የመደመር ትውልድ - Dhaloota Ida'amuu

የመደመር ትውልድ - Dhaloota Ida'amuu አዳዲስና ፈጣን መረጃዎችን ለማግኘት ትክክለኛው ቦታ።
Odeefannoo Haaraafi wayitawaa argachuuf iddoo sirriitti argamtu!

በዐቢቹ ሥራ አቧራዋን አራግፋ በአስደናቂ የለውጥ ጎዳና ላይ ያለች ደሴ ከተማየአብሮነት እና የመዋደድ ተምሳሌት በሆነችዉ ውቢቷ የደሴ ከተማ አስደማሚ የኮሪደር ልማት ስራ እየተከናወነ ነው። የ...
18/07/2025

በዐቢቹ ሥራ አቧራዋን አራግፋ በአስደናቂ የለውጥ ጎዳና ላይ ያለች ደሴ ከተማ

የአብሮነት እና የመዋደድ ተምሳሌት በሆነችዉ ውቢቷ የደሴ ከተማ አስደማሚ የኮሪደር ልማት ስራ እየተከናወነ ነው። የደሴ ከተማ ከቀደምት ስልጡን የኢትዮጵያ ከተሞች ተርታ የምትመደብ እና በዘመናዊው የኢትዮጵያ ታሪክ ውስጥ ስመ ጥር ከሆኑት ከተሞች መካከል በዋናነት የምትጠቀስ ታሪካዊ ከተማ ናት። የደሴ ከተማ ህዝብ ፒያሳ ላይ ተሰባስቦ የኢትዮጵያውያን ባንድራ በመስቀልና በማክበር ያለምንም መቆራረጥ ከ85 ዓመት በላይ ያስቆጠረ ፅኑ ኢትዮጵያዊ ማህበረሰብ ነው። ይህ ትልቅ አርአያነት ያለዉ ምስጉን ተግባር ነዉ፡፡ በቀድሞው ጊዜ የሲራራ ንግድ መዳረሻ የነበረችው ጥንታዊቷ የደሴ ከተማ በመጀመሪያ ምዕራፍ የኮሪደር ልማቷ የብልፅግና ብርሃን ወጋገን ፈንጥቃለች፡፡ በነዋሪዎቿ ልብ ውስጥ የተስፋ ችቦን ለኩሳለች፡፡ ደሴ ለኗሪዎቿ የምትመች ፣ የንግድ፣ የገበያ፣ የምርምርና የቱሪዝም ማዕከል ወደመሆን የሚያስጉዛትን የተስፋ ጎዳና ተያይዛለች። ልማትና ሰላሙን እንደ አይኑ ብሌን የሚጠብቀው የደሴ ከተማ ነዋሪ ለብልፅግናው መረጋገጥ ጊዜና ገንዘቡን ያለስስት በመስጠት፣ አበረታች የሞራል ስንቅ እና የልማት ደጀን ሆኗል። በዚህም ሌላኛዉ የኢትዮጵያ ኩራት ሁናችኋልና ለአመራሩ፣ ሰራተኛው እና ለነዋሪዎቿ የላቀ ምስጋና ይገባል፡፡
#ከእዳወደምንዳ
#የኢትዮጵያብልፅግና

#ኮሪደርልማት

የኢትዮጵያዉያን ተስፋ እየለመለመ ነው!!  የምንለው እንዲሁ ሳይሆን እንደ ጠቅላይ ሚኒስትር  ዶክተር ዐቢይ አህመድ ያለውን አርቆ የሚያስብ እውነተኛ የሚታይ የሚጨበጥ ለውጥ የሚያሳየን መሪ ስ...
18/07/2025

የኢትዮጵያዉያን ተስፋ እየለመለመ ነው!!

የምንለው እንዲሁ ሳይሆን እንደ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድ ያለውን አርቆ የሚያስብ እውነተኛ የሚታይ የሚጨበጥ ለውጥ የሚያሳየን መሪ ስላለን ነው።በአርቆ አሳቢው በብልሁ ለችግሮች እንደማይምበረከክ ደጋግሞ ባሳየው መሪያችን እየታገዝን የተሻለች የበለጸገች ኢትዮጵያን ለትውልድ እናወርሳለን!!

