የመደመር ትውልድ - Dhaloota Ida'amuu

የመደመር ትውልድ - Dhaloota Ida'amuu Odeefannoowwan haaraafi wayitawaa waliin Badhaadhinaa Itoophiyaa mul'isuuf ni hojjenna!
የኢትዮጵያን ብልፅግና የሚያሳዩ አዳዲስና ፈጣን መረጃዎችን የሚያገኙበት ትክክለኛው ቦታ ነው። 👇

የአሜሪካ የአፍሪካ ጉዳይ ፖሊሲ ከኢትዮጵያ ራስን መቻል ፖሊሲ ጋር የተጣጣመ ነውየአለም ሀያላን ፖሊሲያቸውን በአፍሪካ ጉዳይ ላይ እንደገና በሚመለከቱበት ወቅት፣ አሜሪካ ከዕርዳታ ተኮር ተሳትፎ...
05/12/2025

የአሜሪካ የአፍሪካ ጉዳይ ፖሊሲ ከኢትዮጵያ ራስን መቻል ፖሊሲ ጋር የተጣጣመ ነው

የአለም ሀያላን ፖሊሲያቸውን በአፍሪካ ጉዳይ ላይ እንደገና በሚመለከቱበት ወቅት፣ አሜሪካ ከዕርዳታ ተኮር ተሳትፎ ወደ ንግድ፣ ኢንቨስትመንት እና ሀብት ላይ የተመሰረተ አጋርነት መሸጋገሯን እያሳየች ነው። ለኢትዮጵያ ይህ የዕድገት ስትራቴጂ እድሎችን የሚያመጣ ነው።

የዋሽንግተን ጥሪ ከውጭ ዕርዳታ ወደ የጋራ ተጠቃሚነት ወደ ኢኮኖሚያዊ ትስስር ለመሸጋገር ያቀረበችው ጥሪ ኢትዮጵያ ከራሷ የረዥም ጊዜ ራስን የመቻል ፣የኢንዱስትሪ ልማት እና የገበያ መስፋፋት ሂደት ጋር ይዛመዳል። ኢትዮጵያ ከጥገኝነት ይልቅ ኢንቨስትመንትን በማስቀደም ስትራቴጅካዊ ጂኦግራፊ፣ ሰፊ የተፈጥሮ ሀብቷን እና በፍጥነት በማሳደግ ላይ ያለችውን የኢነርጂ እና ማዕድን ሴክተሮችን በመጠቀም ጠንካራ እና ሚዛናዊ አጋርነቶችን መደራደር ትችላለች።
የአሜሪካ አጽንዖት በቀጠናው ግጭቶችን ለመፍታት የረዥም ጊዜ ወታደራዊ ውዝግቦችን በማስወገድ ኢትዮጵያ በአፍሪካ ቀንድ የመሪነት ሚናዋን እንድታረጋግጥ ዲፕሎማሲያዊ ቦታን ከፍቷል።

አሜሪካ ገበያዎቻቸውን ለመክፈት ፍቃደኛ የሆኑ ታማኝ መንግስታትን ስትፈልግ፣ ኢትዮጵያ ተጠቃሚ ለመሆን ተገኝታለች! በመጨረሻም የአሜሪካ መንግስት በአፍሪካ ጉዳይ ያለውን አቋም በሰነዱ ላይ የገለጸው የፖሊሲ ለውጥ ኢትዮጵያ የረዥም ጊዜ የተረዳችውን ነገር አረጋግጧል፡ መጪው ጊዜ በጥንካሬ የሚደራደሩ፣ የሚያለሙ እና ተፈጥሯዊና ሰብአዊ ሀብታቸውን ወደ ስትራቴጂያዊ ጥቅም የሚቀይሩ ሀገራት ነው።

አንድ ሀሙስ ቀረ ቢሉም ከአቅሙም፤ ከአቋሙም ፈቀቅ ያላለው እና እያደር የሚጠብቀውለመጨረሻ ጊዜ ፖስት ያደረግሁት ከሁለት ወራት በፊት፤ እነ እንትና "ይሄ መንግስት አንድ ሐሙስ ነው የቀረው.....
05/12/2025

