው ነገር የለም ግሪንካርዱ ትክክል አይደለም " እንዳላቸውና እሳቸውን ግሪንካርዱ ገና 3 ዓመት እንደሚቀረው እንደነገሩት አስረድተዋል።

ይህን ሲያስረዱ ከግለሰቡ መልስ እንዳልተሰጣቸውና " ሌሎች ሰዎችንም #ዲፖርት እያደረግን ነው " በማለት እንደነገራቸው ገልጸዋል።

ብፅዕነታቸው የአሜሪካ ፓስፖርት እንዳላቸው ገልጸው ፤ " እሱን ምንም ለማድረግ ስላልቻሉ ግሪንካርድ እንወስዳለን በማለት ወስደዋል " ሲሉ ተናግረዋል።

ከሳምንታት በፊት ለአገልግሎት ከሀገር ሲወጡ ብፁዕ አቡነ አብርሃምን ጨምሮ ሌሎችም " ሊያስቀሩህ ይችላሉ " የሚል ነገር ሰምተው እንደነገሯቸው ነገር ግን በአሜሪካ የያዙትን አገልግሎት መተው ስላልፈለጉ ወደ አሜሪካ መሄዳቸውን ገልጸዋል።

ብፅዕነታቸው ወደ አሜሪካ በሄዱበት ወቅት " ኮበለሉ " የሚሉ መረጃዎች ተሰራጭተው እንደነበር ይታወሳል። በኃላም ቤተክርስቲያኗ በሰጠችው መግለጫ ፤ በህጋዊ መንገድ በቤተክርስቲያን እውቅና ከሀገር እንደወጡ ፤ የሚደበቁም ሆነ የሚኮበልሉ የወንጀል ሰው እንዳልሆኑ አሳውቃ ነበር።

ብፁዕ አቡነ ጴጥሮስ የቅዱስ ሲኖዶስ ዋና ጸሐፊ ወደ ሀገር እንዳይገቡ ተከለከሉ‼️ብፁዕ አቡነ ጴጥሮስ የቅዱስ ሲኖዶስ ዋና ጸሐፊ እና የኒውዮርክና አካባቢው ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ በአሜሪካ ...
06/02/2024

ብፁዕ አቡነ ጴጥሮስ የቅዱስ ሲኖዶስ ዋና ጸሐፊ ወደ ሀገር እንዳይገቡ ተከለከሉ‼️

ብፁዕ አቡነ ጴጥሮስ የቅዱስ ሲኖዶስ ዋና ጸሐፊ እና የኒውዮርክና አካባቢው ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ በአሜሪካ የነበራቸውን ሐዋርያዊ አገልግሎት ጨርሰው ቦሌ ዓለም አቀፍ አየር ማረፊያ ሲደርሱ እንዳይገቡ መከልከላቸው ተሰምቷል።

ብፁዕነታቸው ከሳምንታት በፊት በቋሚ ሲኖዶስ እውቅና ወደ ሀገረ ስብከታቸው በመሄድ የአጋእዝተ ዓለም ሥላሴ ዓመታዊ በዓል፣ የከተራና የጥምቀት በዓላትን ከመንፈስ ልጆቻቸው ጋር ያከበሩ ሲሆን ለአዳጊ ሕጻናትም ማዕረገ ዲቁና መስጠታቸው ይታወቃል።

ብፁዕነታቸው በአሁኑ ሰዓት ዓለም አቀፍ አየር ማረፊያው ይገኛሉ ሲሉ መረጃ ሰጭዎቻችን አድርሰውናል ሲል ማኅበረ ቅዱሳን ቴቪ አስታውቋል።

ካዲስኮ አደባባይ አካባቢ የትራፊክ አደጋ ደረሰአዲስ አበባ፣ ጥር 10፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) በአዲስ አበባ ከተማ ከካዲስኮ አደባባይ አለፍ ብሎ በተከሰተ የትራፊክ አደጋ በንብረት ላይ ጉዳት ...
20/01/2024

ካዲስኮ አደባባይ አካባቢ የትራፊክ አደጋ ደረሰ

አዲስ አበባ፣ ጥር 10፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) በአዲስ አበባ ከተማ ከካዲስኮ አደባባይ አለፍ ብሎ በተከሰተ የትራፊክ አደጋ በንብረት ላይ ጉዳት ደረሰ።

በአደጋው በሰው ሕይወት ላይ የደረሰ ጉዳት አለመኖሩን የአዲስ አበባ እሳትና አደጋ ስጋት ስራ አመራር ኮሚሽን አስታውቋል፡፡

በበዓል ወቅት የትራፊክ እንቅስቃሴው ስለሚጨምር ኅብረተሰቡ አስፈላጊውን ጥንቃቄ እንዲያደርግ ኮሚሽኑ መክሯል፡፡

Address

Addis Ababa

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Maze Ethiopia posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share