ኢትዮጵያ በሁሉም መስክ የተሳካለት ሀገር ሆናለች!!በአፍሪካ ቀንድ ያላት ተፅዕኖ ፈጣሪነት እየጎላ መጥቷል። በትላልቅ የሰላም ማስከበር ተልዕኮዎች ላይ ያላት ተሳትፎ፣ የዲፕሎማሲያዊ ግንኙነቶቿ...
18/07/2025

ኢትዮጵያ በሁሉም መስክ የተሳካለት ሀገር ሆናለች!!
በአፍሪካ ቀንድ ያላት ተፅዕኖ ፈጣሪነት እየጎላ መጥቷል። በትላልቅ የሰላም ማስከበር ተልዕኮዎች ላይ ያላት ተሳትፎ፣ የዲፕሎማሲያዊ ግንኙነቶቿን ማጠናከር እና ለአፍሪካ አንድነት ያላት ቁርጠኝነት በአህጉሪቱ ያላትን ድርሻ ከፍ አድርጎታል። በተጨማሪም፣ በዓለም አቀፍ መድረኮች ላይ የራሷን ድምጽ በማሰማት እና በዋና ዋና ጉዳዮች ላይ የራሷን አቋም በማንፀባረቅ ተሰሚነቷን እያሳደገች ትገኛለች። ይህ ሁሉ ጥረት በመጨረሻው ሃያልና ተፅዕኖ ፈጣሪ የሆነች ኢትዮጵያን እውን ለማድረግ ያለመ ነው።

በኢትዮጵያ እየመጣ ያለውን እድገት መካድ ፍፁም ጨለምተኝነት ነውበመዋቅራዊ ሽግግር ውስጥ እያለፈ የሚገኘው የኢትዮጵያ ኢኮኖሚ በዓለም ላይ ፈጣን የኢኮኖሚ እድገት እያስመዘገቡ ከሚገኙ ሃገራት ...
11/07/2025

በኢትዮጵያ እየመጣ ያለውን እድገት መካድ ፍፁም ጨለምተኝነት ነው

በመዋቅራዊ ሽግግር ውስጥ እያለፈ የሚገኘው የኢትዮጵያ ኢኮኖሚ በዓለም ላይ ፈጣን የኢኮኖሚ እድገት እያስመዘገቡ ከሚገኙ ሃገራት ተርታ ሲሰለፍ ሌላው ቢቀር ኢትዮጵያ አባል የሆነችበትን ከBRICS+ ሃገራት ራሱ በቀዳሚነት የሚመደብ ነው።

የ BRICS+ አባል ሃገራት የ 2024/2025 የኢኮኖሚ እድገት ትንበያ እንደሚከተለው ነው፦ [Refer IMF & WB database]

❶ ኢትዮጵያ 🇪🇹 ➛ 6.6%²

❷ ሕንድ 🇮🇳 ➛ 6.2%

❸ ኢንዶኔዥያ 🇮🇩 ➛ 4.89%

❹ የተባበሩት አረብ ኢሜሬት 🇦🇪 ➛ 4%

❺ ቻይና 🇨🇳 ➛ 4.5 %

❻ ግብፅ 🇪🇬 ➛ 4.7%

❼ ኢራን 🇮🇷 ➛ 0.3%

IMF የኢትዮጵያ ኢኮኖሚ እድገትን 6.6% ያሳያል የሚል ትንበያ ያስቀመጠ ሲሆን የኢትዮጵያ መንግስት በበኩሉ የኢትዮጵያ ኢኮኖሚ በ 8% ያድጋል የሚል ትንበያ አለው።

የኢትዮጵያ አጠቃላይ የብድር መጠን $62.5 ቢሊዮን ዶላር ደርሷል የሚል ዘገባ ሪፖርተር ማቅረቡን ተከትሎ አንድ አንድ ሙሾ አውራጆች ሲያላግጡ ታዝበናል። በነገራችን ላይ የተጠቀሰው ዕዳ ከደርግ ዘመን ጀምሮ የተጠራቀመ ሲሆን ከፍተኛ ብድር የተወሰደው በህወሓት/ኢሕአዴግ ዘመን ነው። በባለፉት ስድስት ተከታታይ ዓመታት የለውጡ መንግስት አንዲት ሰባራ ሣንቲም Commercial loan ያልወሰደ ሲሆን ከ $10 ቢሊዮን ዶላር በላይ ዕዳ ከፍሏል። አሰብ ወደባችንን ባስመለስን ቅጽበት የኢትዮጵያ ኢኮኖሚ ዕድገት በትንሹ 25% ጭማሪ የሚያሳይ ይሆናል። ይሄንን እውነታ መካድ ፍፁም ጨለምተኛ ከመሆን ውጭ ሌላ ሊሆን አይችልም።


#ኢትዮጵያ

ዐቢቹ ቀን ከሌሊት የሚተጋው የበለጸገችና የተከበረችን ሀገር ለትውልድ ለማስተላለፍ ነውጠቅላይ ሚንስትር ዶ/ር ዐቢይ አሕመድ ላለፉት ሰባት ዓመታት እየሰራ ያለውን ሥራዎቹን ብንመለከት ሁሉም በ...
11/07/2025