አንድ ሀሙስ ቀረ ቢሉም ከአቅሙም፤ ከአቋሙም ፈቀቅ ያላለው እና እያደር የሚጠብቀው

ለመጨረሻ ጊዜ ፖስት ያደረግሁት ከሁለት ወራት በፊት፤ እነ እንትና "ይሄ መንግስት አንድ ሐሙስ ነው የቀረው..." ብለው ለደጋፊዎቻቸውም ለተቀናቃኞቻቸውም መሐላ የተቀላቀለበት ማረጋገጫ በሚሰጡበት ጊዜ ነበር። እናም "አንድ ሐሙስ የቀረው መንግስት በሚመራት ሀገር "መሐል ሰፋሪ" ከምሆን ብዬ አድፍጬ ብጠብቅም "ወፍ የለም"!😜

ቆይ ግን "አንድ ሐሙስ..." ስንት ቀን ነው?! 🤔

ይኸው ከ10 ሐሙሶች በኋላ ካደፈጥኩበት ስመለስ፤ "አንድ ሐሙስ ቀርቶት እያጣጣረ ነው" የተባለው መንግስት በቦታው መኖር ብቻ ሳይሆን፤ ከአቅሙም፤ ከአቋሙም ፈቀቅ ሳይል ነው የጠበቀኝ

ለማንኛውም እኔ እንደገባኝ ከሆነ ይሄ መንግስት ሚስማር ነው። በስሁት ትንተና ተገፋፍተው፤ ያለ የሌለ ታጣቂ አሰማርተው "አንድ ሐሙስ ነው የቀረው..." እያሉ ሲነርቱት የባሰ ይጠብቃል። የላሉ ብሎኖቹን ያጠባብቃል። ምና'ልባት የሚሻለው እንዳለፉት ሚስማሩን ዝም ብሎ መነረት ሳይሆን፤ የመዶሻውን አቅጣጫ ገልብጦ በሰላማዊ መንገድ gently "ወዝወዝ ጎተት...ጎተት ወዝወዝ".... እያደረጉ መሞከር ነው።

ኢሳያስ ወታደሮቹን ወደ ሱዳን በመላክ የአፍሪካ ቀንድ ሰላምን አደጋ ላይ ጥሏልበሱዳን ውስጥ የኤርትራ ወታደሮች ጣልቃ መግባታቸው የአፍሪካ ቀንድ ሰላም ቀጥተኛ ስጋት ነው። ሻዕቢያ የጀመርችውን...
05/12/2025

ኢሳያስ ወታደሮቹን ወደ ሱዳን በመላክ የአፍሪካ ቀንድ ሰላምን አደጋ ላይ ጥሏል

በሱዳን ውስጥ የኤርትራ ወታደሮች ጣልቃ መግባታቸው የአፍሪካ ቀንድ ሰላም ቀጥተኛ ስጋት ነው።
ሻዕቢያ የጀመርችውን ያልታገባ ጣልቃ ገብነት ማቆም ለባት።የሻዕቢያው መሪ 10,000 ወታደሮችን ወደ ሱዳን የላከው መላዉ ምስራቅ አፍሪካን ሰላም ለማደፍረስ አቅዶ ነው። ይህን ስጋት ከመስፋፋቱ በፊት ባለድርሻ አካላት መተባበር አለባቸው።

አዲስ አበባ! 🥰
05/12/2025

አዲስ አበባ! 🥰

ብልጽግና ለሀገራዊ ስብራቶች ዘላቂ መፍትሔ ለማስቀመጥ እየሠራ ነው።በክቡር ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ የሚመራው የብልጽግና መንግሥት፣ ኢትዮጵያ ለረጅም ጊዜያት ተሸክማ የቆየቻቸውን ሀገራዊ...
05/12/2025