ዐቢቹ ቀን ከሌሊት የሚተጋው የበለጸገችና የተከበረችን ሀገር ለትውልድ ለማስተላለፍ ነው

ጠቅላይ ሚንስትር ዶ/ር ዐቢይ አሕመድ ላለፉት ሰባት ዓመታት እየሰራ ያለውን ሥራዎቹን ብንመለከት ሁሉም በሚባል ደረጃ የኢትዮጵያን ችግር በሆይ ሆይታ ሳይሆን በእርጋታ ከመሰረቱ ለመለወጥ ነው። ይህንን ሂደቱን ደግሞ በቅርቡ ከኢትዮጵያ ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬሽን ጋር ወደ 5 ሰዓት የሚጠጋ ማብራሪያ በማድረግ አረጋግጠዋል። በዚያ ቃለምልል ቁልፍ በሆኑ አገራዊ ጉዳዮች እና የወደፊት የትኩረት አቅጣጫዎች ላይ ሰፊ ማብራሪያ ማካሄዳቸው የሚታወቅ ሲሆን በተጨማሪም ከነጋዴዎች፣ ከመምህራን፣ ከጤና ባለሙያዎች፣ ከኪነጥበብ ባለሙያዎች፣ ከተቃዋሚ ፓርቲ ተወካዮች እና ከሚዲያ ባለሙያዎች ጋር ተከታታይ ውይይቶችን በማድረግ ኢትዮጵያውያንን ከየትኛውም የህብረተሰብ ክፍል በተውጣጡ ርዕሰ ጉዳዮች ላይ ግልፅ አቅጣጫአስቀምጦልናል።
#ዐቢቹ
#ብልጽግና
#ኢትዮጵያ

የባህር በር ለኢትዮጵያ ህዝብ የህልውና ጉዳይ ነው!!!የኢትዮጵያ ህዘብ ለህልውናዉ የማይደራደር ያሰበው የሚያሳካ ቆራጥ ጀግና ህዘብ መሆናችን ጠላትም ወዳጅም ያዉቃል!! ለኢትዮጵያ የባህር በር...
11/07/2025

የባህር በር ለኢትዮጵያ ህዝብ የህልውና ጉዳይ ነው!!!
የኢትዮጵያ ህዘብ ለህልውናዉ የማይደራደር ያሰበው የሚያሳካ ቆራጥ ጀግና ህዘብ መሆናችን ጠላትም ወዳጅም ያዉቃል!! ለኢትዮጵያ የባህር በር ማግኘት የቅንጦት ሳይሆን የህልውና ጉዳይ ነው። የቀይ ባህር ጉዳይ እንደ ሀገር የህልውና ጉዳይ ነው። የህንን በአንድነት ቆሜን ማሳከት አለብን!! ኢትዮጵያ በሀገሪቱ ለዘመናት ስር ሰዶ የቆየውን ድህነት ለማሸነፍ የባህር በር ያስፈልጋታል።የቀይ ባህር ጉዳይ ለሀገር ልማት እና ብልጽግና የህልዉና ጉዳይ ነው።

ዐቢቹ የኢትዮጵያ ኩራት ነው !!የኢትዮጵያ ህዝብ በፈጣሪ የተባረከ በሳል አዕምሮ ያለዉን ጀግና መሪ በማግኘቱ ደስታችን እጥፍ ድርብ ነው። ዐቢቹ ለመላው ኢትዮጵያውያ ትልቅ ቁምነገን የፈጸመ ጃ...
08/07/2025

ዐቢቹ የኢትዮጵያ ኩራት ነው !!
የኢትዮጵያ ህዝብ በፈጣሪ የተባረከ በሳል አዕምሮ ያለዉን ጀግና መሪ በማግኘቱ ደስታችን እጥፍ ድርብ ነው። ዐቢቹ ለመላው ኢትዮጵያውያ ትልቅ ቁምነገን የፈጸመ ጃግና ነው ። የBRICS ቡድን አባል በመሆን በሁሉም መስክ የኢትዮጵያን ጥቅም ለማስከበር እየሰራ ያለ ጀግና መሪ ነዉ!። ይህ ለዛሬው ትውልድ የማይረሳ ድል እና ለመጪው ትውልድ የማይጠፋ ታሪክ ነው።