ብልጽግና ለሀገራዊ ስብራቶች ዘላቂ መፍትሔ ለማስቀመጥ እየሠራ ነው።

በክቡር ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ የሚመራው የብልጽግና መንግሥት፣ ኢትዮጵያ ለረጅም ጊዜያት ተሸክማ የቆየቻቸውን ሀገራዊ ስብራቶች በዘላቂነት ለመፍታት ታሪካዊ ኃላፊነት ወስዶ እየሠራ ይገኛል። ይህ መፍትሔ የሀገሪቱን ታሪክ በጥልቀት ከመመርመር፣ ከዘመኑ ጋር የማይራመድበትን አባዜ በመስበር እና ለነገ ትውልድ ስንቅ የሚሆን ሁሉን አቀፍ ምህዳር በመፍጠር ላይ የተመሠረተ ነው።

መንግሥት ሀገር ተሰብራበት የነበሩትን የታሪክ ቅርሶች ችላ የማለትን አካሄድ በመቀየር፣ እንደገና በማጎልበት የጋራ ብሔራዊ ማንነትን በመገንባት ላይ ትኩረት አድርጓል። ከዚህም ባሻገር፣ በዘርፈ ብዙ የቴክኖሎጂ አብዮት (እንደ ዲጂታል ኢትዮጵያ ፕሮጀክት) በመግባት ከዘመን ጋር አለመራመድን እንደ ትልቅ የዕድገት እንቅፋት ተመልክቶታል፤ ይህም የሀገሪቱን ኢኮኖሚና አገልግሎቶች ለማዘመን ያለመ የነገ ስንቅ ነው።

በተጨማሪም ታላላቅ ሥራዎችን በመጀመር የተፈጥሮ ሀብትን በአግባቡ አለመጠቀምን በመቅረፍ፣ ኢኮኖሚያዊ ዕድገትን ከአካባቢ ጥበቃ ጋር በማጣመር ዘላቂ ብልጽግናን ለማረጋገጥ እየሰራ ነው። በመሆኑም፣ የዐቢይ አሕመድ መንግሥት ታሪክን፣ ቴክኖሎጂን እና የተፈጥሮ ሀብትን በአግባቡ በማቀናጀት ለኢትዮጵያ ህልውና አስጊ የነበሩትን ስብራቶች እየጠገነና ለቀጣዩ ትውልድ የተረጋገጠ ብልጽግናን ለመፍጠር የሚያስችል ጠንካራ መሠረት እየጣለ ነው።

በመንግስት እየተወሰዱ ያሉ የሰላም አማራጮች የሚደነቁ እና የሚወደሱ ናቸው።በመላው ኢትዮጵያ ዘላቂ ሰላምን ለማምጣት የኢትዮጵያ መንግስት እያደረገ ያለው ተከታታይ እና ውጤታማ ጥረት ከፍተኛ አ...
05/12/2025

በመንግስት እየተወሰዱ ያሉ የሰላም አማራጮች የሚደነቁ እና የሚወደሱ ናቸው።

በመላው ኢትዮጵያ ዘላቂ ሰላምን ለማምጣት የኢትዮጵያ መንግስት እያደረገ ያለው ተከታታይ እና ውጤታማ ጥረት ከፍተኛ አድናቆትና ምስጋና ይገባዋል። መንግስት በሰሜኑ የትግራይ ክልል ጨምሮ በቤንሻንጉል ጉሙዝ፣ አፋር፣ ሶማሌ፣ ኦሮሚያ እና አማራ ክልሎች ሁሉ ከተለያዩ አካላት ጋር የሰላም ስምምነቶችን በተደጋጋሚ በማድረግ ግጭቶችን በውይይት የመፍታት ቁርጠኝነቱን በተግባር አሳይቷል።

ከዚህም ባሻገር በሰላማዊ መንገድ የገቡና ስምምነት የፈፀሙ አካላትን እስከ መንግስታዊ መዋቅር ድረስ በማዋቀርና የስራ ድርሻ በመስጠት፣ የሀገር ግንባታ ሂደት ሁሉን አቀፍ እና ይቅር ባይ መሆኑን አረጋግጧል። እነዚህ በሰላማዊ መንገድ ግጭቶችን ለመፍታት እና የብሄራዊ መግባባትን አድማስ ለማስፋት የተወሰዱ ደፋር እርምጃዎች፣ ለትውልድ የሚሻገር ሰላም፣ መረጋጋት እና ብልጽግና መሰረት የሚጥሉ በመሆናቸው፣ በእውነትም የሚደነቁ እና የሚወደሱ ናቸው።