የብሪክስ ጉባኤ ኢትዮጵያ ብሔራዊ ጥቅሞቿን በሚያስጠብቁ ጉዳዮች ላይ ስኬታማ የሆነችበት ነውበብሪክስ 17ኛ ጉባኤ ኢትዮጵያ ጥቅሟን በሚያስጠብቁ ጉዳዮች ላይ ስኬታማ ተሳትፎ ማድረጓን በብራዚል ...
08/07/2025

የብሪክስ ጉባኤ ኢትዮጵያ ብሔራዊ ጥቅሞቿን በሚያስጠብቁ ጉዳዮች ላይ ስኬታማ የሆነችበት ነው

በብሪክስ 17ኛ ጉባኤ ኢትዮጵያ ጥቅሟን በሚያስጠብቁ ጉዳዮች ላይ ስኬታማ ተሳትፎ ማድረጓን በብራዚል የኢትዮጵያ አምባሳደር ልዑልሰገድ ታደሰ ገለፁ። የብሪክስ አመታዊ ጉባኤ በተለያዩ አለምአቀፋዊ ጉዳዮች እና የጋራ ጉዳዮች ላይ በመምከር የጋራ መግለጫ በማዉጣት በስኬት መጠናቀቁን አምባሳደሩ ተናግረዋል።

በጠቅላይ ሚኒስተር ዐቢይ አህመድ (ዶ/ር) የተመራው ልኡካን ቡድን የሀገሪቷን ብሄራዊ ጥቅም በሚያስጠብቁ ጉዳዮች ላይ ስኬታማ ተሳትፎ ማድረጉንም አንስተዋል።

በጉባኤ ዋና አጀንዳ የነበረዉ በማደግ ላይ ያሉ ሀገራት የአየር ንብረት ለዉጥን ለመከላከል መወሰድ ያለባቸው ተጨባጭ እርምጃዎች ምን መሆን አለበት በሚል ሰፊ ዉይይት መደረጉን ገልጸዋል። ኢትዮጵያ በብሄራዊ ደረጃ የያዘችዉ አቋም አፍሪካውያን ከያዙት አቋም ጋር የሚጣጣም ነዉ ያሉት አምባሳደሩ፤ በዚህም ኢትዮጵያ በብሪክስ ያሰማችው አቋም የኢትዮጵያ ብቻ ሳይሆን የመላው አፍሪካ ድምፅ ወክለው የተሳተፉበት መሆኑን ገልጸዋል።


#ኢትዮጵያ
#ብልፅግና

ብዙ መከር አለና ሠራተኛ ሆነን ከሠራተኞች ጋር ለሥራ ከተባበርን በፈጣሪ ድጋፍ በምናብ የነበረ ሁሉ በነጋ በጠባ፣ በጊዜ ሂደት ግዘፍ ነስቶ እውን ሲሆን ዐይናችን ያያል።  እንተባበር! እንበር...
03/07/2025

ብዙ መከር አለና ሠራተኛ ሆነን ከሠራተኞች ጋር ለሥራ ከተባበርን በፈጣሪ ድጋፍ በምናብ የነበረ ሁሉ በነጋ በጠባ፣ በጊዜ ሂደት ግዘፍ ነስቶ እውን ሲሆን ዐይናችን ያያል። እንተባበር! እንበርታ!

03/07/2025

የ 2018 ዓ.ም የፌድራል መንግስት በጀት 1.93 ትሪሊዮን ብር ሆኖ ጸደቀ

03/07/2025

"ስራ ማይወዱ የፖለቲካ ገረወይናዎች፤ ስራ አይወዱም፤አውርተው አዳሪዎች ናቸው!!" 🤟

መላው የታችኛው ተፋሰስ ሃገራት የደስታችን ተካፋይ እንዲሆኑ ጥሪ አቀርባለሁ ጠ/ሚ/ር ዶ/ር ዐቢይ አሕመድበተከበረው በዚህ የህዝብ ተወካዮች ፊት ግብፅና ሌሎች አገራትን ጨምሮ ለመላው የታችኛው...
03/07/2025

መላው የታችኛው ተፋሰስ ሃገራት የደስታችን ተካፋይ እንዲሆኑ ጥሪ አቀርባለሁ
ጠ/ሚ/ር ዶ/ር ዐቢይ አሕመድ
በተከበረው በዚህ የህዝብ ተወካዮች ፊት ግብፅና ሌሎች አገራትን ጨምሮ ለመላው የታችኛው ተፋሰስ ሃገራት በመጪው መስክረም ታላቁ የኢትዮጵ ህዳሴ ግድብ ሲመረቅ የደስታችን ተካፋይ እንዲሆኑ ጥሪ አቀርባለሁ።

Address

Addis Ababa

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when የመደመር ትውልድ - Dhaloota Ida'amuu posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share