ጠቅላይ ሚንስትር አብይ አህመድ! 🌿🥰
05/12/2025

ጠቅላይ ሚንስትር አብይ አህመድ! 🌿🥰

የመቀሌዉ መፈንቅለ ጊዜያዊ አስተዳደር ወደ አድማ ዞሯል ። ሞንጆሪኖ በባጃጅ ስትሸሽ ወጣቶች እያዩ ነው ። ሁሉም አድማዉን ፈርቶ ተደብቋል ። ፍሰሃን ብቻ ይዘውታል ቀሪዎቹ ጄኔራል በሙሉ ተደብ...
04/12/2025

የመቀሌዉ መፈንቅለ ጊዜያዊ አስተዳደር ወደ አድማ ዞሯል ። ሞንጆሪኖ በባጃጅ ስትሸሽ ወጣቶች እያዩ ነው ። ሁሉም አድማዉን ፈርቶ ተደብቋል ። ፍሰሃን ብቻ ይዘውታል ቀሪዎቹ ጄኔራል በሙሉ ተደብቀዋል ። ፍሰሃ የፈለጋችሁትን እናድርግላችሁ ብሏቸዋል ። እስከ ዛሬ ዬት ነበርክ ብለውታል ።

04/12/2025

በአማራ ክልል መንግስት እና በአማራ ፋኖ ህዝባዊ ድርጅት መካከል የተደረገው የሰላም ስምምነት🕊🕊🕊🕊🕊🕊🕊

ኢጋድ ለሰላም ስምምነቱ የእንኳን ደስ አላችሁ መልዕክት አስተላለፈኢጋድ በአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስትና በአማራ ፋኖ ሕዝባዊ ድርጅት መካከል በዛሬው ዕለት በተደረሰው የሰላም ስምምነት የእን...
04/12/2025

ኢጋድ ለሰላም ስምምነቱ የእንኳን ደስ አላችሁ መልዕክት አስተላለፈ

ኢጋድ በአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስትና በአማራ ፋኖ ሕዝባዊ ድርጅት መካከል በዛሬው ዕለት በተደረሰው የሰላም ስምምነት የእንኳን ደስ አላችሁ መልዕክት አስተላልፏል፡፡ ኢጋድ ሁለቱም ወገኖች ለወሰዱት የሰላም እርምጃ አድናቆቱን የገለፀ ሲሆን፣ ሌሎች ቡድኖችም ይህንን ታሪካዊ የሰላም እንቅስቃሴ እንዲቀላቀሉ ጥሪ አቅርቧል። የሰላም ስምምነቱን የአማራ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አረጋ ከበደ እና የአማራ ፋኖ ሕዝባዊ ድርጅትን የወከሉት ካፒቴን ማስረሻ ሰጤ ዛሬ ተፈራርመዋል፡፡በሰላም ስምምነቱ ላይ የኢጋድ ምክትል ዋና ፀሐፊ መሀመድ አብዲ ዋሬ እና የአፍሪካ ሕብረት ኮሚሽን ምክትል ሊቀመንበር አምባሳደር ሰልማ ማሊካ ሀዳዲ ተገኝተዋል፡፡
#ሰላም

ከሰላም ሁሉም ያተርፋል!በአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት እና በአማራ ፋኖ ሕዝባዊ ድርጅት (አፋሕድ) መካከል የዘላቂ ሰላም ስምምነት ተፈርሟል፡፡ ስምምነቱን የአማራ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አ...
04/12/2025

ከሰላም ሁሉም ያተርፋል!

በአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት እና በአማራ ፋኖ ሕዝባዊ ድርጅት (አፋሕድ) መካከል የዘላቂ ሰላም ስምምነት ተፈርሟል፡፡ ስምምነቱን የአማራ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አረጋ ከበደ እና የአማራ ፋኖ ሕዝባዊ ድርጅትን (አፋሕድ) በመወከል ካፒቴን ማስረሻ ሰጤ ተፈራርመዋል። ውይይቱ እና ድርድሩ በአፍሪካ ሕብረት እና በኢጋድ አደራዳሪነት ሲካሄድ ነው የቆየው።

ርዕሰ መስተዳድሩ አረጋ ከበደ በአስተላለፉት መልዕክት፣ ዛሬ ለክልላችን ሕዝብ የመጀመሪያው ትልቅ የሰላም ኩነት የተካሄደበት ቀን ነው ብለዋል።

ከግጭት አሸናፊም ተሸናፊም የለም፣ ከሰላም ሁሉም ያተርፋል፣ ስምምነቱ ለሰላም ወዳድ ሕዝባችን ትልቅ እፎይታን ይሰጣል ነው ያሉት፡፡የሕዝብና የመንግስትን ጥሪ ተቀብለው ዘላቂ ሰላም ለማስፈን ለመጡ ወንድሞቻችን እንደ መንግስት አድናቆትና ክብር አለኝ ብለዋል፡፡

በአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስትና በአማራ ፋኖ ሕዝባዊ ድርጅት መካከል የዘላቂ ሰላም ስምምነት ተፈረመበአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት እና በአማራ ፋኖ ሕዝባዊ ድርጅት (አፋሕድ) መካከል የዘ...
04/12/2025

በአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስትና በአማራ ፋኖ ሕዝባዊ ድርጅት መካከል የዘላቂ ሰላም ስምምነት ተፈረመ

በአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት እና በአማራ ፋኖ ሕዝባዊ ድርጅት (አፋሕድ) መካከል የዘላቂ ሰላም ስምምነት ተፈርሟል፡፡

ስምምነቱን የአማራ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አረጋ ከበደ እና የአማራ ፋኖ ሕዝባዊ ድርጅትን (አፋሕድ) በመወከል ካፒቴን ማስረሻ ሰጤ ተፈራርመዋል።

ውይይቱ እና ድርድሩ በአፍሪካ ሕብረት እና በኢጋድ አደራዳሪነት ሲካሄድ ነው የቆየው።

ርዕሰ መስተዳድሩ አረጋ ከበደ በአስተላለፉት መልዕክት፣ ዛሬ ለክልላችን ሕዝብ የመጀመሪያው ትልቅ የሰላም ኩነት የተካሄደበት ቀን ነው ብለዋል።

ከግጭት አሸናፊም ተሸናፊም የለም፣ ከሰላም ሁሉም ያተርፋል፣ ስምምነቱ ለሰላም ወዳድ ሕዝባችን ትልቅ እፎይታን ይሰጣል ነው ያሉት፡፡

የሕዝብና የመንግስትን ጥሪ ተቀብለው ዘላቂ ሰላም ለማስፈን ለመጡ ወንድሞቻችን እንደ መንግስት አድናቆትና ክብር አለኝ ብለዋል፡፡

የአማራ ፋኖ ሕዝባዊ ድርጅትን (አፋሕድ) በመወከል ስምምነቱን የተፈራረሙት ካፒቴን ማስረሻ ሰጤ በበኩላቸው፣ ማንኛውም ግጭት በመጨረሻ የሚፈታው በውይይትና በድርድር ነው ብለዋል።

ችግሮችና የሀሳብ ልዩነትን በንግግር መፍታት ፖለቲካዊ ሽንፈት ሳይሆን ጥበብና ብልጠት መሆኑን ገልጸው፣ ችግሮችን ለመፍታት ከኢትዮጵያ ታሪካዊ ጠላቶች ጋር ማበር ተገቢ አለመሆኑን አስገንዝበዋል፡፡

የአፍሪካ ሕብረት ኮሚሽን ምክትል ሊቀመንበር አምባሳደር ሰልማ ማሊካ አዳዲ በበኩላቸው፣ ስምምነቱ የሀገሪቱን ቀጣይ መዳረሻ የሚያቃና ነው ብለዋል።

Address

Addis Ababa

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when የመደመር ትውልድ - Dhaloota Ida'amuu posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share